Sunday, July 21, 2013

የእስክንድር ነጋ ደብዳቤ ከቃሊቲ እስር ቤት ለባራክ ኦባማ የተፃፈ


                     



                  ግልፅ ደብዳቤ ለኦባማ አስተዳደር!

                                 እስክንድር ነጋ
 
                             ከቃሊቲ እስር ቤት




 ሁላችንም እንደምናውቀው በሀያኛው ክፍለ ዘመን የመጨረሻ ዓስርታት በተለያዩ ክፍለ አህጉራት ውስጥ ባለ ታዲጊ ሀገር  ህዝቦች የተነሱ የፖለቲካ እና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች በቀዳሚነት በጠመንጃ ኃይሌ የተደገፉ ነበሩ፡፡ ኢትዮጵያም በተመሳሳይ  የታሪክ ክስተት ማለፏን የሚመሰክረው ዛሬም ወታደራዊ ስርዓቱን ብቻ ሳይሆን፣ ይህንን መንገዴ የመረጡትን ጥቂት  የተቃዋሚ ድርጅቶችንም በጦር ኃይል ድል አድርጎ ስልጣን ላይ ያለው ኢህአዴግ መሆኑ ነው፡፡ ይሁንና የቀዝቃዛው ዓለም  ጦርነት ማብቃትና የአሜሪካ ብቸኛ ሌዕለ ሀያል ሀገር ሆኖ መውጣት በኃይል የሚደረጉ ‹‹ፀረ-አምባገነን›› ንቅናቄዎች  ሰላማዊውን መንገዴ ብቻ እንዲከተሉ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡ የለውጡም ዋነኛ መፍትሄ አሜሪካ ለሰላማዊ ትግል  የምትሰጠው ከፍ ያለ ቦታ ብቻ ሳይሆን የምታደርገው እገዛም መሆኑ አከራካሪ አይደለም፡፡ በእርግጥ የአሜሪካ አስተዳደር  በሰላማዊ ትግል ላይ ያለው አቋምና ለትግሉ የሚያደርገው ቀጥተኛ አበረታችነት የሀገሪቱ መስራች አባቶች ካነፁት የሞራሌ እና  የፖለቲካ እሴት እንደሚነሳም አውቃለሁ፡፡  

 ሙሉውን ደብዳቤው ሊንኩን በመጠቀም ዳውን ሎድ በማድረግ ያንብቡት!

https://docs.google.com/file/d/0B6jhgT-afGuONWtmWlBWeXBqWGM/edit?pli=1

No comments:

Post a Comment