Friday, July 31, 2015

ሁሉም በያለበት የነፃነት ትግሉን ይቀላቀል!!!

እኛ ኢትዮጵያውያን ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ የሰውነት መብታችን ተገፎ የዜግነት ነፃነታችን ተረግጦና ተዋርደን የምንገኝበት ጊዜ ቢኖር ዛሬ ነው፡፡ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ እስርና የጅምላ ስደት እንደ ዘመነ ወያኔ የታየበት ዘመን የለም፡፡ ህፃናት በረሀብ ከሚማሩበት ክፍል ውስጥ የሚወድቁበት ፤ ወንድ ልጅ በደህንነት ሀይሎች ታፍኖ የሚደፈርበት፤ ሴት ልጅ በገመድ የታሰረ የባልዋነወ ብልት መንገድ ለመንገድ እንድትጎትት የተደረገበት ዘመን ቢኖር ያሳለፍነው የወያኔ ዘመናት ብቻ ነው፡፡ ባጠቃላይ የሰው ልጅ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ መከራና ሰቆቃ እንድንሸከም የተገደድንበት ዘመን ላይ እንገኛለን፡

በአንፃሩም ስለ ለፃነት ስለ ፍትህና እኩልነት ሲሉ የተሰዉ ዋጋም የከፈሉ፤ አሁንም እየከፈሉ የሚገኙ ጥቂት አይደ ሉ ም፡፡ ከነዚህም አንዱ አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ይህ ለነፃነት ለፍትህና ለ ዲሞክራሲ የሚደረገው ተጋድሎ ውሎ አድሮ ዛሬ ከዋናውና ወሳኝ ከሆነው ምእራፍ ላይ መድረሱ ደግሞ የሁላችንንም ተስ ፋ ያለመለመና የተደፋው አንገታችን ቀና ያደረገ መሆኑና በተቃራኒው የወያኔን ካንፕ ያሸበረ መሆኑ በገሀድ እየታየ የሚገኝ እውነት ነው፡፡

እንግዲህ ይህን ወራዳ ስርአት አስወግዶ በምትኩ ዲሞክራሲያዊ ስርአት ለመተካት የሚደረገው ትግል ዛሬ የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የተደረገው ርብርብ ቀላል ባይሆንም ቀሪውን አጠናቆ ከዳር ለመድረስ ከመቼውም ጊዜ በላይ የእያንዳዱን ኢትዮጵያዊ የተግባር ተሳትፎ የሚጠይቅ፤ ሁሉም ከያለበት ስለ ነፃነት የሚደረገውን የአርነኝነት ትግል በመቀላቀል የድርሻ ውን ሀላፊነት መወጣት ከሚጠይቅበት ወሳኝ ምእራፍ ላይ መድረሳችንን መረዳት ግድ ይላል፡፡

እኛ ኢትዮጵያውያን ያለ ማንም እርዳታና ድጋፍ ዋጋ ከፍሎ ለፃነትን የማሰከበር እንግዳ ሳንሆን በታሪክ የምንታወቅበት መለያችን መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ እንኳን ዛሬ አለም አለም በጠበበችበት ዘመን ቀርቶ ትናንት በጨለማው ዘመን እንኳ እነ ዶ/ር መላኩ በያን ከአኛ አልፎ ለአፍሪካ ነፃነት ፈር ቀዳጅ ሆነው የተገኙበትን ታሪክ ማስታወስ ይገባል፡፡

እናም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኟውም ስፍራ የሚገኝ ሁሉ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል እውቀት ያለው በእውቀቱ፤ ጉልበት  ያለው በጉልበቱ፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ ለመደገፍ ዛሬ ነገ ሳይል አሁኑኑ ከአርበኝነቱ ትግል መቀላቀል ይጠበቅበታል፡፡ ኢትዮጵያዊነታችንን ብቻ ሳይሆን ሰው መሆናችን የሚረጋገጠው ነፃነታችንን አስጠብቀን በነፃነት መኖር ስንችል ብቻ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡

Thursday, July 30, 2015

Obama’s Trip To Africa Fails To Secure Human Rights Commitments


by Sahara Reporters, New York

(Sahara) Despite these meetings, Mr. Obama left Africa without securing any human rights commitment from Ethiopia. In addition, the critiques of various human rights groups who claim Obama’s visit legitimizes the oppressive governments confirm that these past five days in Africa were a trivial international exercise.

On Tuesday, United States President Barack Obama concluded his visit to Kenya and Ethiopia. Besides holding meetings with leaders in the African Union, the Kenyan President Uhuru Kenyatta, the Ugandan President Yoweri Museveni, and the Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn, Mr. Obama also heralded Africa as nation filled with people with “dignity.”

Despite these meetings, Mr. Obama left Africa without securing any human rights commitment from Ethiopia. In addition, the critiques of various human rights groups who claim Obama’s visit legitimizes the oppressive governments confirm that these past five days in Africa were a trivial international exercise.

In June, a report released by the Committee to Protect Journalists (CPJ) put Ethiopia near the top of a list of countries that violate the freedom of journalists. Since May of 2014, the Ethiopian government has forced 34 journalists to leave the country in exile. After Eritrea, Ethiopia continues to be the African country that imprisons the most journalists.

Jeff Smith of the John F. Kennedy Human Rights Center spoke to SaharaReporters and said, “The Ethiopia trip doesn’t fair well for strengthening democratic institutions.”

ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ለምን ያስጨንቃቸዋል?

ሽብሬ ደሳለኝ

ባለፉት 24 ዓመታት ወያኔዎች በሃገር ውስጥ (በሰላማዊ መንገድ) ለውጥ ለማምጣት የሚንቀሳቀሱትን የፖለቲካ ድርጅቶች እና ፖለቲከኞች ከማዳከም አልፈው በአሁኑ ወቅት ምንም አይነት ተጽኖ መፍጠር እንዳይችሉ አድርገዋቸዋል።

አብዛኛዎቹ ፖለቲከኞች የወያኔ አፈና ሲበረታ ከማምረር ይልቅ ፖለቲካውን እርግፍ አድርገው ይተውታል ወይንም ደግሞ ስደት ይወጡና ቀደም ሲል የተሰደደውን የኢትዮጵያ ስደተኛ ተቀላቅለው እንደ አብዛኛው ስደተኛ ቤተሰቦቻቸውን እና እራሳቸውን በኢኮኖሚ የማሻሻል ተግባር ላይ አተኩረው ይቀራሉ። ይህ እየተለመደ የመጣ አካሄድ ወያኔዎቹን ተመችቷቸው ኖረዋል፣ እነ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የጨዋታውን ህግ እስከቀየሩት ድረስ።

በርግጥም አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እና ጓዶቹ ወደ ፖለቲካው ሜዳ ያመጡት አዲስ የጫወታ ህግ ሰርቷል!

ወያኔ አዲሱን የጨዋታ ህግ ከጅምሩ አልወደደውም፣ ከሚቆጣጠረው ግዛት ውጪ የሚደረጉ የለውጥ እንቅስቃሴዎች ኋይት ሃውስ ፊት ለፊት ሻማ ከማብራት ያለፉ እንዳይሆኑ ምኞቱ ነበር። ይህ አልሆነም።

አቶ አንዳርጋቸው እና ጓዶቹ ኢትዮጵያውያን የአሜሪካን ወይንም የእንግሊዝን መንግስት በመለመን ነጻነታቸውን እንደማይቀናጁ ይልቁንም ብረት አንስተው ወያኔን በሚገባው ቋንቋ የማነጋገር አስፈላጊነትን አስተማሩ፣ ወተወቱ፣ የመውጪያ መግቢያ ቀዳዳዎችንም አመላከቱ… ኤርትራ!

ወያኔ በሃገር ውስጥ (በሰላማዊ መንገድ) የሚደረጉ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን ሲያዳፍን፣ ለውጥ ፈላጊው ትውልድ የሃይል አማራጮችን እንደሚያማትር አልጠፋውም፣ ወያኔዎች የለውጥ ፈላጊው ትውልድ የሃይል አማራጮችን በስራ ላይ ለማዋል ተባባሪ/ፈቃደኛ የጎረቤት ሃገሮች እንደሚያስፈልጉት ቀደም ብሎ መተንበዩ አልቀረም (ወያኔ ከደርግ መንግስት ጋር ባደረገው የሃይል ትግል ወቅት ሱዳን እና ሶማሊያ ዋንኞቹ መጠለያው ነበሩ)። ከሃገር ጥቅም ይልቅ ለመንበረ ስልጣኑ ቅድሚያ የሚሰጠው ወያኔ ለኢትዮጵያ አጎራባች ሃገሮች ሁሉ የሚጠይቁትን እየሰጠ (ለምሳሌ ሱዳን ከሃይለስላሴ ዘመን ጀምሮ ይገባኛል የምትለውን የኢትዮጵያ መሬት ከወያኔ ተቀብላለች) በምላሹም ተቃዋሚዎቹን እንዳያስጠልሉ፣ አልፎ ተርፎም ተቃዋሚዎቹን እያደኑ እንዲያስተላልፉለት አግባባቸው። ይሁንና ይህ አካሄድ በጎረቤት ኤርትራ ሊሰራለት አልቻለም።

አንዳርጋቸው ጽጌ እና ጓዶቹ አውርተው አልቀሩም፣ ከኤርትራ መንግስት ጋር የተሳካ ግንኙነት ፈጠሩ፣ ጦርም ማደራጀት ቻሉ፣ ቀደም ሲል ጀምሮ በኤርትራ መሬት ይንቀሳቀሱ በነበሩት ሃይሎች መካከልም መልካም እና መተማመን የሰፈነበት ግንኙነት እንዲኖር አስቻሉ።

ወያኔ ከሚቆጣጠረው ግዛት ውጪ የሚደረገው የለውጥ እንቅስቃሴ እየበረታ መሄዱን በመገንዘብ እንቅስቃሴውን በእንጭጩ ለማስቀረት መንቀሳቀሱ አልቀረም፣ ይህንን ወያኔን እንቅልፍ የነሳ እንቅስቃሴ ወደ ተግባራዊነት እየቀየሩ ባሉት የግንቦት 7 አመራሮች ላይ አነጣጥሮ በተገዙና የተቃዋሚ ካባ በደረቡ ግለሰቦች አማካኝነት አመራሮቹን ከህዝብ ለመነጠል ከፍተኛ ሙከራ ቢያደርግም ውጤቱ አመርቂ አልሆነም። ወያኔ ከዚህ በኋላ ነበር አማተር ሰላዮቹን ወደ ኤርትራ በመላክ አርበኛውን አንዳርጋቸው ጽጌን ለመግደል ሙከራ ያደረገው ይህም አልተሳካም እንደውም ከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ ደረሰበት (ብዙዎች አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጠንቅቀው የማያውቁት ሳይቀሩ የአንዳርጋቸውን ማንነት ለመገንዘብ ቻሉ)።

Monday, July 27, 2015

Obama criticised for calling Ethiopia's government 'democratically elected'

theguardian |  in Addis Ababa

Barack Obama has been criticised by opposition groups and journalists in Ethiopia after referring to the country’s government as “democratically elected”, with one human rights watchdog describing the statement as “shocking”.

The US president was speaking at a joint press conference with Hailemariam Desalegn, the Ethiopian prime minister, after the two leaders held talks in the capital, Addis Ababa.

Although Obama said he had raised issues of good governance – “I don’t bite my tongue too much when it comes to these issues” – he also insisted: “We are opposed to any group that is promoting the violent overthrow of a government, including the government of Ethiopia, that has been democratically elected.”

Answering questions from journalists later, Obama repeated the phrase: “We are very mindful of Ethiopia’s history – the hardships that this country has gone through. It has been relatively recently in which the constitution that was formed and the elections put forward a democratically elected government.”

Hailemariam’s party and its allies won 100% of seats in parliament two months ago. The opposition alleged the government had used authoritarian tactics to secure victory, including intimidation, arrests and violently breaking up rallies. At the time, the US said it remained “deeply concerned” by restrictions on civil society, media, opposition parties and independent voices and views.

But Ethiopia remains a key security ally for the US in the fight against the Islamist militant group al-Shabaab. It has also become an economic battleground with China, which has delivered huge infrastructure projects in Africa’s second most populous nation.

Critics accused Obama of granting legitimacy to the regime. Reeyot Alemu, a columnist released earlier this month after four years in jail on terrorism charges, said: “It’s not ‘democratically elected’ because there was only government media and people did not get enough information.

“They also arrested many opposition leaders and journalists. They won the election by using human rights violations. How can it be democratically elected? It is completely false. I wish Barack Obama had sent a strong message.”

Friday, July 24, 2015

ህወሓት በፈጠራቸው ድርጅቶች ውስጥ ተኩኖ ህወሓትን ማዳከም አርበኝነት ነው!

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ለኢህአዴግ እና አጋር ድርጅቶቹ አባላት የሚከተለው መልዕክት ማስተላለፍ  ይሻል።

ህወሓት ጥቂት አባላትና ደጋፊዎች ይዞ ታላቂቷን ኢትዮጵያ ለማንበርከክ እና ሀብቷን ለመመዝበር  እናንተን መጠቀሚያ ያደረጋችሁ መሆኑን የምታውቁት ነው። እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴድ የተባሉ ድርጅቶች የራሳቸው ድርጅታዊ ነፃነት የሌላቸው የህወሓት አገልጋዮች መሆናቸው እነሱ ራሳቸው የሚነግሯችሁ ከመሆኑም በላይ እናንተም በዕለት ተዕለት ተግባራችሁ የምትታዘቡት ሀቅ ነው። እነዚህ ድርጅቶች ህወሓትን ለማስደሰት ሲሉ የራሳቸውን ሕዝብ የሚያስሩ፣ የሚገድሉ፣ የሚዘርፉ፣ ከቀየው የሚያፈናቅሉ፣ መኖሪያ ቤቱን የሚያስፈርሱ መሆናቸው እናንተም እየተሳተፋችሁበት ያለ ሥራ ነውና የምታውቁት ነው። “አጋር ድርጅቶች” የሚል ስያሜ የተሰጣችው  አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊ እና ኢሶዴፓ “አጋር” ሳይሆን የህወሓት ጀሌዎች መሆናቸው እናንተም እኛም የምናውቀው ነው። እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴድ፣ አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊና ኢሶዴፓ  የተባሉ አድርባይ ድርጅቶች ባይኖሩ ኖሮ ህወሓት ለ24 ዓመታት ኢትዮጵያዊያን እየገደለና እያሰረ፤ እየዘረፈ በውሸት ምርጫና በውሸት ዲሞክራሲ ስም ፍጹም የሆነ ዘረኛ፣ ከፋፋይ፣ አምባገነናዊ ሥርዓት በመላው ኢትዮጵያ ውስጥ ሊያሰፍን ባልቻለም ነበር። ህወሓት በኢትዮጵያዊያን አናት ላይ እንዲፈነጭ እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ድርጅቶች አስተዋጽዖ  ከፍተኛ  ነው።

ይህ ብቻም አይደለም። እናንተ አባል ሆናችሁ ድጋፍ ባታደርጉላቸው ኖሮ እነዚህ አድርባይ ድርጅቶች ባልኖሩም ነው። ስለሆነም ህወሓት በኢትዮጵያዊያን አናት ላይ እንዲፈነጭ፣ እናንተ ብቻ ሳትሆኑ ልጆቻችሁ እና የልጅ ልጆቻችሁ በሎሌነት እንዲያድጉ፤ ጥቂቶች በልጽገው ብዙሃኑ እንዲደኸዩ  እናንተ በግል አስተዋጽዖ አድርጋችኋል።

ብዙዎቻችሁ እነዚህ አድርባይ ድርጅቶችን የተቀላቀላችሁት በኑሮ ግዴታ፣ በትዕዛዝ፣ በአማራጭ እጦት ሰበብ፣ የሰብዓዊ ተፈጥሮችን አካል በሆነው የመንፈስ ደካማነት ምክንያት እንደሆነ፤ ድርጅታችሁ በሕዝብ ላይ የሚያደርሰው በደል እያያችሁ ህሊናችሁ እንደሚቆስል እናውቃለን። አንዳንዶቻችሁ ውስጣችሁ እያነባ እጆቻችሁ ኢፍትሀዊ ተግባር እንደሚፈጽሙ እናያለን። ኢህአዴግ እንደማፊያ ድርጅት መግባት እንጂ መውጣት የማይቻልበት ሆኖ እንዳገኛችሁት እናውቃለን። “ይህንን ድርጅት ከለቀቅኩ የሚጠብቀኝ እስር፣ አልያም ሥራ ማጣት ነው። ያኔ ምን ይውጠኛል? ትዳሬ፣ ልጆቼ፣ ወላጆቼ እንዴት ይሆናሉ?” የሚል ስጋት እንዳለባችሁ እንገነዘባለን። ህወሓትን በመርዳት ያቆማችሁት ሥርዓት እንኩዋንስ ለሌላው ለእናንተም ከፍርሃት ነፃ ሊያደርጋችሁ አለመቻሉን እናውቃለን። ድርጅታችን አርበኞች ግንቦት 7፣ እናንተ ያላችሁበት አጣብቂኝ ቀላል እንዳልሆነ ይገነዘባል። በዚህም ምክንያት ይህንን ጥሪ ለእናንተ ያቀርባል።

ሀገራዊና ሕዝባዊ ስሜት ያላችሁ፤ ለራሳችሁና ለቤተሰቦቻችሁ ክብር የምትጨነቁ፣ ለልጆቻችሁና ለልጅ ልጆቻችሁ ሎሌነትን  ሳይሆን ክብርን  ማውረስ የምትፈልጉ የኢህአዴግ እና የአጋር ድርጅቶቹ አባላት ሆይ! አባል የሆናችሁባቸውን ድርጅቶች ሳትለቁ፤ ኢህአዴግም ሆነ አጋር ድርጅቶቹ ውስጥ እያላችሁ ለህሊናችሁ፣ ለልጆቻችሁ፣ ለቤተሰቦቻችሁና ለሀገራችሁ የምትሠሩበት መንገድ ተመቻችቶላችኋልና ተጠቀሙበት።

የአገራችን የነፃነት ተጋድሎ ታሪክ እንደሚያስተምረን አርበኝነት ሁለት ዓይነት ነው። አንዱ በገሀድ፣ በግላጭ፣ በውጊያ ሜዳ የሚታይ አርበኝነት ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ፣ በጠላት ጉያ ውስጥ ተኩኖ፣ ጠላትን መስሎ  የሚደረግ አርበኝነት ነው። ሁለተኛው ዓይነት አርበኝነት በተለምዶ  “የውስጥ አርበኝነት” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በተግባርና በውጤት ከአደባባይ አርበኝነት በምንም የማይተናነስ የጀግንነት ሥራ ነው። የውስጥ አርበኛ፣ አርበኛ ነው። የውስጥ አርበኛ ገድሉ  በታሪክ የሚወደስ፣ በአርዓያነቱ የሚጠቀስ የሀገሩ የቁርጥ ቀን ልጅ  ነው።

ህወሓት ለሽብር ጥቃት ተዘጋጅቷል፤ እንጠንቀቅ!


ዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ፣ በሕዝባዊ ኃይሎች ላይ ሊወስድ ያሰበው እርምጃ ተቀባይነት እንዲያገኝለት የሽብር ተግባር ፈጽሞ በአርበኞች ግንቦት 7 ላይ ለማላከክ ወስኗል። እንዲህ ዓይነቱ እኩይ ተግባር ህወሓት ስልጣን ከመያዙ በፊትም በኋላም ሲያደርገው የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ህወሓት እንዲህ ዓይነቱ ኢሰብዓዊና ዘግናኝ ተግባር ለመፈፀም የሚያስችሉ እኩይ ስለልቦና እና ልምድ አለው።

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ በቅርቡ የጀመረው የነፃነት ትግል የፈጠረበት መደናገጥ ለመሸፈንና ንቅናቄውን በኢትዮጵያ ሕዝብና በዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብ ለማስወገዝ ያግዘኛል ብሎ ያመነበት ይህን ዘግናኝ ሴራ ከሳምንት በፊት ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁቱን አጠናቆ የነበረ ቢሆንም በወቅቱ የነፃ ሚዲያ አባላት ደርሰውበት ለሕዝብ ይፋ በማድረጋቸው እንዲዘገይ ተደርጎ ነበር። አሁን በደረሰን መረጃ ደግሞ ሴራው ከበፊቱ በባሰ እና ይበልጥ አውዳሚ በሆነ መጠን ተግባራዊ ለማድረግ የህወሓት “ስውር” መንግሥት ወስኗል። በዚህም ምክንያት ይህ የማስጠንቀቂያ መግለጫ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ በማያሻማ ሁኔታ እንዲገነዘብ የምንፈልገው ሀቅ የሚከተለው ነው። አርበኞች ግንቦት 7 በደረሰው መረጃ መሠረት ህወሓት በሰላማዊ ዜጎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ወስኗል። የእቅዱ ዓላማ ዘግናኝ እርምጃ በንፁሃን ዜጎችና ሕፃናት ላይ በማድረስ “የሽብር ጥቃቶች ሰለባ” ነኝ በማለት የኢትዮጵያ እና የዓለም ዓቀፉ ማኅበረሰብ አዘኔታ ማግኘት ነው። የዩ. ኤስ. አሜሪካ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን የሚጎበኙ መሆኑ ደግሞ ይህንን እቅድ ተግባራዊ የማድረግ ጉጉቱ እንዲጨምር አድርጓል። ስለሆነም ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ በህወሓት የሽብር አደጋ ውስጥ ነች። የቦሌ ዓለም ዓቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ እና ወደዚያ የሚያደርሰው መንገድ፣ የአፍሪቃ ኅብረት ጽ/ቤት እና የአሜሪካ ኤምባሲ ህወሓት በሽብር ጥቃት ዒላማነት ከመዘገባቸው ውስጥ ቀዳሚዎቹ ናቸው።

አርበኞች ግንቦት 7 በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚቃጡ የሽብር ጥቃቶችን መቃወም ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ተባብሮ ያመክናል። ይህ በህወሓት የተደገሰልንን የሽብር ጥቃት ማምከን ይኖርብናል። እኩይ እቅድን አስቀድሞ አውቆ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ አንድ ዓይነተኛ የሽብር መከላከያ ዘዴ ነው። በዚህ ረገድ በአገዛዙ ውስጥ ያላችሁ የሕዝብ ወገኖች ባለውለታዎች ናችሁ።
የእያንዳንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሕይወት መለኪያ በሌለው መጠን ውድና ክቡር ነው። በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ዜጋ የህወሓትን እኩይ ሴራ ተገንዝቦ ራሱን፣ ቤተሰቡንና አካባቢውን ከጥቃት እንዲጠብቅ አርበኞች ግንቦት 7 በጥብቅ ያሳስባል።

Tuesday, July 21, 2015

የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ጉዞ…

ክንፉ አሰፋ

“…ከዚህ በኋላ ህዝብ ሰብስቦ ማውራት ላቆም ነው። ጊዜው ተቀይሯል። ትግል ለደካማ መንፈስ አይሆንም። ትግል መውደቅን ይጠይቃል። ሲወድቁ ግን ለመነሳት መሞከርን ይጠይቃል። ስንወድቅ ልታዩን ትችላላችሁ ስንነሳ ግን ታዩናላችሁ … ” ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ይህንን የተናገሩት የአስመራ ጉዟቸው ከመሰማቱ ጥቂት ቀናት በፊት ነበር። ንግግሩ ለብዙዎች ግርታ መፍጠሩ አልቀረም። ከቀናት በኋላ የኤርትራን ምድር ሲረግጡ “ስንነሳ ግን ታዩናላችሁ…” ማለታቸው ግልጽ ሆነ።

ከምርጫ 97 በፊት ዶ/ር ብርሃኑ በፖለቲካ ስብእናቸው የሚታወቁት ለሰላማዊ ትግል ባላቸው የከረረ አቋም ነበር። በእስር ቤት ሆነው በጻፉት “የነጻነት ጎሕ ሲቀድ፤ …” መጽሐፋቸው ሰላማዊ ትግል ያለውን የሞራል፣ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ የበላይነት ምሳሌ እያስቀመጡ ዘርዝረዋል።

ለዚህም ነበር ከሰላማዊ ትግል ወጥተው “ሁለገብ ትግል” ለማካሄድ ማቀዳቸውን ሲገልጹ ለብዙዎች ድንገተኛ እና አስደንጋጭ የሆነው። የጦርነትን አስከፊ ገጽታ ሲነግሩን የነበሩ እኝህ ምሁር በአንድ ግዜ ወደ ተቃራኒው የትግል ስልት ሲዞሩ ያቀርቡት የነበረው ምክንያት በወቅቱ ብዙዎችን ሊያሳምን አልቻለም። ምክንያቱም አመጽ ወይንም ጦርነት ከባድ ነገር ነው። ገንዘብ እና ግዜን ይበላል። ከሁሉም በላይ የህይወት መስዋእነትን ይጠይቃል። የሰላማዊ ትግሉ ስልቶች ገና በደንብ አልተፈተሹም የሚሉም ጥቂቶች አልነበሩም።

ከአምስት ግዜ ምርጫ በኋላም ህወሃት ሕዝብ ላይ መቀለዱን አላቆመም። በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉትንም ጭራሽ ወደ ጫካ እንዲገቡ፣ አልያም እንዲሰደዱ አማራጭ መስጠት ያዙ። የትጥቁን መንገድ “ጨርቅ ያርግላችሁ” ሲሉም አሾፉ።

የ “ምርጫ 2007″ ውጤት በተሰማ ማዕግስት ከዴንቨር-ኰሎራዶ አንድ የቀድሞ ህወሃት ታጋይ ስልኬ ላይ ደውሎ እንዲህ አለኝ። “ግዜው የኛ ነው። ገና መቶ አመት እንገዛችኋለን። ታዲያ ስንገዘችሁ ዝም ብለን አይደለም። እየረገጥን እንገዛችኋለን…” ሰውየው እኔ እንድናገር እንኳን እድል አልሰጠኝም። ስለምርጫው ውጤት በድረ-ገጾች ላይ የሰጠሁት አስተያየት እንዳበሳጨው ገባኝ። በትግርኛ እና በአማርኛ እያቀላቀለ ተሳደበ። ዘር እና ሃይማኖትን ጭምር እየጠራ ተሳደበ። በትእቢት የተወጠረው ይህ ሰው ሙሉ ስሙን እና አድራሻውን ሳይቀር ይናገር ነበር። “ከፈለግክ ቅዳኝ። ማንንም አንፈራም!” ይል ነበር። እርግጥም ድምጹ በቴሌፎኔ መቅጃ ሳጥን ውስጥ ቀርቷል። ይህንን አጸያፊ ስድብ መልቀቁ ወገን ከወገን ማጋደል ይሆናል በሚል እሳቤም ለግዜው ይዤዋለሁ።

ማንነትን የሚፈታተን፣ ክብርን የሚነካ ንግግር ነው። ስድቡን ሁሉ በትእግስት ከሰማሁ በኋላ አንድ ቃል ብቻ ተናግሬ ስልኩን ዘጋሁት። “ትዕቢት ውድቀትን ትቀድማለች።”

የያዝኩትን ትንሽ መረጃ በመንተራስ ስለሰውየው ማንነት አንዳንድ ነገር ማወቅ ቻልኩ። ሰባት አመት የህወሃት ትግል ውስጥ የነበረ ሰው ነው። ይህ ግለሰብ ዴንቨር ኮሎራዶ ከአመታት በፊት ሲገባ ባዶ እጁን ነበር። አሁን ግን ሚሊየነር ሆኗል። የህወሃትን የተዘረፈ ገንዘብ በዶላር ለማጽዳት ወደ ዴንቨር የሚላኩ ሰዎች ቀጥር ቀላል አይደለም። እየረገጥን ገዝተን፣ እየረገጥን እንዘርፋለን፣ ይህንንም አሜን ብላችሁ ተቀበሉ ነው የሚሉን። ከባዶ ተነስተው መጠን የሌለው ስልጣን እና ገንዘብ ሲያካብቱ፤ በያዙት ነገር ይታወራሉ። ድንቁርና ሲታከልበት ደግሞ ስልጣናቸው ዘለአለማዊ፣ ሃብታቸውም የማያልቅ ይመስላቸዋል።

Obama’s trip to Ethiopia alarms some human rights activists

by Juliet Eilperin and David Nakamura | The Washington Post

President Obama embarks on a trip to Africa this week that includes a controversial stop in Ethiopia, where the authoritarian government has come under sharp international criticism for its handling of political dissent.

The Ethi­o­pia visit has raised hackles among human rights advocates who question the administration’s level of concern about human rights, as it seeks to advance new security and economic goals on a continent where good governance and democratic freedoms often do not top the priority list.

“The decision to go to Ethiopia greatly undermines the stated goals and commitments of this administration when it comes to support for human rights, the rule of law and good governance in Africa and beyond,” said Sarah Margon, Human Rights Watch’s Washington director. “It shows that it ranks priorities and shows that security and development often trump human rights concerns, which is a very short-sighted policy approach.”

Dozens of journalists left Ethiopia last year, saying they faced threats from the government because of the work they do. In April 2014 the government charged seven bloggers known as Zone 9 and three reporters under the country’s anti-terrorism law; a few months later the owners of six private publications were charged under Ethiopia’s criminal code. In early July the government released two bloggers and four journalists, though according to the Committee to Protect Journalists at least a dozen members of the media remain jailed on terrorism charges.

Ethi­o­pia’s ambassador to the United States, Girma Biru, described Obama’s decision to visit his country as “confirmation of the strong relationship that’s been built between the two countries.”

Biru said prosecuting journalists was not evidence of human rights violations. “If a journalist, or a teacher, or a professor, or a farmer is supporting these types of groups to instigate violence, then he should be charged,” he said. “But the fact that he is carrying the name of ‘journalist’ should not save him from being charged on this ground.”

White House aides acknowledge that visits like the one to Ethi­o­pia can bestow a measure of credibility to foreign governments and often use the lure of a presidential visit to win diplomatic concessions from non-democratic and repressive regimes. Obama often meets with members of civil society during his overseas visits, as a way of encouraging independent groups to pursue their goals in the face of government opposition.

Sunday, July 19, 2015

ሊቀመንበራችን ትግል ሜዳ ውስጥ ነው!- መግለጫ

ሐምሌ 12 2007 ዓ.ም.

ህወሓት በኢትዮጵያዊያን እና በኢትዮጵያ ላይ ያሰፈነው ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ እንዲያበቃ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈኑበት የፓለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲመሠረት እና የሀገራችን አንድነት በጠንካራ መሠረት ላይ ለማኖር አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ተገዶ የገባበት የመረረ የአመጽ ትግል መጀመሩን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያዊያን የነፃነት አርበኞች በጀግነትና በጽናት እየታገሉ ነው።

ይህ ትግል በባርነትና በነፃነት መካከል የሚደረግ ወሳኝ ትግል ነው። የዚህ ትግል ውጤት የእኛ የዚህ ዘመን ትውልድ ሕይወት ብቻ ሳይሆን የአገራችንን የወደፊት ታሪክ፤ የልጅ ልጆቻችንን ሕይወት ይወስናል። በዚህም ምክንያት ይህንን ትግል በድል መወጣት ግዴታችን ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ለነፃነት ግድ ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከጎናችን ሊቆም ይገባል።

አርበኞች ግንቦት 7 አመራሩን ሁኔታዎች በፈቀዱ መጠን እና ትግሉ በሚጠይቀው ቦታ እንዲገኙ የሚያደርግ መሆኑ ሲገልጽ ቆይቷል። አሁን ትግሉ በደረሰበት ደረጃ የአመራሩ በትግሉ ሜዳ ውስጥ መገኘት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ሊቀመንበሩን ጨምሮ አመራሩን ወደ ትግሉ ሜዳ አንቀሳቅሷል። በዚህም መሠረት የንቅናቄው ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ ትግል ሜዳ ወርዷል።

ትግሉ መሯል። ወሳኝ የሆነ ትግል ውስጥ ገብተናል። የትግሉ መሪዎች የሕይወት መስዋዕትነት እሚከፈልበት ቦታ ይገኛሉ። በአሁኑ ሰዓት የንቅናቄው አመራር በተሟላ ሁኔታ በትግሉ ሜዳ ውስጥ እንዲገኝ ማድረግ ተችሏል። ኢትዮጵያዊያን እጅ ለእጅ ተያይዘን ዘረኛው የህወሓት አገዛዝን ከጫንቃችን ለማስወገድ ቆርጠን እንድንነሳ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።

ኢትዮጵያን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ የሚያወጣው አርበኞች ግንቦት 7 ብቻ አይደለም። ስለሆነም ከሌሎች ድርጅቶች ጋር የሚደረገው ትብብር ቀዳሚ ትኩረት ከተሰጣቸው ሥራዎች አንዱ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመጽ ለድል እንዲበቃ ይታገላል። ኢትዮጵያዊያንም በያሉበትም በተመሳሳይ ልዩነቶቻቸውን አቻችለው በህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ ላይ ክንዳቸውን እንዲያነሱ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።

A message from Patriotic Ginbot 7: Dr. Berhanu Nega joined his comrades in the ground

Dear Ethiopians:

As you already know, our struggle has reached a crucial milestone in which our comrades have begun paying the ultimate sacrifice in battling the TPLF-led regime in Ethiopia.

Armed struggle was never a method of struggle of our choice. The TPLF-regime has closed all peaceful avenues and has left us with the choice to become enslaved in our home land or to fight by any means necessary.

Therefore, the man who Ethiopians have once peacefully elected as mayor of the capital of Ethiopia, Addis Ababa, Dr. Berhanu Nega, chairman of Patriotic Ginbot 7, has joined his comrades in arms on the ground where the soldiers of Patriotic Ginbot 7 have begun waging the battle to free Ethiopia.

As we have confidence in the victory of good over evil, we have no doubt that Dr. Berhanu Nega and other leaders of our organization will effectively lead our organization and our beloved people to freedom, justice and democracy!

Victory to the Ethiopian people!
Patriotic Ginbot7

Saturday, July 18, 2015

The Ethiopian Justice System Has Collapsed

Dimtsachin Yisema, Washington D.C. Task Force

The state trials of two years long against the members of the Ethiopian Muslims Arbitration Committee, a body delegated by a collective of individual Muslim communities from throughout Ethiopia, concluded with the expected guilty verdict on July 6, 2015, though the ruling had arisen from no basis. The kangaroo court, held under the leash of the ruling regime, has time and time again demonstrated its purpose to be to advance the political agenda of the TPLF instead of the cause of justice. The court shamelessly reached its empty guilty verdict despite the political prosecutor’s failure to produce any tangible evidence supporting the charges against the Arbitration Committee members. However, there was no lack of coached and coerced eye witnesses as well as fabricated and doctored video & audio evidences.

Because of our leaders’ relentlessness in maintaining their innocence and their refusal to relinquish their God-given freedom of religion, they are now prone to the subjugation of a greater deal of unforeseen inhumane treatment. Their support network, however, will continue to stand by them and ensure that justice prevails in the end.

For the last several years, the Ethiopian government has been insisting that Ethiopian Muslims must accept and associate themselves with the Al-Ahbash cult whose main tenets go astray from the fundamental doctrines of orthodox Islam. The government had achieved its goals of infiltrating the Muslim community first by appointing members of the sect to the Islamic Affairs Supreme Council (IASC), then by imprisoning Imams who refused to cooperate and replacing them with Ahbashi political associates. Despite the glaring mountain of evidence, the Ethiopian government has consistently denied the accusation of imposing this sect upon its Muslim population, but its blatant denial has only been an evasive path for them to continue with their despotic interference in the communal affairs of its religious communities.

The Arbitration Committee, a unique delegation composed of religious leaders and scholars, elderly and young alike, as well as intellectuals from different fields, was initially recognized by the Ethiopian government as the genuine representative of the voice of the 40 million Muslims who elected them, as was evident by their engagement in a 7-month long negotiations with the committee prior to turning the tables and reversing its disposition. The purpose of these negotiations was to find a solution to the three demands of the Muslim community which included: 1) Letting the Muslim community elect the their own officers to the IASC; 2) Returning the administration of Awoliya College, the only Islamic higher education institute in Ethiopia, to the Muslim community; and 3) Ceasing the imposition of the Ahbashi ideology on the Muslim community. These demands

አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ ጥቃት የመሰንዘሩ እድምታዎች

እድምታው በወያኔ ጎራ

– ለወትሮው ጭቃ በመትፋት የሚታወቀው የወያኔ ሹማምንት እና ካድሬዎች አንደበት የመኮማተር አዝማሚያ ታይቶበታል። በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ኢትዮጵያውያን አፈናው እና ጫናው በዛብን ሲሉ “መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ” በማለት የሚታወቁት ወያኔዎች የጦርነትን አስከፊነት መስበክ ጀምረዋል።

– ኢትዮጵያን እንደ ሃገር፣ የኢትዮጵያን ታሪክ እንደታሪክ እውቅና ለመስጠት እጅግ የሚጠየፉት ወያኔዎች “እምዬ ኢትዮጵያ” ማለት አብዝተዋል።

– ኤርትራን ከእናት ሃገርዋ ኢትዮጵያ ለመገንጠል፣ ኢትዮጵያን ባህር በር አልባ ለማድረግ ከሻብያ ጋር ተቀናጅተው ኢትዮጵያን ሲወጉ የኖሩት ወያኔዎች ኤርትራ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላት ናት በፍጹም ከኤርትራ ጋር አትነካኩ ሲሉ እየተደመጡ ነው። የወያኔዎቹ ቁንጮ መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት ከኤርትራ ጋር ስላላቸው ግንኙነት ሲጠየቅ “ግንኙነታችን እንደ መርፌና ክር ነው” ማለቱን ራዕዩን የወረሱት ወያኔዎች የአርበኞች ግንቦት 7 ምት አስረስቷቸዋል። ሌላኛው የወያኔዎች ቁንጮ ስበሃት ነጋ “ኤርትራ ጥቃት ቢሰነዘርባት ወያኔ ከኤርትራ ጎን ተሰልፎ ይዋጋል” ማለቱን የአርበኞች ግንቦት 7 ጠንካራ ጡጫ አስረስቷቸዋል።

– ቀደም ሲል ከኤርትራ ባለስልጣኖች ጋር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመነጋገር እንደሚፈልግ ያሳወቀው አሻንጉሊቱ ሃይለማርያም ደሳለኝ አርበኞች ግንቦት 7 ጥቃት በሰነዘረ ማግስት “ኤርትራ አሸግራናለች የኢትዮጵያን ህዝብ አስፈቅደን ጦርነት እንገጥማለን” ብሏል።

– በተለያየ ጊዜ አርበኞች ስለሚፈጽሟቸው ጥቃቶች እውቅና ላለመስጠት ሲል ትንፍሽ የማይለው ወያኔ፣ “አንድ ጊዜ በአካባቢው በመሬት ይገባኛል የተነሳ የነበረ ግጭት ነው” ሲል በሌላ ጊዜ ደግሞ “የሻብያ ተላላኪዎችን ደመሰስኩ” በማለት በተዘዋዋሪም ቢሆን ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር በመፋለም ላይ እንደሚገኙ አምኗል።

የተቃዋሚ ጭንብል በለበሱት ጎራ የአርበኞች ግንቦት 7 ጥቃት የመሰንዘር እድምታ

– ላለፉት በርካታ ዓመታት የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ሃይሎች ውጤት ማስመዝገብ ሲጀምሩ ውዥምብር በመንዛት፣ የሃሰት ከፋፋይ ዜናዎችን በማሰራጨትና የትግሉን ግለት ለማቀዝቀዝ ሙከራ በማድረግ የሚታወቁ ግለሰቦች የአርበኞች ግቦት 7ን ድንገተኛ ጥቃት መሰንዘር ተከትሎ ባልተቀናጀ መልኩ አደባባይ እየወጡና እራሳቸውን እያጋለጡ ይገኛሉ።

Wednesday, July 15, 2015

Why is TPLF releasing some bloggers and journalists now?

Kirubeal Bekele

This is not a difficult question to answer. However, we still need to inform our people why TPLF all of a sudden is freeing a few journalists. The fact that TPLF is releasing them now without the so-called TPLF-style “judicial process”, that TPLF usually claims when arresting and putting journalists on trial, is suspicious.

Their release is good news for their families and to some extent for all of us. But since it does not have any legal basis for their release, it is even more doubtful and may even be more dangerous increasing the likelihood of being arrested again. One reason we know for sure is that TPLF is not releasing the bloggers and journalists because it wants to or as a sign of compromise. Based on our experience, this is unlikely. We and TPLF know each other too well for so long, we can speculate easily why TPLF released them.

There are mainly two or three possible reasons.

President Obama’s visit to Ethiopia

There is a lot of pressure on President Obama from human rights groups and even the US media to stay away from visiting Ethiopia which is well-known for human rights abuses within the country. It is possible Obama may have demanded Ethiopian authorities the release of journalists as a pre-condition to visit Ethiopia. President Obama may have done this to silence his critics and find a face saving way to legitimatize his visit. In addition, President Obama may be looking to get the Ethiopian American votes for the democratic candidate in the upcoming 2016 presidential elections. Right now, it does not look like Ethiopian-Americans will vote for democrats in this election.

ሰቆቃ በማዕከላዊ (በነገረ ኢትዮጵያ)

‹‹እጄን ወደ ላይ አስረው ብልቴ ላይ ሀይላንድ አንጠልጥለውበታል፡፡ ሴቶቹ ሀይላንዱን የሚበቃቸውን ያህል ያወዛውዙታል፡፡ በዚህም ምክንያት ከጥቅም ውጭ ሆኗል፡፡ የዘር ፍሬየን ከጥቅም ውጭ አድርገው ዘሬን እንዳልተካ አድርገውኛል፡፡ ሽንቴንም መቆጣጠር አልችልም፡፡››

አበበ ካሴ

እኔ አበበ ካሴ እባላለሁ፡፡ የሰሜን ጎንደር ተወላጅ ነኝ፡፡ በማዕከላዊ እስር ቤት ከ5 ወር በላይ ታስሬለሁ፡፡ ከዚህ መካከል 4 ወር ከ25 ቀናት በጨለማ ቤት ተቆልፎብኝ ቆይቻለሁ፡፡ ማዕከላዊ በነበርኩበት ወቅት የሁሉም እግርና እጆቼ ጥፍሮች ተነቅለዋል፡፡ አንዳንድ ቀን እጄ ላይ የሆነ ነገር ስለሚወጉኝ ጥፍሮቼ ሲነቀሉ አላውቅም፡፡ ስነቃ ነው መነቀላቸውን የማውቀው፡፡ ከዛም ቁስሉን እየነካኩ ያሰቃዩኛል፡፡ ማደንዛዣ ለምን እንደሚወጉኝ አላውቅም፡፡ ጥፍሮቼን ሲነቅሉኝ ብቻ ሳይሆን ሌላ ጊዜም ራሴን እንድስት ያደርጉኛል፡፡ እጅና እግሬን አስረው እንደ ፍሪጅ ያለ እቃ ውስጥ ያለ በረዶ ውስጥ ያስቆሙኛል፡፡ ለብዙ ሰዓት በጣም ቀዝቃዛ የሆነ ቦታ ላይ እስክደነዝዝ ቆሜ እውላለሁ፡፡ እስኪበቃቸው ከደበደቡ በኋላ እጅና እግሬን አስረው ከምርመራ ክፍሉ በታች በሚገኝ ምድር ቤት ክፍል ውስጥ ያለ ጉድጓድ ላይ ጥለውኝ ይሄዳሉ፡፡ ጉድጓዱ ጉንዳንን ጨምሮ ተባዮች ያሉት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ እግሬንና እጄን አስረው ዘቅዝቀውኝ ይሄዳሉ፡፡ የመጣው ሁሉ ዝዋዥዌ እንደሚጫወት ህፃን ወዲያና ወዲህ ያደርገኛል፡፡ ገልብጠው አስረው ሲዘቀዝቁኝ በአብዛኛው ራሴን እስታለሁ፡፡ እግርና እጄን ከወንበር ጋር ያስሩኛል፡፡

ከወንዶች በተጨማሪ ሴቶችም ይመረምሩኛል፡፡ ሴቶቹ የሚመረምሩኝ ራቁቴን አርገው ነው፡፡ እነሱም ራቁታቸውን ሆነው ነው የሚመረምሩኝ፡፡ አሁን ለመናገር የማልደፈርው አፀያፊ ነገርም ፈፅመውብኛል፡፡ ይህን አፀያፊ ነገር የሚፈፅሙት አደንዛዥ እፅ እየተጠቀሙ ነው፡፡ ይህን ሲያደርጉ በአይኔ አይቻቸዋለሁ፡፡ መርማሪዎቹ ሰውነቴን በኤሌክትሪክ አቃጥለውኛል፡፡ ኤሌክትሪኩን የሚሰኩት ደረቴና የውስጥ እግሬ ላይ ነው፡፡ በዚህም የውስጥ እግሬ ተገልብጦ ሌላ ሰውነት አምጥቶ ነበር፡፡ እጄን ወደ ላይ አስረው ብልቴ ላይ ሀይላንድ አንጠልጥለውበታል፡፡ ሴቶቹ ሀይላንዱን የሚበቃቸውን ያህል ያወዛውዙታል፡፡ በዚህም ምክንያት ከጥቅም ውጭ ሆኗል፡፡ የዘር ፍሬየን ከጥቅም ውጭ አድርገው ዘሬን እንዳልተካ አድርገውኛል፡፡ ሽንቴንም መቆጣጠር አልችልም፡፡ ይህን ያህል አሰቃይተው ከጥቅም ውጭ ስሆን ቂሊንጦ አምጥተው ጣሉኝ፡፡ 11 ወር ያህል አልጋ ላይ ነበርኩ፡፡ በኤሌክትሪክ ግርፊያው ምክንያት ግራ ሰውነቴ ሽብ ሆኖ ነበር፡፡ ግራ እግሬ መንቀሳቀስ አይችልም ነበር፡፡ በምርኩዝ ነበር የምሄደው፡፡ አሁን እያነከስኩ ነው የምሄደው፡፡

በተለይ ማዕከላዊ ውስጥ ይህን ያህል የሚሰቃዩኝ አንደኛ የሚያግዛችሁ አገር ማን ነው በሚል ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ አማራ ክልል ውስጥ እንድትንቀሳቀሱ የሚተባበሯችሁን የብአዴን ባለስልጣናት ስም ተናገር እያሉ ነው፡፡ በሶስተኛ ደረጃ የሚያሰቃዩኝ የት የት ቦታ ነው የሰለጠንከው እያሉ ነው፡፡

እዚህ ቂሊንጦ ከመጣሁ በኋላም ያሰቃዩኛል፡፡ ወጣቶች እንዳይቀርቡኝ ያስፈራሩዋቸዋል፡፡ ማንም ጠርቶ እንዳይጠይቀኝ እየተደረገ ነው፡፡ ጨለማ ክፍል ወስደውም አስረውኝ ያውቃሉ፡፡ እነሱ ደብድበው ከጥቅም ውጭ ካደረጉኝ በኋላ የምደገፍበትን ምርኩዝም ቀምተውኛል፡፡ ‹‹ይህኮ የጦር መሳሪያ አይደለም፡፡ እንጨት ነው፡፡ ለምን ትቀሙኛላችሁ? ደግሞም እናንተ ናችሁ እንዲህ ያደረጋችሁኝ፡፡›› ብያቸው ነበር፡፡ የሚሰሙ ሰዎች አይደሉም፡፡ የታሰርኩበት ክፍል ውስጥ እንድተኛበት የተሰጠኝ ቦታ ሽንት ቤቱ አጠገብ ነው፡፡ ሽንት እየሸተተኝ ነው የምተኝው፡፡ ‹‹ወደ ሌላ ቦታ ቀይሩኝ!›› ስላቸው ‹‹ደግሞ ለአንተ ይህ አንሶህ ነው?›› ይሉኛል፡፡ ያ ሁሉ ድብደባ ደርሶብኝ አልጋ ላይ በነበርኩበት ወቅት ወጣቶቹ ህክምና እንዳገኝ ወደ ሀኪም ቤቱ ወሰዱኝ፡፡ እነሱ ግን ‹‹ለአንተ ህክምና ሳይሆን ጥይት ነበር የሚገባህ›› ብለው መለሱኝ፡፡ እንዲህ እያሉ ለምን እንደማይገድሉኝ ይገርመኛል፡፡
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ልጆችዋ ለእልቂት፣ ለስደት፣ ለግድያ እየተዳረጉ ነው፡፡ በአካልም ሆነ በስነ ልቦና ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ነው፡፡ ዓለም ለሰው ልጅ ምቹ በሆነችት ከዓለም ውጭ ሆነናል፡፡ የመገናር፣ የመሰብሰብ፣ የመደራጀት በአጠቃላይ ሰው የሚያደርጉንን መብቶች ተነጥቀናል፡፡ ከሰው የማንቆጠርበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡ ገዥዎቻችን ህዝብን እየገደሉና ከሰው በታች አድርገው እየገዙም ቢሆን ግን ዓለምን እያታለሉ ነው፡፡ በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ሁሉ የሚደረገው የአንድን ቡድን የበላይነት ለማስፈን መሆኑ ነው፡፡ እንዲጠፋ ሆን ተብሎ ጥቃት የሚደርስበት ህዝብም እንዳለ እያየን ነው፡፡ ግን ኢትዮጵያ የ95 ሚሊዮን ህዝን ሀገር ናት፡፡

Tuesday, July 14, 2015

Ethiopian journalist on fear of returning to prison

By Andrew Harding | BBC News

It’s never an easy decision: Should I interview someone who wants to talk in public, but who knows that a word out of line could mean arrest and imprisonment?

I’ve wrestled with the issue before in Myanmar, also known as Burma, Zimbabwe, Iraq and elsewhere.

Ethiopian journalist Tesfalem Waldyes sat in a hotel in Addis Ababa last weekend, and decided it was necessary to speak out.

“I’m afraid. I’m still scared that I might go back to prison… Maybe today, maybe this afternoon.

“[Journalism here] is a very dangerous job, because there’s this red line that was marked by the government, and we don’t know when we crossed that red line,” he said.

‘Totally absurd’

Last week Mr Tesfalem was unexpectedly released from a remand prison outside the capital, along with four colleagues.

He and eight other bloggers and journalists had been imprisoned for well over a year, facing trial under Ethiopian anti-terrorism legislation – accused of working with forces seeking to overthrow the state.

“It’s totally absurd…. Our work has appeared in newspapers, magazines.

“We are only doing our jobs,” he said, declining to speculate on whether the timing of his release was linked to a big UN development summit being hosted in Ethiopia this week, or President Barack Obama’s visit later in the month.

Sunday, July 12, 2015

በአሜሪካን ሀገር ሎሳንጀለስ ከተማ በአርበኞች ግንቦት 7 ህዝባዊ ስብሰባ ላይ ለትግሉ ማጠናከሪያ ከ37 ሺ ዶላር በላይ መዋጮ ተሰበሰበ

በሎሳንጀለስ ከተማ የአርበኞች ግንቦት 7 ህዝባዊ ስብሰባ በተሳካ መልኩ መጠናቀቁን ከስፍራው የደረሰን ሪፖርት ያመላክታል።

ቅዳሜ ጁላይ 11, 2015 በተደረገው ህዝባዊ ስብሰባ የድርጅቱ አመራር አቶ ኤፍሬም ማዴቦ በአካል እና እንዲሁም ከለንደን አቶ ብዙነህ ጽጌ በስካይፒ በተገኙበት ታላቅና ባይነቱ ልዩ ና የደመቀ ዝግጅት በማድረግ በሎሳንጀለስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወያኔን ለመጣል ለሚደረገው ትግል ህዝባዊ ሃይሉ ህይወቱን እየሰጠ እኛ በገንዘብ የማንረዳበት ምንም ምክንያት በሚል ሀገራዊ ስሜት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ከ37ሺ በላይ የአሜሪካን ዶላር ለአርበኞች ግንቦት 7 አበርክተዋል።

አቶ ኤፍሬም ለተሰብሳቢው ሲገልጹ አርበኞች ግንቦት 7 ታሪካዊ እና ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚፈጠረው ዲሞክራሲያዊ እና ፍትሃዊ ስርአት አርበኞቹ ስለኢትዮጵያ እየተጋደሉ ነው ትግል መራራ ነው። ይህን ወደን ሳይሆን ተገደን እንድንገባ የተደረግንበት የነጻነት የህልውና ትግል ነው። ብለዋል

አቶ ብዙነህ በበኩላቸው ታሪካዊው ጉዞ ተጀመረ እንጂ አልተጨረሰም። የእናንተ ደጀንነት ለኢትዮጵያ ጅግኖች ብርታት ነው። ወቅቱ በወሬ የምንወጠርበት ሰይሆን በስራ እና በተግባር የምንፈተንበት ሰአት ላይ ነን። ትግሉ የአርበኞች ግንቦት 7 እለታዊ ስራ ነው። ኢትዮጵያ ከህወሃት መንጋጋ እስክትላቀቅ ድረስ ስራችን ላይ በማተኮር ተባብረን ወደ ነጻነት የምናደርገው ጉዞ ይቀጥላል። ሲሉ ተናግረዋል።

ሎሳንጀለስ በርካታ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የሚገኙባት ከተመማ ስትሆን ይህ ስብሰባ በአይነቱ ልዩ በርካታ ህዝብ የተገኙበት እንደነበር አዘጋጆቹ ገልጻዋል። ለአካባቢው ህዝብም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ይህ የምናደርገው ስራ ከብዙው ጥቂቱ ነው ሲሉ የቻፕተሩ ተወካይ ተናግረዋል።

የሐይለማርያም ደሳለኝ የጭንቀት ንግግር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋን አስታወሰኝ!!

በቅዱስ ዮሃንስ

ከሰሞኑ የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ሰራዊት የሕወሓትን ጦርን እያርበደበደና ድባቅ እየመታ መሆኑን ተከትሎ  የሕወሓት ሹማምንት የሚይዙት የሚጨብጡት ነገር እንደጠፋባቸው ከተዘበራረቀ ንግግራቸው መረዳት ይቻላል። ከሕወሓት መንደር ትንቅንቁን በተመለከተ አስተያየት ለመስጠት ቀድሞ ብቅ ያለው የጠቅላይ ሚንስትሩ አማካሪ ጌታቸው ረዳ ሲሆን ግለሰቡ ስለሁኔታው ሲናገር "ግንቦት ሰባት የሚባል ድርጂት የለም፤ ምንም ጦርነት የለም፤ ገንዘብ ማሰባሰቢያ አጀንዳ ናት" በማለት የተለመደ የቅጥፈት እምቢልታውን መንፋቱ የሚታወስ ሲሆን የሕወሓቱ ቅጥረኛ ጌታቸው ይህንን ባለ ሳልስት እንኳ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የትንቅንቁን መካረር ያራደው የሕወሓት ቡድን በአሻንጉሊቱ ሃይለማርያም ደሳለኝ አማካኝነት ፓርላማ ሰብስቦ ሕወሓት ‘‘ከሻዕብያ’’ ለሚመጣው ትንኮሳ ተመጣጣኝ እርምጃ ሲወስድ መቀየቱን አስታውሶ ‹‹ ‘’የሻዕብያ’’ መንግስት ይህንን ድርጊቱን የሚቀጥል ከሆነ ህዝብ አስፈቅደን አስፈላጊውን እርምጃ እንወስዳለን›› ሲል ተደመጠ። ትላንት ከትላንት ወዲያ ሲክዱት የነበረውን ሃቅ ዛሬ ውጥረትና ፍርሃት ሲንጣቸው ለአደባባይ አበቃው። በዚህ ሁሉ መተረማመስ ውስጥ ታዲያ የሹማምንቱን ግራ መጋባትና እርስ በእርስ የሚጣረዝ አስተያየት በሕወሓት መንደር የነገሰውን የፍርሃት ድባብ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ሲሆን እኔን ፈጽሞ የገረመኝ ነገር ግን ሕወሓት በአሻንጉሊቱ ሃይለማርያም ደሳለኝ አማካኝነት ያስነገረውና ጦርነቱን ‘’ከሻዕብያ’’ ጋር ለማያያዝና ርካሽ ድጋፍ ከህዝብ ለማግኘት ያደረገው ጉዞ ነው።

በጣም ነው የሚደንቀው። የጠይቅላይ ሚኒስትር ተብየውን ንግግር ሳደምጥ በቅጽበት በአንድ ወቅት የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ የሆነውን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ፍጹም አረመኔያዊ ውንብድ በሆነ መንገድ ከየመን ሰነአ ታፍነው ለጨካኞቹ የሕወሓት ወሮበሎች ተላልፎ መሰጠታቸውን አሰመልክቶ ቃላቸው ለኢሳት የሰጡትን የየአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ሊቀመንበር የዶ/ር ብርሃኑ ነጋን ንግግር አስታወኝ።  ዶ/ር የኢትዮጵያን ፖለቲካ በተለይም የሕወሓትን የማፍያ ቡድን ጠንቅቀው በማወቃቸው ይመስለኛል ብዙ ጊዜ የሚናገሩት ነገር ሆኖ አየዋለሁ። ዶ/ር ብርሃኑ ነገ ከነገ ወዲያ የትጥቅ ትግሉ የመቀስቀሱ ነገር አይቀሬ በመሆኑ እና ትንቅንቁ ሲጀመር ሕወሓት ህዝብን በማደናገር ርካሽ ድጋፍ ሊያገኝበት ይራወጣል ብለው ላሰቡት ነገር ቀድመው ምላሻቸው በቃልመጠይቁ ላይ ሰጥተዋል። ዶ/ሩ በቃለ መጠይቁ ወቅት የሰጡትን ማብራሪያና ጥሪ በተመለከተ በዚህ ሰአት እየሆነ ላለው ነገር ግልጽ የሆነ አቋም እንዲኖረን ይረዳል ብየ ሰለ አሰብኩ ለየኢትዮጵያ ህዝብ ለማቅረብ ወደድኩኝ። ምንም እንኳ ፍርዱ የህዝብ ቢሆንም ከትላንት ጀምሮ ሕወሓት በቅጥረኛው ሃይለማርያም አማካኝነት እያስነፋው ባለው የውሸት ነጋሪት ሕዝብ እንዳይሸውድ ለማሳሰብ እወዳለሁ።

ወደ ዋናው ጉዳይ ስመለስ በቃለ መጠይቁ ጊዜ ከዚህ በኋላ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ጦርነት ቢነሳ ምክንያቱ ምን ሊሆን ይችላል ተብለው የተጠየቁት ዶ/ር ብርሃኑ ምላሻቸውን የሰጡት እንዲህ በማለት ነበር ‘‘ከዚህ በኋላ ለሚንሳው ጦርነት ምክንያቱ ባድመ አይደለም፤ የጦረነቱ ምክንያት አሰብ አይደለም፤ የጦርነቱ ምክንያት ሌላ ነገር አይደለም። የጦርነቱ ምክንያት የወያኔን ስልጣን የሚቀናቀኑ የዲሞክራሲ ሃይሎችን ማጥፋት እንፈልጋለንና ይህንን ለማድረግ ደግሞ እናንተን (የኤርትራ መንግስትን) ማጥፋት አለብን ብሎ የሚነሳ ነው’’ ሲሉ ቁርጥ ያለ መልስ ሰጥተዋል። ዶ/ር ብርሃኑ በማከልም ጦርነቱን በተመለከተ የጥንቃቄ መልዕክታቸውን ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲህ በማለት ነበር ያስተላለፉት፤ ‘‘አሁን የምትዋጋው ያለኀው የውጭ ሃይል ወሮህ፤ የውጭ ሃይል ለመመለስ አይደለም። አሁን የምትዋጋው ያለኅው ላለፉት 23 አመታት በዘር እየከፋፈለ፤ እየረገጠ ሲገዛህ የነበረውን ስርአት አንተን ነፃ ለማውጣት የሚፈልጉ የዲሞክራሲና የነፃነት ሃይሎችን ለማጥፋት እሄዳለው ብሎ  የሚነሳ ጦርነት ነው። ’’

እዛ ጦርነት ላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ከማን ጋይ ይሰለፋል ለሚለው ለእኔ ቅንጣት ታክል ችግር ያለው issue አይደለም። ስለዚህ በምንም መልኩ ሲታይ ይሄ የሚያዋጣ ስሌት ነው ብየ አላማንም በወያኔ በኩል። ግን ወያኔ የሚሰራው ስራ የሚያዋጣውን ስሌት ነው እየወሰደ የሚል ሃሳብ ካቆምኩ ብዙ ጊዜ ነው። ብዙ ለእነሱም ቆምንለት ለሚሉትም ለምኑም ይጠቅማል የሚባሉ ነገሮች ፊት ለፊት እየተነገራቸው እምቢ እያሉ የሃይልና የጉልበትን የዝርፊያን መንገድን ብቻ መስመራችን ብሎ የያዘ ውንበዴ ሃይል ባለበት ሁኔታ ምክንያታዊ መንገድ የቱ ነው ብለህ ልታሰላ አትችልም።

Tuesday, July 7, 2015

የመከላከያ፣ የፌደራል ፖሊስ፣ የልዩ ኃይል እና የሚሊሻ ጦር ሰራዊት አባላት ሆይ! የምትሞቱት ለማን ነው?

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ በረሃ ወርዶ ነፍጥ በማንሳት ወደ ጦርት የገባው ተገዶ ነው፡፡ ያስገደደውም ተፋላሚው ቡድን አሁን በስልጣን ላይ የሚገኘው የህዝባዊ ሓርነት ትግራይ አገዛዝ ነው፡፡ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ አገዛዝ ምን፣ ምን አይነት ግፍ እና በደል እያደረሰ እንደሚገኝና ምን አይነት መንግስታዊ ስርዓት እያራመደ እንዳለ ለእናንተ ለመከላከያ፣ ለፌደራል ፖሊስ፣ ለልዩ ኃይልና ለሚሊሻ ጦር ሰራዊት አባላት መንገር ለቀባሪው ማርዳት ነው፡፡ ምክንያቱም እናንተም የአገዛዙ የግፍ ሰለባ ሌላኛው አካል ስለሆናችሁና ፍዳውን እያየ ከሚገኘው ህዝብ አብራክ ስለተከፈላችሁ የህዝቡ ብሶት ብሶታችሁ ስለሆነ ነው፡፡

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ የሚዋጋው በጉልበት ስልጣን ይዞ በመንግስትነት ስም ኢትዮጵያን እያዋረደ፣ ህዝቧን እየገደለ እያስገደለ፣ እያሰረ፣ እያሰደደ፣ እያስራበ እና እያሳረዘ የሚገኘውን ህወሓት የሚሰኝ ዘረኛ ቡድን በኃይል ደምስሶ ህዝቡን ብቸኛው ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት ለማድረግ በማለም ነው፡፡ አርበኞች ግንቦት 7 ህወሓትን በጥይት በመደብደብ ገድሎ ጉድጓዱን አርቆ በመቆፈር ከቀበረው በኋላ የሽግግሩን ሂደት ከማገዝና የህዝቡ የስልጣን ባለቤትነት በተግባር እንዲረጋገጥ ከማድረግ ውጭ በምርጫ ተወዳድሮ የመንግስት ስልጣን የመያዝ ዓላማ ፈፅሞ የለውም፡፡ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞካራሲ ንቅናቄ ስልጣን የህዝብ እና የህዝብ ብቻ አንዲሆን አንጂ አምርሮ የሚታገለው መንግስት የመሆን ምኞት ኖሮት አይደለም፡፡ በታሪክ እስካሁን ከተደረጉት የነፃነት ትግሎች የአርበኞች ግንቦት ሰባትን ትግል ልዩ የሚያደርገው አንዱና ዋነኛው ጉዳይ ይሄ ነው፡፡

እኛም እናውቃለን፣ የኢትዮጵያ ህዝብም ያውቃል፣ እናንተም ታውቃላችሁ የአገሪቱን ሀብት እየዘረፉ በብልፅግና ላይ ብልፅግና እየተጎናፀፉ፣ ከመኪና መኪና እያማረጡ፣ በዲዛይነር የተሰራ ሱፍና ከረባት እየለበሱ፣ ጮማ እየቆረጡ ዊስኪ እየተራጩ፣ የተንደላቀቀ የቤተ መንግስት ህይወት የሚመሩት የህወሓት ባለስልጣናት ወደ ስልጣን ሲመጡ ምንም የከፈሉት ዋጋ የለም በድሃው የኢትዮጵያ ህዝብ ልጅ ደም እንጂ፡፡ አሁንም ስልጣናቸውን ማስቀጠል የሚፈልጉት የደሃውን ህዝብ ልጅ ለጦርነት በማሰለፍ በእሱ ደም እንጂ እነሱና ዘመድ አዝማዶቻቸው ምንም የሚከፍሉት ዋጋ አይኖርም፡፡

መከላከያ ሰራዊት፣ ፌደራል ፖሊስ፣ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ ሆይ! በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ሞትክ፣ በሶማሊያ ጦርነት ሞትክ፣ ኦጋዴን፣ ጋምቤላ፣ ሚዛን ቴፒ፣ አርማጭሆ... ላይ ደጋግመህ ሞትክ አሁን ደግሞ ትግራይ ክልል ውስጥ እየሞትክ ትገኛለህ፡፡ በአንተ ክቡር ህይወት፣ በአንተ ደምና አጥንት፣ በአንተ ታሪክ... ሊወድቅ የዘመመው የህወሓቶች የስልጣን ደሳሳ ጎጆ ለጊዜውም ቢሆን ተደግፎ ቆሞ አየህ እንጂ ለአንተ፣ ለቤተሰብህ፣ ለአገርህ ኢትዮጵያ፣ ለበቀልክበት ህዝብ ምን አተረፍክ? ባንተ ሞት እነማን ሹመትና ሽልማት እንዳገኙ ኑሯቸው እንደ ተቃና አንተው ራስህ ጠንቅቀህ ታውቀዋለህ፡፡ የምትሞተው አንተ፤ የምትዋረደው አገርህ ኢትዮጵያ፤ የሚረገጠው የወለደህ ህዝብ፤ የምትሞትለት መልሶ እየገደለህ የሚገኘው አንተው ራስህን ነው፡፡

Sunday, July 5, 2015

UN demands release of British activist jailed in Ethiopia amid torture fears

The Foreign Office has pushed for consular access to Andargachew Tsige with no tangible results, since the British citizen was abducted in Ethiopia a year ago

The UN has demanded the immediate release of a Briton held on death row in Ethiopia for more than a year, an intervention that campaigners say exposes Britain’s poor diplomacy towards the case.

Experts from the UN Human Rights Council have advised Ethiopia to pay Andargachew Tsige “adequate compensation” before sending him home to London, an abrupt hardening of its position on the case at a time when Britain pursues a softly, softly approach with no tangible reward.

Internal Foreign Office emails, disclosed for the first time, reveal that even before Tsige was kidnapped and jailed in an unknown location in June 2014, British officials had voiced fears at “the real risk of torture if [Tsige is] returned to Ethiopia”, along with “fair trial concerns”.

An eight-page judgment from the UNHRC’s working group on arbitrary detention handed to Ethiopia suggests such fears have been realised, saying that there is “reliable evidence on a possible situation of physical abuse and mistreatment which could amount to cruel, inhuman and degrading treatment.”

Tsige, 60, a father of three from London, and known to friends as Andy, was arrested in Yemen’s main airport while in transit and forcibly removed to the Ethiopian capital, Addis Ababa.

He is prominent in Ethiopian politics, having been leader of opposition party Ginbot 7, which has called for democracy, free elections and civil rights. The government has accused him of being a terrorist and in 2009 he was tried in his absence and sentenced to death.

Saturday, July 4, 2015

በህወሓት አገዛዝ እየተሰቃዩ ላሉ ወገኖቻችን ደህንነት የሚደረገው ዓለም አቀፍ ጫና ይቀጥል!

ከሣምንት በፊት የብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን የሚመለከት አንድ መግለጫ አውጥቷል። በዚህ መግለጫው፣ አንዳርጋቸው ጽጌ ለአንድ ዓመት ሙሉ መሠረታዊ የሆኑ የታሳሪዎች መብት እንኳን ተነፍጎት ባልታወቀ እስር ቤት የሚገኝ መሆኑ እና በእንግሊዝ ባለሥልጣናትና በቤተሰቦቻቸው እንዲጠየቅ፣ ቋሚ የቆንስላና የህግ ምክር እንዲያገኝ በተደጋጋሚ የቀረበው ጥያቄ በወያኔ አገዛዝ ውድቅ መደረጉ በሁለቱ አገራት መካከል ያለው መልካም ግንኙነት የሚያሻክር መሆኑ ከወትሮው ጠንከር ባሉ ቃላት ገልጿል። አዲስ አበባ የሚገኘው የብሪታኒያ አምባሳደርም እንደዚሁ ከተለመደው ዲፕሎማሲያዊ ለስላሳነት ወጣ ያለ ያለ መግለጫ አዲስ አበባ ውስጥ ለሚታተመው ሪፓርተር ጋዜጣ ሰጥቷል። እነዚህ የሰሞኑ የእንግሊዝ መንግሥት መግለጫዎች በቀና የሚታዩ ቢሆንም የብሪታኒያ መንግሥት ማድረግ ይገባው ከነበረው እና ማድረግ ከሚችለው አንፃር ሲታይ ብዙ ይቀረዋል። የአውሮፓ ኅብረት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ በተደጋጋሚ አንስቷል። የተባበሩት መንግሥታትም የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያያዝ ጉዳይ ምርመራ እንዲደረግበት እንቅስቃሴ ጀምሯል። ከላይ የተዘረዘሩት ኩነቶች፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ያለሟቋረጥ የሚያደርጉት ውትወታ ውጤት እያመጣ መሆኑ ያሳያል። ይህ ጥረት ለወደፊቱም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።

በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ “አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አስልጥኖ አሰማርቷችኋል” ተብለው እንደተለመደው በሀሰት የተከሰሱ ወገኖቻችን “አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚገኙ መከላከያ ምስክር እንዲሆኑን ይታዘዝልን“ ብለው ሲጠይቁ ዳኛ ተብየው “የት እንደሚገኙ የማይታወቁ ሰውን በመከላከያ ምስክርነት ማቅረብ ይከብዳል” ብሎ ሲናገር ተደምጧል። አቶ አንዳርጋቸው ለምስክርነት ይቅረብ አይቅረብ ብይን ሊሰጥበት ቀጠሮ ተይዟል።

አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የነፃነት አርበኛው የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የእስር አያያዝ ሁኔታ ዓለም ዓቀፍ የዲፕሎማሲ አጀንዳ በሆነበት በዚህ ወቅት በህወሓት አገዛዝ በተሾመ ዳኛ “የት እንደሚገኙ የማይታወቁ” መባሉ አሳሳቢ ጉዳይ አድርጎ ይመለከተዋል። አርበኞች ግንቦት 7፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የተከሳሾች፣ የአቃቤ ህጉና የዳኛው ምልልስ ለተባበሩት መንግሥታት፣ ለአውሮፓ ኅብረትና ለእንግሊዝ መንግሥት እንዲደርስ እንዲያደርጉም ያሳስባል።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ብቻ ሳይሆን በህወሓት እስርቤቶችና ከእስር ቤቶች ውጭ ባልታውቁ ቦታዎች ታስረው እየተሰቃዩ የሚገኙ ወገኖቻችን ሁሉ እና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃ የሚወጣው፣ ኢትዮጵያዊያን በሚያደርጉት ሁለገብ ትግል ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል። ስለሆነም ራሳችንን፣ ወገኖቻችንና አገራችን ነፃ ለማውጣት የምናደርገው ትግል ማጠናከር ግዴታችን ነው። እኛ ራሳችን እንጂ ማንም ነፃነታችንን አያጎናጽፈልንም።

Ethiopians say Obama trip will send wrong signal to repressive regime in homeland

by Pamela Constable | The Washington Post

When Barack Obama entered the White House, many Ethio­pian immigrants in the Washington area cheered. When he gave a speech in Ghana in 2009, vowing to promote democracy and human rights across Africa, they were thrilled. But now that Obama will soon visit Ethi­o­pia, many members of the region’s largest African emigre group are up in arms.

Their concern is that his trip later this month — the first by a sitting American president — will send the wrong message and bolster a regime that has intimidated opponents, manipulated elections and sent dozens of journalists to prison.

“Mr. Obama is supporting a dictatorship and giving legitimacy to tyranny,” declared Serkalem Selassie, 39, a refu­gee in Arlington. “Day by day, things are getting worse. There is no freedom to speak, to meet. Anyone who writes can be jailed for associating with terrorism.”

For Selassie, a former newspaper publisher who fled her homeland two years ago and now works at a parking garage, the anger is deeply personal.

Her husband, journalist Eskinder Nega, is in prison serving an 18-year sentence for treason. Selassie was also sent to jail in 2005, and her son Nafkot, 9, was born while she was in custody. She has not been permitted to communicate with her husband in two years.

“No photos, no letters — nothing is allowed,” said Selassie, stylish but haggard-looking. Her son still suffers from his experiences as a young child. “He saw them take his father away in handcuffs and call him a terrorist,” she said. “He kept asking what that meant.”
Obama’s trip will underscore the delicate balancing act of U.S. relations with the Addis Ababa government, a crucial ally in a volatile region that also regularly flouts democratic norms. The ruling party has maintained power for 24 years since the violent overthrow of a Marxist dictator.

U.S. officials have long praised the government in Addis for its success in economic development and food security, its reliability as an ally in the war on terror and its generous supplying of troops for U.N. peacekeeping missions. In turn, the United States sends substantial amounts of aid.

At the same time, Washington has been critical of the country’s poor rights record. The State Department’s human rights report for 2014 included a long list of official abuses, including arrests and jailings without charge, political trials and sweeping use of a 2009 anti-terrorism edict to silence the media.

Wednesday, July 1, 2015

Ethiopia: Respect court rulings and release opposition members

Ethiopian authorities must stop harassing two men and two women linked to the opposition Semayawi (Blue) Party, and immediately release them from detention, Amnesty International said as they were expected to face fresh charges in court today in the capital Addis Ababa.

 “On five separate occasions over the course of the last 10 days, three different courts have ordered the police to release these four people,” said Michelle Kagari, Deputy Regional Director for East Africa, the Horn and Great Lakes. “Their continued detention is blatantly unlawful and in clear violation of their rights to liberty and a fair trial.”

 Woyneshet Molla, Ermias Tsegaye, Daniel Tesfaye and Betelehem Akalework were arrested in April this year and charged with inciting violence during a rally in the capital. They remained in custody awaiting trial. The four were convicted at the Federal First Instance Criminal Court at Kirkos on 22 June 2015 and sentenced to two months in prison. The judge however ordered their immediate release on the basis that they had already served their time, but the police ignored court orders and returned them to Kality and Kilinto prisons.

 They were released the following morning, but police and security officials immediately re-arrested the four without a warrant and brought them to Kasanchiz 6th police station. On 25 June, they were presented on the same charges before the same judge that had ordered their release. He dismissed the case and again ordered their immediate release but the police did not comply and instead unsuccessfully sought to have another judge in the same court accept the case.

 The following day the police brought the four before a new judge at Keraa Federal First Instance Court, on new charges of threatening witnesses to their original case. In a hearing on 30 June the court accepted the case, but ordered that the accused be released on bail pending the case’s resumption today. Again, the police disregarded court orders and the four remain in custody.

 Separately, the Federal High Court Lideta Branch on 29 June accepted to hear the public prosecutor’s appeal against the original verdict, but refused their request to keep the four in custody. The appeal has been adjourned until 3 July.

“This charade must come to a halt. These four men and women have already served their jail term. This blatant disregard for judicial orders, and attempts to press fresh charges amounts to persecution, and takes harassment and intimidation to new heights,”

Said Michelle Kagari, Deputy Regional Director, Amnesty International.