Friday, November 28, 2014

የእስክንድር ነጋ ያገባኛል ባይነት!

በላይ ማናዬ

‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››

ይህን ያለው ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ነው፡፡ እስክንድር ነጋን ካወኩት ወዲህ እንደዛሬ በኃይለ ቃል ሲናገር ሰምቼው አላውቅም፤ ወይም ትዝ አይለኝም፡፡ ዛሬ (ህዳር 19/2007 ዓ.ም) እኩለ ቀን ላይ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሆኖም ሁኔታው ሁሉ እንደማንኛውም ቀን አልነበረም፡፡ በር ላይ ስደርስ በርከት ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት ሰሞኑን እያካሄዱት ያለውን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማስመልከት እስክንድር ነጋን፣ አንዱዓለም አራጌን እና ሌሎችንም ሊጠይቁ በቦታው ተገኝተው ነበር፡፡

በጠዋት ቂሊንጦ የሚገኙ ወዳጆቼን ጠይቄ አብረውኝ ከነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ነበር ወደ ቃሊቲ ያመራሁት፡፡ ቃሊቲ የተገኘው ሰው ሁሉ መጠየቅ የሚፈልገውን ሰው እና ሙሉ አድራሻውን እያስመዘገበ ሳለ በመሐል እኔም እስክንድርን መጠየቅ እንደምፈልግ ነግሬ ተመዘገብኩ፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ግን ስማችሁ ከዚህ ቀደም ያልተመዘገባችሁ አሁን መግባት አትችሉም መባሉን መዝጋቢ ፖሊሱ አረዳን፡፡ እኔ እና ትንሽ ሰዎች መግባት ስንችል አብዛኛው ሰው ግን መግባት እንደማይችል ተነገረን፡፡

በዚህ ሁኔታ እስክንድር ጋር ደርሰን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ አንድ የአንድነት ፓርቲ አባል ሰሞኑን ፓርቲያቸው እስረኞችን በተመለከተ በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ ለእስክንድር ያብራራለት ጀመር፡፡ እስክንድር በተለመደ ጥሞናው ሲያዳምጠው ቆይቶ፣ በግሉ የተሰማውን እና መሆን ቢችል ያለውን ነጥብ ተናገረ፡፡ በመሐል ወጣቱ የአንድነት አባል ወደ እስክንድር ጠጋ ብሎ ሌሎች ተጨማሪ ጉዳዮችን ሲነግረው ድንገት አንድ የፖሊስ አዛዥ ጨዋታቸውን እንዲያቆሙና እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እንዲገባ፣ ወጣቱ የአንድነት አባል ደግሞ ወደ ውጪ እንዲወጣ በትዕዛዝ ማጣደፍ ያዘ፡፡

ይህኔ እስክንድር ለስለስ ባለ አነጋገር ምንም እንዳላጠፋን በመግለጽ ፖሊሱ መረጋጋት እንዳለበት አስረዳ፡፡ የፖሊስ አዛዡ ግን ጭራሽ ብሶበት ወጣቱ በቶሎ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ‹ፖለቲካ ማውራት አቁሙ› የሚል ሆነ፡፡ ይህን ተከትሎ እስክንድር ድንገት በኃይለ ቃል ተናገረ፡፡ ‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው!›› አለ እስክንድር በስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡

Thursday, November 27, 2014

ተማሪዎች፣ መምህራን እና የተቋማት ፕሬዚዳንቶች ለአመጽ ተነሱ!

ዘረኛውና አምባገነኑ የህወሓት አገዛዝ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ከካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከላትነት ለይቶ የማያይ ስለመሆኑ በተቋማቱ ውስጥ የሚደረጉ ተግባራት ማረጋገጫዎች ናቸው። ለዚህ ተግባሩ በሰነድ ደረጃ መቅረብ ከሚችሉት የቅርብ ጊዜ ማስረጃዎች ዋነኛው በህዳር 2007 ዓ.ም. በሥራ ላይ የዋለው “የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢህአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጀት ማንዋል” የተሰኘው በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላለፈው ሰነድ ነው። ይህ ሰነድ፣ የህወሓት አሳፋሪ የትምህርት ፓሊሲ ባፈጠጠ መልኩ የተገለፀበት፤ የኢፌዴሪ መንግሥት ተብሎ በሚጠራው የህወሓት አገዛዝ ተቋም እና በህወሓት/ኢህአዴግ ፓርቲ መካከል ለይምሰል እንኳን ልዩነት አለመኖሩ በግላጭ የሚታይበት ሰነድ በመሆኑ በዚህ ርዕሰ አንቀሳችን በስፋት ልንዳስሰው ወስነናል።

ሰነዱ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ መርዙን መርጨት የሚጀምረው ገና በመግቢያው ስለማንዋሉ አስፈላጊነት ሲገልጽ ነው። ማንዋሉ “ከምንም በላይ የብጥብጥና የሁከት መንስኤ የሆነውን ተማሪ በኢህአዴግ አመራር አባላት እየታገዙ ለመያዝ የሚያስችል ነው” በማለት ህወሓት ተማሪውን የሚመለከተው “ከምንም በላይ በብጥብጥ መንስኤነት” መሆኑ፤ ለዚህ መድሀኒቱ ደግሞ ተማሪውን በኢህአዴግ አመራር አባላት “መያዝ” መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ይገልፃል። ቀጥሎም “በምርጫው ሊፈጠር የሚችለውን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሁከትና ብጥብጥ ለማስቆም በማደራጀት መረጃ ለመጥለፍ አመችነቱ የላቀ እንደሚሆን ታምኖበታል” በማለት መረጃ መጥለፍ የዩኒቨርስቲዎችና የትምህርት ሚኒስቴር ሥራ እንደሆነ አድርጎ ያቀርባል።

የማንዋሉን ዓላማዎች በሚገልፀው ክፍል ደግም “… የከፍተኛ ትምህርት የትምህርት የልማት ሰራዊት ግንባታን ወይም የፓለቲካ ሰራዊት ግንባታ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተደራጀና በተናቀጀ ሁኔታ በማቀጣጠልና በማስቀጠል … ምርጫ 2007 ውጤታማ ለማድረግ እና የኢህአዴግን አሸናፊነት ለማረጋገጥ ነው” በማለት ተቋማቱን የኢህአዴግ የምርጫ መሣሪያ መሆናቸውን፤ ግባቸውም የኢህአዴግ አሸናፊነትን ማረጋገጥ መሆኑ ይገልፃል።

በገጽ 3 ላይ ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች “በኢህአዴግ ላይ ያላቸው አቋም የወረደ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በማንኛውም ተቃውሞ ድምፅ ከተጠሩ፤ ሰልፍ የሚያደምቁ፤ ተቃውሞን ከግብ ለማድረስ ሁነኛ መሳሪያ ናቸው። ተማሪዎች በየትኛውም ሐገር እንደታየው አደባባይን የመያዝ ህዝብን አስተባብረው ለተቃውሞ የማሳደም እድላቸው የሰፋ በመሆኑ ከዚህም ሲያልፍ፤ የኢህአዴግ ምከታን በመቃወም ለጠላት ጎራ ተሰልፈው የመታጠቅ እድላቸው ከፍተኛ ነው” ሲል “በወጣቱ እጠላለሁ” የሚለው የህወሓት/ኢህአዴግን ስጋት አፍረጥርጦ ያወጣል። ትንሽ ወረድ ብሎ ደግሞ “በተለይ በአሁኑ ሰዓት ፈተና ላይ የጣለን የምርጫ ጉዳይ እንደምናሸንፍ ቃል የተያዘለት ቢሆንም፤ ፈተናዎች የሚፈጠሩት በህዝብ እና በራሱ ታማኝ ባልሆኑ ሃይሎች ማለትም በመንግስት ክንፍ አይቀለበስም ብሎ ማሰብ አይቻልም። በዚህም ቀድሞ መዘጋጀት ያለበት እና ለሁከት እና ለብጥብጥ መሳሪያ ሊሆን የሚችለው የህዝብ ክንፍ የተማረው ሃይል ሊሆን ስለሚችል ሊታሰብበት ይገባል” ሲል በተማረው ወጣትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሠራተኞች ላይ ያለው ጥርጣሬና ፍርሃት ምን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ይገልፃል።

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለአዳሩ ሰልፍ የእውቅና ደብዳቤ አስገባ


• ቦታው መስቀል አደባባይ እንዲሆን ወስኗል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ከህዳር 27/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28/2007 ዓ.ም ለሚደረገው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ለአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የእውቅና ደብዳቤ አስገባ፡፡

ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የገባው ደብዳቤ በሰማያዊ፣ መኢዴፓ እና ኢብአፓ ተፈርሞ የገባ ሲሆን የእውቅና ደብዳቤውንም ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ ሊቀመንበር፣ የከንባታ ህዝቦች ሊቀመንበርና የትብብብሩ ም/ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርጌሎ፣ አቶ ግርማ በቀለ ከኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና የትብብሩ ፀኃፊ እና የመኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ ገንዘብ ያዥ አቶ ኑሪ ሙደሲር አስገብተዋል፡፡

የትብብሩ አመራሮች ወደ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍሉ በሄዱበት ወቅት የአቶ ማርቆስ ተወካይ ለሆኑት አቶ ፈለቀ አበበ ደብዳቤውን ለመስጠት ጥረት ቢያደርጉም ተወካዩ ‹‹የከንቲባ ጉዳዮች ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው የለም፡፡ እሱ ካልመራበት መቀበል አንችልም›› በሚል ደብዳቤውን አልቀበልም እንዳሏቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ ወደ አቶ አሰግድ ቢሮ ቢያቀኑም እንዳላገኙዋቸው ጨምረው ገልጸዋል፡፡

Wednesday, November 26, 2014

ማስፈራራትና አፈና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችንና ሠላማዊ ሕዝባዊ የለውጥ ንቅናቄዎችን አይቀለብስም !!

ከ9ኙ ፓርዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ

የኢተፖፓ ትብብር አባላት በደረስንበት ስምምነት መሠረት የአጭር ጊዜ የጋራ ዓላማችንን ማስፈጸሚያ ተግባራት የመጀመሪያ ዙር ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል መርህ የአንድ ወር ዕቅድ አውጥተን ወደ ሥራ እንደገባን በገዢው ፓርቲ/መንግሥት ለ07/03/07 በታቀደው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ የዕውቅና ጥያቄ ሂደትና በዕለቱ የተፈጸመውን ሴራ በሚመለከት ‹‹በቢሮክራሲያዊ ሴራ የዜጎችን ህገመንግሥታዊ መብት ማፈን ሠላማዊ ትግሉን አያቆመውም //›› በሚል ርዕስ ሕዳር 08 ቀን 2007 ዓ.ም. ባወጣነው መግለጫ የድርጊቱን ህገወጥነትና ኢህገመንግሥታዊነት አሳይተን ለባለድርሻ አካላት አፍራሽ አካሄዱ እንዲስተካከልና ለዚህ ከምናደርገው ሠላማዊ ትግል ጎን እንዲቆሙ ጥሪያችንን ማስተላለፋችን ይታወሳል፡፡ በመቀጠልም ዕቅዳችንን በመከለስ የቀጣይ ተግባራት ዝግጅታችንን ጀምረናል፡፡ በዚሁ መሰረት ለ21/03/07 ላቀድነው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በ10/03/07 በአባል ድርጅታችን የመላው ኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ/መኢዴፓ/ አማካኝነት የዕውቅና ጥያቄ ደብዳቤ ይዘን በአካል ብንቀርብም ሁለት ቀን አመላልሰውን በመጨረሻ የአዲስ አበባ መስተዳድር የከንቲባ ጽ/ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው ይመኑ ደብዳቤኣችንን ለመቀበል ፈቃደኛ ያለመሆናቸውን ከመግለጽ አልፈው ‹‹የአብዬን እከክ ወደ እምዬ…››እንዲሉ ቢሮኣቸው ደብዳቤውን አስቀምጠን ስንወጣ ወንጀል ነው በማለት ለማስፈራራት ሞክረዋል፡፡

ባለፈው ሣምንት በተፈጸመብን ሴራ ያለመንበርከካችንን ከቀረበው ደብዳቤ የተረዱ የሚመስሉት እኚሁ ባለሥልጣን በቀጣዩ ቀን(12/03/07 ዓ.ም) የባለፈውን የአደባባይ ስብሰባ እንዲያስተባብር ኃላፊነት በሰጠነው ሰማያዊ ፓርቲ ላይ ‹‹ማስጠንቀቂያ›› በሚል ለተጨማሪ ማስፈራሪያ ደብዳቤ ጽፈዋል፡፡ይህ ዛሬ በወህኒ የሚገኙ በሽብርተኝነትና ህገመንግሥት በመጣስ በሚል የታሰሩ የፓርቲ አመራሮችና አባላት፣የኃይማኖት መሪዎች፣ጋዜጠኞች ፣ብሎጌሮች፣ከገዢው ፓርቲ የተለየ አመለካከት ያላቸውን ዜጎች በመፈረጅ ለማሰር፣ ማሰቃት… የተከደበትን ስልት፣ዛሬም በእኛም ሆነ ሌሎች ላይ እየተሞከረ ያለውን የማስፈራራትና የማሸማቀቅ ሙከራ ከሚያስተውሰን በቀር በህጋዊና ሠላማዊ ትግላችን የሚፈለገውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ስለተዘጋጀን የሚፈራ አልተገኘም፣ ከቁብ አልቆጠርነውም፡፡

በዚያው ዕለት(12/03/07 ዓ.ም) በአካል ተገኝተን አንቀበልም የተባልነውን ደብዳቤ በመንግሥታዊው የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በፈጣን መልዕክት አገልግሎት/ኢ.ኤም.ኤስ/ በቁጥር eg156846735et ብንልክም የቱም የመስተዳድሩ አካል ደብዳቤውን ለመቀበል ፈቃደኛ ያለመሆኑ በ16/03/07 ከፖስታ አገልግሎቱ ተገልጾልናል፡፡ ይህ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 12 የተቀመጠውን ‹‹የመንግስት አሠራር ተጠያቂነት›› የጨፈለቀ ድርጊት በተገለጸልን ተመሳሳይ ጊዜ ደብዳቤውን የጻፈው የመላው ኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ/መኢዴፓ/ ሊቀመንበርና የትብብሩ ፋይናንስ ኃላፊ (ደብዳቤውን ሲያቀርቡ አንቀበልም የተባሉት) አቶ ኑሪ ሙዴሲር ‹‹ በመኪና ተገጭተው መደባደብ በሚችሉ ጀግና›› እና ግብረ-አበሮቻቸው ተደብድበው በአካላቸው ሦስት ቦታዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ይህ ትናንት በአቡበከር ላይ የተሞከረውን ተመሳሳይ የፈጠራ ውንጀላና ክስ የሚያስታውሰን ሲሆን ክሱ የማያዋጣ መሆኑ ሲታወቅ ‹‹ ተገጭቶ የሚደበድብ›› ወሮበላ ወደማሰማራት መሸጋገሩን ያረጋግጣል፡፡ እነዚህ ድርጊቶች በገዢው ፓርቲ/መንግስት የሚፈጸሙ ከተለመዱ የፈጠራ ውንጀላ፣እሥራት፣ድብደባ … የፍርኃቱ እርከን ወደከፋ ደረጃ መሸጋገሩን ከማረጋገጣቸው በተጨማሪ ቀጣይ ትግላችን የሚጠይቀውን ከፍተኛ መስዋዕትነት ያመለክታሉ እንጂ የህዝቡን የለውጥ ፍላጎትና ለዚያ የሚደረገውን ትግል አፍነው አያቆሙም ፣ለውጡን አያስቀሩትም፡፡ ትብብሩን ከትግሉ እንዲያፈገፍግ አያደርጉም፡፡

Tuesday, November 25, 2014

እስክንደር ነጋ አሸባሪ ከተባለ ጆን ኬሪና አል ባራዴየም አሸባሪዎች ናቸው ማለት ነው!

 በግርማ ካሳ

በየትም የሰለጠነው አለም እንደሚደረገው፣ በአገርና በሕዝብ ላይ ችግር የሚፈጥር ወንጀለኛ መያዝና መቀጣት አለበት። ሕግ መከበር አለበት። ይሄ ብዙ አያከራክረንም። ነገር ግን «ሕግ፣ ሕግ» እየተባለ፣ ፍጹም ሕገ ወጥ የሆኑ ተግባራት፣ ሕግ አስከባሪ ነን በሚሉ የሕወሃት/ኢሕአዴግ ገዢዎች እየተፈጸመ መሆኑን ነዉ አጥበቀን የምንቃወመዉና የምናወግዘው። የምንታገለውም። ሕግ ሁላችንንም በእኩልነት የሚዳኝ መሆኑ ቀርቶ፣ ጥቂቶች እንደፈለጉ የሚገለባብጡት፣ የመጨቆኛ መሳሪያ በትር መሆኑ ነዉ እያሳሰብን ያለው።

በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በተደረገ ስብሰባ ላይ «እንችላለን! በሌሎች የአፍሪካ ሃገሮች እንደሚቻል አይተናል። ኢትዮጵያ ከእነሱ ቢያንስ ቢያንስ አታንስም። ታሪክ እንስራ!» ሲል እስክንደር ነጋ ተናግሮ ነበር። በተለያዩ ድህረ ገጾች ላይ ይሄንን አቋሙን ሳይፈራ በግልጽ አስፍሯል። እንግዲህ በግብጽ የታየውን እንቅስቃሴ መደገፉ ነው ሽብርትኛ አስብሎ ወደ ወህኒ ያስወሰደው።
«እስክንደር፣ በግብጽ የተከሰተዉ በኢትዮጵያ እንዲከሰት መፈለጉና በዚያ ዙሪያ መንቀሳቀሱ በምን መስፈርትና ሚዛን ነዉ ሽብርተኘንት ተደርጎ ሊወሰድ የሚችለው ? » በሚለው ላይ አንስተን ትንሽ እንበል።

በግብጽ የነበረው እንቅስቃሴ ፍጹም ሰላማዊ የነበረ እንቅስቃሴ ነዉ። ከዚህ እንቅስቃሴ መሪዎች መካከል የነበሩ አንዱ ዶክተር ሞሃመድ አል ባራዴ ይባላሉ። በተባበሩት መንግስታት የአለም አቀፍ ኑክሊያር ኤጀንሲ ሰብሳቢ ሆነው ለበርካታ አመት ያገለገሉ የተከበሩ ሰው ናቸው። እንደ ሳዳም ሁሴን የመሳሰሉ ሽብርተኛ መንግስታት ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች በማከማቸት ለአለም ስጋት እንዳይፈጥሩ የታገሉ፣ የሰላም ሰዉ ናቸው። እኝህ ሰውና የሚመሩት ድርጅታቸው እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር በ2005 የሰላም ኖቤል ተሸላሚ ሆነዋል። ታዲያ ሰላማዊ በሆነ መልኩ፣ አምባገነኑ የሙባረክ መንግስት ለሕዝብ ፍቃድ ተጠያቂ እንዲሆን፣ የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ፣ መታገላቸው እኝህ የሰላም የኖቤል ተሸላሚን ሽብርተኛ ያደርጋቸዋልን ?

በአዲስ አበባ ጆን ኬሪ፣ ሃርድ ቶክ ቢቢሲ ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተማሪዎች ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሰጥተው ነበር። የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ቴዎድሮስ አዳኖም በዚያ ነበሩ። ጆን ኬሪ ንግግራቸውን ሲጀመሩ የተናገሩትን ማንሳት እፈልጋለሁ። በግብጽ ስለነበረው ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሽብርተኘንት ብሎ ስለሚጠራዉ፣ እንቅስቃሴ ሲናገሩ የሚከተለዉን ነበር ያሉት፡

«…the greatest concern has to be the lack of the fulfillment by governments in many countries, of the aspirations of people. Particularly the creation of jobs, and tሀ educational opportunities that are needed, for this modern world….In Egypt, that was not a revolution that was moved by Islamism, or any ideology ….It was young people.. ..it was you ..people who came to the square , and twitted each other , texted each other , e-mail each other and brought people»

Monday, November 24, 2014

30 ደቂቃዎችን በዝዋይ እስር ቤት (ግዞት)

‹‹በብርቱ ታምሜያለሁ›› አበበ ቀስቶ

በላይ ማናዬ

ዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በቦታው ተገኝቼ ለመጠየቅ እቅድ ከያዝኩ ረዘም ያሉ ቀናት አልፈዋል፡፡ እንዲያውም ጉዞው ከወዳጆቼ ጋር ሰብሰብ ብለን ቢሆን እንደሚመረጥ ተነጋግረንበት ነበር፡፡ ሆኖም ግን የዕለት ከዕለት ሩጫችን አላወላዳ ብሎን ባቀድነው ጊዜ ወደ ዝዋይ መጓዝ ሳንችል ቆይተናል፡፡ አርብ ህዳር 12/2007 ዓ.ም ግን እንዳሰብነው ሰብሰብ ብለንም ባይሆን በመጨረሻ አብሮኝ ከተጓዘው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ባልደረባ ወጣት ፍቅረማርያም አስማማው ጋር ከአዲስ አበባ በጠዋት ተነስተን ወደ ዝዋይ አምርተን ለ30 ደቂቃዎች ያህል የናፈቅናቸውንና የናፈቁንን እስረኞች ልንጎበኝ በቅተናል፡፡

ዝዋይ ለመድረስ ከ2 ሰዓት በላይ ጉዞ ማድረግ ነበረብን፤ በጠዋት ቃሊቲ መነሐሪያ በመገኘት የዝዋይን ትራንስፖርት ለመያዝ ስንገኝ መልካም አጋጣሚ ተከሰተ፡፡ አጋጣሚው እኛ ወደምንሄድበት ዝዋይ እስር ቤት ሊሄዱ የተሰናዱትን የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም እና ሌላ የስራ ባልደረባውን ያገናኘ ነበር፡፡ ቁጥራችን መጨመሩ ለእኛም ለምንጠይቃቸው እስረኞችም መልካም ነበር፡፡

ከተማዋ እንደደረስን ወደ አንድ አብረውኝ የተጓዙት ወዳጆቼ የሚያውቁት ቤት አመራን፤ ቡና በፔርሙስ ለመያዝ፡፡ ‹‹ተመስገን ደሳለኝ በእጅጉ ቡና ይወዳል አለኝ›› ታናሽ ወንድሙ፡፡ ቡናውን አስቀድተን ከከተማዋ ትንሽ ወጣ ብሎ ወደሚገኘው እስር ቤት አመራን፡፡ ጉዞው ደግሞ በጋሪ ነበር፡፡ ወደእስር ቤት የሚወስደው መንገድ እጅግ አቧራማ በመሆኑ ተጓዦች አቧራውን መልበሳቸው እሙን ነው፡፡ በእግር ለመጓዝ የፈቀደ ካለ ድልህ ቲባን በጫማዎቹ ልክ ይዋኝበታል፡፡ የእኛ ጉዞ በጋሪ ቢሆንም ከአቧራው ማምለጥ ግን አይቻልም፡፡

እስር ቤቱ በር ደርሰን ከጋሪ እንደወረድን ወደጥበቃዎቹ ቀርበን የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስም ሰጥተን የእኛን ሙሉ አድራሻ አስመዘገብን፡፡ የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስናስመዘግብ ‹‹ምኑ ነህ?›› የሚለው ጥያቄ ይነሳል፡፡ ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…እያልን አስሞላን፡፡ መዝጋቢ ፖሊሶቹ ቀና እያሉ በጥያቄ ያዩናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ወገኖች ‹ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…› ተብለው እንጂ ሌላ በምን ይገለጻሉ ታዲያ! በዚህ መሰረት የአራት እስረኞችን ስም አስመዘገብን፤ እነሱም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ናቸው፡፡ ጥብቅ ፍተሻውን አልፈን ልናያቸው የጓጓንላቸውን እስረኞች ወደምንገናኝበት ቦታ አመራን፡፡

ታሪክን ማደብዝዝም ማጥፋትም አይቻልም!

በአለማችን በተለይ አፍሪካ ዉስጥ የአገርን ብሄራዊ ኃብት የሚዘርፉ፤የህዝብን መብት የሚረግጡና አገርን እነሱ ባሰኛቸዉ አቅጣጫ ብቻ ይዘዉ የሚነጉዱ አያሌ ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት አሉ። እነዚህ ህዝብን የሚበድሉ መንግስታት ሁሉም በጥቅሉ አምባገነን ይባሉ እንጂ በመካከላቸዉ ጎላ ብሎ የሚታይ ትልቅ ልዩነት አለ። ሀኖም የቱንም ያክል ልዩነት ቢኖርም እንደ ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች እንመራዋለን የሚሉትን ህዝብ የሚንቁና የኛ ነዉ የሚሉትን አገር የሚጠሉ አምባገነን መንግስታት የሉም፤ በታሪክም ኖረዉ አያዉቁም። አምባገነን መንግስታት የስልጣን ዘመናቸዉን ለማራዘምና ከስልጣን ጋር ተያይዞ የሚመጣዉን ክብር፤ ዝናና ጥቅማ ጥቅም እንዳይቋረጥ ሲሉ የሚቃወማቸዉንና ለስልጣን ዘመናቸዉ አደጋ ነዉ የሚሉትን ሁሉ ያስራሉ፤ ይደበድባሉ ወይም ይገድላሉ። እነዚህን ነገሮች የወያኔ መሪዎችም ያደርጋሉ፤ ነገር ግን በወያኔና በሌሎቹ አምባገነን አገዛዞች መካክል እጅግ በጣም ትልቅ ልዩነት አለ። ለምሳሌ ወያኔዎች ዘረኛ አምባገነኖች ናቸዉ፤ የወያኔ መሪዎች ኢትዮጵያን እንደ ጥገት ላም አንጂ እንደ አገራቸዉ አይመለከቱም። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያን፤ ህዝቧንና ታሪኳን ይንቃሉ፤ ያንኳስሳሉ።

ባለፉት አምስትና ስድስት አመታት በግልጽ እንደተመለከትነዉ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ገበሬ ከመሬቱ አፋናቅለዉ ለምለም መሬቱን ለባዕዳንና ለህወሓት የጦር መኮንኖች ሰጥተዋል። መሬቴንና ቤቴን አልለቅም ብሎ የተቀናቀናቸዉን ደግሞ በጅምላ ገድለዋል። በከተሞች ዉስጥም ከተሜዉን ምንም ካሳ ሳይከፍሉት ዕድሜ ልኩን ከኖረበት ቤቱ እያፈናቀሉ ከነቤተሰቡ ሜዳ ላይ ጥለዉት መሬቱን ባለኃብት ለሚሏቸዉ የወያኔ ባለሟሎች ሰጥተዋል። በአጠቃላይ የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ አንድነት፤ በታሪኳና በህዝቧ ላይ እንዲህ ነዉ ተብሎ ለመናገር የሚዳግት ትልቅ በደል ፈጽመዋል። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በእናት አገራችን ላይ ያደረሱት በደል ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለምና ዛሬ ወደዚያ ዝርዝር ዉስጥ አንገባም፤ ዛሬ ትኩረት የምንሰጠዉ ወያኔ ደግሞ ደጋግሞ ከዘመተባቸዉና ሙሉ ኃይሉን ካሳረፈባቸዉ የአገራችን እሴቶች አንዱ ታሪካችን ነዉና የዛሬዉ ቆይታችን በዚሁ በታሪካችን አካባቢ ይሆናል።

ታሪክ በአንድ አገር ዉስጥ እያንዳንዱ ትዉልድ ከሱ የቀደመዉ ትዉልድ በግል፤ በቡድንና በማህበረሰብ ደረጃ የተጓዘበትን መንገድ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ካለፈዉ የምንማርበትና የወደፊቱን ጉዟችንን ለመጀመር በመረጃነት የሚያገለግለንን እዉቀት የምናገኝበት የጥበብ ድርሳን ነዉ። የማንም አገር ታሪክ ዉብ ሆኖ የሚያምርና የማያምር ሁለት ገጽታዎች አሉት፤ የማያምረንን የታሪክ ጠባሳ ወደ ኋላ ሄደን ማከም በፍጹም እንደማንችል ሁሉ የወደፊቱን ታሪካችንንም የብዙ ማህበረሰባዊ መስተጋብሮች ዉጤት ነዉና ያሰኘንን ቅርጽና ይዘት ልንሰጠዉ አንችልም። የታሪክ ዋናዉና ትልቁ ቁም ነገር የታሪኩ ባለቤት የሆነዉ ማህብረሰብ እራሱን ወደ ኋላም ወደ ፊትም የሚመለትበት መስኮት መሆኑ ነዉ። ምንም አይነት ታሪክ የሌለዉ ህብረተሰብ የለም፤ ካለም ከየት አንደመጣና ወዴት አንደሚሄድም አያዉቅም።

አገራችን ኢትዮጵያ ረጂምና ጥንታዊ ታሪክ ካላቸዉ ጥቂት አገሮች ዉስጥ አንዷ ናት። ይህ ረጂም ታሪካችን ደግሞ አንገት ቀና የሚያስደርግ የድልና የገድል ታሪክ አንደሆነ ሁሉ አንገት የሚያስደፋ የግፍና የበደል ታሪክም አለበት። የዛሬዉ ትዉልድ ኢትዮጵያዊ ካለፈዉ ታሪኩ ከበደሉም ከገድሉም ተምሮ የወደፊት አካሄዱን ከሞላጎደል መቆጣጠር የሚችል እድለኛ ትዉልድ ነዉና አባቶቹ ባቆዩለት ታሪክ ሊኮራ ይገባል። አንድ ህዝብ በታሪኩ እንዲኮራ ደግሞ ታሪኩ በተደጋጋሚ ሊነገረዉ ሊተረክለትና በጽሁም መልክትም በገፍ ሊቀርብለት ይገባል። የአገራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ለዚህ የታደለ አይደለም ፤ ምክንያቱም እንመራሀለን የሚሉት መሪዎቹ ታሪኩን የሚያንቋሽሹና የሚንቁ መሪዎች ናቸዉ።

Friday, November 21, 2014

መምጫውን የማያውቅ መድረሻውን ያጣል

ታሪክ ለሰው ልጅ ስሩና መሠረቱ ነው።ታሪኩንና መምጫውን የማያውቅ ህዝብ መድርሻውን የማያውቅና ራሱንም ለባርነት አሳልፎ የሰጠ ይሆናል፡፡ ለክብሩ ለእርሱነቱ ለህብረቱና ለነፃነቱ ፀንቶ መቆየት እና የጥንካሬውና ተሳስሮ የመዝለቂያው ሰንሰለት ታሪኩ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የአሜሪካ ባርያ ፈንጋዮች ትናንት በገፍ ከአፍሪካ በባርነት ያመጡዋቸው አፍሪካውያን አንድ ቀን በአንድ ቆመውና በህብረታቸው ጠንክረው ራሳቸውን ነፃ ለማውጣት እንዳይነሱ ሀ ብለው የነጠቋቸው ማንነታቸውን፤ ታሪካቸውንና መገኛቸውን ነበር፡፡ እንደ እቅዳቸውም እነሆ ዛሬ አብዛኛው ጥቁር አሜሪካዊ እኔ ማን ነኝ? መምጫዬስ ከወደየት ነው? በሚሉና በመሳሰሉ ጥያቄዎች ተተብትቦ ለምላሹ ሲውተረተር መገኘቱ፤ እንዲሁም ዛሬም ከተገዢነት መንፈስ ራሱን አላቆ በሁለት እግሩ ለመቆም ሲታትር ይገኛል፡፡

ሌላው የኢጣልያ ወራሪን ሀይል ቅስም የሰበረውና በአለም አቀፍ ደረጃ ቅሌት ያከናነበው የአድዋ ጦርነት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ቅሌት በደም አጥቦ ሀያልነቱን ለአለም ለማሳየት በሞከረበት ሁለተኛው ወረራ ወቅት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የአድዋ ጦርነት የመሩት የአፄ ሚንሊክ ሀውልትን ከጥልቅ ጉድጓድ መቅበር እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ባጠቃላይ አንድ ህዝብ እንደ ህዝብና ሀገር ጠንክሮና በነፃነት ኮርቶ ለመኖር ብሎም ከትውልድ ትውልድ መሸጋገር መቻል ከማረጋገጫው አንዱ የትናንት ማንነቱና የመገኛ ታሪኩ መሆኑን ከላይ በምሳሌነት ያነሳናቸው ነጥቦች ያረጋግጣሉ፡፡

ታሪክ ለአንድ ህዝብ የማንነቱ መገኛ፤ የመገኛው ምንጩና መምጫውን የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን የነገ መዳረሻውን የመመልከቻ መነፅርና ጠንክሮ የመንቀሳቀሻው ጉልበቱ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ መሳሪያ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ አንድ ህዝብ ታሪኩ ከጠፋ ሊገጥመው የሚችለው ችግርና ፈተና እንዲህ በቀላሉ የሚገመት ያለመሆኑንና እንደ ህዝብ እንደ ሀገር ቀጣይነቱን በቀላሉ መፍትሄ ከማይገኝለት ፈተና ውስጥ ይከተዋል ማለት ነው፡፡

ኢትዮጵያችን ዛሬ ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ ህልውናዋ አደጋ ላይ የወደቀበት መሆኑ ለማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ባለፉት 23 አመታት በዘረኞቹ የወያኔ ጉጅሌዎች እጅ ከወደቀችበት እለት ጀምሮ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆኑ የታሪካችንና የባህልችን ዋና ዋና እሴቶች ዋነኛ ኢላማ ሆነዋል፡፡ ይህንንም በተደጋጋሚና በግልፅ ከወያኔው መሪ እስከ ተራ ደጋፊው የሚወረወረው በትር ያረጋግጣል፡፡ ጉጅሌዎቹ የነፃነት ምልክት የሆነውንና በዕልፍ አዕላፋት ደም መሥዋዕትነት ፀንቶ የቆየውን ሰንደቅ ዓላማ በሶ መጠቅለያ ጨርቅ ከማድረግ ጀምረው ዛሬ በምሁራን ጥረትና በእያንዳንዱ ዜጋ ድጋፍ የተሰባሰቡት የታሪኮቻችን መዛግብት በጥንቃቄ ከተቀመጡበት (ቤተ-መዛግብት) እያወጡ ከማውደምና ለስኳር መጠቅለያነት እስከ መሸጥ ደርሰዋል፡፡

Thursday, November 20, 2014

ምርጫ ሲባል አማራጭ ሳያሳጡ መሆን ይኖርበታል!!!

                                  አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
              UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

                         ምርጫ ሲባል አማራጭ ሳያሳጡ መሆን ይኖርበታል!!!

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
...
በሀገራችን ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ጊዜ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚደረግ በመንግስት በኩል በከፍተኛ ደረጃ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት የተከናወኑት አራት ምርጫዎች ያየን እንደሆነ በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ወደፊት ሊወስዱ እንዳልቻሉ እሙን ነው፡፡ ይህም ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት በተለያየ መንገድ ሲገልፅ ቆይቷል፡፡ በተቃራኒው መንግስትና ገዢው ፓርቲ በፍፁም መለየት በሚያስቸግር ሁኔታ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ሆነው ተቀናጅተው ለአንድ ለአውራ ፓርቲ ግንባታ እየሰሩ እንደሆነ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህ የመንግሥትና የገዢው ፓርቲ ተግባር ምርጫን ያለ አማራጭ እንዲሆነ እያደረገው እንደሆነ ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡

በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ አባላት ላይ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ዘመቻ በሚባል ደረጃ እየተካሄደ ያለው አፈናና እስር፤ ከዚህም ባሻገር ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ ክልከላውና ወከባው ተጠናከሮ መቀጠሉ፤ ገዥው ቡድን የምር ተቃዋሚ ፓርቲ ናቸው ብሎ የሚያስባቸው ፓርቲዎች ለማዳከምና ከምርጫው ውድድር ውጪ ለማድረግ ያለው ቁርጥ አቋም የሚያሳይ ነው። ይህ የገዢው ቡድን አካሄድ በሀገራችን ዴሞክራሲያዊ የሆነ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት እንዲመሰረት ፍላጎት እንደሌለው በደንብ የሚያረጋግጥ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃና ፍትሐዊ በሆነ ምርጫ የሚፈልገውን ፓርቲ እንዲመርጥ እድል ሊጠሰው ሲገባ በሥርዓቱ በእኩል ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳያካሄድ የተለያዩ ጫናዎች እየተደረጉበት የሚካሄዱት ምርጫዎች ሁሉ ትርጉም አልባ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡ ይህ የገዢው ቡድን ሀላፊነት የጎደለው እንቅስቃሴ በተግባር የሚደግፈው ከሠላማዊ ትግል ይልቅ የኃይልና የአመፅ መንገድ እንደሚሆን የተረዳ አይመስልም፤ ይልቁንም በሠላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉትን ፓርቲዎች ወደ አላስፈላጊ መስመር በመግፋት ሀገራችን ወደ ብጥብጥና ወደ እርስ በእርስ ጦርነት እንድትገባ የሚያደርግ ሁኔታ እየተከተለ ነው የሚገኘው። በሥልጣን ላይ ያሉት ወገኖች ይህ አሳሳቢ ሁኔታ በትክክል እንዳያዩ ጭፍን የሥልጣን ጥም ጋርዷቸዋል፡፡

Tuesday, November 18, 2014

ታሪካችን የደብተራ ነው አላችሁኝ?

ከዋልን ካደርን ገና ብዙ ጉድ እንሰማለን። የኢትዮጵያን ታሪክ ማጠልሸት ሰሞኑን እንደ ወረርሽኝ ሆኗል። የኢትጵያን ታሪክ የደብተራ ተረት ነው ብሎ ማጣጣል፣ ደብተራን ከአማራ ጋር ብቻ ማያያዝ ያለማወቅ በሽታ ካልሆነ ምን ይባላል? አለማወቅን ማወቅ ጤና፣ አለማወቅን አለማወቅ ደግሞ በሽታ ነው።

ደብተራ ያየውን የሰማውን በከተበ ለምን ይንቋሸሻል? የደብተራ ጥፋቱ አስቀድሞ መሰለጠኑ ነው፤ ፊደል የስልጣኔ በር ነው፤ ደብተራ ደግሞ ፊደል የቆጠረ የመጀመሪያ ሰው ነው፤ የኢትዮጵያ ደብተሮች በጊዜያቸው ከነበሩት ሰዎች አስቀድመው የሰለጠኑ ናቸው፤ ስልጣኔውን ያገኙትም በፊደል በኩል ነው። አስቀድመው በመሰልጠናቸውም፣ ለሁላችንም የሚሆን ነገር ጽፈው አለፉ። ባይሰለጥኑ ኖሮ ታሪክን ለመጪው ትውልድ ስለማስተላለፍ አይጨነቁም ነበር። ከደብተራ ውጭ ታሪክን ለመጪው ትውልድ ጽፎ ስለማስቀረት ያሰበ ማን ነው? ተራው ገበሬ ዝናብ መጣ ሄደ፣ ተራው ነጋዴ አሞሌ ተወደደ ረከሰ፣ ተራው ወታደር ድንበር ሰፋ ጠበበ፣ ንጉስ ግብር ጨመረ ቀነሰ ከማለት ውጭ ታሪክ ጽፎ ስለማስተላለፍ ተጨንቆ ያውቃል? ስለጥበብ ስለውበት ተጨንቆ የጻፈውም ደብተራው ነው።

ደብተራ ባየው በሰማው፣ የጆግራፊ እውቀቱ፣ የእግሩ ጥንካሬ፣ የቀለም አቀባበሉና እድሜው በፈቀደለት መጠን ጻፈ። ሲጽፍ ይጨምራል፣ ይቀንሳል። የጨመረውን የቀነሰውን ማስተካከል ከደብተራ የተሻለ እውቀት ያገኘው የሁዋለኛው ትውልድ ሃላፊነት ነው። ታዲያ እንዲህ ሲባል ደብተራን በማድነቅ እንጅ በማንቋሸሽ አይጀመርም። ኒውተን ጋሊሊዮን አንቋሾ ጥናት አልጀመረም፣ አንስታይን ኒውተንን አንቋሾ አልተነሳም። የኛ ዘመንኛ ጻፊዎች ደግሞ የሁዋላውን አንቋሾ መጀመር እውቀት ይመስላቸዋል። ጽሁፋቸውም በውሃ ላይ እንደበቀለ ተክል የሚሆነው ለዚህ ነው፣ ስር አልባ ነው፤ እፍ ቢሉት እንደ ላባ በኖ ይጠፋል።
አሁን ደብተራ ባይጽፍ ኖሮ ታሪካችን የሰሃራ በታች ካሉት አገራት ይለይ ነበር?። ከሰራሃ በታች ካሉ አገራት በራሱ ቋንቋ ታሪኩን ጽፎ ያስቀረ ከእኛዋ ኢትዮጵያ ውጭ ሌላ አለ? አብዛኛው የጥቁሩ የአፍሪካ ታሪክ የተጻፈው በቅኝ ግዛት ጊዜ አይደለምን? ፈረንጆቹ ለእነሱ በሚጥማቸው መንገድ አይደለም የከተቡት? ምንጫቸውስ ምንድነው? ህንጻዎች እና ቁሳቁሶች አይደሉም? ታዲያ ደብተራ ታሪክ ጽፎ ባስቀረ፣ ድንጋይና ቁሳቁስ ከመፈለግ ባዳነ ለምን ይሰደብ?

Sunday, November 16, 2014

የሰንደቅ አላማችን ጠላት ወያኔና ወያኔ ብቻ ነዉ!

ሰንደቅ አላማ ለአንድ አገር ህዝብ የኩራት፤ የአልበገር ባይነት፤ የአንድነትና የታሪክ ተከታታይነት ምልክት ነዉ። ሰንደቅ አላማ በአንድ በኩል የወደፊቱን ብሩህ ተስፋ ክወዲሁ እያሳየን እየዟችሁ የሚለን፤ በሌላ በኩል ደግሞ በምናብ ወደኋላ እየወሰደን የድልና የመስዋዕትነት ታሪላችንን የሚያስታዉሰን የነጻነት፤ የሠላምና የብሩህ ተስፋ ማህደር ነዉ። የአገራቸን የኢትዮጵያ አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ሰንደቅ አላማ ትናንትናና ከትናንት ወዲያ በተስፋፊዎች አለመደፈራችንን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ዘረኞች የጫኑብንን የመከራ ቀንበር በቆራጥነት ሰብረን ነገና ከነገ ወዲያ የነፃነት አየር እንድንተነፍስ አስረግጦ የሚነግረን የአንድነታችን፤ የተገጋድሏችንና የድላችን ልዩ ምልክት ነዉ። አንድን ኢትዮጵያዊ ሰንደቅ አላማ ላንተ ምንህ ነዉ ብለን ብንጠይቀዉ ጥያቄዉን ዕድሜህ ስንት ነዉ ተብሎ እንደሚጠየቅ አንድና ሁለት ቃል ብቻ ተናግሮ አይመልስም። ሰንደቅ አላማም በአንድና በሁለት ቃላት ምንነቱ የሚገለጽ ተራ ቃል አይደለም። ኢትዮጵያዉያን ተማሩ አልተማሩ፤ ደሃ ሆኑ ኃብታም ፤ወንጀለኛ ሆኑ ወይም ሠላማዊ ለአገራቸዉ ሰንደቅ አላማ የተለየ ቦታ አላቸዉ። ሰዎች የአገራቸዉን ሰንደቅ አላማ የሚወዱትና ለሰንደቅ አላማዉ በክብር መዉለብለብ የህይወት መስዋዕትነት የሚከፍሉት ስለታዘዙ ወይም ስለ ሰንደቅ አላማዉ ተነግሯቸዉ አይደለም። በእርግጥም የሰንደቅ አላማ ክብርና የአገር ፍቅር ለሰዎች ሰንደቅ አላማዉን አክብሩ፤ አገራችሁን አፍቅሩ እየተባለ የሚነገር ነገር አይደለም። አገርንና ወገንን ማክበርና መዉደድ ሰንደቅ አላማን ከማክበርና ከማፍቀር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነዉ።የሰንደቅ አላማ ልዪ ክብርና የአገር ፍቅር ሰዎች ተወልደዉ ከሚያድጉበት ማህበረሰብ፤ ከቤተሰብ፤ ከጎረቤትና ከጓደኛ እንደ ምግብና እንደ ዉኃ እየበሉና እየጠጡ የሚያገኙት የሰዉነትና የዜግነት መገለጫ ታላቅ እሴት ነዉ።

ለዚህም ነዉ የማንም አገር ዜጋ አገሩ ዉስጥ ቢኖር ወይም ካገሩ ዉጭ፤ ቢታሰር ባይታሰር፤ ሀብታም ቢሆን ወይም ደሃ፤ የኔ ነዉ የሚለዉን የእናት አገሩን ሰንደቅ አላማ በፍጹም የማይረሳዉ። ከአገራቸዉ ዉጭ የሚኖሩ ሰዎች ደግሞ በተለይም ኢትዮጵያዉያን በተለያዩ ምክንያቶች የሚኖሩባቸዉን አገር ዜግነት ቢወስዱ እንኳን ሰንደቅ አላማቸዉን ባዩና ባስታወሱ ቁጥር የሚሰማቸዉ አገራዊ ስሜት እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ – እንዲያዉም ከአገራቸዉ ተሰድደዉም ሆነ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከአገራቸዉ ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ሰንደቅ አላማቸዉን ባዩ ቁጥር የአገራቸዉ፤ የወንዛቸዉ ፤ ተወልደዉ ያደጉበት መንደርና የልጅነት ትዝታቸዉ ባአይናቸዉ ላይ እየመጣ ዕንባ በዕንባ ይተናነቃሉ። ሰንደቅ አላማ ለአንድ አገር ህዝብ አንድ ነገር ነዉ፤ ብዙ ነገር ነዉ፤ ሁሉም ነገር ነዉ። ሰንደቅ አላማ ህዝብን ያስተባብራል፤ ያከባብራል፤ ያዋድዳል፤ መስዋዕትነትን፤ ፍቅርንና ብልፅግናን ያመለክታል።

Wednesday, November 12, 2014

ጊዜው የሕዝባዊ እምቢተኝነት ነው!!!

በአሁኑ ወቅት በአገራችን በከተሞችና በገጠሮች እየታዩ ያሉ ምልክቶችን በጥንቃቄ የመረመረ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መታዘቡ አይቀርም።

በአንድ በኩል፣ ወያኔ የተወገደባት፣ ፍትህ የሰፈነባትና የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ሆና የማየት ተስፋችን እየለመለመ ነው። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጂም ዓመታት በሕዝብ ላይ ሰፍኖ የነበረው የፍርሀት ደመና እየገለጠ በመሆኑ ተዘግተው የቆዩ አንደበቶች መናገርና “ይኸ ሁሉ ግፍ ለምን?” ብለው መጠየቅ ጀምረዋል። ይህንን መነቃቃት በአስተሳሰብም፣ በተግባርም፣ በኪነጥበብም እያየነው ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች ለውጥ በአገራችን ሊመጣ እንደሚችል ከማመን አልፎ ራሳቸውን በለውጥ አምጭ ኃይልነት መመልከት ጀምረዋል። በርካታ ወጣቶች ወያኔን በትጥቅ ለመገዳደር የወሰኑ ወገኖቻችንን እየተቀላቀሉ በዚህም ምክንያት ጉልበታቸውን እያፈረጠሙ ነው። የለውጡ እርሾ ከሲቪሉ አልፎ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በኢሕአዴግ ድርጅቶች ውስጥም እየተብሰለሰለ ነው። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት፣ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚጠቀምበት ኃይል መሆኑ እያበቃ በአንፃሩ የትግሉ አጋር የሚሆንባቸው ሁኔታዎች እየታዩ ነው። በሁሉም የሠራዊቱ ክፍሎች ጉምጉምታው ወደ ጩኸት እየተቀየረ በመሆኑ ሠራዊቱ በአለቆቹ ላይ የሚነሳበት ጊዜ እሩቅ አይደለም። በተለያዩ ምክንያቶች ህወሓትን ወይም ህወሓት የፈጠራቸውን ድርጅቶች የተጠጉ በአጠቃላይ ኢሕአዴግ በሚባለው ስብስብ ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችንም “ለመሆኑ ማንን ነው እያገለገልን ያለነው?” ብለው በመጠየቅ ላይ ናቸው። በዚህም ምክንያት ወያኔ ውስጡ እየተረበሸ ነው። ከኢትዮጵያም ውጭ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ ዘንድ ያለው ቁጣና ዝግጁነት ከወትሮው እጅግ የላቀ ነው። በአጭሩ፣ በሁሉም አቅጣጫ፣ ደረጃ በደረጃ የሕዝባዊ እምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል።

በአንፃሩ ደግሞ፣ የጨለማ ንጉሥ የሆነው ወያኔ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብን ወደ ፍርሀት ቆፈን ለመመለስ እስሩን ከመቸውም በላይ ያጧጧፈበት ጊዜ ነው። በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በአፋር በሶማሊ ... በመላው ኢትዮጵያ ብሩህ ራዕይ የሰነቁ ወጣቶችና አዛውንት ታድነው እየታሰሩ ናቸው። የወያኔ እስር ቤቶች በአርቆ አስተዋይ ዜጎቻችን ተሞልተዋል። ወትሮም ከፍተኛ የነበረው ስደት ብሶበታል፤ ለእውነት በጽናት የቆሙ ጋዜጠኞች ወይ ታስረው፣ አልያም ተሰደው አልቀዋል። የወያኔ የግዴታ ስልጠና አገሩን እያመሰው ነው። የኢትዮጵያዊያን ኑሮ በእጦቶች የታጀበ ሆኗል። የነፃነት እጦት፣ የፍትህ እጦት፣ የመብራት እጦት፣ የስኳር እጦት፣ የዘይት እጦት፣ የታክሲ እጦት፣ የመኖሪያ ቤት እጦት፣ እጦት፣ .... እጦት።

Monday, November 10, 2014

ግልጽ ደብዳቤ ”ለጠቅላይ ሚኒስትር” ኃይለማርያም ደሳለኝ

ከታሳሪ ዞን 9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስታችንን ያክብሩ!

ሠላም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር!? እንዴት ነዎት? ያስታውሱ ከሆነ የዛሬ ሁለት ዓመት አካባቢከፊሉ የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች ‘ግልፅ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ’

“ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እባክዎትን የተለያዩ የመንግስት አካላት የሕገ መንግስታችንን ድንጋጌዎች እየጣሱ ነውና እርስዎም በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 74/13/ መሠረት ሕገ መንስቱን የማስከበርና የማክበር ግዴታ ስላለብዎት ሕገ መንግስቱን ያክብሩ” በማለት አንዲት አጭር ደብዳቤ ፅፈንልዎት ነበር፡፡

ድንገት በተለያዩ ምክንያቶች የጻፍንልዎትን ደብዳቤ ካላነበቡት ወይም ማስታወስ ካልቻሉ ዛሬ ይሄን ማስታወሻ ስለምንፅፍልዎት ግለሰቦች አንድ ሌላ ማስታወሻ እንስጥዎ፡ ከ6ወራት በፊት /በሚያዚያ 2006 ዓ.ም/ ሶስት ጋዜጠኞችንና ስድስት ጦማሪያንን ‘ሕገ መንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ በመሞከር ወንጀል ጠርጥሬያችኋለሁ’ በማለት መንግስትዎ ልማታዊ ርምጃ (አብዮታዊ ርምጃ እንደሚባለው) ወስዶ ነበር፡፡

እኛም የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች የዚህ ‘ልማታዊ ርምጃ’ ሰለባ የሆንን ግለሰቦች ነን፡፡በርግጥ ከሁለት ዓመታት በፊት ‘ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስቱን’ ያስከብሩልን በማለት ጥያቄ ያቀረብንልዎት ግለሰቦች ‘ከ6 ወራትበፊት ሕገ መንግስቱን ለመናድ ሞክራችኋል’ በማለት መንግስትዎ ሲያስረን ሕገ መንግስቱ እንዲከበር ጠይቀን ሕገ መንግስቱን ለመናድ በመሞከር ወንጀል ተጠርጥረን ስንታሰር እስሩ በጣም ግራ አጋብቶን ነበር፡፡በዚህ ያልቆመው መንግስትዎ ክሱን ‘ሕብረተሰቡንና ሀገሪቱን ለማሸበር አቅዳችኋል ሞክራችኋል አሲራችኋል…’ በማለት ወደ ‘ሽብርተኝነት’ያሳደገው ሲሆን እርስዎም ከዚህ ጋር በተያያዘ ሃሳብዎትን ሲሰጡ ስለተመለከትንዎ ትንሽ ቅሬታ ይዘን መጣን፡፡

በቅድሚያ አሁን ያለንበትን ሁኔታ በትንሹ ብናስረዳዎት ቅሬታችንን ለመረዳት ያስችልዎታልና አንዳንድ ጉዳዮችን እንንገርዎት፡፡
ይሄን ማስታወሻ በምንፅፍልዎት ወቅት ከታሰርን ከ 200 ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን፣ነገር ግንጉዳያችን ገና በቅድመ ክስ (Pre Trial) የክርክር ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ ይሄ የሆነበት ዋነኛ ምክንያትም መንግስትዎ እንኳን ለእኛ ለተከሳሾች ለከሳሽ አካልም ግልፅ ያልሆነ ክስ በማቅረቡ ነው፡፡ ይሄንንም ስንል ልትፈፅሙት ነበር የተባለው ‘የሽብርተኝነት ድርጊት’ ሳይጠቀስ ‘በቃ የሽብርተኝነት ድርጊት ልትፈፅሙ ነበር’ በማለት በጨበጣ ስለመጣብን ነው፡፡

Ethiopia 2014: I Always Remember in November and in...

ALEMAYEHU G MARIAM 

Oh, Cruel November 2005! 

In 2005, Ethiopians faced unspeakable horrors. Following the parliamentary elections in May of that year, hundreds of Ethiopian citizens who protested the daylight theft of that election were massacred or seriously shot and wounded by police and security personnel under the exclusive command and control of the late regime leader Meles Zenawi. An official Inquiry Commission established by Zenawi documented that 193 unarmed men, women and children demonstrating in the streets and scores of other detainees held in a high security prison were intentionally shot and killed by police and security officials. An additional 763 were wounded**.

Every November since 2007, I have written consecratory (sanctifying) memorials in remembrance of the hundreds of innocent victims of the Meles Massacres. In my first memorial tribute in 2007,“Remember, the Ethiopian Martyrs of June and November, 2005 Forever!”, I reminded my readers that it was our moral duty “to bear witness for the dead and the living” in Ethiopia, to borrow a phrase from Elie Wiesel, the Holocaust survivor.
We must remember the victims of the Meles Massacres because, as Elie Wiesel said, we have “no right to deprive future generations of a past that belongs to our collective memory. To forget would be not only dangerous but offensive; to forget the dead would be akin to killing them a second time.”

I must confess that November is the cruelest month for me. If I could, I would skip straight from October to December. If I had the power, I would outlaw November. If there were no November, I would not have to remember. Mark Twain said, “If you tell the truth, you don't have to remember anything.” He was wrong. If you tell the truth you remember everything, especially the lies, the cries, the crimes and the massacres.

It is important for me to remember and to tell the truth about the crimes against humanity committed by the late Meles Zenawi and his criminal enterprise known as the Tigrean Peoples Liberation Front (TPLF). When Meles Zenawi ordered the massacre of hundreds of unarmed protesters in June and November 2005, he wanted to send a clear and unmistakable message to the Ethiopian people that he is so ruthless that he will kill, slash and burn on an industrial scale to keep himself and his TPLF in power forever. Meles Zenawi was an astute student of Reichsführer Heinrich Himmler: “The best political weapon is the weapon of terror. Cruelty commands respect. Men may hate us. But, we don't ask for their love; only for their fear.”

Sunday, November 9, 2014

የፈርዖኖች ድንኳን እየፈረሰ ነው!

“ዓረብ ስፕሪንግ” እየተባለ ስለሚነገረው ህዝባዊ አብዮት ብዙ ተብሏል። ያ ህዝባዊ አመፅ ለውጥ አምጥቷል።ማን ይነካኛል ብሎ ዜጎቹን መከራ ሲያበላ የነበረው የቱኒዚያው ቤኒ ዓሊ ዛሬ የተረሳ ግለሰብ ሁኗል። እኔ ከሌለው ይህች አገር ትጠፋለች ሲል የነበረው ጋዳፊ ከተደበቀበት የአይጥ ጉድጓድ ውስጥ ተጎትቶ ወጥቶ እንደ ውሻ ተቀጥቅጦ ሙቷል። ሆስኒ ሙባረክም እንዲሁ ተርስቶ ቀርቷል። የየመንም አምባገነን አገር ጥሎ ሂዷል።በሶሪያም አምባገነኖች ከእንግዲህ ተረጋግተው ህዝባቸው ላይ የሚያላግጡበት ዘመን አብቅቷል።

በቱኒዚያዊው ሙሃመድ ቦዛዚ መስዋዕትነት የተጀመረው ህዝባዊ ዓመፅ ብዙ የዓረብ አገራትን አዳርሷል። ይህ ህዝባዊ አመፅ ከዓረቡ ዓለም ባሻገር ወደ ጥቁር ህዝቦች ተሽጋግሯል። ቡርኪና ፋሶዎች ለ27 ዓመት ስልጣኑን ሙጥኝ ብሎ የኖረውን ብሌስ ኮምፓዖሬን ከተቆናጠጠው የስልጣን ወንበር ላይ አባረውታል።

ብሌስ ኮምፓዖሬ የገዛ ወገኑን ሠላም እያሳጣ በጎሬቤት አገሮች ዋና አስታራቂ፤ የሠላም ሰው መስሎ ለመታየት ይኳትን ነበር። አሜርካኖች ቁልፍ ወዳጃችን ይሉትም ነበር። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በጎረቤት አገሮች መረጋጋት ዋና ተዋኒያኒ እያለ ያሞጋግሰው ነበር። ብሌስ ኮምፓዖሬ የራሱ እያረረበት፤ የጎሬበቱን እያማሰለ የአሜሪካኖችንና የአውሮፓዊያንን ቀልብ ይዞ ድፍን ሃያ ሰባት ዓመት በስልጣን ተንጠላጥሎ ኑሯል።

የቡርኪናው ብሌስ ኮምፓዖሬ 27 ዓመት ስልጣን ላይ ሲቆይ እንደ ህወሃት ከገዛ ህዝቡ ድምፅ ይልቅ የሌሎችን ድምፅ መስማት ይመርጥ ነበር። ህዝቡ ነፃ ምርጫ ይደረግ፤ ዜጎች በመረጡት መሪ ይመሩ፤ አገር አይታመስ ቢሉት ሊሠማ አልወደደም። ከዚህ ከወገኑ ድምፅ ይልቅ ከባህር ማዶ “ቁልፍ ወዳጃችን” ለሚለው ድምፅ ይገዛ ነበር። በጎረቤት አገሮች ውስጥ አስታራቂ እና ሽማግሌ እኔ ነኝ ብሎ ራሱን በመሾም ላይ ታች እያለ ሌሎችን ለማስደሰት ይንከላወስ ነበር።ይህ ግን ክብር አልሆነለትም።

አልቃይዳና ቦኩ ሃራምን የመሰሉ አሸባሪ ኃይሎች በተነሱ ግዜ ለብሌስ ኮምፓዖሬ ሰርግና ምላሽ ሆነለት። አሸባሪነትን ለመዋጋት የአሜሪካኖች ምርጥ ወዳጅ ለመሆን በቃ። የአየር ክልሉንም ለአሜሪካን የስለላ አውሮፕላኖች እንደልብ ፈቀደ።አሜሪካኖችም በወቅቱ ወዳጅ ብለው የጠሩትን ግለሰብ የሚፈፀመውን ኢ-ዲሞክራሲያዊ ሁኔታ እና የሚፈፀመውን ሰብዓዊ መብት ጥሰት አይተው እንዳላዩ ሆነው ልክ ለህወሃት እንደሚያደርጉት የገንዘብና ሌሎች እርዳታዎችን መለገሳቸውን ቀጥለው ነበር። አሸባሪ ተብለው የተፈረጁ ኃይሎች በየቦታው የመፈጠራቸው ሁኔታ ለህወሃቶችም የተመቻቸ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው የሚካድ አይደለም።

ኮምፓዖሬ በመፈንቀለ መንግስት ስልጣን ከጨበጠ በኋላ ምርጫ በተካሄደ ቁጥር እርሱና ፓርቲው ምርጫ አካሂደን አሸንፈናል እያሉ ለ27 ዓመት በስልጣን ቆይተዋል። በሌላ መልኩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫው የተጭበረበረ እንደሆነ ቢናገሩም ሰሚ ሳያገኙ ኑረው ነበር። ግዜው ደርሶ የህዝብ ቁጣ ገንፍሎ ከፍርሃት በላይ ሆነና ኮምፓዖሬ ሃያ ሰባት ዓመት ሙሉ ከተዘባነነበት ቤተ-መንግስት ሾልኮ ለሰደት ተዳረገ።

የህወሃቱን ፖለቲካ የአዋጁን በጀሮ!

ህወሃት በተፈጥሮው የፖለቲካ ብዙህነት ወይም ብዝሃነትን ማቻቻል የሚባል ነገር አያውቅም። ሌላው ቀርቶ በራሱ በድርጅቱ ውስጥ የሚነሱ የተለዩ ሃሳቦችን ሁሉ እንደጠላት ሃሳብ ፈርጆ ሰዎችን ደብዛቸውን ማጥፋት የተለመደ የህወሃት አሰራር ነው። ይህን የህወሃት ባህርይ በቅጡ ለመረዳት በቅርቡ የቀድሞው የህወሃት አመራር አባል የነበረው አቶ ገብሩ አስራት የጻፈው መጽሃፍ ጥቂት ገጾች በማየት መረዳት ይቻላል። ተቃዋሚ ፓርቲ ሰላማዊም ሆነ አልሆነ በህወሃት እንደጠላት ነው የሚቆጠረው።

ሰሞኑን ከትግራይ የህዝብና የመንግስት ግንኙነት ቢሮ ከሚባለው መስሪያ ቤት በትግረኛ ተጽፎ ለአባለት በሚስጥር የተሰራጨ ደብዳቤ ማንኛውምንም ተቃዋሚና ከህወሃት ውጭ የሚያስብና ህወሃትን የማይከተል ሁሉ “ፀላኢቲ” ጠላቶች ሲል ይፈርጃል። በዚህ ባለ 5 ገጽ ደብዳቤ ውስጥ እነዚህን “ፀላኢቲ” እንዴት እንደሚያሳድዱ፣ እንዴት እንደሚያዋክቡና እንደሚያጠፉ የሚመክር መመሪያ የሚሰጡ ሃሳቦች ተቀምጠዋል። በደብዳቤው ላይ ከአናቱ ሆነው የሚያስተዳደሩትን ወገናቸውን እንኳን አይለይም። በአጭሩ እኛ እንዳንመርጥ የሚፈልግ፣ የሚቀናቀንና ሌሎች ሰላማዊ ፓርቲወችን የሚመራና የሚደግፍ ሁሉ ፀላኢቲ ነው።

ይህ ለ2007 ዓ.ም የክትትል ስራ የተመደበው የህወሃት ቡድን ስራውን የሚያከናውነው ከታክስ ከፋዩ በሚገኝ የመንግስት ገንዘብ መሆኑ ይታወቃል።

ዘንድሮ የምርጫ አመት መሆኑን ተከትሎ የፀላኢቲ ክትትልና አፈና ከአሁን ተጠናክሮ በመካሄድ ላይ መሆኑም እየታየ ነው። ጠንካራ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ በየክልሉ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን ሁሉ በመታፈንና ወህኒ በመውረድ ላይ ናቸው።
የህወሃት ኢህአዴግ መሪዎች በአለም ዙሪያ ነጻነቴን የሚል የህዝብ ድምጽ በሰሙ ቁጥር የሚሰማቸውን ድንጋጤ የሚቀንሱት ዜጎችን በማፈን፣ በመግደል፣ በማሰቃየትና በማሰር ብቻ ነው።

ለህወሃት ምርጫና መድብለ ፓርቲ መልክን አሳምሮ ተቀባይነት ወደ ምእራባውያን ለልመና ለመውጫ እምጅ ዴሞክራሲያዊ ምርጫና የህዝብ ልእልና የሚባል ነገር ባጠገባቸው እንዲያልፍ ስለሚፈልጉ የሚያደርጉት አለመሆኑን በብዙ መንገዶች አሳይተውናል። ከህወሃት ውጭ ያልህ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ አንተ ለወያኔ/ህወሃት ፀላኢቲ ጠላት ነህ። ወገኖቼ ብለህ የምታስብ ሁሉ ይህን የሚስጥር ደብዳቤያቸውን በማየት ብቻ ሳይሆን በተግባር አይተሃልና።

Thursday, November 6, 2014

መልዕክት ከቃሊቲና ከቂሊንጦ

የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ የዝግጅት ክፍል አባላት ወደ ቂሊንጦና ቃሊቲ እስር ቤቶች በማቅናት እስረኞችን ጠይቀዋል፡፡ እስረኞቹ ያስተላለፉትን መልዕክት ነገረ ኢትዮጵያ እንደሚከተለው ጠቅለል አድርጋ አቅርባዋለች፡፡

‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ አይቀርም›› እስክንድር ነጋ

በማህበራዊ ድረ-ገጽም ሆነ በሌሎች አጋጣሚዎች መልካም ልደት ለተመኛችሁልኝ ሁሉ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ የቡርኪናፋሶው አምባገነን መውደቁን በመስማቴ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ይህ ለእኔ ውድ የልደት ቀን ስጦታየ አድርጌ እቆጥረዋለሁ፡፡ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥም ለውጥ የሚቀር አይደለም፡፡ የእኛ ችግር ከማንም የባሰ ነው፡፡ ቱኒዚያ ላይ የተጀመረው አብዮት ሰሜን አፍሪካ አንቀጥቅጧል፡፡ ኢትዮጵያ ከሰሜን አፍሪካ አገራት ይልቅ ለእነ ቦትስዋና ትቀርባለች፡፡ የቦትስዋና ጉዳይ ሌሎቹንም ማነቃነቁ የማይቀር ነው፡፡ ይህ ለውጡ ቅርብ እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ አይቀርም፡፡

‹‹ቂሊንጦም ገደብ አለብኝ›› አብርሃ ደስታ

አሁን ደህና ነኝ፡፡ ማዕከላዊ ምርመራ ማዕከል ሳለሁ ጨጓራ በጣም ያመኝ ነበር፡፡ እዛ ያለው ምግብ ነበር ያሳመመኝ፡፡ ከሰማያዊ ወጣቶች ምግብ ከውጭ መምጣት ከጀመረ ወዲህ ተሽሎኛል፡፡ አሁንም ቂሊንጦ እየመጡ እየጠየቁን ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ የሰማያዊ ወጣቶችን እጅግ በጣም አመሰግናለሁ በሉልኝ፡፡

እዚህ እስር ላይ ያለን ሰዎች ከውጭ ምን መረጃ አለ የሚለውን ነው የምንፈልገው፡፡ አሁን ወደእናንተ ስመጣ ጎብኝ ይፈልገኛል ብዬ የእስር ቤቱን ተወካይ አስፈቅጄ ነው የመጣሁት፡፡ ገደብ አለብኝ፡፡ እኔ እና በእኛ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ የሆነው ዘላለም ወርቃገኘሁ ጠያቂ ሲመጣ ለኃላፊዎች በጎብኝዎቻችን እንደተፈለግን ሳንናገር መውጣት እንደማንችል ተነግሮናል፡፡

‹‹ስለእኔ የእስር ጉዳይ ማሰብ አልፈልግም›› አንዱዓለም አራጌ

እኔ ለሀገሬና ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲሆን የምፈልገው መልካም ነገር መቼ ይፈጸማል የሚለው እንጂ እኔ መቼ ከእስር እወጣለሁ የሚለው አሳስቦኝ አያውቅም፡፡ ሰላማዊ ትግል በባህሪው ውጤቱ በጎ ነው፡፡ እኔና መሰሎቼ በሰላማዊ ትግል ነው የምናምነው፡፡ በዚህ የትግል ስልት ደግሞ ለውጥ ሲመጣ ማየት እሻለሁ፡፡ ስለእኔ የእስር ጉዳይ ማሰብ አልፈልግም፡፡ በጋራ ቤታችን ኢትዮጵያ መልካም ነገሮች እንዲሆኑ እፈልጋለሁ፡፡ ይህ ነው የእኔ ምኞት!

Tuesday, November 4, 2014

‹‹ጥቁሩ አብዮት›› እና ኢትዮጵያ

በጌታቸው ሺፈራው

ከሳምንታትበፊት ከጓደኞቼ ጋር እስክንድር ነጋን ልንጠይቀው ወደ ቃሊቲ አቅንተን ነበር፡፡ በወቅቱ ስለ ለውጥ አውርቶ የማይጠግበውን እስክንድርንስለ ኢትዮጵያ መጻኢ እድል ስንጠይቀው የመለሰልን ቀላል ግን ደግሞ የሚገርም መልስ ነበር፡፡ እስክንድር ተስፋ አስቆራጭ የሚመስለውትግል ፍሬያማ ሊሆን እንደሚችልና በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚነሳው ጥያቄን ልክ እንዲህ ነበር ያስረዳን፡፡

‹‹እነጋናን፣ ዛምቢያን፣ እና ሌሎቹንም የአፍሪካ አገራት ነጻ እንዲወጡ ኢትዮጵያ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጋለች፡፡ አብዛኛዎቹ የአፍሪካአገራት አሁን ነጻ ካወጣቻቸው ኢትዮጵያ የተሻለ ዴሞክራሲ ገንብተዋል፡፡ እኛ እየጠየቅን ያለነው እንደነዚህ አገራት አይነት ስርዓትእንዲሰፍን ነው፡፡ የቅንጦት ጥያቄ አልጠየቅንም፡፡ መጠየቅ ከነበረብን እጅግ ትንሹን ነው እየጠየቅን ያለነው፡፡››

ከሶስትቀናት በፊት እስክንድር እኛ ነጻ አውጥተናቸው ከእኛ ይሻላሉ ካላቸው አገራት መካከል ቡርኪናፋሶዎች ለስርዓቱ ሌላ ጥያቄ አንስተውራሳቸው ሲመልሱት ስመለከት ያስታወስኩት እስክንድርን ነው፡፡ እኛ ምንም ጥያቄዎች ሳይመለስልን እነሱ ሌላ ጥያቄዎችን እያነሱ እራሳቸውመመለሱን ተያይዘውታል፡፡

ቡርኪናፋሶምንም እንኳ እንደ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ድሃ ብትሆንም እንደ እኛ 6ና 7 ሚሊዮን ህዝብ አይራብባትም፡፡ ምንም እንኳእስከ ትናንትና ድረስ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ላይ የተቆናጠጠ መሪ ያስተዳድራት የነበር ቢሆንም ፓርቲዎችና ህዝቡ ሀሳቡንየሚያንጸባርቅባቸው ሚዲያዎችና ሌሎች ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ዘርግታለች፡፡ ገና እ.ኤ.አ በ1990 ጀምሮ ሬድዮና ቴሌቪዥንንበግል በመያዛቸው ህዝቡ ለአማራጭ ሚዲያ ቅርብ ነው፡፡ ኢንተርኔት ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚደረገው በስርዓቱ አይታፈንም፡፡ቡርኪናፋሶ እንደ ኢትዮጵያ ጋዜጠኞች በጅምላ እስር ቤት የሚታጎሩባት፣ በገዥው ፓርቲ ጫና የሚሰደዱባት፣ ሚዲያዎች የሚታፈኑባትናየሚዘጉባት አገር አይደለችም፡፡

ባለፉትአመታት ለአጭር ጊዜ ከሶስት የማይበልጡ ጋዜጠኞች ታስረዋል፡፡ ባለፉት 20 አመታት በሚዲያው ታሪክ አስከፊው የሚባለው የአንድጋዜጠኛ ባልታወቁ ሰዎች መገደል ብቻ ነው፡፡ በቡርኪናፋሶ ያለፉት 20 አመታት ታሪክ ውስጥ በሚዲያው ጠባሳ ነጥብ ተደርጎየሚወሰደውና የውጭ ተቋማት ጫና ለማሳደር የሚጥሩበት ጉዳይም የዚህ ጋዜጠኛ ሞት ነው፡፡ ከአምስት አመት በፊት አንድ ጋዜጠኛየ‹‹እንገድልሃለን›› ማስፈራሪያ ስለደረሰበት ዓለም አቀፍ የጋዜጠኛ ማህበራት አሁንም ድረስ ስርዓቱን በመውቀሻነትይጠቀሙበታል፡፡ በቡርኪና ፋሶ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብሰባ እንዳያደርጉ፣ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይወጡ አይከለከሉም፡፡ የአገሪቱ ሲቪክማህበራት ኢህአዴግ መራሹ ‹‹መንግስት›› ስር ካሉት የተለዩ ናቸው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በሽብር ስም ወህኒአይወረወሩም፡፡ በአጭሩ ቡርኪናፋሶ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚጠየቁትን አብዛኛዎቹን የፖለቲካ ጥያቄዎች መልሳለች፡፡

የግንቦት 7 ንቅናቄ በጣሊያኗ መዲና ሮማ ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ አካሄደ

ባሳለፍነው እሁድ የግንቦት 7 ንቅናቄ በጣልያን ዋና ከተማ ሮማ ያካሄደው ህዝባዊ ስብሰባ በስኬት ተጠናቀቀ። በህዝባዊ ስብሰባው ላይ በሮማ እና አጎራባች ከተሞች የሚኖሩ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት እንደነበር ተመልክቷል። የንቅናቄያችን ም/ ሊቀመንበር አቶ አበበ ቦጋለ በህዝባዊ ስብሰባው ላይ በክብር እንግድነት ተጋብዘው የተገኙ ሲሆን አቶ አበበ ቦጋለ ከኢትዮጵያውያን ጋር ሰፊ ወቅታዊ አገራዊ ውይይት በማድረግ የንቅናቄያችንን የትግል ስልቶች ማለትም ህዝባዊ ተቃውሞ፤ ህዝባዊ አመጽና፤ ህዝባዊ እምቢተኝነት በተመለከተ ሰፊ ገለፃ ካደረጉ በኋላ ለተግባራዊነታቸው እየተደረገ ያለው ሰፊ ርብርብ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ ጥሪ ማቅረባቸው ታውቋል። አቶ አበበ ከተሳታፊዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ መስጠታቸውም ታውቋል።

በህዝባዊ ስብሰባው ላይ የተገኙት ኢትዮጵያውያን ንቅናቄው አሁን ላይ የደረሰበት የትግል ደረጃ እንዲሁም በንቅናቄው የተተገበሩትን የትግል ስልቶች በማድነቅ፤ የግንቦት 7 ንቅናቄ የጉጅሌው ወያኔ አገዛዝን ለመገርሰስ የጀመረውን ትግል ከዳር ለማድረስ የሚጠበቅባቸውን ማንኛውም አይነት መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያኑ በገንዘብ፤ በሰው ሃይልና በዕውቀት ረገድ ድጋፍ በማድረግ ከንቅናቄው ጎን እንደሚሰለፉ ቃል ኪዳን መግባታቸውም ተመልክቷል። በህዝባዊ ስብሰባው ላይ የቀረበላቸውን የተቀላቀሉን ጥሪ በመጠቀም ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ኢትዮጵያውያን በአባልነት እንዲሁም በደጋፊነት በመመዝገብ ግንቦት 7 ትን መቀላቀል መቻላቸውም ታውቋል።

የእንግሊዝ መንግስት ለጉጅሌው ወያኔ አገዛዝ ይሰጥ የነበረውን የ 27 ሚሊዮን ፓውንድ እርዳታ መሰረዙ ታወቀ

የእንግሊዝ መንግስት ከግብር ከፋዮች የሚሰበሰብውን ገንዘብ በንጹሃን ኢትዮጵያውያን ላይ መጠነ ሰፊ ኢ ሰብአዊ ድርጊትን እየፈጸመ ላለው ለፋሽስቱ ወያኔ አገዛዝ መለገሱ ተገቢ አይደለም ሲሉ በአገሪቱ ያሉ አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቶችና የህግ አካላት ከፍተኛ የተቃውሞ ዘመቻ መክፈታቸውን ተከትሎ አገሪቱ ለጉጅሌው አገዛዙ ትሰጥ የነበረውን እርዳታ ለማቆም እየተገደደች መሆኗዋን ለማወቅ ተችሏል። የተቃውሞ ዘመቻውን ተከትሎ የእንግሊዝ አለማቀፍ የትብብር ተቋም ለጉጅሌዎቹ ሹማምንትና ቅጥረኛ ካድሬዎች ከ 70 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ ወጭ በማድረግ በደህንነት ዙሪያ የሚሰጠውን ልዮ የማስተርስ ዲግሪ ስልጠና ማቋረጡን ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በዚህ በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ደግሞ እንግሊዝ ለጉጅሌው ወያኔ አገዛዝ የፖሊስ አባላት ማጠናከሪያ የምትለግሰውን ድጎማ ማቋረጧን ቴሌግራፍ የተባለው የአገሪቱ ታላቅ ጋዜጣ ዘግቧል። ጉጅሌዎቹ በአገሪቱ እያደረሱት ያለው መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብት ጥሰት ለእርዳታው መቋረጥ አብይ ምክንያት መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን የእንግሊዝ መንግስት ለፖሊስ አባላት ማጠናከሪያ በሚል ሲሰጥ የነበረው እርዳታ 27 ሚሊዮን ፓውንድ እንደነበርም በጋዜጣው ተመልክቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የጉጅሌው ወያኔ አገዛዙ በግንቦት 7 ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ በሆኑት በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የፈጸመው የውንብድና ተግባርን ከኢትዮጵያውያን በተጨማሪ አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችንና ማስቆጣቱ የሚታወቅ ሲሆን በተለይ መቀመጫቸውን በእንግሊዝ ያደረጉት የተለያዩ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች፤ የህግ አካላትና የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የእንግሊዝ መንግስት ለፋሽስቱ ወያኔ አገዛዝ እየሰጠ ያለውን ድጋፍ በአስቸኳይ እንዲያጤን የሚጠይቅ የተጠናከረ ዘመቻ ለመክፈታቸው አብይ ምክንያት መሆኑ ተነግሯል። ድርጅቶቹ በቅንጅት በእንግሊዝ መንግስት ላይ እሳደሩት ያለው የተቃውሞ ዘመቻ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተመለከተ ሲሆን እንግሊዝ ከዜጎቿ የምትሰበሰበውን የግብር ገንዘብ ኢትዮጵያውያንን እየገደለ፤ እያሰረና እያሰደደ እንዲሁም በኢትዮጵያውያን ላይ ኢ ሰብአዊ ድርጊት እየፈጸመ ላለው ፋሽስታዊ አገዛዝ ፈጽሞ መስጠት እንደሌለባት አበክረው እየጠየቁ እንደሚገኙ በእንግሊዝ የሚታሙ የተለያዩ ጋዜጦች መዘገባቸውን ለማወቅ ተችሏል።

Monday, November 3, 2014

የወያኔ ግፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ

ዘረኛዉ ወያኔና ባለሟሎቹ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላና በሸኮ መዠንገር አካባቢ የሚያካሄዱትን የማንአለብኝነት የመሬት ዝርፍያና ዜጎችን እርስ በርስ በማጋጨት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያደርጉት አራዊታዊ ሩጫ የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ህዝብ ይህ ነዉ ተብሎ ሊነገር የማይችል እልቂት እየተፈጸመበት ነዉ። የመዠንገር ህዝብ የሞትና የህይወትን ያክል የማይወጣዉ ምርጫ ስለቀረበለት ተወልዶ ያደገበትን የአባቶቹንና የአያቶቹን አካባቢ ለቅቆ በመዉጣት እራሱን ለመከላከል ባደረገዉ እንቅስቃሴ የብዙ ንጹሃን ዜጎችና ቁጥራቸዉ ቀላል የማይባል ምስኪን ወታደሮችም ህይወት ማለፉ በይፋ እየተሰማ ነዉ። ይህንን ተከትሎ ግፈኞቹ የወያኔ መሪዎች በአካባቢዉ ብዙ ዘመን በቆዩ ብሄሰቦች መካክል ሆን ብለዉ ግጭት እንዲነሳ እያደረጉ በህዝብ መካክል ግጭትትና ዕልቂት የተነሳ በማስመሰል በአካባቢዉ ከፍተኛ ሰቆቃ በመፈፀም ላይ ይገኛሉ።

በዚህ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እየደረሰ ላለዉ መጠነ ሰፊ ግጭትና ዕልቂት ተጠያቂዉ በአካባቢዉ ለዘመናት አብሮ በመደጋገፍ የኖረዉ ህዝብ ሳይሆን የዚህ አሰቃቂ ዕልቂት ባለቤትና ጠንሳሽ ህወሓትና ዘረኛ መሪዎቹ መሆናቸዉን ለአንድም ደቂቃ ሊዘነጋ አይገባም። ይህ ግጭት ሊነሳ የቻለዉ ህወሓት የአካባቢዉን ደሃ ገበሬ ከትዉልድ መሬቱ ላይ እያፈናቀለ መሬቱን ለከፍተኛ የጦር መኮንኖቹና የኔ ለሚላቸዉ ባለሟሎቹ በማከፋፈሉ መሆኑን ይህንን ግፍ የሚሰማ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ልብ ሊለዉ ይገባል። ህወሃት የአማራን ተወላጆች አካባቢዉ የእናንተ አይደለምና ዉጡ እያለና እያፈናቀለ በሌላ በኩል ግን በየክልሉ የአካባቢዉን ነዋሪ እያፈናቀለ የራሱን ሰዎች የመሬት ባለቤት ማድረጉ አዲስ የጀመረዉ ክስተት ሳይሆን ቆየት ያለና ስር የሰደደ የወያኔ አሰራር ነዉ።

ይህ ዛሬ በጋምቤላና በአካባቢዋ እየደረሰ ያለዉ ግፍና መከራ ለአካባቢዉ ህዝብ ብቻ የሚተዉ ነጠላ ችግር ሳይሆን በአጠቃላይ ወያኔ በአገራችን ላይ ሆን ብሎ በማድረስ ላይ ያለዉ ችግርና መከራ አካል ነዉ። በጋምቤላ ዉስጥ የፈሰሰዉና እየፈሰሰ ያለዉ የሴቶች፤ የወጣቶች፤ የአረጋዉያንና የህጸናት ደም ለሁላችንም የነጻነት ጥሪ እያቀረበልን ነዉ። ይህ የነጻነት ጥሪ ሰምተን የምናልፈዉ ወይም ነገ እንደርሳለን በለን በቀጠሮ የምናልፈዉ ጥሪ አይደለም። ጥያቄዉ የአገርና የዜጎች ህልዉና ጥያቄ ነዉና ነገ ዛሬ ሳንል አሁኑኑ ይህንን የነጸነት ጥሪ ሰምተን ምላሽ ልንሰጠዉ ይገባል።

አማራ! አማራ! አማራ! ብቸኛዉ የወያኔ ዘፈን

“ሞኝና ወረቀት የያዙትን አይለቁም” የሚለዉ ቆየት ያለ ያለ የአገራችን ተረት ትርጉም ያልገባዉ ሰዉ ካለ የቅኔ አዋቂ መፈለግ ወይም መጽሐፍ ማገላበጥ የለበትም። ማድረግ ያለበት ቀላል ነገር ቢኖር ወያኔንና የወያኔን ስራ ትኩር ብሎ መመልከት ብቻ ነዉ። በመሠረቱ ወረቀት የያዘዉን አለመልቀቁ ወያኔን ጨምሮ ሁላችንም የምንፈልገዉ ነገር ነዉና ወረቀት ሊመሰገን ይገባል። ሞኝ የያዘዉን አለመልቀቁና ከግዑዙ ወረቀት ጋር መነጻጸሩ ግን ሞኝ አማራጭ የሚባል ነገር የማያዉቅና ግዜና ሁኔታ ሲለዋወጡ ያቺኑ በልጅነቱ የያዛትን አቋም ሙጭጭ አድርጎ እንደያዘ እድሜ ልኩን የሚኖር የሀሳብ ደሃ መሆኑን ያመለክታል። ሞኝን ሞኝ እያለን የምንጠራዉም በዚህ ደካማና ግትር አቋሙ የተነሳ ነዉ። ወያኔ ጫካ ዉስጥ እያለ ለአስራ ሰባት አመት፤ ከጫካዉ ወጥቶ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ደግሞ ለሃያ ሦስት አመታት የያዛቸዉን አቋሞችና የወሰዳቸዉን እርምጃዎች ረጋ ብሎ የተመለከተ ሰዉ ወያኔ፤ ወረቀትና ሞኝ ያላቸዉን የቅርብ ግኑኝነት በቀላሉ መመልከት ይችላል። ሦስቱም አንድ ነገር ከያዙ ሌላ የመያዝ ፍላጎትም ችሎታም የላቸዉም። አዎ! በእርግጥም ሞኝ በሞኝነቱ፤ ወረቀት የተፈጥሮ ጠባዩ በመሆኑ ወያኔ ደግሞ የወረቀትም የሞኝም ጠባይ ስላለዉ ሦስቱም የያዙትን አይለቁም።

የወያኔ መሪዎች ምን ለትግል አነሳሳችሁ ተብለዉ ሲጠየቁ በወጣትነታችን ጠመንጃ ተሸክመን ጫካ እንድንገባ ያስገደደን በወቅቱ ኢትዮጵያ ዉስጥ ስር ሰድዶ የነበረዉ የብሄር ብሄረሰቦች ጭቆና ነዉ ብለዉ ነዉ አፋቸዉን ሞልተዉ የሚመልሱት። ዉሸታቸዉን ነዉ። የወያኔ መሪዎች በተለይ ሁለቱ በፀረ ኢትዮጵያ አቋማቸዉ የሚታወቁት መለስ ዜናዊና ስብሀት ነጋ ለትግል ያነሳሳቸዉ የብሄር ብሄረሰቦች ጭቆና ሳይሆን በአማራ ብሄረሰብ ላይ ያላቸዉ ከፍተኛ ጥላቻ ነዉ። ዛሬም አነዚህ ሁለት ፀረ አማራ ግለሰቦች የፈጠሩት ህወሓት የሚባል ዘረኛ ድርጅት ፀረ አማራ ከመሆኑ የተነሳ ከሌሎች የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች በተለየ መንገድ የገባበት ቦታ ሁሉ እየተከታተለ የሚያጠቃዉ ይህንኑ መከረኛ የአማራ ብሄረሰብ ነዉ። ወያኔዎች ለአማራ ብሄረሰብ ያላቸዉን ጥላቻ ላለፉት 34 አመታት በስድብ፤ በንቀትና አማራዉን በጅምላ በማንኳሰስ አሳይተዋል። ባለፉት አስር አመታት ደግሞ ኦሮሚያ፤ ቤንች ማጂና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ዉስጥ የአማራ ተወላጆችን ይህ የእናንተ አገር አይደለምና ወጡ እያሉ አማሮችን ከዉሃ ዉስጥ የወጣ አሳ አድርገዋቸዋል።

ባለፉት ሃያ ሦስት አመታት በግልጽ እንዳየናቸዉ የወያኔ መሪዎች አማራዉን በመዝለፍና በማፈናቀል ብቻ አልተገቱም፤ ይልቁንም አማራዉን ኢትዮጵያ ዉስጥ ለተከሰቱ ችግሮች ሁሉ ብቸኛ ተጠያቂ በማድረግ ይህንን በህዝብ ቁጥሩም ሆነ በታሪክ ስፋቱ አንጋፋ የሆነዉን ብሄረሰብ በሌሎቹ የአገራችን ብሄረሰቦች እንዲጠላና በአይነ ቁራኛ እንዲጠበቅ አድርገዋል። በዚህ የተነሳ ወያኔ ባለፉት ሃያ አራት አመታት ጠፍጥፎ የፈጠሯቸዉ በየክልሉ የሚገኙ የፖለቲካ ምስለኔዎች ምንም አይነት ችግር ባጋጠማቸዉ ቁጥር የችግራቸዉ መንስኤ አድርገዉ የሚወስዱት የአማራዉን ብሄረሰብ ነዉ። ዛሬ በአንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች፤ ቤንች ማጂና ቤኒሻንጉል ዉስጥ አማራዉን አገርህ አይደለምና ዉጣ የሚባለዉ የዘረኝነት አባዜም ቢሆን የዚሁ ወያኔ ለረጂም አመታት በህዝብ መካከል ሆን ብሎ የዘራዉ ጥላቻ ዉጤት ነዉ።

በመጥፋት ላይ ያለው የወልቃይት ጠገዴ ፀለምት ህዝብ

ሁኔ አቢሲኒያ

የኢሳቱ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና እንግዳ ሆነው ቀርበው የነበሩት አንጋፎቹ ፖለቲከኞች አቶ ቻላቸው አባይ እና አቶ ጎሹ ገብሩ በወልቃይት ጠገዴ ህዝብና እየተፈፀሙበት ስላሉት ኢሠብዐዊ ድርጊቶች ዙሪያ ሠፊ ውይይት አካሂደው ነበር ውይይቱ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ስለአካባቢው ፖለቲካ ከፍተኛ መረጃ የሚሠጥ ከመሆኑም በላይ አሳዛኝ የሆኑ እውነታዎች የተነሡበት ነበር፡፡

የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር በትግርኛ አጠራሩ ህወሀት ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ግፎችን በወልቃይት ህዝብ ላይ እንደፈፀመ ያስረዱት ተወያዮቹ በ1984 በአካባቢው ይኖር የነበረው ቁጥሩ ከ83,000 በላይ እንደነበር ገልፀው በአሁኑ ወቅት ይህ አሐዝ ወደ 48,000 እንደወረደ ለማወቅ ተችሏል 35,000 ያህል የወልቃይት ጠገዴ ፀለምትን ህዝብ ምን ዋጠው መቼም ሁሉም ሠው በእርጅና እና በበሽታ ሞቷል አይባልም ቢሞትስ አካባቢው ላይ ሟች ብቻ ነው እንዴ ያለው ተወላጅ አይኖርም የወልቃይት ማህፀኖች ልጅ አያፈሩም?

ህወሀት ገና ጫካ በነበረበት ሠዓት ከድርጅቱ አመራሮች አንዱ የሆነው ስብሐት ነጋ መኮንን ባዘዘው ወይም በትግል ስሙ ዮሴፍ ባዘዘው የተባለን አባቱ የወልቃይት እናቱ የትግራይ ሰው ከሆኑ ቤተሰብ ውስጥ የተገኘን ታጋይ የወልቃይት ህዝብን ከትግራይ ጋር የመገንጠል ፍላጎት እንዲያጣራ እና ጥናት እንዲሠራ በሚል ወደወልቃይት ይላካል ሪፖርቱ ግን ለእነ ስብሐት ነጋ እና ጓደኞቹ አስደንጋጭ ነበር አንድም የወልቃይት ህዝብ ከትግራይ ህዝብ ጋር አብሮ በመሆን ከኢትዮጵያ መገንጠል እንደማይፈልግ በማሳወቁ የህወሀት አመራሮች ጥርስ ውስጥ እንደገባ አቶ ቻላቸው እና አቶ ጎሹ ያስረዳሉ፡፡ በዚህ ቂም በቀል ውስጥ የገባው ህወሀት አቶ ልጅዓለም የተባሉ የ80 ዓመት አዛውንትን ጨምሮ በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችን መግደል፣ማሠር እና ማሳደድ ጀመረ፡፡ የወልቃይት ህዝብ ከሞት ለማምለጥ በርካታ ጥረትን ቢያደርግም ተሳክቶለት ከሞት የተረፈው ግን እጅግ ጥቂቱ ነው፡፡