Saturday, October 31, 2015

አይኔ አያየ እዚህ ዉስጥ አልገባም – መሠረት ሙሌ (ኤፍሬም ማዴቦ ከአርበኞች መንደር)

መብራቱን አጥፍቼዉ አልጋዬ ላይ የወጣሁት በግዜ ነዉ። አለወትሮዬ እንቅልፍ የሚባል ነገር በአይኔ አልዞር ብሎኝ ከጨለማዉ ጋር ፊት ለፊት ተፋጥጠናል። የነፋስ ሸዉታ እንኳን የማይሰማበት ደረቅ ሌሊት ነዉ። ጨላማዉ አይን ይበሳል። እቤቱ ዉስጥ ያለዉ ሰዉ ሁሉ ተኝቷል። ቀኑን በሠላም ላዋለኝ አምላክ ምስጋና ሰጥቼ ሌሊቱንም አደራ ብዬዉ ፀሎቴን ጨረስኩ። ያ ምቀኛ እንቅልፍ ግን አሁንም እንደከዳኝ ነዉ። ትንሿ አልጋዬ ላይ ግራ ቀኝ እያልኩ ተገለባበጥኩ። እንቅልፍ ተጎትቶ የሚመጣ ይመስል አሁንም አሁንም ላይ ታች እያልኩ አልጋዉ ላይ እራሴን ጎተትኩት . . . እንኳን እንቅልፍ ሊወስደኝ ጭራሽ አይኖቼ መርገብገባቸዉን ያቆሙ ይመስል ቀጥ ብለዉ ቀሩ። ከተጋደምኩበት ብድግ ብዬ መብራቱን አበራሁና ለመንገድ ከያዝኳቸዉ ሁለት መጻህፍት አንዱን አዉጥቼ ማንበብ ጀመርኩ። እኔ ላንብበዉ ወይ መጽሀፉ ያንብበኝ አላዉቅም። ጧት ስነሳ ግን “The Architecture of Democracy” የሚል መጽሐፍ ደረቴ ላይ ተለጥፎ ነበር። ሰዐቴን ሳየዉ ከሌሊቱ ስምንት ሰዐት ተኩል ይላል። ከአልጋዬ ላይ ዘልዬ ወረድኩና ሰዉነቴን ታጥቤ ልብሴን ከለበስኩ በኋላ መኪናዉ ዉስጥ ገብቼ “I’m ready” አልኩ። የመኪናችን መብራት ጨለማዉን እየገላለጠዉ የአስመራ ከረንን መንገድ ተያያዝነዉ። መኪናዉ ዉስጥ ከገባሁ በኋላ እንደገና አፌን የከፈትኩት ባሬንቱ ደርሰን ቁርስ ሳዝ ነዉ። ባሬንቱ በግዜ መድረሳችን ደስ ቢለኝም የቀረን መንገድ ርዝመት ታየኝና ቁርስ መብላቴን ትቼ . . . በሰዐት ይህን ያክል ብንጓዝ እያልኩ ዋናዉ ጉዳያችን ቦታ የምንደርስበትን ሰዐት ማስላት ጀመርኩ። የስሌቱ ዉጤት ከሦስት ሰዐት ሲበልጥብኝ ተናደድኩ። ቀሪዉ መንገድ ገና ሳልጀምረዉ ሰለቸኝ። በተፈጥሮዬ መንገድና መኃላ ሲረዝም አልወድም።

ተሰነይ ስንደርስ መኪናዉ ዉስጥ የነበረዉ ሰዉ ሁሉ ቡና ካልጠጣሁ አለ። መኪናችንን አቁመን በቁማችን ቡናችንን ፉት አድርገን መንገዳችንን ተያያዝነዉ። እሁድ ጥቅምት 7 ቀን 2008 ዓም አርበኞች ግንቦት ሰባትን የፈጠሩት ሁለት ድርጅቶች ከተዋሃዱ በኋላ ለሁለተኛ ግዜ የሰለጠኑ ታጋይ አርበኞች የሚመረቁበት ቀን ነበር። ከዚህ ቀደም እንደዚህ አይነቱን የምርቃት ዜና የምሰማዉ በኢሳት ሬዲዮና ቴሌቭዥን ብቻ ስለነበር እቦታዉ ደርሼ የምረቃዉን ስነስርዐት ለማየት የነበረኝ ጉጉት እጅግ በጣም ከፍተኛ ነበር። የምሳ ሰዐት ከመድረሱ በፊት በቀኝ በኩል ዋናዉን መንገድ ለቅቀን ዉስጥ ዉስጡን ወደ ምርቃቱ ቦታ የሚወስደዉን ኮረኮንች መንገድ ተያያዝነዉ።

ግቢዉ ዉስጥ ያለዉ ጥድፊያና ግርግር አንድ ትልቅ ዝግጅት መኖሩን በግልጽ ይናገራል። የተለያየ ወታደራዊ ዩኒፎርም የለበሱና መሳሪያ የተሸከሙ አርበኞች ግቢዉን ሞልተዉታል። ያነገቱትን ጠመንጃ ስመለከት ቆራጥነታቸዉ ታየኝ። በቀጭኑ ተጎንጉኖ ማጅራታቸዉ ላይ የወደቀዉን ፀጉራቸዉን ሳይ ቴዎድሮስና ዮሐንስ ትዝ አሉኝ። ፈገግታ በፈገግታ የሆነዉን ፊታቸዉን ስመለከት ደግሞ የእናት አገሬ ኢትዮጵያ ትንሳኤ ደጃፍ ላይ መሆኑ ታየኝና የኔም ፊት እንደነሱ በፈገግታ ተሞላ። ተራ በተራ እየመጡ “ጋሼ አፍሬም” እንደኳን ደህና መጣህ ብለዉ ሲጠመጠሙብኝ በአንዱ ትከሻዬ ፍቅራቸዉ በሌላዉ ጀግንነታቸዉ ዘልቆ ሰዉነቴ ዉስጥ ገባ። ጥንካሬያቸዉ በጅማቴ ፍቅራቸዉ በደም ስሬ ዘለቀ። እኔነቴ ሲታደስና በአገሬ ላይ ያለኝ ተስፋ ሲለመልም ተሰማኝና ደስ አለኝ። አዎ ደስ አለኝ . . . እየመጣ የሚሄድ ግዜያዊ ደስታ ሳይሆን የዉስጥ አካላቴን የዳሰሰ ዘላቂ የመንፈስ ደስታ ተሰማኝ። በጣም ደስ የሚልና በአሁኖቹ ቋንቋ “የሚመች” ቀን ነበር። የዕለቱን ዝግጅት ለማየት መቸኮሌን ያወቁት እግሮቼ የምረቃዉ በዐል ወደሚከበርበት ዳስ- ፍትህ፤ ነጻነትና እኩልነት የናፈቀዉ ልቤ ደግሞ ወደ ወደፊቷ ኢትዮጵያ ይዘዉኝ ጭልጥ አሉ፡ . . . ለካስ የወደፊቷ ኢትዮጵያ ሩቅ አይደለችም።

የአርበኞች ግንቦት 7 ስብስቦችን በመላ አገሪቱ እናደራጅ!


የኢትዮጵያ ወጣቶች የህወሓት አገዛዝ በአገራችን ላይ የሚያደርሰውን በደል የሚገልጹ እና ከዚህ በደል መገላገያ መንገድ የሚያመላክቱ ፓስተሮች በግድግዳዎችና ምሰሶች ላይ እየለጠፉ፤ በራሪ ወረቀቶችን እየበተኑ እና የግድግዳ ላይ ጽሁፎችን እየፃፉ ነው። ባለፈው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ በተለያየ መጠን ቢሆንም በአገሪቱ አብዛኛዎቹ ትላልቅ ከተሞች ውስጥ ይህ የቅስቀሳ ዘዴ ተግባራዊ ሆኗል። ይህ ተግባራዊ ሥራ የአርበኞች ግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ያሉ መሆኑ ተጨባጭ ማሳያ ሆኗል።

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች የሚገኙ ወጣቶች እያደረጉት ያለውን እንቅስቃሴ ያደንቃል፤ ተግባሮቻቸው ባነሰ ኪሳራ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በጠንካራ ሥነ ሥርዓት በተዋቀሩ የአርበኞች ግንቦት 7 ስብስቦች እንዲመሩ ያበረታታል። ከተግባራዊ ሥራዎች ጎን ለጎን የድርጅት አቅም ግንባታ መሠራት ያለበት አቢይ ጉዳይ መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 በአጽንዖት ያስገነዝባል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ አባላትና ደጋፊዎችች ለድርጅትና ለአባላት ጥንካሬ ተገቢውን ትኩረት እንዲሰጡ አበክሮ ያሳስባል።

ነፃነት ናፋቂ ወጣቶች የሚያደርጉት የሕዝባዊ እምቢተኝነት መገለጫ ተግባራት ዓይነታቸው እየተቀያየረ እንዲቀጥል በእቅድ መመራትና በድርጅት መታገዝ አለባቸው። የመረጥነው ሁለገብ የትግል ስትራቴጂ እምንፈልገው ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ላይ እንዲያደርሰን የኢትዮጵያ ሕዝብ በሁለቱም የትግል ስልቶች አኳያ መደራጀት ይኖርበታል።

በዚህም መሠረት ለሕዝባዊ አመጽ ጠንካራ የአርበኛ ሠራዊት ማደራጀት እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለሕዝባዊ እምቢተኝነትም ጠንካራ ድርጅት በኢትዮጵያ ከተሞችና ገጠሮች፤ በሥራና በመኖሪያ አካባቢዎች ማደራጀት ይገባል። ስለሆነም በከፍተኛ ምስጢር የተደራጁ እና በከፍተኛ ብቃት የሚመሩ የአርበኛ ግንቦት 7 ክበባት በየቦታው፣ በብዛት እና በጥንቃቄ መደራጀት ይኖርባቸዋል። ድርጅት ድርጅት የሚሆነው ደግሞ በሥነ ሥርዓት ሲዋቀርና በብቃት ሲመራ ነው። ስለሆነም ነፃነት ናፋቂ የሆነ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በሥነ ሥርዓት በተዋቀሩ ትናንሽ ስብስቦች ራሱን እንዲያደራጅ፤ የፓለቲካ፣ የታሪክ እና የጠቅላላ እውቀት ግንዛቤውን ለማዳበር እንዲሁን መሠረታዊ የደህንነት ጥበቃ ክህሎቶችን እንዲያጎለብት ጥረት እንዲያደርግ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ መስጠት አስፈልጓል።

Friday, October 30, 2015

‘‘..... ይሄ አንዱ ተልዕኮና የትግሉ አካል ነው!’’ ታጋይ ዘመነ ካሴ

በቅዱስ ዮሃንስ

ላለፉት 24 ዓመታት የሕወሓት ቅልብ የሆኑ የፌደራል ፖሊሶችና ወታደሮች የኢትዮጵያ ህዝብን እንዳሻቸው ሲረግጡ፤ ሲበድሉና ሲጨቁኑ፤ መብቱን ለመጠየቅ አደባባይ የወጣውን ህዝብ በጠራራ ፀሃይ ያለ ርህራሄ በጥይት እየቆሉ ሲገድሉ፤ የኢትዮጵያን ህዝብ የደም እንባ ሲያስነቡ አንዳች እንኳ ትንፍሽ ሊሉ ያልፈቀዱ ሰዎች ትላንት የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ወታደር በነዚሁ የስርዓቱ አስፈፃሚ ፖሊሶች ላይ እርምጃ መውሰዱን ተከትሎ ማጉረምረም ምን የሚሉት ፈሊጥ ይሆን!?! ፈጽሞ ሊገባኝ ስላልቻለ ነው። ኧረ ጎበዝ በጣም ያስተዛዝባል። በነገራችን ላይ በአሁኑ ሰዓት የሕወሓት አስፈፃሚና ጠባቂ የሆኑ የፌደራል ፖሊሶችና ወታደሮች በቁጥር ጥቂቶች መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል። ቁጥራቸው ቀላል የሚይባሉ መለዮ ለባሾች ከነፃነት ሀይሎች ጋር ሚስጥራዊ ግንኙነት ፈጥረው የውስጥ አርበኝነት ተግባራቸውን በትጋት እየፈፀሙ እንደሚገኙ መዘንጋት የለበትም።


ለማነኛውም ወደ ዋናው ነጥቤ ስገባ በደንብ ሊሰመርበት የሚገባው አብይ ጉዳይ አርበኛ ታጋይ አምሳሉ ተሾመ የፈፀመው አኩሪ ጀብዶ አንዱ ተልዕኮና የትግሉ አካል መሆኑ ነው። ታጋይ ዘመነ ካሴ በኢሳት እንደነገረን። አዎ! የኢትዮጵያ ህዝብን የሚበድሉ፤ የሚጨቁኑና የሚገድሉ የሕወሓት አስፈፃሚዎችን ከምድረ ገፅ ማፅዳት። አስፈፃሚ አካላት ከሌሉ የሕዝብ ጠላት የሆነው የሕወሓት አገዛዝ ሊኖር ስለማይችል። ስለዚህ በሕወሓት ጉያ ስር ተወሽቀው የኢትዮጵያ ህዝብን እየበደሉና እያስለቀሱ ላሉ ግለሰቦች ሁሉ የማንቂያ ደውሉ ተደውሏል ማለት ነው። ከወዲሁ በደንብ ሊያስቡበት ይገባል። አዎ! ግለሰቦቹ ከእኩይ ድርጊታቸው በፍጥነት ታቅበው በሕዝብ ወገን በመሰለፍ የነፃነት ትግሉ አካል መሆን የሚገባቸው አጣዳፊ ሰዓት ላይ ተደርሷል። አለያ ትርፉ የከፋ ይሆናል። ሌላው ደግሞ አንዳንድ ተቃዋሚ ነን ባዮች ያልጠራ አቋማቸውን በጊዜ ቢፈትሹና ቢያስተካክሉ መልካም ይመስለኛል። የመወላወያ ሰዓት ረፍዷል። የኢትዮጵያ ህዝብ ከተያያዘው የነፃነት ትግል ጎን መሰለፍ አለያ ከጠላትና ከጨቋኞቹ ጎራ መሰለፍ። አዎ! ትግሉ አንድ ጥግ ላይ ብቻ መርገጥ ወደ ሚጠይቅበት ወሳኝ ምዕራፍ ተሸጋግሯል!

ከሰንደቁ ፊትም በኋላም (ከሠራዊቱ ድምፅ ራዲዮ)

አንደሚታወሰዉ ባለፈዉ አመት እንደ አዉሮፖዉያን ዘመን አቆጣጠር በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያዉያን ሰልፈኞች መስከረም 29ቀን 2014 ዓም እጅግ ሥርአታዊ ዲሲፕሊን የተሞላዉ ጥያቄ አንግበዉ ወደ ኢትዮጵያ ኢምባሲ ሄደዉ ነበር። በሰላማዊ ሰልፎች የተለመደዉን የገማ እንቁላል፤የበሰበሰ ቲማቲም፤ቆመጥና ድንጋይ እንደመሣርያ ይዘዉ አልሄዱም። በእለቱ የተቃጠለ የወያኔ ንብረትም ሆነ የተዘረፈ የወያኔ ሀብት አልነበረም። ያ ተግባር አሁን በሥልጣን ላይ ያለዉ የወያኔ ዘረኛ አገዛዝ የተካነበት ሞያ ስለሆነ ወደዚያ የተሰማራ አልነበረም። በዚያ ሠልፍ ላይ የተሰማሩ ወጣት ኢትዮጵያዉያን ልባቸዉ ሲነድ የቆየበትን አንድና አዲስ አይነት እንቅስቃሴ አሳይተዋል። ይኸዉም የኢትዮጵያ ሕዝብ ለአያሌ ዘመናት የጀግንነቱ ማረጋገጫ፣የነፃነቱ ምልክትና የተስፋዉ ፅኑ ማስረጃ አድርጎ ሲመለከተዉ የኖረዉን ሰንደቅ አላማ በግቢዉ ዉስጥ ለማዉለብለብ ችለዋል። “ወድቃ የተነሳችዉ” ሰንደቅ ዓላማ የፍትህና የርትህ ተስፋ መሆንዋን ሕዝቡ የሚቀባበለዉ እዉነታ ነበር። አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማችንን እየተመለከተ ወራሪዉን የኢጣልያ ሠራዊት የመታዉን የአድዋ መቶ ሺህ ሠራዊት የምናስታዉስበትና ለጥቁር ሕዝብ ሁሉ የአርነት አርማ አድርገን የምንቆጥረዉ ነዉ። ይህቺ ሰንደቅ ዓላማ ከሃምሳ በላይ ለሆኑ የአፍሪካ አገሮች ነፃነት አስተዋፅኦ አድርጋለች። ከሰላሳ የሚልጡ ሰንደቅ ዓላማዎች የዚችን ታሪካዊ አገር አርማ የተቀበሉና የተከሉ ናቸዉ።

አንድ አገር የሚደፈረዉ ብሄራዊ አርማዉና የነፃነት መታሰቢያዎቹ በተነኩ ወቅት ነዉ። ከዉጭ የሚመጣ ወራሪ ኃይል መከሰቻዉ የማንነቱ ማስረጃ የነፃነቱና የጀግንነቱ ማረጋገጫና የብሄራዊ ኩራቱ ምልክት የሆነዉ እንደ ሰንደቅ ዓላማ ያለ የክብር አርማ ሲረገጥ ነዉ። የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ የአሸናፊነትና የጀግንነት ተቀባይነት ያገኘዉ በቀጥታ በተዘመተበት መንግሥት ጭምር ነዉ።

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የአሸናፊነትና የጀግንነት ተቀባይነት ያገኘዉ በቀጥታ በተዘመተበት መንግሥት ጭምር ነበር። ስለሆነም ኢጣልያና እንግሊዝ ኤርትራ ዉስጥ ከስልሳ አመታት በላይ ሲቆዩ በደብረ ቢዘን በኦፊስየል የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ሲዉለበለብና እያንዳንዱም ኤርትራዊ ኢትዮጵያዊ ሰርግና ልደት ክርስትናና ሞት በዚችዉ ሰንደቅ ዓላማ ሲያጌጥ በመኖሩ ነበር።

በኢሳት ቴሌቪዥን ላይ አንድ ኢትዮጵያዊ እንደገለጡት ይህንን ሰንደቅ ዓላማ ሕዝቡ ብቻ ሳይሆን ግመሎቹ ፈረሶቹና በቅሎዎቹ ጭምር የሚያዉቁትና የሚያከብሩት ነበር። የኢሳዉ ባላባትና መሪ ደጃዝማች ኡጋዝ ሃሰን እንደጠቀሱትም “ግመሎቹ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ሲያዩ ሸብረክ ብለዉ ያሳልፉታል” ሁላችንም የትናንት ትዉልዶች ይችን ሰንደቅ ዓላማ በተማሪነት ዘመናችን በጠዋት መዝሙራችን አዉለብልበን ማምሻዉ ላይ አዉርደን አጣጥፈንና አክብረን እናድራለን። በመንገድ ላይ ሆነን ሰንደቅ ዓላማችን ሲከበር ቆመን አብረን እናከብራለን።

የዚችን አገር አንድነት ለመጠበቅ ከመላዉ ኢትዮጵያ የተዉጣጣ የአገር ዳር ድንበር ጠባቂ የሆነዉ የመከላከያ ሠራዊታችን ሰንደቅ ዓላማችን ሥር ተንበርክኮ ቃልኪዳን ሲገባ ኖሯል። ለዚች የነፃነት ዓርማ ክብር ሥፍር ቁጥር የሌለዉ የመከላከያ ሠራዊታችን ሕይወቱን ሰዉቶላታል።ቀባሪ ያጣዉ ጀግና አሁንም ለተተኪዎቹ ትዉልዶች ልዩና ዘላለማዊ ጥሪዉን እያቀረበ ነዉ። ካስከበረዉ የናቱ ማሕፀን ሆኖ “እኔ የሞትኩላትን አገር አንተም የማስከበር ግዴታ አለብህ” እያለ አደራህን እያሳሰበህ ነዉ። የጎበናና ከአብራኩ የተከፈለዉ አበበ አረጋይ፣ ሃይለማርያም ማሞ፣የአሉላ አባነጋ፣ የበላይ ዘለቀ፣ የበቀለ ወያ፣የአብዲሳ አጋ፣ የቶላ በዳኔ ነፍሶች ጥሪ ሊሰማህ ይገባል።

Ethiopia keeps ‘not free’ position in Freedom House latest report


  • A significant number of service interruptions in the name of routine maintenance and system updates resulted in worsening service across the country. Internet services on 3G mobile internet networks were reportedly unavailable for more than a month in July and August 2014 (see Restrictions on Connectivity).
  • A growing number of critical news and opposition websites were blocked in the lead up to the May 2015 elections (see Blocking and Filtering).
  • Six bloggers of the prominent Zone 9 blogging collective arrested in April 2014 were officially charged with terrorism in July 2014; two of the bloggers were unexpectedly released and acquitted in July 2015, joined by the four others in October (see Prosecutions and Arrests).
  • A university political science teacher known for his Facebook activism and another blogger were arrested and charged with terrorism in July 2014, among three others (see Prosecutions and Arrests).
  • Online journalists in the Ethiopian diaspora were attacked with Hacking Team’s sophisticated surveillance malware (see Technical Attacks).
Introduction: 


Ethiopia, the second most populated country in sub-Saharan Africa, has one of the lowest rates of internet and mobile phone connectivity in the world. Telecommunication services, in general, and the internet, in particular, are among the most unaffordable commodities for the majority of Ethiopians, as poor telecom infrastructure, the government’s monopoly over the information and communication technologies (ICTs) sector, and obstructive telecom policies have significantly hindered the growth of ICTs in the country, making the cost of access prohibitively expensive.

Despite the country’s extremely poor telecommunications services and a largely disconnected population, Ethiopia is also known as one of the first African countries to censor the internet, beginning in 2006 with opposition blogs. Since then, internet censorship has become pervasive and systematic through the use of highly sophisticated tools that block and filter internet content and monitor user activity. The majority of blocked websites feature critical news and opposition viewpoints run by individuals and organizations based in the diaspora. In the lead up to the May 2015 general elections, a growing number of critical news and opposition websites were blocked, while select tools, such as Storify and a popular URL shortening tool Bitly, remained blocked throughout the year. The government also employs commentators and trolls to proactively manipulate the online news and information landscape, and surveillance of mobile phone and internet networks is systematic and widespread.

Monday, October 26, 2015

‘Bury me in England’ – new fears for British father kidnapped to Ethiopia

Reprieve: A British father of three who has been held for 16 months in incommunicado detention in Ethiopia has suggested he may die in prison.

Andargachew ‘Andy’ Tsege, whose British partner and children live in London, was abducted at an airport in Yemen in June 2014 and rendered unlawfully to Ethiopia. He spent a year in secret detention, and was subjected to months of ‘interrogations’, before being recently moved to a prison that has previously been described as a ‘gulag.’ Andy is a prominent critic of Ethiopia’s ruling party, and has received an in absentia death sentence on charges relating to his political views.

Since his kidnap, Andy has been refused access to a lawyer or his family, and has not been charged with any crime or subjected to any form of legal process. Lawyers at human rights organization Reprieve have been barred from visiting him.

It’s now emerged that Andy is afraid that he will soon die; he has asked the British government to ensure that he is buried in England, and told his children to “be brave.” In the comments – made recently during a rare, closely monitored visit by Britain’s ambassador to Ethiopia – Andy also revealed that:


  • The Ethiopian authorities have not allowed him outside his cell for months;
  • He is an effective ‘ghost prisoner’ – the Ethiopian authorities have not told him what charges or sentence he faces, and he has no prisoner number;
  • He has demanded a lawyer, but the request has been refused;
  • He has been refused access to an independent doctor, despite illness.

The UN has condemned Mr Tsege’s ordeal and ordered Ethiopia to release him, but the British government – a close ally of Ethiopia – has so far limited itself to requesting proper consular access and ‘due process’ to be followed in his case. Last week, Foreign Office Minister Grant Shapps MP hosted a trade event in London with the Ethiopian Foreign Minister and other officials, promising in his remarks that the UK would stand “shoulder to shoulder” with them. Foreign Secretary Philip Hammond later revealed that he had raised Andy’s case with his Ethiopian counterpart during the visit, but that he had not asked for Andy’s release.

Sunday, October 25, 2015

The Opposition Dilemma and the Road Ahead

By: Eyassu Gebrehiwot

We Ethiopians carry the burden and brunt of Tigray liberators merciless oppression and persecution for so long. Without changing a single political and social views and policies that it brought from the jungle in 1991, the TPLF regime has continued to be the hegemon and belligerent force in the Ethiopian political landscape. With no sign of real change and reform beyond GIGO cycle, garbage in-garbage out cycle, they conduct every five years and dare to call ‘election’ we see no effort and will to change any policy and political position by the Tigray Liberation led regime in the last quarter of a century. As a result we bear the pains of exile, persecution, mental and physical harassment and inhuman treatment.

If we fail to create the wherewithal to bring change to our nation and home that no other place substitute, it is not because of TPLF’s strength and invincibility. But it is only because of the oppositions’ division and lack of common vision. Although others can assist our cause, the quintessential factor to advance freedom, equality, justice and economic change in Ethiopia, conviction and clarity of purpose is all that is needed from the forces of freedom and liberty. Yes, we have to believe that we are the ones we are waiting for!

In its quarter of a century grip on power a government that continue to beg international food assistance to feed the millions of people it cared less and while others suffer under untold social and economic malaises that make them leave their homeland under dangerous and inhuman conditions should not be given let alone another five years term but one more day. It does not matter whether the West and the rest get this in their head or not. What matters most is whether it gets in our head and if we are willing and able to commit ourselves to take the highway to get our country back and establish a new beginning by bridging the gaps and filling the holes between different opposition groups and sub-regional actors committed to our cause. It is only then the era of misery, exile, injustice and violation of human and political rights would come to an end.

It does not require telling for anyone, since it is true as the sky is blue, that in international state relations priorities of states are set in terms of how best each nation can fulfil their national interest first and foremost. It would be senseless than sensible for anyone to expect fairness and righteousness dictate any foreign nation’s actions and behaviors with regards to the situation in Ethiopia. Be it the West or East they are all guided by principles that best fulfils their private interest out of any situation in Ethiopia, or Africa in general. That is how it was yesterday, it is today and continue to be in the future. So, it would be in our best interest to stop getting excited – in anger and delight – when the West or the rest has taken certain policy decisions with regards to the TPLF regime. I assure you, when the opposition becomes strong enough in human and logistical capacity to face-off TPLF the West and others would start to listen as they never had and they will start to reconsider their policy position towards TPLF, which is guided neither by reason or principle.

Without social quest for a new idea and system that incorporated above all freedom and liberty of citizens, the developed Western states that we die crossing deserts and oceans to be part of would not have been the elephants of international relations today. They became what they are not because they are white or bright. If it was not for their decision, passion, conviction and action to make their institutions work better they would have been no different to what and where most African, Latin American and Asian countries find themselves. But, when ordinary people rise up and refuse to settle to a status-quo they do extraordinary and magical things, for themselves and to the generation that will follow. As they say ‘Freedom is not free.’ To create the political, economic and legal systems that we see in the West and we are jealous of and wish to have for ourselves they have sacrificed their time, energy, material and above all lives.

Most Western democracies are a result of tremendous blood shed between those who fought to keep the status-quo and the people who dared to take their own future in their own hands. The British Civil War from 1642-1659 made a precedent for the monarch to consult parliamentarians in the exercise of his power there by ending absolute monarchy. The will and sacrifice of the people of the American colonies to free themselves and be the masters of their destiny by breaking out of the grip of the British Empire has led to today’s giant of international relations- the United States of America- the global power breaker and leading economy in the world. Similarly, the 1789 French revolution; the Italian and German (re) unification wars in the second half of the 19th c. as well as many others were responsible for the unprecedented economic and political transformation that followed through the adoption of new systems and principles that governed their social, economic and political relations.

The West and Our Quest for Freedom

The west needs Ethiopia, Africa in general, to have strong men who can avoid anarchy and chaos and do business with them in spite of their repressive and brutal treatment of their citizens. It was not long ago we heard Pres. Barack Obama calling the TPLF regime in Ethiopia ‘democratically elected’ causing an uproar from many corners. What ignited that uproar was his blunt denial of reality and clear derailment from the tracks of principled diplomacy and idealism the President himself spoke passionately about on many occasions. Had Mr. Obama repeated the very speech he made in Kenya about how ethnic and tribal politics would end up tearing a country apart to the Ethiopian audience, we would not have asked for more. I don’t think Mr. Obama is oblivious to the political reality in Ethiopia. Since he knows that Ethiopia is a ‘democracy’ he should have too known how political parties under the ‘democratic regime’ are organized and to what end.

Thursday, October 22, 2015

Eskinder Nega Wins 2015 PEN Canada One Humanity Award

Eskinder Nega wins PEN Canada One Humanity award at 36th International Festival of Authors

TORONTO, Oct. 19, 2015 – The Ethiopian journalist Eskinder Nega will receive PEN Canada’s One Humanity Award on the opening night of the 36th International Festival of Authors (IFOA 36). The award, valued at $5,000, is presented at PEN’s annual gala to a writer whose work transcends the boundaries of national divides and inspires connections across cultures.

Mr. Nega, an independent journalist, was arrested in September 2011 under the provisions of Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation for criticizing the detention of a prominent government critic, and disputing the government’s assertion that detained journalists were terror suspects. At his trial the judge reportedly accused Nega of using “the guise of freedom” to “attempt to incite violence and overthrow the constitutional order” through a popular revolt similar to those of the Arab Spring.

Convicted on June 27, 2012, Nega was sentenced to 18 years in prison. In December 2012 the United Nations Working Group on Arbitrary Detention said the sentence violated free expression and due process rights under international law. The UN group called for his immediate release. On May 2, 2013, the Ethiopian Federal Supreme Court upheld both the conviction and the sentence.

Nega is one of eight journalists and bloggers currently jailed in Ethiopia under the Anti-Terrorism Proclamation, according to PEN International’s case list. Six others were released in July 2015 after being held for periods ranging from 16 months to four years under the same legislation.

Since its 2010 UN Universal Periodic Review (UPR), Ethiopia has repeatedly used its Anti-Terrorism Proclamation to arbitrarily arrest, prosecute, and imprison independent journalists and opposition activists. Ahead of Ethiopia’s 2014 UPR, a shadow report by PEN International and the Committee to Protect Journalists found the Proclamation overbroad and inconsistent with international law. The use of the Anti-Terror Proclamation to stifle the independent media has been condemned both by regional human rights bodies and the UN.

Wednesday, October 21, 2015

ሶማሊያ የሚገኙ የጦር ሠራዊት አባላት ሲበደሉ ያመናል!

የተባበሩት መንግሥታት ማኅበር የሚሰጠው ገንዘብ ህሊናቸውን በሰወራቸው፤ የህወሓት አባላት በሆኑ ጄኔራሎች አዝማችነት ሶማሊያ የገባው ኢትዮጵያዊ ድሃ ወታደር እጣ ፈንታ በጣም አሳዛኝ ደረጃ ላይ ደርሷል። በየእለቱ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮች እየተገደሉ፤ አስከሬናቸው በጎዳናዎች እየተጎተተና እየተቃጠለ ነው። ሶማሊያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት ወገኖቻችን ናቸውና በእነርሱ ላይ የሚደርሰው ስቃይ ይሰማናል፤ ሲበደሉ ያመናል፤ ጭንቀታቸው ይጨንቀናል። ወገኖቻችን ናቸውና የደህንነታቸው ጉዳይ ያገባናል።

የህወሓት ጄኔራሎች ሙሉ ትኩረታቸው ያለው በእያንዳንዱ ወታደር ስም ከተባበሩት መንግሥታት በሚያገኙት ገንዘብ መጠን ላይ ነው። ለሶስት ሣምንታት ብለው የገቡበት ጦርነት እነሆ አስር ዓመታት አስቆጥሯል። አንዱ የገቢያቸው ምንጭ ነውና ጦርነቱ ለሌላ አስር ዓመታት ቢራዘም ለእነሱ ደስታቸው ነው። ኢትዮጵያዊው ምስኪን ወታደር ግን አዛዦቹ እንዲያልቅ በማይፈልጉት ጦርነት ውስጥ ገብቶ መስዋዕትነት ይከፍላል፤ ሲወድቅ የሚያነሳው የለም፤ መስዋዕት ሲሆን የክብር አሸናኘት የለውም፤ ቤተሰቦቹም ይኑር ይሙት አያውቁም። ይህ ሁላችንንም ሊያስቆጣ የሚገባ ግፍ ነው።


ኢትዮጵያን ለመታደግ ብሎ የዘመተን ወታደር ስለኢትዮጵያ ግድ በማይሰጣቸው፤ ጥቅማቸውን ብቻ በማሳደድ ላይ ያሉ አዛዦች ቸልተኝነት ምክንያት ለስቃይ፣ ሰቆቃና ውርደት መዳረግ የለበትም። በሶማሊያ በሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ የሚደርሰው በደል በሁላችም ላይ የደረሰ በደል ነው፤ በእነርሱ ስብዕና ላይ እየደረሰ ያለው ውርደት በአገራችን ላይ የደረሰ ውርደት ነው።
የጦሩ አዛዦቹ በወታደሩ ስቃይና ሞት ከብረው የከተማ ድሆችን እያፈናቀሉ ሕንፃዎችን እየገነቡ፤ የባንኩን፣ የኢንሹራንሱን፣ የገቢና ወጪ ንግዱን እያጧጧፉ ነው። የወታደር ልብስ ቢለብሱም፤ “ጄኔራል እከሌ” ተብለው ቢጠሩም በተግባር መጥፎ ነጋዴዎች እንጂ ወታደሮች አይደሉም። እነዚህ የስም ጄኔራሎች በጦርነት ውስጥም የሚታያቸው ንግድና ገበያ ነው። በእንደነዚህ ዓይነቶች አዛዦች ተመርቶ ጦርነትን ማሸነፍ አይቻልም።

አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ በህወሓት የጦር አዛዦች ብቃት ማነስ፣ ስግብግብነትና ቸልተኝነት ሳቢያ በሶማሊያ እየሞቱ፣ እየቆሰሉ፣ አስከሬናቸው እየተዋረደ ስላለው ኢትዮጵታዊያን የሚሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።
ከሶማሊያ ውጭም የኢትዮጵያ ወታደር የሚገኝበት ሁኔታ እጅግ አሳዛኝ ነው። በተለይም በሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደር እንደ ስሙ “የአገር መከላከያ ሠራዊት” በመሆን ፋንታ ወገንን ማጥቂያ ሠራዊት እየሆነ ነው፤ አገርን በመከላከል ፋንታ ወገንን ማጥቃት የሠራዊቱ የዕለት ተዕለት ተግባር ሆኗል። ለዚህ አሳፋሪ ተግባር ሠራዊቱ ራሱ መላ ሊፈልግለት ይገባል።

Tuesday, October 20, 2015

የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት አስመረቀ!!

የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት አስመረቀ፡፡

 አርበኞች ግንቦት 7 በሁለት ድርጅቶች ማለትም በኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር እና በግንቦት 7 ንቅናቄ ውህደት ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ከተመሰረተ በኋላ ከትናትና በፊት እሁድ ዕለት ጥቅምት 7 ቀን 2008 ዓም ለሁለተኛ ጊዜ ብዛት ያላቸውን አርበኛ ታጋዮች ለሦስት ወራት አሰልጥኖ አስመርቋል፡፡

እነዚህ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሁለተኛ ዙር ተመራቂ አርበኛ ታጋዮች ለሦስት ተከታታይ ወራት የተሰጣቸውን የፖለቲካ፣ የወታደራዊ እና ሌሎች ተያያዥ የሆኑ የመረጃና ደህንነት ትምህርቶችን በሚገባ ወስደው በሁሉም መስክ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ ነው ሊመረቁ የቻሉት፡፡

እጅግ በጣም ደማቅ በሆነ ስነ-ስርዓት በተከናወነው የምረቃ በዓል ላይ ከተለያዩ ቦታዎች ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች የታደሙ ሲሆን የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር አርበኛ ታጋይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድርጅቱ የትምህርትና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ታጋይ ተስፋሁን ተገኝ ንግግር በማሰማት ለተመራቂ አርበኛ ታጋዮች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከውህደቱ ኋላ የመጀመሪያውን ዙር ሰልጣኞች ያስመረቀው ግንቦት 2 ቀን 2007 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል፡፡

Monday, October 19, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ በሚኒሶታ ደማቅ ህዝባዊ ስብሰባ አካሄደ!!

ይህ የምናደርገው መሰዋእትነት በሂዎታችን ለአንዴና ለመጨረሻ የሚደረግ ታሪካዊ መሰዋእትነት ነው ፤ ይህ የመጨረሻው እንደሚሆን አትጠራጠሩ ትግሉ እየፈጠነ ነው.. አቶ ናእምን የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የውጪ ዘርፍ ሃላፊ በሜኒሶታ ካደረጉት ንግግር

የአርበኞች ግንቦት 7 የገቢ ማሰባሰቢያ ሂደት ቀጥሎ ቅዳሜ በሜኒሶታ ያደረገው ህዝባዊ ስብሰባ የተዋጣና በአይነቱ ልዩ የሆነ እንደነበር ተገልጾል።

የከተማው ነዋሪ ታላቅ ተሳትፎ ያድረገበት ፣ የሁሉም የእምነት አባቶች የተሳተፉበት በዚህ ዝግጅት አቶ ናእምን የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የውጪ ዘርፍ ሃላፊ ና የግንባሩ የምክር ቤት አባል በተገኙበት ታሪካዊ የተባለለት ደማቅ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ሂደት ተደርጎል። አቶ ናእምን ህዝቡ አሁን ሁሉም ተሞክሮ የቀረውን ብቸኛና ወደን ሳይሆን ተገደን የገባንበትን ታሪካዊ ሀገርን የማዳን የነጻነት ትግሉን የምንቀላቀልበትና የምንረዳበት ጊዜ አሁን ነው። ምናልባትም በሂዎታችን ለነጻነት የምናደርገው የመጨረሻ እርዳታ እና መሰዋእትነት ሊሆን የሚችል ትግል ላይ ነው ያለነው። ኢትዮጵያ በታሪኮ እንደ ወያኔ ያለ የሀገር ውስጥ ወራሪ ጠላት ገጥሞት አያውቅም። ይህን ትግል በኢትዮጵያ ለሚደረገው የዴሞክራሲ; የነጻነት የፍትህ ትግል የመጨረሻ እንደምናደርገው አትጠራጠሩ ብለዋል።

በሜኒሶታ አዘጋጅ ኮሚቴ የጣይቱ ልጆች ፎቶ ግራፍ ለጫራታ ቀርቦ ከፍተኛ በሆነ ሽያጪ መሸጡን ገልጸው በርካታ ገንዘብ ለድርጅት ማስገባታቸውን አስታውቀዋል። ይህን ዝግጅት ያዘጋጀው በሜኒሶታ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ተሰባስበው እንደሆነም ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ይህ በንዲህ እንዳለ ባለፈው ሳምንት በጆርጂያ አትላንታም ድርጅቱ የተሳካ የገቢ ማሰባሰብ እንዳደረገ ገልጾልናል። የአትላንታ የአርበኞች ግንቦት 7 ቻፕተር እንደገለጸው በዚሁ ዝግጅትም አቶ ናእምን ተገኝተው ሰፊ ማብራሪያ በቪዲዮ የተደገፈ ዝግጅት ለተሳታፊው አቅርበዋል።

Ethiopian Drought Threatens Growth as Cattle Die, Crops Fail

(Bloomberg) – Saado Osman straps two bulging sacks of United Nations wheat to her donkey, one of the few animals the 70-year-old eastern Ethiopian herder has left since the rains stopped.

Like millions of others in the Horn of Africa nation she depended on that precipitation to provide fodder and water for her livestock. Now drought has killed 20 of her cattle and goats, leaving her family of 10 with just four animals.

“There is hunger here,” Saado said as she stood among a crowd receiving food relief in Afdem town in Ethiopia’s Somali region on Oct. 8. “For one year it has not rained.”

Rain failure from February to May this year in Ethiopia, one of Africa’s fastest growing economies, was compounded by a short and erratic primary wet season from June to September. That’s left 8.2 million people in need of emergency support, with the crisis set to worsen through September next year, according to the UN.

The effect may spread to the economy: agriculture accounts for 40 percent of output, employs almost 77 percent of Ethiopia’s 97 million people and receives significant government support, according to the World Bank.

Exacerbating the drought is El Nino, the periodic warming of the tropical Pacific Ocean in the area around the Equator. Ethiopia’s economy, which has averaged about 10 percent growth over the past decade, contracted by more than 3 percent in 2003, the last time El Nino occurred.

Ethiopia’s economy has diversified into services since then, and agriculture is less rain-dependent, meaning growth of about 10 percent is still achievable in the 12 months to July 7, said Abraham Tekeste, a junior finance minister. “It’s going to be a very challenging fiscal year,” he told reporters Thursday in the capital, Addis Ababa. “The El Nino effect is very clear.”

Ethiopia will spend 4 billion birr ($191 million) combating the drought this year and needs donor support, said Mitiku Kassa, who heads the government’s disaster response committee. There are plans to import 627,000 metric tons of wheat and 20,000 tons of edible oil, he said in an interview in Addis Ababa. In total, 15 million people may need food aid in 2015, and an extra $340 million is required for relief efforts this year, the UN said.

The number of children needing emergency treatment for malnutrition reached 43,000 in August, more than during any month in the last major Ethiopian humanitarian crisis in 2011, according to the UN.

“I think we have properly managed the disaster,” Mitiku said. “It’s not out of the control of the government and development partners.”

Saturday, October 17, 2015

ውሸት ውሎ አድሮ መጋለጡ አይቀርም!!!


ሥልጣንን በጠመንጃ አፈሙዝ ተቆጣጥሮ ያለው የወያኔ አገዛዝ ካለመታከት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ተአምር ሊመስል በሚችል መንገድ እያሳደኩ ነው እያለ ሲዋሽ አመታት ተቆጥረዋል። በተለይ ምዕራባዊያንን ሲያታልልበት የነበረው የዲሞክራሲ ጭንብል በምርጫ 97 ከተገፈፈበት ወዲህ ላለፉት አስር አመታት ባለ ሁለት አሃዝ እድገት አስመዝግቤያለሁ እያለ እጅ እጅ እስኪለን ድረስ በባዶ ሜዳ ስለ ልማትና የዕድገት ሲነግረን ሰነበቷል።

ወያኔ በጉልበት በሚያስተዳድራት ኢትዮጵያ የልማትና የእድገት ፕሮፓጋንዳ ስለ ሰበአዊ መብትና ስለዲሞክራሲ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለማፈኛና አፍ ለማዘጊያነት በማገልገል ላይ ይገኛል ። አለማቀፍ የሰባአዊ መብት ተቋማት ስለሰበአዊ መብት ጥሰት ለሚያቀርቡት አቤቱታ ሁሉ የሚሰጠው መልስ “ኢኮኖሚውን እያሳደግን ነው” የሚል ነው። ኢኮኖሚ ማደግ አለማደጉን ትርጉም የሚኖረው ከህዝብ የእለተ ተእለት ኑሮ ጋር ሲያያዝ መሆኑ ሁሉ ትርጉም አጥቷል። ራበኝ የሚለው ሰው ሁሉ ጠገብኩ ማለቱ ነው ተብሎም ይተረጎማል።

የውሸት ነገር ውሎ አድሮም ቢሆን መጋለጡ አይቀርምና ይኼው በቅርቡ የተከሰተው ድርቅ የወያኔን የውሸት ፕሮፓጋንዳ ክንብንብ ገፎታል። አለም በሙሉ አስር አመት ሙሉ በሁለት አሃዝ ሲያድግ የነበረ ኢኮኖሚ ባለበት ሃገር ውስጥ አንዲት የድርቅ አመት ካለርሃብና ልመና እንዴት መሻገር አቃተው የሚል ጥያቄ በሰፊው በማንሳት ላይ ነው። ወያኔ ለዚህ ጥያቄ መልስ የለውም። በአለም ዙሪያ ያለው ተመክሮ ሁሉ የሚያሳየው ወያኔ አድጌበታለሁ ብሎ ሲለፍፍ ከኖረው አሃዝ በታች በግማሽ ያደጉ ሃገሮች እንኳ አንድም ጊዜ አንድ የድርቅ ዘመን መሻገር አቅቶአቸው ሲንገዳገዱና መንግሥታቸው ለልመና ሲሄድ አለመታየቱን ነው።

ኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔ የሚያወራውን ያህል ያልሆነ ቢሆንም በአንዳንድ ከተሞች አካባቢ የሚታየው እድገት የተገኘው ከውጭ መንግስታት የገንዘብ ብድር፣ በአለም አቀፍ ተቋማት እርዳታ፣ ስደተኛው ኢትዮጵያዊ በገፍ በሚልከው ገንዘብና ወያኔ ከድሃውና ከነጋዴው ከዝርፊያ ባላነሰ ሁኔታ በሚሰበሰበው ግብርና መዋጮ የተገኘ እንጂ ወያኔ ባስፋፋው ኢንዱስትሪና ልማት እንዲሁም ሀገር ውስጥ በፈጠረው ሀብት አለመሆኑ የሚታወቅ ነው።

የወያኔ ሹማምንትና አገልጋዮች ሀብት በሀብት መሆናቸውን እንደ እድገት ካልቆጠርን በስተቀር ህዝባችን ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ኑሮውን እንኳን መደጎም አልቻለም ።በዝርፊያ ገንዘብ ሹማምንቱና የወያኔ ባለምዋሎች የገነቡትን ፎቅ የሀገር ልማት ነው ካላልን በስተቀር እውነተኛና የህዝብ ህይወት ከመሰረቱ የሚቀይር ልማት አገር ውስጥ አለመካሄዱ ትንሽ ገለጥ ሲያደርጉት የሚታይ ሃቅ ነው። አንድ የድርቅ ወቅት መሻገር አቅቶት ብዙ ሚሊዮኖችን ከረሃብና እልቂት መታደግ ያልቻለ ኢኮኖሚ አስር አመት ሙሉ በሁለት አሃዝ አድጓል ብሎ የሚያምን ሰው ሊኖር አይችልም።

Wednesday, October 14, 2015

በባህርዳር፤ በጎንደር እና በአጎራባች ከተማ ወጣቶች ኮርተናል!

በቅዱስ ዮሃንስ

በባህርዳር፤ በጎንደር እና በአጎራባች ከተማ ወጣቶች ኮርተናል! የፍርሀት ግድግዳን ደረማምሰዋልና!

ይህ አኩሪ የነፃነት ትግል አድማሱን አስፍቶ በሌሎችም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል!

ሰሞኑን የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ በባህርዳር፤ በጎንደር እና በአጎራባች ከተሞች የትግል ጥሪ ወረቀቶችን ለህዝብ በመበተን ሰፊ ስራ ሰርቷል። ስራዎች የተሰሩት ደግሞ እዚያው በሚኖሩ ነፃነት ናፋቂ የንቅናቄው አባላትና ደጋፊ ወጣቶች ነው። ድንቅ ስራ! አዎ! ይህ በሕወሓት አገዛዝ የተንገፈገፉት የአካባቢው ወጣቶች የነፃነት ትግሉን በአደራ ለመቀበላቸው አብይ ማረጋገጫ ነው። ይህ አኩሪ የትግል ንቅናቄ በሌሎቹም ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች ዘንድ በምሳሌነት ተወስዶ፤ አድማሱን አስፍቶ መቀጠል ይኖርበታል። እኛ ወጣቶች ሀገራችን በሕወሓት አገዛዝ ከተጋረጠባት እልቂትና የመፈራረስ አደጋ የማዳን ታሪካዊ አደራ አለብን! ሀገራችንን ማንም የወጭ ሀይል ደርሶ ከመበታተን አያድንልንም። ነፃነታችንንም እንዲሁ ማንም ሌላ አካል ደርሶ ሊያጎናጽፈን ፈጽሞ አይችልም። የሁሉም ነገር መፍትሄው በእጃችን ነው! አዎ! የሕወሓት አገዛዝ ለኢትዮጵያ የማይበጅ አጥፊ ስርዓት መሆኑን አውቀን በፅናት ለመታገል መወሰን! ከዚያ በየ አካባቢያችን መደራጀት፤ ከአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር ግንኙነት በመፍጠር ተጨባጭ ትግል ማድረግ መጀመር። አለቀ!! ለአብነትም ከሰሞኑ በባህርዳር፤ በጎንደር እና በአጎራባች ከተማ በሚኖሩ ወጣቶች እየተደረገ ያለውን ሰፊ ንቅናቄ መመልከት በቂ ነው። ይሄን ስናደርግ ብቻ ካሰብነው የነፃነት ዓለም በቶሎ እንደርሳለን። ሀገራችንንም ከተደቀነባት የመበታተን አደጋ እናድናታለን።

አዎ! ከሰሜን፤ ደቡብ፤ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ያለን ወጣቶች በዘር በሀይማኖትና በጎሳ ሳንከፋፈል በአንድነት በመነቃነቅ በአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦ ከዳር ለማድረስ የሞት ሽረት ትግል ማድረግ አለብን። ሰዓቱ ደግሞ አሁን ነው!! ተነሱ!!! ሁላችንም እንነሳ!!!

በአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የተጀመረው የነፃነት ትግል በኢትዮጵያ ወጣቶች ፊታውራሪነት ከዳር ይደርሳል!!

ከአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር ወደ ፊት!!

ወገን እማማ ኢትዮጵያ ተርባለች … የድረሱልኝ ጥሪዋንም እያሰማች ነው?!

የ1966ቱ እና የ77ቱ ዓይነት የረሃብ እልቂት ከመድረሱ በፊት ለወገኖቻችን እንድረስላቸው!

ከፍል- ፪

በዲ/ን ኒቆዲሞስ

በአገራችን በኢትዮጵያ የተከሰተውን የረሃብ አደጋ አስመልክቶ ከሰሞኑን በመጀመሪያ ክፍል ያስነበብበኳችሁን ጽሑፍ ባወጣሁ ማግሥት አንዲት በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የሆነች ወዳጄ የRFI ድረ-ገጽ ‹‹Sever Drought Threatens Millions of Ethiopia›› በሚል ርዕስ በአገራችን ስለተከሰተው ረሃብ የሚያትት ጽሑፍ በሾሻል ሚዲያ ላከችልኝ፡፡ ይህ የrfi ድረ ገጽ ያስነበበው ጽሑፍ እንደሚያትተው የኤሊኒኖ ክስተት በምሥራቅ አፍሪካና በኤዥያ በሚገኙ አገራት ባስከተለው የአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት አገራችን በድርቁ በከፍተኛ ኹኔታ ተጠቂ መሆኗን ዘግቦአል፡፡

ይህ ዘገባም አገራችን ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ1984-85 በርካታዎች ከቀዬአቸው በተፈናቀሉበትና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ካለቁበት የረሃብ ክስተት ጀምሮ አገሪቱ በምግብ እህል ራስን የመቻል ጥያቄ ውስጥ የወደቀች አገር መሆኗን በመግለጽ፤ የዘንድሮ በዝናም እጥረት ምክንያት የተከሰተው የድርቅም ከምሥራቅ አፋር ክልል እስከ ደቡብ ሶማሊያ ያለውን ሰፊ ቦታ እንደሚሸፍንና ረሃቡ በእነዚህ ቦታዎች ላይም ከፍተኛ የሆነ ማኅበራዊና ሰብአዊ ቀውስ እያደረሰ እንዳለ ይገልጻል፡፡
ይኸው rfi.fr ድረ ገጽ የተባበሩት መንግሥታት ባስነበበው ጽሑፉ ከጥቂት ወራት በፊት ያወጣውን ፬.፭ ሚሊዮን ተረጂዎች ቁጥር በአሁን ሰዓት ድርቁ ወደ ሌሎች የአገሪቱ ክልሎች በመስፋፋቱ የተነሣ ወደ ፰ ሚሊዮን እንዳሻቀበና ቁጥሩ ከዚህም በላይ ሊጨምር እንደሚችል ጠቁሟል፡፡

ይህን በአገራችን የተከሰተውን የረሃብ አደጋ በተመለከተ በአፋርና በሶማሌ ክልሎች ባደረጓቸው ሰፊ ምርምሮችና ጥናቶች የሚታወቁት የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ክርስቶፈር ክላፕሃም ለRFI በሰጡት ጠቅለል ያለ አስተያየት፡- ‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት ላለፉት ዐሥር ዓመታት ድርቅን ይህን ተከትሎም ሊከሰት የሚችለውን ረሃብን ለመከላከልና ዜጎቼ በምግብ እህል ራሳቸውን የሚችሉበትን የተሳካ ውጤታማ የሆነ ሥራን ሠርቼያለሁ በሚልበት በዚህ ወቅት እንዲህ ዓይነቱ የረሃብ አደጋ መከሰቱ ነገሩን እንቆቅልሽ ያደርገዋል ሲሉ ነው፡፡ አስተያየታቸውን የሰጡት፡፡

The Ethiopian government having established what is generally considered to be quite an efficient system for controlling the effects of drought and malnutrition is probably embarrassed and surprised that such a serious issue has risen, Christopher Clapham, a Professor specialized in the region at Cambridge University, told to rfi. አሳዛኙ እውነታ ደግሞ ይህ የረሃብ አደጋ በቀጣይ ዓመታትም ተባብሶ የሚቀጥል መሆኑን ነው ጥናቶች የሚጠቁሙት፡፡

ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት የኢትዮጵያ መንግሥት 33 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ መድቦ ድርቁ የከፋ አደጋ ባደረሰባቸው የአገሪቱ ክልሎች አፋጣኝ የሆነ የምግብ እህል እርዳታ እያደረገ መሆኑን ቢናገርም የተባበሩት መንግሥታት ከሰሞኑን ባወጣው ዘገባ ግን ለረሃብ የተጋለጡ ወገኖቻችንን ቁጥር መሻቀቡንና እነዚህን ወገኖቻችንንም ለመታደግ ከ237 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ እንደሚያስፈልግ ጠቅሶአል፡፡

መንግሥት ዘግይቶም ቢሆን በአገሪቱ የተከሰተውን ድርቅ አስመልክቶ ለጋሽ አገራትና ዓለም አቀፍ እርዳታ ድርጅቶች እጁን እንዲዘረጉለት የተማጸነ ቢሆንም ድርቁ በአገሪቱ የጋረጠውን የከፋ የረሃብ አደጋና እልቂት በተመለከተ ግን ሰፋ ያለና የተብራራ መረጃ በመስጠት በኩል ጉልህ ችግር እንዳለበት የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና መገናኛ ብዙኃን በሰፊው እየተናገሩና እየወቀሱ ነው፡፡

በአገራችን በተለያዩ ጊዜያት የተከሰቱትን የረሃብ አደጋዎች ከወዲሁ አስቀድሞ በመግለጽ፣ ቅድመ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ረገድና በረሃብ የሚያልቁ ወገኖቻችንን ለመታደግና አደጋውን ለመቀነስ መወሰድ ስላለበት አፋጣኝ ዕርምጃዎችን በተመለከተ ትልቅ ችግር እንዳለ ግልጽ ነው፡፡ የኢሕአዴግ መንግሥት ፈጣን ልማትና ዕድገት እያስመዘገብን ነው፣ ሚሊዬነር የሆኑ አርሶ አደሮችንና አርብቶ አደሮችን እያፈራን ነው፣ ረሃብ ካሁን ወዲያ ታሪክ ይሆናል እያለ ባለበት ወቅት እንዲህ ዓይነቱ አንገትን የሚያስደፋ የረሃብ አደጋ መከሰቱ ራሱን በደንብ መፈተሽ እንዳለበት ትልቅ መሳያ ይመስለኛል፡፡

ይኸው የረሃብ አደጋ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ብቻ ሣይሆን በከተሞችም እየተስፋፋ ያለ መሆኑን መስማት፣ ማወቅ ደግሞ እጅጉን የሚያሰቅቅ ነው፡፡ የፌዴራሉ መንግሥት መቀመጫና የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት በሚገኙባትና የአፍሪካ ርእሰ መዲና በምትባለው በአዲስ አበባ ሣይቀር ባሉ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ሕፃናት በረሃብ የተነሣ በትምህርት ገበታቸው ላይ እያሉ ተዘልልፍለፈው እወደቁ መሆናቸውንና እንዲሁም በኑሮ ውድነት ምክንያት በርካታ ቤተሰቦች በፈረቃ ለመብላት መገደዳቸውን በአገሪቱ የሚገኙ እንደ ሪፖርተር ጋዜጣና ሸገር ራዲዮ በተለያዩ ጊዜያት ዘግበዋል፡፡

በተለይ በብዙዎች ዘንድ አፍቃሪ ኢሕአዴግ፣ እንደው ያሰበውንና የተመኘውን ያህል ሰሚ ጆሮ፣ አስተዋይ ልቦና አላገኘም እንጂ የመንግሥት መልካም መካሪና ዘካሪ እንደሆነ አብዝቶ የሚታማው የሪፖርተር ጋዜጣ ባለፈው እሑድ ዕትሙ ርዕሰ አንቀጹ ላይ፡- ‹‹በድርቅ ለተጎዱትም ሆነ ለከተማ ድኅነት ፈጣን ምላሽ ያስፈልጋል›› በማለት ያስነበበው፣ በአደጋ ማስጠንቀቂያ የታጀበው ርዕሰ አንቀጹ አገሪቱ ያለችበትን እውነታና የተጋረጠባትን የረሃብ አደጋ ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ነው ለማለት ያስደፍራል፡፡

ዘንድሮ በአገራችን የተከሰተውን ድርቅና ይህንም ተከትሎ በአገራችን የተከሰተውን የረሃብ አደጋ በተመለከተ መንግሥትም ሆነ በአገሪቱ ውስጥ ያሉ የመገናኛ ብዙኃን ሰፊ ሽፋን ሰጥተው እየዘገቡት ነው ብሎ ለመናገር አያስደፍርም፡፡ ያው በታሪካችን እንደምናውቀው ሺዎች ከቀዬአቸው ካልተፈናቀሉና ካልሞቱ በስተቀር ‹‹ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም›› እንደሚባለው እየሆነ ያለ ነው የሚመስለው፡፡

ታሪካችን እንደሚነግረን በ፲፱፻፷ዎቹ በአገራችን ሰሜናዊ ክፍል በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው ሲፈናቀሉና ለአሰቃቂ ሞት ሲዳረጉ የዘውዱ መንግሥት በክብረ በዓልና በሌሎች ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ነበር ተጠመዶ የነበረው፡፡ እናም በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቹን ከቀዬአቸውና ላፈናቀለውና ለአሰቃቂ ሞት ለዳረጋቸው ለነበረው የረሃብ አደጋ ምላሽ የሰጠው ዘግይቶ ነበር፡፡

በወቅቱ ይህ የረሃብ እልቂት እንዴት ወደ አደባባይ ሊወጣ እንደቻለ በሰማኒያዎቹ በሰሜን አሜሪካ ይታተም በነበረው ‹‹ሰምና ወርቅ›› በተባለው ጥናታዊ መጽሔት ‹‹ድርቅና ጠኔ በኢትዮጵያ›› በሚል ጥናታዊ ጽሑፋቸው ውስጥ ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ እንዲህ ገልጸውት ነበር፡፡ በወቅቱ የረሃቡን መከሰት የሰሙት ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ፣ ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም፣ ዶ/ር አሉላና ለሌሎች የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ባልደረቦቻቸው በግላቸው ሴስና አውሮፕላን ተከራይተው ረሃቡ የከፋ አደጋ ወዳደረሰበት ወደ አገራችን ሰሜናዊ ክፍል መረጃ ለመሰብሰብ ተጓዙ፡፡

ከወሬ ባለፈ በዓይናቸው ያዩትና ምስክር የሆኑበት የረሃብ አደጋና የወገኖቻቸው አሰቃቂ የሆነ እልቂት እጅጉን ልባቸውን የነካቸው እነዚህ ምሁራን በድርቅ የተጋለጡትን የአገሪቱን ግዛቶች፣ በረሃቡ የተነሣ እጅጉን የተጎዱትን ወገኖቻቸውን በማነጋገር በምስልና በቪዲዮ ያሰባበሰቧቸውን መረጃዎች በፕ/ር መስፍን አማካኝነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ እንዲታይ ተደረገ፡፡

ይህን አሰቃቂ የሆነ የወገኖቻቸውን እልቂት፣ የሞት ጥላ ያንዣበባቸውን፣ ቆዳቸው ገርጥቶና አንጀታቸው ተጣብቆ፣ ከሰው መልክና ወዘና የወጡትን ወገኖቻቸውን፣ በእናቶቻቸው ደረት ላይ ተጣብቀው የሟች እናቶቻቸውን ጡት ሲመገምጉ የሚታዩ ሕፃናትን ምሰልና ቪዲዮ የተመለከቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ማኅበረሰብ ወገኖቻችን በረሃብ እያለቁ አንማርም፣ መንግሥት የረሃቡን እልቂት ለለጋሽ አገራትና ለዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ያጋልጥ በሚል ያስነሱት ዓመፅ ቀስ በቀስ ተባብሶ ለዘውዱ ሥርዓት መገርሰስ ምክንያት ሊሆን እንደበቃ እናውቃለን፡፡

Finally Hailemariam Desalegn Appeals for Food Aid

Ethiopia Appeals for Food Aid Following Poor Crop Yields

(AP) – Ethiopia’s government is calling for international assistance to help feed 8.2 million people after erratic rains devastated crop yields.

Climate shocks are common in Ethiopia and often cause poor or failed harvests that lead to acute food shortages.

The government has allocated $192 million for food and other aid and is appealing for $596 million in assistance from the international community for the remainder of 2015, said Mitiku Kassa, secretary of the Ethiopian Disaster Prevention and Preparedness Committee.

More than 300,000 children are in need of specialized nutritious food and a projected 48,000 more children under 5 are suffering from severe malnutrition, according to a government assessment conducted in September.

The situation is “incredibly serious,” said John Aylieff, an official in Ethiopia with the U.N.’s World Food Program, who said Ethiopia needs the international community to help remedy the worst effects of El Nino conditions.

The conflict in South Sudan is also exacerbating the food insecurity situation, said Dennis Weller, the USAID mission director in Ethiopia. Since the outbreak of violence in South Sudan in mid-December 2013, hundreds of thousands of South Sudanese refugees have fled to Ethiopia and are living alongside local communities.

Saturday, October 10, 2015

ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጀርባ


ከሁለት አመት በፊት በቂ ህዝባዊ ምክርና ውይይት ያልተካሄደበት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተግባር ላይ ለማዋል የተደረገው ሙከራ በበርካታ የኦሮሞ ተማሪዎች ተቃውሞ እንደገጠመውና በየኮሌጁ በተነሱ ተቃውሞዎች ሳቢያ በርካታ ወጣቶች በወያኔ እንደተገደሉ ብዙዎች በእስር እየማቀቁ እንዳሉ ይታወቃል። ግጭቱ የፈጠረው ቀስል ገና ባላገመ ማግስት በአሁኑ ወቅት የህወሃቱ አባይ ጻሀይ በውድም በግድም ፕላኑ “ይተገበራል” ብሎ በዛተው መሰረት ተግባር ላይ ለማዋል ሰሞኑን ሽር ጉድ ተይዟል።
ከዚህ ማስተር ፕላን በስተጀርባ የተደበቀው የህወሃትና ጀሌዎቹ አላማ በአግባቡ አለመተንተኑ የፕላኑ ተቃዋሚዎች ኦሮሞዎች ብቻ በመሆናቸው ጥያቄው የግዛት ስፋትና ጥበት ወይም ባለቤትነት ጉዳይ መስሎ ይታይ እንጂ ነገሩ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚያስቆጪና ተቃውሞ ሊያስነሳ የሚገባው ደባ ነው። ከህወሃት/ ወያኔ ማስተር ፕላኑ ጀርባ የመሬት ዝርፊያ እቅድ እንዳለው አርበኞች ግንቦት 7 ከእስከ አሁኑ ተመክሮና ባህሪያቸው በግልጽ ማየት ይቻላል ብሎ ያምናል። እስከዛሬ ባለን ተመክሮ ከተማውን በማስፋፋት ስምና መሬት የመንግስት ነው የሚለውን ሰበብ በመጠቀም ድሃ ገበሬዎችን በማፈናቀል የተዘረፈውን መሬት ልብ ማለትና ማስታዎስን ያሻል።

በሀገራችን ቅጽበታዊ ሚሊየነር የሆኑት የወያኔ ሹማምንት፣ ዘመዶቻቸውና ባለሟሎቻቸው ዋናው የሃብታቸው ምንጪ ድሆችን በማፈናቀል በገፍ እየዘረፉ የሸጡትና የተቆራመጡት መሬት ነው። የአዲስ አበባ መሬት የወያኔ የወርቅ ማእድን ጉድጓድ ከሆነ ቆይቶል። በየከተማው ዙሪያ ያሉ ምስኪን ገበሬዎች የረባ ካሳ እንኮን ስላላገኙ ከግብርና ወጥተው ወደኩሊነትና የቀን ሰራተኝነት ተበታትነው ቤታቸው ፈርሶ ይገኛል።

የወያኔ መንግስት ይህን ማስተር ፕላን ስራ ላይ ለማዋል የሚስገበገብበት ዋናው ምክንያት የሀገርና ከተማ ልማት ጉዳይ አይደለም። የከተማው መሬት ተዘርፎ በማለቁ ሌላ በገፍ የሚዘረፍ መሬት ለማመቻችት ብቻ ነው። ችግሩ ለምን ፕላን ኖረ፣ አዲስ አበባ በአግባቡ ማደግና መልማት የለባትም የሚል አይደለም። ቁምነገሩ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን በቅጽበት እያፈናቀለና እየደኸዩና ቤተሰብ እየፈረሰ፤ በጥቂት ህገ ወጥ ባለስልጣናት የሚደረገው ሀፍረት የለሽ ዝርፊያ ነው ችግሩ። በመሆኑም ይህን የዝርፊያ ተግባር ብሄረሰብ ሳንለይ ሁላችንም ልንቃወም ይገባል። ይህ ማስተር ፕላን የህግ የበላይነትና ተጠያቂነት በሌለበት ሁኔታ ስራ ላይ በአግባቡ ስራ ላይ መዋል አይችልም። በፕላኑ የተጠቃለለውን ህዝብና አካባቢ ሊጠቅም የማይችል ፕላን ሊሆን የሚችለው የዝርፊያ ፕላን ብቻ ነው።

Thursday, October 8, 2015

ሥርዓታዊ ክሽፈት “Systemic Failure” (ይሄይስ አእምሮ)

“በሉ እናንተም ሂዱ እኛም ወደዚያው ነው፤ ዱሮም ምንገደኛ ፊትና ኋላ ነው፡፡”

“አፄ ምኒልክ ከልምድዎ አንዳንድ እያለ ቀረልዎ፤
አምናስ አለማያ ነበሩ፣ ዘንድሮን ወዴት ዋሉ፡፡” ዳዊት

“ከአባ ቁፋሮ እሸት ተበልቶለት” እንዲሉ እዚህና እዚያ ጥርዥ ብርዥ ከሚሉ እጅግ ጥቂት ለኅሊናቸው ያደሩ የሀገር አለኝታ ወገኖቻችን መካከል አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ብቻ ብዙ ተለዩን፡፡ ነፍሳቸውን ይማርልን፤ ከስቃይ ወደስቃይ አያስገባብን፡፡

ፈረንጆች “When an old man dies, a big library is closed.” የሚሉት ምሣሌያዊ አባባል አላቸው፡፡ ሁላችንም የምንጋራው ነው – እናም “አንድ አንጋፋ ሰው ሲሞት አንድ (ትልቅ) ቤተ መጻሕፍት እንደተዘጋ” ቢቆጠር ለዚህ እውነት ሙሉጌታ ሉሌ ዓይነተኛ ምሣሌያችን ነው፡፡ ጋሽ ሙሌ ጠላትም ወዳጅም ሊክደው የማይቻለው ተንቀሳቃሽ ኢንሣይክሎፒዲያ ነበር፡፡ አንባቢ ብቻ አልነበረም፤ ያነበበውን የማይረሣና ባስፈለገ ጊዜ ሁሉ የሚጠቀምበትም ነበር፡፡ ለሀገሩና ለወገኑ የሠራውን ታሪክ ይዘክረው እንጂ እዚህ ዘርዝሬ መጨረስ አልችልም፡፡ አይሞከርምም፡፡ ለተወሰነ ጊዜ አብሬው ለመሥራት በመታደሌ ያን በማስታወስና እንደጀግና የብዕር ሰውነቱም የሁላችንም ሰብኣዊ ሀብት በመሆኑ እግዚአብሔር ነፍሱን እንዲምራት፣ ለቤተሰቡና ለወዳጅ ዘመዶቹም መጽናናትት እንዲልክልን አንድዬን እየለመንኩ ይህች መጣጥፍ ለርሱና ሰሞኑን በሞት ለተለዩን ውድ ኢትዮጵያውያን መታሰቢያ ትሆንልኝ ዘንድ ክቡራን አንባቢዎቼን በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታም በተለይ በስፖርቱ ቤተሰብ እጅግ ተወዳጅ የነበረውና ለእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ በነበረው ሞልቶ የሚፈስ ፍቅር በብዙዎቻችን ዘንድ በስፋት የሚታወቀው አቶ አቤሴሎም ይህደጎ ከሙሌ ጋ የሰማዩን ሠረገላ ተጋርቶ በአንድ ወቅት ተለይቶናል፡፡ አቤን ነፍሱን ይማርልን፤ የሚወዳት ሀገሩ የእምዬ ኢትዮጵያ አምላክ ዋጋውን በሰማይ ቤት ይክፈልልን፡፡ የጀብዱ ሥራ ባለቤት የነበረው ኮሎኔል ባጫ ሁንዴንም የተነጠቅነው በዚሁ ሰሞን ነው፡፡ ሀገራችን ደህና ሰው አይበረክትላትም፡፡ ስንትና ስንት ሀገር ሻጭና ቸርቻሪ ወምበዴ እያለ እነዚህን እርሾዎች ወሰደብን፡፡ ከርሱ ጋር ማን ይታገላል? የሚገርመው አጋጣሚ ግን ወያኔዎች በዘርና በነገድ ሊለያዩን ሲሞክሩ አጅሬ ሞት ግን መማር አንፈልግም እንጂ ለመማር ዝግጁ ለሆንን ዜጎች የእነዚህን ሦስት ምርጥ ዜጎች ዘውጋዊ ማንነትና በአንዴ መጠራት ልብ ብለን አንድ ከማያደርጉን ነገሮች ይልቅ አንድ የሚያደርጉን ነገሮች እንደሚበዙ መረዳት በተገባን ነበር፡፡ በፈጣሪ ዘንድ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ … ብሎ ነገር እንደሌለና ማዳላት የሰው ባሕርይ እንደሆነ ሞትም በኮታ የሚጠራ በሚመስል መልኩ ለማንም ሳያዳላ ከሁሉም በመውሰድ በአንድ ሰሞን የማይረሳንን ትምህርት ሰጥቶናል፡፡

የሕዝብ ሰው በኪነ ጥበቡም፣ በሥነ ጽሑፉም፣ በስፖርቱም፣ በወታደራዊ መስክም፣ ወዘተ. በመሆኑ በቅርቡ የተለየችንን ብርቅዬ የመድረክ ፈርጥ ሰብለ ተፈራንም ማስታወስ ይገባኛል፡፡ አንድ ታዋቂና ዝነኛ ሰው ሲለይ ከየቤተሰቡ አንድ ሰው እንደተለዬ ይቆጠራልና የእርሷም መለየት ብዙ ጉድለትን በየቤታችን እንደሚያስከትል የታመነ ነው፡፡ የሁሉንም ነፍስ ይማርልን፤ ይህን ሠራሽ/አልሠራሽ ብሎም አይጠይቅብን፡፡ የሕዝብ ሰዎች እንዲበዙልንና ከጠፋንበት ባድማ መሬት ፈልገው እንዲያወጡን ፈጣሪያችን ይዘዝልን፡፡

የኔ ሀዘን አንዳንዴ ቅጥ የለውምና ይቅርታችሁን፡፡ እናም በያዝነው ወር መጀመሪያ ገደማ በሕይወት እያለ በቁም ሞት የተለየንን የዴምሕቱን ሞላ አስገዶም ነፍስ ፈጣሪ እንዲምርልንና በአብርሃምና በያዕቆብ ነፍሳት አጠገብ እንዲያኖርልን እንጸልይለት – ወዶና ፈቅዶ እንዲያ አልሆነምና፡፡ በሥጋው የሞተ ትልቅ ዕዳ ተወጥቷልና ግልግል ነው፡፡ የሞላና የነሞላ ዓይነቶቹ ሞት ግን የትውልድ መጠቋቆሚያና የታሪክ መዘባበቻ ሆኖ መቅረትን ስለሚያስከትል፣ በዚያም ላይ ቀሪው ቤተሰባቸው በሀፍረት እየተሸማቀቀ አንገቱን ደፍቶ ለመኖር ስለሚገደድ ይህ ዓይነቱ ሞት እጅግ የሚያሰቅቅና ከሆድና ከምድራዊው የዘረኝነት አባዜ ጋር የሚቆራኝ ከፍተኛ ጉዳት አለው፡፡ ሰውን ያህል ትልቅ ፍጡር ውሻ ይመስል ደምና አጥንት እያነፈነፈ የመጨረሻ ነው ተብሎ በሚጠበቅ ወሳኝ ሰዓት ላይ ያመኑትን የዋሃን የትግል ጓኞቹን ከድቶ ወደጎሣዊ ጎራው ከተቀላቀለ ይህ ነገር ከሆድም በላይ ነውና በወዲያኛው ዓለምም በፈጣሪ ዘንድ ሳይቀር ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍል እንደሚችል ማንም ወገን ሊገነዘብ ይገባዋል፡፡ ፈጣሪ የሰውን ልጅ ሲፈጥር ትግሬና አማራ ብሎ ሳይሆን በጎልዳፋው ግዕዜ “ንግበር (?) በአርአያነ ወበአምሳሊነ” ብሎ ከዐፈርና ከምራቅ አዋህዶ ሠራው እንጂ እንደወያኔዎች የደንቆሮዎች ዘፈን የሰው ግርድና አመሳሶ እንዲኖረው ጥቁርና ነጭ ወይም 11 ቁጥርና ዝናር ባገቴ አድርጎ አልነበረም – እነዚህ ቅጥልጥሎች ፍጹም ሰውኛ እንጂ መለኮታዊና ተፈጥሯዊ እንዳይደሉ ለመጠቆም ኮሌጅ መበጠስና ጥናትና ምርምር ማካሄድ አያስፈልግም፡፡ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያውያንም በዘርና በጎሣ ተለያይተው ሞተው ከዚች ከዓለም የቆዳ ስፋት አኳያ የበሬ ግምባር ከማታክል መሬት የተገኙ የአዳምና የሔዋን ዘሮችን በቋንቋ፣ በሃይማኖትና በነገድ ለመከፋፈል የተደረገው ከፍተኛ ወያኔዊ ጥረት በእጅጉ ያስደምማል፤ በዚህ ሸውራራ የወያኔ የዘር ቀመር አንዱን ለሞት ሌላውን ለሀብትና ለሹመት ማብቃት ከዘቀጠ ሰይጣናዊ አስተሳሰብ የሚመነጭና የመጨረሻ ዕጣ ፋንታን ጨለማ የሚያለብስ የርኩሳን መናፍስት የተረገመ ተግባር ነው ፡፡ ይህን የወያኔ የክፋት መንገድ ተከትሎም ሕዝብን መካድና የትግልን መንፈስ ለመበረዝና ለመከለስ መሞከር ከሰውነት ደረጃ የሚያወጣና በቁም ነፍስ ይማር የሚያሰኝ ነውረኛ ድርጊት ነው፡፡ ነገን ለሚያውቅ ሰው አሣፋሪነቱ ወደር አይገኝለትም፤ ችግሩ የዚህ ብልሹ ቲያትር ተዋንያን ሆድ እንጂ ጭንቅላት ብሎ ነገር አልፈጠረባቸውም፤ የአባቶቻቸው የባንዳዎቹ ልጆች ከመሆናቸውም በተጨማሪ እከሌ ከእከሌ ሳይባል የውጪ ጠላቶቻችን ልዑካንና በቀደምት ጀግኖች ኢትዮጵያውያን የጋራ ትግል ከሽፎ የነበረ ቆይቶና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በተለዬ ሥልት አንሠራርቶ የተከሰተ ኢትዮጵያን የመበታተን ግልጽ ሤራ ለማራመድ የተመረጡ ቅጥረኞች ናቸው፡፡ ቀን የሰጠው ቅል ድንጋይ እንደሚሰብር እነዚህም የባንዳ ልጆች ፈረንጆች የባረኩላቸውና ካለማሽን በዕውቅ የተሰናዳላቸው የክፍለ ዘመኑ ትልቅ ሎተሪ ወጥቶላቸው ለጊዜው ይሠሩትን አጥተው በአረመኔያዊ ድርጊቶቻቸው ውጤት ምክንያት በደስታ ሰክረው ይታያሉ፡፡ የተሰጣቸው ቀን ማለቁን ግን እንኳን እነሱ እኛም ያወቅን አንመስልም፡፡ ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን – ሃያታቸው አልቋል፤ ቁጥባቸው መንምኗል፤ የጀዛቸውን ሊያገኙ ዐውድማቸው ተለቅልቆ ሊበራዩ ጊዜው ደርሷል፡፡ ብሮባጋንዳ እንዳይመስልህ ወንድሜነህ፡፡ ዕድሜ ለምን ብቻ፡፡ “እንዲህ ጨሶ ጨሶ የነደደ እንደሆን፤ ያመዱ ማፍሰሻ ሥርፋው ወዴት ይሆን” ተብሎ በቁጪት የተቀነቀነው ዛሬ በ”ፈሪዎች” ዘመን ሣይሆን የፈጣሪን ፍርድ በማይቀጣጠቡበት የጥንት ዘመን ነው፡፡ Hence, TPLF cannot be an exception, though it is against all exceptions. As a matter of natural bent, nihilists like TPLF are always anti generalizations, including exceptions, taking into account the saying, “All generalizations have exceptions.”

ለማንኛውም በሞላ አስገዶም ፈለግ ለሚመሩ በሀገር ውስጥና በውጪ ላሉ ጭንጋፍ ዜጎቻችን ሁሉ ፈጣሪ ምሕረቱን ሰጥቷቸው ነፍሳቸውን ወደገነት እንዲያስገባላቸው እየተማጠንኩ ወደዋናው ርዕሴ ልግባ፡፡

Sunday, October 4, 2015

7.5m going hungry as Ethiopia crisis worsens

ADDIS ABABA: The number of hungry Ethiopians needing food aid has risen sharply due to poor rains and the El Nino weather phenomenon with around 7.5 million people now in need, aid officials said on Friday.

That number has nearly doubled since August, when the United Nations said 4.5 million were in need - with the UN now warning that without action some "15 million people will require food assistance" next year, more than inside war-torn Syria.

"Without a robust response supported by the international community, there is a high probability of a significant food insecurity and nutrition disaster," the UN Office for the Coordination of Humanitarian Affairs, OCHA, said in a report.

The UN children's agency, Unicef, warns over 300 000 children are severely malnourished.
The Famine Early Warning Systems Network (FEWS NET), which makes detailed technical assessments of hunger, predicted a harvest "well below average" in its latest report.
"Unusual livestock deaths continue to be reported," FEWS NET said. "With smaller herds, few sellable livestock, and almost no income other than charcoal and firewood sales, households are unable to afford adequate quantities of food."

Ethiopia, Africa's second most populous nation, borders the Horn of Africa nation of Somalia, where some 855 000 people face need "life-saving assistance", according to the UN, warning that 2.3 million more people there are "highly vulnerable".

El Nino comes with a warming in sea surface temperatures in the equatorial Pacific, and can cause unusually heavy rains in some parts of the world and drought elsewhere.

Hardest-hit areas are Ethiopia's eastern Afar and southern Somali regions, while water supplies are also unusually low in central and eastern Oromo region.

Sensitive issue
Food insecurity is a sensitive issue in Ethiopia, hit by famine in 1984-85 after extreme drought.
Today, Ethiopia's government would rather its reputation was its near-double-digit economic growth and huge infrastructure investment - making the country one of Africa's top-performing economies and a magnet for foreign investment.

Friday, October 2, 2015

ድርጅታችንን እናጠንክር፤ በጽናት እንታገል!


“የአርበኞች ግንቦት 7 አባል በመሆኔ እኮራለሁ” እያሉ በአገዛዙ የይስሙላ ችሎት ሳይቀር በድፍረት የሚናገሩ ወጣቶች ተፈጥረዋል። ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲ፣ ለእኩልነትና ለሀገር አንድነት መስዋዕትነት መክፈል የሚያኮራ ተግባር መሆኑ በተግባር የሚያሳዩ ወጣቶች መጥተዋል፤ አሁን በርካቶችም እየመጡ ነው። ወያኔ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በማኅበረሰባችን ውስጥ የዘራው የፍርሀትና የአድርባይነት ስሜት በራሱ በወያኔ የአገዛዝ ዘመን ተወልደው ባደጉ ወጣቶች እየተናደ፤ በምትኩ ሊጠፋ ተቃርቦ የነበረው የአገር ፍቅርና የአርበኝነት ስሜት እያንሰራራ ነው። ቅንነት፣ ሀቀኝነት እና ጽናት ከተጣሉበት ጉድጓድ አቧራቸውን አራግፈው እየተነሱ ነው። በማኅበረሰባች ውስጥ ትልቅ የስነልቦና አብዮት እየተካሄደ ነው።

ከስነልቦና ለውጡ ጋርም በተግባር የአገር አድን ሠራዊትን የመቀላቀል ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ ነው። ወጣቶች የአገራቸው ባለቤት መሆናቸው ተገንዝበው የፓለቲካ ሥርዓት ለውጥ ለማምጣት በቁርጠኝነት መነሳታቸው ተስፋ ሰጪ ነገር ነው። 

አርበኞች ግንቦት 7 በዚህ የለውጥ ወቅት ውስጥ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አጽንዖት ልንሰጣቸው ስለሚገቡ የድርጅትና የሥነሥርዓት (ዲሲፕሊን) አስፈላጊነት ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና በተግባርም መተርጎም አስፈላጊ ነው ብሎ ያምናል።
ወጣቶች ትግሉን ለመቀላቀል መሻታቸው መልካም ነገር ነው። ሆኖም ግን በድንገት ብድግ ብለው መንገድ ከመጀመር ይልቅ ከሚያምኗቸው ወዳጆቻቸው ጋር የመሠረቱት፤ ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋርም ትስስር የፈጠረ ስብስብ አካል ሆነው መቆየታቸው እጅግ አስፈላጊ ነው። 


በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሆኖ የሚስጢር ድርጅት ማዋቀር አስቸጋሪ መሆኑ የማያጠራጥር ቢሆንም የማይቻል ነገር ግን አይደለም። ወጣቶቻችን በአምባገነን ሥርዓት ውስጥም ሆነው በዲሲፕሊን የታነፀ ድርጅት የመፍጠርን ክህሎት መላበስ ይገባቸዋል። ይህንን ማድረግ ስንችል ነው የህወሓትን ፀረ-አገርና ፀረ-ትውልድ ተግባር ማክሸፍ የምንችለው። ትግሉን በሁሉም የኢትዮጵያ ግዛቶች ማቀጣጠል የምንችለው በየአካባቢው የተደራጀ የለውጥ ኃይል ሲኖረን ነው። ስለሆነም የምስጢር የተደራጀ አካል በየመኖሪያና የሥራ አካባቢዎቻችን ሁሉ እንዲኖር ማድረግ ከአጣዳፊ ሥራዎቻችን አንዱ እናድርገው። 


ሁለተኛው ነጥብ ሥነሥርዓትን የሚመለከት ነው። ሥነሥርዓት ከሌለ ድርጅት የለም። የህወሓት አገዛዝ ያሳደረብን ጎጂ የባህል ተጽዕኖ ከባድ በመሆኑ ራሳችንን በሥነሥርዓት ለማነጽ መልፋት ይጠበቅብናል። አገራችንና ራሳችንን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ አውጥተን የተሻለ ሥርዓት ማምጣት የምንችለው ራሳችን፣ ድርጅታችን እና ተግባሮቻችን ለሥነሥርዓት ተገዢ ስናደርግ ነው። የነፃነት ታጋዮች ራሳቸውን ለሥነ ሥርዓት ያስገዙ መሆን ይኖርባቸዋል። አስተሳሰባችን ራሱ ሥነ ሥርዓት የያዘ ሊሆን ይገባዋል። እንደዚሁም ሁሉ ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት የታነጹ ሊሆኑ ይገባል። 

የትጥቅ ትግልና ግራ የሚያጋባ አስተያየት



 በፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

በኢትዮጵያ ትከሻ ላይ የተቆለፈውን ቀምበር ለማላቀቅ ቍልፉ የትጥቅ ትግል መሆኑ በተነሣ ቍጥር ከአንዳንድ ሰዎች የሚሰጠው አስተያየት ግራ የሚያገባ ነው። ገዢዎቹና ደጋፊዎቻቸው ቢቃወሙ ይገባኛል። የሚሰጡት አስተያየት ግን ሕፃንን ሳይቀር የሚያሥቅ ነው።ጦርነት በቃንይላሉ።አትንኩንማለታቸውን የማናውቅ ይመስላቸዋል። ጦርነት ካላስፈለገ፥ ለምን ከንጉሣዊው አስተዳደር ጋር ተዋጉ? ለምን ከደርግ ጋር ተዋጉ? ጨቋኝ ገዢ የት አገር ነው በሌላ መንገድ ሥልጣን ለሕዝብ ሲለቅ የታየው? የምሥራቁ ዓለም ጨቋኞች የወደቁት በሕዝብ ዐመፅ ነው ማለት፥ የምዕራቡን ዓለም ከባድ እጅ ሚና መርሳት ይሆናል።

የኛዎቹ ጦርነት ከመረራቸው፥ ሕዝብን ወደጦርነት የሚመራ በደል አይሥሩበት። ምን ጊዜም ቢሆን የትጥቅ ትግል የመጨረሻው አማራጭ ነው። የትጥቅ ትግል የሚያደርሰው ጉዳት በአንዱ ወገን ላይ ብቻ አይደለም። መሣሪያ የሚያነሣ መሣሪያ ማንሣት የሚያመጣበትን ጉዳት ሳያውቅ አይነሣም። ሰው ሆኖ እንደከብት መገዛት ያልቻለ ሰው በቃኝ ሲል፥ ክብሩን በመጠበቁ ከተቀመጡበት ተነሥቶነወርየሚባል እንጂ፥ በባርነት ጥላ ሥር ተቀምጦ የሚተች አይደለም።ጦርነት መርሮናልየሚለውን ምክር መገዛት ለመረረው አይመክሩም።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚመጣ ግራ አጋቢ አስተያየትጦርነትስ አስፈላጊ ነው፥ ግን . . .” የሚለው ነው። ይህ አስተያየት በቅን አሳብ፥ የተሰጠ ሊሆን ይችላል። ግን አዛኝ መስሎ፥ ቀምበረኛውን ለመደገፍ የተሰጠ አስተያየት አለመሆኑ በምን ይታወቃል? እውነተኛ አሳቢና ሠጊ ሰው አስተያየቱን የሚሰጠው ሲጠየቅ፥ ካልተጠየቀም በግሉ ትጥቅ ያነሡትን ፈልጎ በጨዋ ደምብ መንገር ነው። ሳይጠየቁ ተነሥቶ በይፋ ምክር መስጠት ግን ሰሚው ሕዝብ ትግሉን እንዳይደግፍ መገፋፋት ነው። የትጥቅ ትግል ከታመነበት እንዲፋፋም የማይፈለግበት ምክንያት ምንድን ነው?

ትጥቅ ትግል የራስን ሕይወት ለወገን ነፃነት መሠዋት ማድረግ ነው። ሌላ ዓለማ የሌለው ሰው መሣሪያ ሲያነሣ፥ እንዴት ይኸንን የሚሰነዘርበትንና የሚሰነዘርለትን ምክር ሳያስብበት ራሱን ለመሥዋዕትነት ያቀርባል? የሚካኼደው የትጥቅ ትግል የሚያዋጣ የመሰለው እርዳታውን ያቅርብ፤ የማያዋጣ የመሰለው ለምንድን ነው የሚቃወመው? ተቃውሞው ማንን ለመጥቀም ነው? ለታጋዮቹ አስቦ ከሆነ፥ ከባለቤት ያወቀ ቡዳ ነው።የኔን ያህል የማሰብ ችሎታ የላችሁምማለት ነው። እንዴት ነው ለታጋዮቹ ያልተገለጠ ሥጋት ለምክር ሰጪዎቹ የተገለጠው?

አንዳንዱ ደግሞ፥ይኸው እንታገላለን ሲሉ ዓመታት አሳለፉ፥ ግን አንዳች ውጤት አላሳዩምይላል፤ ውጤት እንዲያሳዩ የቀጠራቸውና ካልሆነላቸው የሚያሰናብታቸው ሹም ይመስል። አርፎ መቀመጥ ስንት ውጤት አሳየ? ሌሎችን ሙከራዎችምአንዳች ውጤት አላሳዩምብለን እንንቀፋቸዋ!ውይስ ውጤት አሳይተዋል?