Tuesday, December 31, 2013

ያለፉት ስህተቶች ትምህርት እንጂ ማነቆ አይሁኑ

በግርማ ካሳ 

እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር፣ ኖቬምበር 17 ቀን 1996 ነበር። በሰርቢያ (የቀድሞ ዩጎስላቪያ) ፣ የክልል ምርጫ ይደረጋል። በቩክ ድራስኮቪች የሚመራዉ SPO ፣ በቬስና ፔሲች የሚመራዉ GSS እና ሌሎች ድርጅቶች በአንድ ላይ ሆነው አብላጫ ድምጽ ያገኛሉ። ነገር ግን በወቅቱ የነበሩ አምባገነን ባለስልጣናት፣ እነ ስሎቦዳን ሚሎሶቪች አጭበረበሩ። ከኖቬምበር 17 1996 እስከ ፌቡሩያሪ 11 1997 ድረስ፣ «ሌክስ ስፔሲአሊስ» የሚል፣ ሕዝባዊ ተቃዉሞዎች በስፋት ተደረጉ። ባለስልጣናቱ፣ የሕዝቡ ሰላማዊ ተቃዉሞ አይሎ መምጣቱን ሲያዩ አፈገፈጉ። የተቃዋሚዎች ስብስብ በክልል ምርጫዉ ያገኙትን ምርጫ ተቀበሉ። ሊበራል ዴሞክራቱ ዞራን ጂንጂች የአገሪቷ መዲና የቤል ግሬድ ከንቲባ ሆኑ።

ብዙም አልቆየም፣ በተቃዋሚዎች መካከል ችግር መታየት ጀመረ። በቩክ ድራስኮቪች የሚመራዉ ፓርቲና በዞራን ጂንጂች በሚመራዉ ፓርቲ መካከል ልዩነቶች ተፈጠሩ። መካረር መጣ። የሕዝብን ጥያቄ አንግቦ በጋራ መቆም ተሳናቸው። በአደባባይ መወጋገዝ ጀመሩ። በአመቱ አገራዊ የፕሬዘዳንት ምርጫ ሲደረግ የሚሎሶቪች የሶሻሊስት ፓርቲ በቀላሉ ስልጣኑን ጨበጠ። የተለፋበት፣ የተደከመበት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ከሸፈ። አምባገነኖች አሸነፉ። በሕዝብ ትግል የተገኙ ዉጤት እንደገና ተቀለበሱ። ዞራን ጂንጂችም ከናካቴዉ ከተመረጡበት የቤልግሬድ ከንቲባነት ተነሱ።

በ1998 በየክልሉ ተማሪዎች «ኦትፖር» ( በሰርቢያን ቋንቋ እምቢተኝነት) በሚል ስም ከታች ወደ ላይ የሆነ እንቅስቃሴ ጀመሩ። የተከፋፈሉ የፖለቲካ ደርጅቶች በአንድ ላይ እንደገና ተሰባሰቡ። ካለፉት ስህተቶች በመማር፣ ፍጹም ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ ለሚቀጥለው ምርጫ መዘጋጀት ጀመሩ። ከፍተኛ ጫና እየተደረገም ዝግጅቱ ተጧጧፈ። የገዥዉ ፓርቲ ደጋፊዎችን የመሳብ ሥራ በስፋት ተሰራ። በዚህም ምክንያት በርካታ የገዢዉ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ተቃዋሚዎችን መቀላቀል ጀመሩ። ኢቫን ስታምቦሊች ፣ የሚሎሶቪች አጋር የነበሩ ፖለቲከኛ ፣ ተቃዋሚዎች በመቀላቀላቸውም በሚሎሶቪሽ የደህንነት ሰራተኞች ታፍነው ተገደሉ።

ሴፕቴምበር 2000 ዓ.ም ምርጫ ተደረገ። የሚሎሶቪች ምርጫ ቦርድ፣ አሁንም የተጭበረበረ የምርጫ ዉጤት ይፋ አደረገ። ያንን አስከትሎ ኦክቶቦር 200 ዓ.ም ፣ ትልቅ ተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ። ምርጫ ቦርድ የምርጫዉን ዉጤት ወደ ነበረበት እንዲመልስ ተገደደ። የተቃዋሚዎች እጩ የሆኑት ኮስቶኒሳ እንዳሸነፉ ተገለጸ። የሚሎሶቪች ስልጣን ፍጻሜ ሆነ።

Monday, December 30, 2013

ጠ/ሚ ኃ/ማርያምን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ሊከሰሱ ነው!

*ኢቴቪና ፌዴራል ፖሊስም ይከሰሳሉ

በዘሪሁን ሙሉጌታ

በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በቅርቡ ከተላለፈው ‘‘ጅሃዳዊ ሃራካት’’ ዘጋቢ ፊልም ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ከፍተኛ የሀገሪቱ የመንግስት ባለስልጣናት ላይ የወንጀልና የፍትሃብሔር ክስ ሊመሰረት ነው። ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ባሻገር በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢሬቴድ) እና በፌዴራል ፖሊስ ተመሳሳይ ክስ ይመሰረትባቸዋል።

ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናቱ እና የተጠቀሱት ተቋማት ላይ ክስ የሚመሰረተው ሰሞኑን ‘‘ጃሃዳዊ ሃራካት’’ በሚል በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ደርጅት የቀረበው ዘጋቢ ፊልም በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በሕግ ጥላ ስር ያሉትን ተጠርጣሪዎች መብት ሲጣስ መከላከል ባለመቻላቸው፣ ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀማቸው፣ በሕዝብ ሐብት ያለአግባብ በመገልገላቸው፣ የተሰጣቸውን የሕዝብ አደራ ባለመወጣታቸውና በሃይማኖት ጣልቃ በመግባታቸው የወንጀልና የፍትሐብሔር ክስ ይመሰረትባቸዋል። ክሱን የሚመሰርቱት በአሁኑ ወቅት በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ጉዳያቸው በሕግ እየታየ ባሉት ተጠርጣሪዎች ጠበቆች አማካኝነት ሲሆን ክሱም በሁለት ደረጃ ተከፍሎ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል።

ክሱን እያዘጋጁ ከሚገኙት ጠበቆች አንዱ የሆኑት ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ክሱን በማስመልከት በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ በመንግስት ባለስልጣናት ላይ የሚመሰረተው ክስ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይቀርባል ብለዋል። በኢቲቪ ላይ የሚመሰረተው የፕሬስ ክስ ቀጥታ በከፍተኛው ፍርድ ቤት የሚቀርብ ሲሆን ክሱም ከሞራል ጉዳት ጋር እንደሚያያዝ ጠበቃው አስታውቀዋል።

ይድረስ ለብአዴን አባላት

በረከት ስምዖንና አዲሱ ለገሰ ወደ ባህር ዳር አቅንተው ነበር። መቸስ በረከት ስምዖን አማራ ካልሆንኩ ሞቼ እገኛለሁ ብሎ አለመንደሩ የአማራ ህዝብ መሪ እኔ ነኝ ብሎ ከአማራ ህዝብ ፊት ሲቆም አለማፈሩ ያስገርማል። አዲሱ ለገሰም እንደ በረከት ራሱን የአማራ ህዝብ ወኪል እኔ ነኝ ይላል።እነዚህ ሁሉት ህወሃት የሠራቸው ፍጡራን ባህር ዳር እንዲወርዱ ያደረጋቸው ብአዴን ተዳክሟል ተብሎ መታሠቡ ነበር።

እንግዲህ በእንበረከት የአስተሳሰብ ደረጃ ብአዴን ተዳከመ ሲባል ምን ማለት ይሆን?

ከጥቂት ደካማ ካድሬዎች በቀር ሌሎች እንደ ሰው ማሰብ የሚችሉ የብአዴን አባላት አገሪቷ እየሄደች ያለችበት መንገድ ያሳስባቸዋል። ህወሃት በአማራ ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ የሚያንገበግባቸው በርካታ ናቸው። ጉርፋርዳ እና ቤንሻንጉል አገራችሁ አይደለም ተብለው አማሮች ከኖሩበት ቀየ ተፈናቀለው ሜዳ ላይ የመውደቃቸው ድርጊት የእግር እሳት ሁኖ የሚለበልባቸው ብዙዎች አሉ። በዚህ ሁኔታ ያዘኑና የተቆጡ የብአዴን ካድሬዎች ድርጅቱ ቆሜለታለው የሚለው ፍትህ የት አለ፤ እኩልነትስ ከወዴት አለ፤ ኢትዮጵያስ የሁላችን አገር ነች የምትባለው መገለጫው ምንድ ነው እያሉ ይጠይቃሉ። እነዚህ ጥያቄዎች በካድሬዎች መካከል መመላለስ ሲጀምሩ ድርጅቱ ተዳክሟል ተብሎ ግምገማ ይካሄዳል።

በረከት እና አዲሱ ነፃነትን ሳያውቁ ራሳቸውን ነፃ አውጪ አድርገው የሚቆጥሩ የህወሃትን ዙፋን ከመጠበቅ የዘለለ ምንም ሚና የሌላቸው ያልሆኑትን ለመሆን የሚውተረተሩ ደካሞች መሆናቸውን እናውቃለን። እነዚህ ግለሰቦች ስለ አማራ ህዝብ ነፃነትና ክብር ይሠራሉ ብሎ ማሰብ የሚቻልበት ሁኔታ የለም። በረከትና አዲሱ በህዝብ መካከል እየኖሩ የህዝብ ፍቅር የሌላቸው፤ ከህዝቡ ጋር መኖርንም የማያውቁ፤ እለት ዕለት በሚፈጥሩት የፍርሃት አረንቋ ውስጥ የሚኖሩ እና ሠላም የራቃቸው ግለሰቦች ናቸው። ከእነዚህ ግለሰቦች እውነትን ፈልጎ ማግኘት፤ ነፃነትን ጠይቆ መቀዳጀት፤ ለፍትህ ጥያቄዎች መልስ ማግኘት የሚቻል አይደለም። የአማራ ህዝብ ከጉራፋርዳ እንዲወጣ የተደረገበት ምክንያት ምንድ ነው ተብለው ሲጠየቁ የጠባቦች ጥያቄ ብለው ይሳደባሉ። አያቶቻችን በደምና አጥንታቸው ያቆዩልንን ድንበር አፍርሳችሁ ለባእዳን ለምን ትሰጣላችሁ ሲባሉ የጦርነት ናፋቂ ጥያቄ እያሉ ይዘባበታሉ። እንደምን ሁኖ ከሁለት ሚሊዮን በላይ አማራ ከቁጥሩ ጎድሎ ተገኘ ሲባሉ የትምክህተኞች ወሬ እያሉ ይሳለቃሉ። አዎን እነበረከት ስምዖን የሚፈልጉት ዜጎች ስድባቸውን ተሸከመው እንዲኖሩላቸው እንጂ እውነትን፤ ፍትህን እና እኩልነትን እንዲጠይቁ አይደለም።

ደም ሰጥቶ ነፃነት የተከለከለው ህዝብ (አብርሃ ደስታ – የሽሬው ስብሰባ ጉዳይ)

(ኢ.ኤም.ኤፍ) ትላንት እሁድ ለት በሽሬ እንዳስላሴ፤ የአረና ፓርቲ ህዝባዊ ስብሰባ የሚያደርግበት ቀን ነበር። ህዝቡ በዚህ ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ግልብጥ ብሎ መጣ። ሁኔታው ያስደነገጣቸው የህወሃት ካድሬዎች ይህ ስብሰባ እንዳይደረግ ከፍተኛ ጥረት አደረጉ። ይህንን ጠቅላላ ሁኔታ፤ የአረና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት የሆነው አብርሃ ደስታ ከስፍራው ዝርዝር ዘገባ አቅርቧል። ሙሉ ዘገባው ከዚህ የሚከተለው ነው፤ ያንብቡት።

ሽሬ ከመቀሌ በስተ ሰሜን ምዕራብ በ320 (?) ኪሎ ሜትር ርቀት የምትገኝ ከተማ ናት። በአውቶቡስ ጉዞ ከሰባት እስከ ስምንት ሰዓት ይወስዳል (እኛ ስምንት ሰዓት ፈጅቶብናል)። ከመቀሌ ማይመኽደን፣ አጉላዕ፣ ዉቅሮ፣ ነጋሽ፣ እንዳተካ ተስፋይ፣ ፍረወይኒ (ስንቃጣ)፣ ማይመገልታ፣ እዳጋሓሙስ፣ ዓዲግራት፣ አሕዘራ፣ ሴሮ፣ እንትጮ፣ ማርያም ሸዊቶ፣ ዓድዋ፣ አክሱም፣ ዉቅሮማራይ፣ ሰለኽለኻ አቋርጠን ሽሬ እንዳስላሴ ገባን።

ሽሬ ለም መሬት ነው። ሰፊና ሜዳማ የእርሻ መሬት አለ። ህዝቡ እንግዳ አክባሪ ነው። ሽሬ የሆነ ደስ የሚል ነገር አለው። ግን ባከባቢው ብዙ ማሕበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች አሉ። ይሄን ጉዳይ ሌላ ግዜ እመለስበታለሁ። አሁን ግን ወደ የስብሰባው ጉዳይ እንግባ።

ዓረና መድረክ በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ህዝባዊ ስብሰባ ለመጥራት ወሰነ። ስብሰባው የሚያዘጋጅ የዓረና ቡድን ወደ ከተማው ተላከ። በከተማው ስብሰባ ለማድረግ የሚያስችል ፍቃድና መሰብሰብያ አዳራሽ እንዲሰጠን ጠየቅን። ከአንድ ቀን በኋላ ስበሰባ ማድረግ እንደምንችል ፈቅደው አዳራሽ ግን እንደተያዘ ነገሩን። አዳራሽ መከራየት እንደምንችል ካልሆነ ደግሞ በሆነ ሜዳ ማካሄድ እንደምንፈልግ ነገርናቸው። ከአንድ ቀን በኋላ ተነጋግረው አዳራሽ ፈቀዱልን (ሜዳ ላይ ስብሰባ ከተደረገ ለነሱ ጥሩ አለመሆኑ ያውቁታል)።

አዳራሽ ካስፈቀድን በኋላ ሓሙስና ዓርብ ቀሰቀስን። ከአስር ሺ በላይ በራሪ ወረቀት ተበተነ። በማይክሮፎን ተጠቅመን መረጃው ለህዝብ አዳረስን። የከተማው ካድሬዎች በእግርና በመኪኖች እኛን እየተከታተሉና የሽሬ ህዝብ ለኛ ያለው ስሜት ይሰልሉ ነበር። ያኔ ካድሬዎቹና ሰላዮቹ በኛ ላይ ያደረሱት ምንም ተፅዕኖ አልነበረም። የተቀደደብን ወረቀትም ጭራሽ አልነበረም (በሌሎች አከባቢዎች ካድሬዎቹ ወረቀት ተቀብለው የሚቀዱ ነበሩ)። ዓርብ ቤት ለቤት ቀሰቀስን።

ካድሬዎቹና ሰላዮቹ የህዝቡን ጥሩ አቀባበል ለሚመለከታቸው አካላት ሪፖርት አደረጉ። ዓርብ ከሰዓት የከተማው የካቢኔ አባላት ተሰብስበው በጉዳዩ ተወያዩ። ዓርብ ማታ (ከምሽቱ አንድ ሰዓት) የከተማው ከንቲባ አቶ መረሳ አታክልቲና ምክትል ከንቲባው መምህር ሃይለ አዳነ ወደ ማዘጋጃቤት ጠርተው ቅስቀሳ ማቆም እንዳለብን ነገሩን። ስላደረግነው ቅስቀሳ በቂ መረጃ መሰብሰባቸው፣ በጉዳዩ ካቢኔ መሰብሰቡና እስካሁን የተደረገ ቤት ለቤት ቅስቀሳ በቂ መሆኑ መግባባት ላይ መደረሱ ተነገረን።

በጀግኖች አባቶቻችን ደም የተቦካው ሉአላዊ ግዛታችን ላይ የሚደረገውን ስውር ሴራ ያለማወላወል በፅናት እንታገለዋለን!!! ከሰማያዊ ፓርቲ (ሰማያዊ) የተሰጠ መግለጫ

ታኅሣሥ 20 ቀን 2006 ዓ.ም. (December 30, 2013) 

የኢትዮጵያንና የሱዳንን ድንበር የማካለሉ ሥራ ከመስከረም 29 ቀን 2002 ዓ.ም. (October 9, 2009) ጀምሮ እየተከናወነ እንደሆነ፣ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የሚታተመው ዕለታዊ የሱዳን ጋዜጣ ሱዳን ትሪቢውን (Sudan Tribune) በመስከረም 8 ቀን 2002 ዓ.ም. (September 18, 2009) መዘገቡ ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያና የሱዳን የድንበር ጉዳይ ያንገበገባቸው ኢትዮጵያውያን በሀገር ውስጥና በውጪ የሚኖሩት ዜጎቻችንም ራሳቸውን በተለያዩ “ኮሚቴዎች” እና “ግብረ ሃይሎች” በማደራጀት ለጉዳዩ ክፈተኛ ትኩረት እንዲሰጠው ሲጥሩ ቆይተዋል፡፡ ፓርቲያችን (ሰማያዊ)፣ ለነዚህ ሀገር ወዳድ ዜጎች ያለውን ከፍተኛ አክብሮት ለመግለጽ ይወዳል፡፡

ሆኖም፣ የነዚህን ሀገር ወዳድ ዜጎችና አፍቃሪ-ኢትዮጵያውያን ጥሪና መግለጫዎች ከቁብም ካለመቁጠር፣ በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ-ኢህአዲግ መንግሥት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ሥውር የሥልጣን ማራዘሚያ ደባዎችን እየሸረበ እንደሚገኝ አጋልጠዋል። ወያኔ ራሱ ያቋቋመው “የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር ኮሚቴ” አባላት ራሳቸው በተለያዩ ቃለ-ምልልሶች እንዳጋለጡት፣ ወያኔ በአባቶቻችን ደም ተላቁጦ ለተቦካውና የበርካታ ሰማዕታትን ህይወት ላስከፈለው የኢትዮጵያ ድንበርና የግዛት ሉዓላዊነት ግዴለሽነቱን በተግባር አሳይቷል፡፡ የኢትዮጵያንም ሉዓላዊ ግዛትና ድንበር “በጫካ ውሎችና ስምምነቶች” እያመካኘ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ታሪካዊ ጠላቶች አሳልፎ መስጠቱን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡

ይህንንም ከፍተኛ የሆነ የሃገር ክህደትና ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ለማስተባበል በመገንዘብ፣ የወያኔ-ኢህአዲግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረ-ገጹ ላይ በመስከረም 2002 ዓ.ም መጨረሻ ላይ አንድ የማደናገሪያ መግለጫ አውጥቶ ነበር። ከዚህም የማደናገሪያ መግለጫ ውስጥ የሚከተሉትን ሦስት(3) አበይት ጉዳዮች መገንዘብ ይቻላል። እነርሱም፦

1ኛ. የኢትዮጵያና ሱዳን የፖለቲካ ኮሚቴ (Ethio-Sudan Political Committee) ተብሎ የሚጠራ ከፍተኛ አካል መኖሩንና የኢትዮጵያና የሱዳን የጋራ ድንበር ኮሚቴም (Ethio-Sudan Joint Boundary Committee) በፖለቲካው ኮሚቴ ሥር እንደሚሠራ አረጋግጧል፤ የዚህ የኮሚቴ መዋቀርና የአሰራር ሂደቱም ለረጅም ዓመታት ከኢትዮጵያ ሕዝብ አይንና ተደብቆ የቆየ እንደሆነና፣ ወያኔ-ኢህአዲግም በሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ክትትል መጋለጡን ሲያውቅ ተጨንቆ ያወጣው ምስጢር ነበር።

2ኛ. የኢትዮጵያና የሱዳን የጋራ የድንበር ኮሚቴም (Ethio-Sudan Joint Boundary Committee) ከጥቅምት 5 ቀን 2002 ዓ.ም. (October 15, 2009) እስከ ግንቦት 2002 ዓ.ም.(May 2010) ድረስ የኢትዮጵያና ሱዳን ድንበርንና አካባቢውን ሙሉ በሙሉ እንደሚቀይስና ቅኝት እንደሚያደርግም ገልጾ ነበር፡፡ ይህ ደግሞ ወያኔ ሲጋለጥ ያወጣው ሌላው ምስጢር ሲሆን፣ (ሱዳን ትሪቢውን ያወጣውን ዜና የሚያጎለምስ) እና የሱዳን ሃገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ድንበሩን ለማካለል የሚያደርገውን ዝግጅት የሚያስተጋባ ነው።

3ኛ. የድንበር ክለላው ከግንቦት 2002 ዓ.ም. ( May 2010) በኋላ እንደሚደረግና ከዚህም ጋር አያይዞ ወያኔ-ኢህአዲግ ያለፉት የኢትዮጵያ መንግሥታት አምነው የተቀበሉት የድንበር ክልል እንዳለ አስምስሎ ለማቅረብም ጥረት አድርጎ ነበር፡፡ በመሆኑም፣ ወያኔ-ኢህአዲግ አሁን የሚያካሂደው “የድንበር-ክለላ ሂደት” ዳግም ድንበርን የመከለል ተግባር ( re-demarcation ) እንደሆነ መግለጹ ለመግለጽ ሞክረዋል፡፡ ይህ ማደናገሪያና ተራ ልፈፋ፤ የኢትዮጵያን ህዝብ ለማወናበድና ግዛቱን በጫካ ውሎችና ስምምነቶች አማካይነት አሳልፎ ከመስጠት የዘለለ ኢምንት እውነታ የለውም፡፡ ይሄንን በተመለከተም ያጠኑት ሊቃውንትንና በግዛቱ ላይ የሚኖሩትን ዜጎች ምስክርነት ሊያገኝ አልቻለም፤ አይችልምም፡፡

Sunday, December 29, 2013

ናትናኤል መኮንን የ2014 የአመቱ ሰው

በግርማ ካሳ

የአንዲት ትሁት ኢትዮጵያዊት ባላቤትና የልጅ አባት ነዉ። የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት ወጣት አመራር አባል ነዉ። በፓርቲዉ ዉስጥ፣ በዉጤት ላይ የተመሰረተ፣ የሰለጠነ ሰላማዊ ፖለቲካ የሚያራምደዉ, የአንድነት ፓርቲ አደራጅ ነዉ። በሐሰት የሽብርተኝነት ክስ ይከሰሳል። ምንም እንኳን በአገራችን የሕግ ስርዓት እንደሌለ ቢታወቅም፣ የአገዛዙን ሕገ-አራዊነትን ለማጋለጥ ሲል፣ ራሱን ለመከላከል ሞከረ። ሕግን በማመዛዘን ሳይሆን ከሕወሃት/ኢሕአዴግ ፖሊት ቢሮ በተሰጠ የፖለቲካ መመሪያ መሰረት፣ ከሌሎች የትግል አጋሮቹ ከነአንዱዋለም አራጌ፣ እስክንድር ነጋ ከመሳሰሉት ጋር፣ ጥቁር ካባ በለበሱ ዳኛ ተብዬ ካድሬዎች በሽብርተኝነት ወንጀል ጥፋተኛ ተባለ። የ18 አመታት እስራት ተበየነበት። ይህ ወጣት ናትናኤል መኮንን ይባላል።

የተከሰሰበት ችሎት ይሰማ በነበረ ወቅት፣ ናትናኤል መኮንን በፍርድ ቤት ከተናገራቸው የተወሰኑትን፣ አንባቢያን ምን ያህል የተከበረ፣ ትልቅ እና አስተዋይ መሪ ፣ የአንድነት ፓርቲ እንዲሁም እኛ ኢትዮጵያዉያን እንዳለን ይረዱ ዘንድ፣ እንደሚከተለው አቅርበናል፡

«ክቡር ፍ/ቤት፡- እኔ እንኳን ሰውን ያህል ክቡር ፍጡር ስለመግደል ላሴርና የህዝብ ሀብት፣ የሆኑትን መሰረተ ልማቶች ስለማውደም ላቅድ ቀርቶ አፈናን፣ ጭቆናንና ግፍን በሰላማዊ መንገድ ከመታገልና ከመቃወም ውጭ የገዥውን ፓርቲ አባላትና አመራሮች እንኳን በጥላቻ ዓይን ተመልክቼ አላውቅም፡፡ ወደፊትም አልመለከታቸውም፡፡ ነገር ግን በፅናት አምርሬ እታገላቸዋለሁ፡፡ አፈናቸውን እንዲያቆሙ ከቁልቁለት ጉዟቸው እንዲመለሱ፤

ክቡር ፍ/ቤት፡- ሽብር የእኔ መገለጫ አይደለም፡፡ አገዛዙ እንዳለው እኔ ባለስልጣናትን ለመግደልና የህዝብ ሀብት የሆኑትን መሰረተ ልማቶች ለማውደም ያሴርኩ፣ ያቀድኩና በሽብር የተፈረጀ ድርጅት አባል ያልሆንኩና ከኢትዮጵያ ጋር በጦርነት ሁኔታ ላይ ካለው የሻዕቢያ መንግስት ጋርም የተባበርኩ ሳልሆን በሰላማዊ መንገድ የሚታገለው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ መስራችና የም/ቤት አባል ለአንድነት አላማዎች ተፈፃሚነት በቁርጠኝነት የምታገል፣ እንኳን ከሻዕቢያ ጋር ልተባበር፡- ከሻዕቢያ ጋር በመተባበር ሀገሬን የባህር በር ያሳጣትን ወያኔን የምታገል ለሀገር አንድነትና ክብር የምታገል፣ ሀገር ወዳድ ዜጋ ነኝ።

Saturday, December 28, 2013

ፖለቲካ ጨለማን ተገን አድርጋ ወንጌል ስትሆን !

በአሌክስ አብረሃም  

ወገኖቸ እሰብካችኋለሁ !!

በደሌ ቢራ አትጠጡ እንደተባለ ሰምታችኋል...... እኔ ግን እላችኋለሁ ባጠቃላይ አልኮል መጠጥ አትጠጡ ! ለጤና ጠንቅ ነውና !! መጠሃፉ ‹‹ደሃ ድህነቱን እንዲረሳ የወይን ጠጅ ስጠው ›› ቢልም እኛ ኢትዮጲያዊያን <አስራ አንድ> በመቶ እያደግን ያለን ሃብታም ህዝቦች ነንና እኛን አይመለከትም ! አዎ ! መጠጥ አገር እያጠፋ ነው ትዳር እየበጠበጠ ነው ይሄ ሁሉ ያማረበት ጠጭ ብርጭቆውን በቄንጥ ይዞ ውሰኪውን የሚከነብል ይሄን ሆንኩ ሳይል ወጋኝ ፈለጠኝ ሳይል ድንገት የሚከነበለው ለምን ይመስላችኋል ......መጠጥ .....መጠጥ ነው ወገኖቸ !!

ህዝቤ ቁሞ ይንከላወሳል እንጅ ጉበቱ እኮ የለም .....ሳንባውኮ በጥቃርሻ ተዥጎርጉሮ የሚያፈስ ኮርኒስ መስሏል ......ነብሱ አድፏል ! ይሄ ሁሉ የሆነው በምንድን ነው በመጠጥ !! መጠጥ እንዝህላል ያደርጋል ግዴለሽ ያደርጋል ዋጋ ቢስ ያደር .... ጋል ወገኖቸ ......ዛሬ እኮ ምፅአት ቀርባለችና ንስሃ ግቡ ሲባል ‹ሎ...ል› የሚል ወጣት ነው እያፈራን ያለነው ....

ትውልዱ በቀቢፀ ተስፋ የሚይዝ የሚጨብጠውን አጥቷል ቤተስኪያኖቻችን ርግብና ዋነስ ሰፍሮባቸው ካለሰው እየዋሉ ቡና ቤቱ በሰው ተጨናንቋል ..... ጭፈራ ቤቱ ካፍ እስከገደፉ ሞልቷል .....ስለሳምሶን ታሪክ ሰምታችኋል (ለነገሩ መቸ መጠሃፉን ታነቡና ፌስ ቡክ ላይ አፍጥጣችሁ እየዋላችሁ ) ሳምሶን ታላቅ የህዝብ ነፃአውጭ ነውና ሲረገዝ እናቱ የአልኮል መጠጥ በአፏ እንዳይዞር እግዜር አዟት ነበር !

ለትውልድ የምታስብ ሴት እንዲያ በክብርና በቅድስና ትኖር ዘንድ መፅሃፉ ያዛል ! ዛሬ ግን ሴቶቻችን በየመሸታው አኮሌ ሙሉ መጠጥ ሲገለብጡና ሲያሽካኩ ያመሻሉ ያድራሉ የረከሰ ትውልድ ከሰካራም እናት ይወለድ ዘንድ ስምንተኛው ሽ ቀርቧል ! ወንዱ መቸስ አንዴውኑ ጠጥቸ ልሙት ብሏል !

ደግሞኮ የድሮ መጠጥ ሲያሰክር ጀግና ያደርጋል የልብን ያናግራል ‹‹በቃኝ ባርነት ...በቃኝ ጭቆና ›› የሚል ሰካራም ዛሬ አይታችሁ ታውቃላችሁ ?.....የለም ! ወንዱ ሰክሮም ፈሪ ባይሰክርም ፈሪ ነው ! ቤቱ ገብቶ ሚስቱና ቤተሰቡ ላይ ነው የሚደነፋው ! ወገኖቸ ስካር ድሮ ቀረ !!

እኔ ኣላውቅም ፈራሁ ጃዋር

በሄኖክ የሺጥላ

የበደሌ ቢራ ፋብሪካ ከ ኣዲስ ኣበባ 483 ኪ.ሜ  ርቀት ላይ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ኢሉ-ኣባ-ቦራ ( Eloo The father of  Holstein  Friesian) ኢልባቡርከተማ በሁለት መቶ ሃምሳ ሺ ስኩውር ሜትር ይዞታ ላይ ስራውን እንደ ኣውሮጳውያን ኣቆጣጠር በ 1993  ማከናወን የጀመረ ትልቅ የቢራ ማምረቻ ድርጅትነው።

ኢሊባቡር መልካም ምድራዊ ኣቀማመጡም ሆነ ምድራዊ ልምላሜው፥ እንደ በቆሎ ፤ ገብስ፤ ጤፍ፤ የቅባት እሎች፤ ማር፤ ከነ ቦራ ደሞ ወተት፤ ቅቤ እና ወዘተየሚዘራባት፤ የሚታጨድባት፤ የሚቆረጥባት፤ የሚታለብባት ሃገር እንድትሆን ኣድርጉዋታል።

ኢሊባቡርን የጽሁፌ መንደርደሪያ ኣደረኩ እንጂ ዋናው ነጥቤ እሱ ኣይደለም። ዛሬ መናገ ወይም መጻፍ የፈለኩት ቴዲ ኣፍሮ በቅርቡ በመላው ኢትዮጵያ የሙዚቃዝግጅቱን እንዲያሳይ ወኪል የሆነውን የበደሌ ቢራን ያለመጠጣት ኣድማ ( boycotting)  በመላው ኢትዮጵያ ይደረግ ዘንድ ኣንዳንድ ግለሰቦች የጀመሩትን ነገርሰምቼ፤ ለምን በደሌን፤ ለምን ቴድን የሚል ጥያቄ ለሚጠይቁ፤ መልስ የሚመስለኝን ለመተየብ፤ ከተቻለም ለማሳየት መመኮር በመሻቴ ነው ።

ቴዲ ኣፍሮ በቅርቡ በጋዜጣ ላይ ስለ ኣድዋ ድል በሰጠው ኣስተያየት የተቆጡ፤ የተቀየሙ ግለሰቦች፤ ቴዲ ኣፍሮ ጥቁር ሰው ብሎ ንጉስ ሚኒሊክን፤ ከዛም በላይየኣድዋ ድልን በመዘከሩ የተበሳጩ የህብረተሰብ ኣካሎች፤ ቴዲ ኣፍሮ ከዚህ ቀደም ጃ ያስተሰርያል ብሎ በመዝፈኑ ቂም የቁዋጠሩ ሰዎች፤ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በሊግ ኦፍ ኔሽን በ 1936  የኢጣልያንን የተለከለ  የኬሚካል መሳሪያ መጠቀምን በመቃወማቸው፤ ኢትዮጵያን የ ዩናትድ ኔሽን ኣባል በማድረጋቸው፤ ቅራኔዎችን ኣብርደው ያፍሪካን ህብረት በመመስረታቸው፤ ለነዚህ ጉልህ ኣስተዋጾዎቻቸው በመዝፈኑ፤ ለነዚህ ለተጠቀሱት መልካም ስራቸው መታሰቢያ የጭንቅላቱ ውጤትየሆነውን ምዚቃ በማበርከቱ፤ ቴዲ ኣፍሮ ፤ ኣቀንቃኝ ና ኣዝማሪ ፤ ገጣሚና ሰኣሊ፤ ሃያሲና ደራሲ፤ ጸሃፊ ተውኔቱና ብላታው፤ ኣፉን በለጎመበት ዘመን፤ በብእሩየታሪክ ጋሻ፤ በግጥሙ ለቆሰለ ታሪክ ማገገሚያ፤ በዘፈኖቹ ( ከ ማሊ ሱፊዎች ባልተናነሰ መልኩ) የነብስን ክር እየተጫነ ያላስለቀሰው፤ ያላስተከዘው፤ ሰው እንደሌለየገባቸው ሰዎች፤ በይበልጥም የኣድዋ ድል፤ የጥቁር ኣንበሳዎች ድል መሆኑን ያሳየበት በመሆኑ እና ይህም የሚያማቸው ሰዎች፤ ዛሬ በደሌ ቢራ ቴዲ ኣፍሮንስፖንሰር ስላደረገ፤ በደሌ ቢራን  ያለመጠጣት ኣድማ ጠርተዋል። ኣሁን ቴዲ ኣፍሮን ኣብዶ በረንዳ ( የጫት ማከፋፈያ በረንዳ ነው) ቢሆን ስፖንሰር ያረገው ምን ሊሉ ነበር።። ባረገው እና የተከታዮቻቸውን መልስ ባየን።  ኣንድ ጊዜ ቆይ ጠብቁኝ ሳቄ መጣብኝ ያለው ተናጋሪ ማን ነበር።

የጋዜጠኞች እስር መንግስትን፣ ማህበራትንና ፓርቲዎችን እያወዛገበ ነው

መቀመጫውን በኒውዮርክ ያደረገው ሲፒጄ የተሠኘው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ጋዜጠኞችን በማሠርና በማንገላታት ኢትዮጵያ ከአለም ሁለተኛ ናት ማለቱን መንግስት እና በሃገሪቱ የሚገኙ የጋዜጠኞች ማህበራት አምርረው ሲያወግዙ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በበኩላቸው፤ በእርግጥም ሃገሪቱ ጋዜጠኞችን እያሠረች ነው፤ ደረጃው ይገባታል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጋዜጠኞች ህብረት ፕሬዚዳንት አቶ አንተነህ አብርሃም፤ “ሲፒጄ የሃገራችንን ስም ለማጥፋት ስለሚፈልግ ነው እንጂ፣ በፃፈው ፅሁፍ የታሠረ አንድም ጋዜጠኛ የለም፡፡ 3 ጋዜጠኞች የታሠሩት አሸባሪ ተብለው ነው” ብለዋል፡፡ በማህበራችን ጥረት በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች እስር ቆሟል ሲሉም ተናግረዋል አቶ አንተነህ። የኢትዮጵያ ነፃ ጋዜጠኞች ማህበር (ኢነጋማ) ሊቀመንበር አቶ ወንደሰን መኮንን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሙያው ጋር በተያያዘ የታሠረ ጋዜጠኛ እንደሌለ ገልፀው፣ የታሠሩ ጋዜጠኞች ጉዳያቸው ሌላ ቢሆንም መፈታት አለባቸው ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል፡፡

የሲፒጄን መግለጫ እንደማይቀበሉትና ድርጅቱ የራሱ ተልዕኮ እንዳለው አቶ ወንደሰን ጠቁመው፤ “ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሠር በአለም ሁለተኛ መሆን አትችልም፤ ሆናም አታውቅም” ብለዋል። የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል በበኩላቸው፤ “ሲፒጄ የፖለቲካ አጀንዳ ያለውና መንግስትን በሃይል ለመለወጥ ከሚንቀሣቀሡ ድርጅቶች ጋር የተሰለፈ ድርጅት ስለሆነ፤ በተግባር ከጋዜጠኝነት ጋር ምንም ግንኙነት የለውም” ብለዋል፡፡ አቶ ሽመልስ፤ “እናንተ መቼ ታሠራችሁ? የማታውቁት ከማርስ የመጣና ‘የታሠረ ጋዜጠኛ አለ እንዴ?’ ሲሉም ጠይቀዋል። የሲፔጂ የአፍሪካ ወኪል፣ በ97 ምርጫ የቅንጅት አመራር የነበረና የኢትዮጵያን መንግስት በሃይል ለመገልበጥ የሞከረ ግለሠብ ያሉት አቶ ሽመልስ፤ እንዲህ ያሉግለሠቦች እየፈተፈቱ የሚያቀርቡለትን ነገር ሲፒጄ እየተቀበለ ያስተጋባል ብለዋል፡፡ ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት ዶ/ር መረራ ጉዲና በሠጡት አስተያየት፤ መንግስት ጋዜጠኞችን እንደሚያስርና እንደሚያንገላታ ለማረጋገጥ እስር ቤት ሄዶ ማየት ይቻላል ብለዋል፡፡

የሃገሪቷን ኢኮኖሚ ለሞት የዳረገው የወያኔ ባለስልጣናት የውጭ ምንዛሬ ዘረፋ

የሕወሓት ስውር እጆች የግል ባንኮችን እያዳከማቸው ነው!!!

በምንሊክ ሳልሳዊ 

የውጭ ምንዛሬ ማለት ለአንድ ታዳጊ ሃገር እጅግ እንቁ የሆነ እና ሊንከባከቡት ሊያሳድጉት የሚገባ ብቸኛ የኢኮኖሚ ዋልታ ሲሆን ይህንንም በቁጠባ እና ብልሃት በተሞላበት የኢኮኖሚ አስተዳደር ከያዙት ትልቅ የኢኮኖሚ ግብ ላይ የሚያደርስ ነው:: የሃገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ግኝት ምርኩዞች በላኪዎች እና በውጪ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከሚልኩት መሆኑ እሙን ነው::በላኪነት ስራ ላይ በብዛት ተሰማርተው የሚገኙት የገዢው መደብ አባላት እና ዘመድ አዝማዶቻቸው እንዲሁም በጥቅም ትሥሥር ላይ የተለጠፉ አቆርቋዥ ነጋዴዎች ንግድን ሽፋን ሃገሪቷን በማራቆት ስራ ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ::የወያኔ ባለስልጣናት ደሞ ከውጪ አገር ዜጎች ጋር የውስጥ ሽርክና በመፍጠር በጥቅም ትሥሥር ከመሬት ጀምሮ እስከ ማንኛውም ማተሪያሎች ከቀረጥ ነጻ ወደ ሃገር ውስጥ ሲገቡ በኢንቨስትመንት ስም ከሚመሰረተው ድርጅት ጋር የማይገናኙ ውድ እቃዎች ሳይቀሩ ገብተው ሃገሪቷ ማግኘት የሚገባትን እንዳተገኝ ባለስልጣናት ጋሬጣ ሆነዋል::

የወያኔ ባለስልጣናት ቤተሰቦች እና ዘመድ አዝማዶች በላኪነት ስራ ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ በግልጽ የሚታወቅ...ገንዘብን ምንም አይነት ዋስትና ሳያሲዙ በአነስተኛ ወለድ እየወሰዱ የማይከፍሉ እና ሰነድ የሚያስጠፉ ሲሆን ያለምንም ቀረጥ እና ታክስ ወደ ውጭ ሃገር ምርቶችን በመላክ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሃገር ቤት ከማምጣት ይልቅ በተለያዩ የአውሮፓ እና የኢሲያ ሃገራት ባንኮች ይዶሉታል::

ብሄራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬን ለመሸጥ እና ለመግዛት ዋጋ ቢወስንም የወያኔ ቴሌቭዥን ይህንን ቢናገርም በተግባር ግን እየተምታታ ያለው የውጭ ምንዛሬ ሂደት የግል ባንኮች ግን የውጭ ምንዛሬ መግዣ ዋጋን ወደጎን በመተው ከወያኔ የላኪ ድርጅቶች የውጭ ምንዛሬ በመሸጫ ዋጋ ሲሸምቱ እየተገኙ በዝምታ ታልፈዋል:: ይህም በሃገሪቷ የኢኮኖሚ ሂደት ላይ እንቅፋት የሆነ ሲሆን አንዳንድ ላኪዎች ከመንግስት ባንኮች የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሬ በተዘዋዋሪ ለግል ባንኮች ሲቸበችቡ እየታየ በዝምታ እየታለፈ ነው::የሕወሓት ስውር እጆች የግል ባንኮችን እያዳከማቸው ነው::በመተማ በሞያሌ በመልካ ጀብዱ በኩምሩክ በሁመራ በሃርትሼክ ወዘተ በኢትዮጵያ ዙሪያ ገባ የድንበር ከተሞች ላይ በከፍተኛ የኮንትሮባንድ ንግድ ላይ የተሰማሩት በአብዛኛው የወያኔ አባላት እና የአከባቢ ባለስልጣናት ካድረዎች ከሚወጡ የሃገር ውስጥ ምርቶች የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ለግል ጥቅማቸው እንደሚያውሉት ታውቋል::ይህም ጉዳይ በከፍተኛ ደረጃ ከብሄራዊ ባንክ ጀምሮ እስከ ድንበር ከተሞች የባንክ ቅርንጫፎች ድረስ በሙስና መረብ የተያያዘ የባለስልጣናት ስውር እጆች የተደባለቁበት ነው::

መሰረታዊ ለሆኑ የገቢ እቃዎች የጠፋው የውጭ ምንዛሬ ለሃገሪቱ የፖለቲካ ፍጆታ የመከላከያ እና የደህንነት መዋቅሮች ሲመደብ ማየት በህዝብ ጉሮሮ ላይ ቆሞ ስልጣንን በማስረዘም ሃገርን እየገደሉ መሆኑ በአደባባይ እያየነው ያለነው ሃቅ ነው:; የብሄራዊ ባንክ ከጊዜው የገዢ መደቦች ጋር በማበር የሃገርን ሀለቄታዊ የኢኮኖሚ ጥቅሞች አሳልፎ እየሰጠ ከባንክ አሰራር ውጭ ከፖለቲካው ጋር ግንኘነት ያሌላቸው አስመጪ ነጋዴዎች ማግኘት ያለባቸውን የውጭ ምንዛሬ ባለማግኘታቸው በ20 እና 30 % ጭማሪ ምንዛሬዎችን በመግዛት ጋሬጣ የተፈጠረባቸው ሲሆን ይህ ሁሉ የገዢው መደብ አባላት የፈጠሩት የውጭ ምንዛሬ ዘረፋ በሃገሪቷ ላይ የኑሮ ውድነት እንዲሰራፋ አድርጎታል::

Friday, December 27, 2013

ትግሉ የሁሉንም ተሳትፎ የሚጠይቅበት ወሳኝ ምእራፍ ላይ ደርሷል!!!

ራሱን የብሄረ አማራ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ብሎ የሚጠራው ድርጅት በከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ ውስጥ ገብቷል። የህወሃትን ዙፋን ከመጠበቅ ባለፈ ምንም ሚና የሌላቸው የብአዴን አመራሮች ያለፉትን ሶስት ወራት በተለያዩ መንገዶች የድርጅቱን አባሎች ሲገመግም ከርመዋል። በግምገማዎች ላይ እንደተረጋገጠው ብአዴን የህወሀትን ዙፋን ሊሸከሙ የሚችሉ ወጣቶችን ኮትኩቶ ለማሳደግ አለመቻሉ ነው። በብአዴን ውስጥ ለሚታየው የውስጥ ትርምስ በድርጅቱ ውስጥ የሚገኙ የግንቦት7 አባላትና ደጋፊዎች እየተጫወቱት ያለው ሚና በሌሎች ድርጅቶች ውስጥ ላሉ የንቅናቄው አባላት ጥሩ ትምህርት የሚሰጥ ነው። የንቅናቄው አባሎችና ደጋፊዎች በድርጅቱ ውስጥ የታቀፉ ወጣቶችን የፖለቲካ ግንዛቤ ከማሳደግ ጀምሮ ፣ የንቅናቄውን መረብ እስከ ወረዳዎች በመዘርጋት ከፍተኛ ሚና በመጫወት ላይ ናቸው። ሰሞኑን በገሀድ በየግምገማዎች ላይ ሲነገር እንደነበረው ብአዴን እወክለዋለሁ ከሚለው የአማራ ህዝብ ሙሉ በሙሉ ተነጥሎ በአየር ላይ የተነሳፈፈ ድርጅት ሆኗል።

ይህን እውነታ ዘግይተው የተረዱት የብአዴን ዙፋን ጠባቂ አመራሮች የሚይዙትን የሚጨብጡትን በማጣት የተለያዩ ውሳኔዎችን እያሳለፉ ነው። ታማኝ የሚሉዋቸውን ካድሬዎች በየወረዳዎች በመላክ በግንቦት7 የሚጠረጠሩትን ወይም የግንቦት7 አባሎች ናቸው ተብለው ከሚገመቱ ሰዎች ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ግንኙነት አላቸው ተብሎ የሚታሰቡትን ሰዎች በመያዝና በማሰቃየት ሌላው ወጣት ንቅናቄውን እንዳይቀላቀል ለማድረግ እቅድ ነድፈው ለመንቀሳቀስ አስበዋል። እንዲሁም አንድ ለአምስት የተባለውን አደረጃጀት በመስሪያ ቤቶች፣ በቤተሰብ፣ በትምህርት ቤቶችና በተለያዩ ተቋማት ላይ በስፋት በማውረድ፣ የሰውን የእለት ተእለት እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር አልመዋል። ወጣቱ አካባቢውን እየለቀቀ ግንቦት7ን ለመቀላቀል የሚያደርገውን እንቅስቃሴ የአካባቢ ፖሊሶችንና የድንበር ጠባቂዎችን በማጠናከር ለመቆጣጠር ውሳኔ አሳልፈዋል።

Thursday, December 26, 2013

የቁጫ ህዝብ ጥያቄ የሚፈታው የዜጎች መብት ሲከበር ነው!! ከአንድነት ፓርቲ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

አንድነት ፓርቲ ልዩ ጠቅላላ ጉባኤውን ታህሳስ 19 እና 20/2006ዓ.ም ያደርጋል 

ኢህአዴግ በሚከተለው የዘረኝነት ፖሊሲና የከፋፍለህ ግዛው አገዛዝ መርህ ዛሬ በሃገራችን የአንድ አካባቢ ህዝብ በሌላው አካባቢ በነፃነት ሰርቶ የመኖር ህገ-መንግስታዊ መብት በገዢው ፓርቲ አመራር አባላት ሴራ ሲጣስ ይታያል፡፡ ባሳለፍናቸው አመታት በማንነታቸውና በእምነታቸው ምክንያት ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው ተረግጠው በአስርና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ተወልደው ወልደው ሃብት ንብረት ካፈሩበት መሬት ተፈናቅለውና በዚሁ ሳቢያ ለስደትና ለልመና የመዳረጋቸው ሚስጢር በማናቸውም መልኩ የኢህአዴግ አምባገነናዊ አገዛዝ ድምር ውጤት ነው፡፡

ካለፈው አመት መጨረሻ አካባቢ በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን በቁጫ ወረዳ ህዝብና ነዋሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን እስራት፤ ስደት፤ ወከባና እንግልት እንዲሁም ሞት በተለያየ የመገናኛ ብዙሃን ድህረ ገፆች መረጃው በስፋት መቅረቡን ተከትሎ ፓርቲያችን በዚህ ጉዳይ ላይ የፖለቲካ አቅዋም ለመያዝ እንዲያስችለው አንድ በፓርቲው ከፍተኛ አመራር የሚመራ ቡድን ወደ ቦታው በመላክ የተሰበሰበውን መረጃ የፓርቲው ብሄራዊ ምክር ቤት ታህሳስ 13ቀን 2006ዓ.ም በጠራው አስቸካይ ስብሰባ በቁጫ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የፖለቲካ አለመረጋጋት መርምሮ ውሳኔ አስተላልፉዋል፡፡

Tuesday, December 24, 2013

የጥራት እና ደረጃ መዳቢ ባለስልጣን መ/ቤት እና ህ.ወ.አ.ት

ነጻነት ይበልጣል (ከጀርመን)


ዛሬ ላስነብባችሁ ያሰብኩት ቀደም ሲል የጥራት እና ደረጃዎች መዳቢ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ተብሎ ይጠራ ስለነበረው አሁን ለአራት ተከፋፍሎ እንዲጠፋ ስለተደረገ ተቋም ነው፡፡ መስሪያቤቱ ምርት እና አገልግሎችን በመቆጣጠር የሸማቹን ደህንነት እና ጤንነነት ማስጠበቅ ፤ የገቢና ወጪ ምርቶችን ጥራት በመከታተል ጉልህ ድርሻ እንዲያበረክት ታስቦ የተቋቋመ ነው፡፡መስሪያቤቱን ለረጅም ዓመታት በበላይነት ይመሩ የነበሩት አቶ መሳይ ግርማ ሲባሉ በውስጡ የፍተሻእናካሊብሬሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የሰርተፊኬሽ አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የኢንስፔክሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የደረጃዎች ዝግጅት ዳይሬክትሬት፣ የስልጠናአገልግሎት ዳይሬክትሬት እና የፋይናንስ ዳይሬክትሬት እና ሌሎች የአገልግጎች ዘርፎች ነበሩት፡፡አቶ መሳይ መስሪያቤቱን ከ16 ዓመት በላይ አስተዳድረዋል፡፡ድንገት ባልተጠበቀ ሰዓት ከአቶ መሳይ እውቅና ውጭ 3 ሰዎች አቶ ተክኤ ብርሀኔ ከመቀሌ፣አቶ ደቻሳ ጉሩሙ ከጅማ እና አቶ ዳንኤል ዘነበ ከሀረርጌተመልምለው ወደ መስሪያቤቱ ተመደቡ፡፡ሰዎች ሳይፈለጉ መመደባቸው ብቻ ሳይሆን በወቅቱ እንዲከፈላቸው የተፃፈላቸው የደመወዝ መጠንም በመስሪያቤቱ የደመወዝ ስኬል የሌለ፤ ካላቸው የትምህርት እና የስራ ልምድ ጋር ምንም አይነት ዝምድና ስለሌለው አቶ መሳይ መክፈል አልችልም በማለት አንገራገሩ፡፡እነሱ መች የዋዛ ቢሆኑ እና እስከ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተዘረጋ ሰንሰለት ስለነበራቸው በስልክ ተደውሎላቸው ሳይወዱ በግድ መክፈል ጀመሩ፡፡ እነዚህ ሰዎች በ2002 ዓ.ም ለሚካሄደው ምርጫ ቅድመ ዝግጅት እንዲረዳ ከየክልሉ ተፈልገው የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ሀዋርያ ሁነው ወደ ፌዴራል መንግስት የመጡ ናቸው፡፡ተክኤ በስፓርት ፣ደቻሳ በሂሳብ እና ዳንኤል በማኔጅሜንት ተመርቀዋል፡፡ሲመጡ የሚያርፉበት የኪራይቤቶች የሚያስተዳድረው ሰፋፊ ግቢየተዘጋጀላቸው ሲሆን ዳንኤል ከአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጽ/ቤት አጠገብ፤ተክኤ እና ደቻሳ ደግሞ 22 አካባቢ ባለ ሰፋፊ ግቢ እንዲኖሩተመቻችቶላቸዋል፡፡

ዋናው የቅርብ ጊዜ አላማቸውም በ2002 ለሚደረገው ምርጫ የመንግስት ሰራተኛውን ከኢህአዴግ ጎን ማሰለፍ እና ቀጣይ አመራሮችን ማዘጋጀትነው፡፡በዚህም መሰረት ባሉበት ቀበሌ በምርጫ ጣቢያ ሀላፊነት ተመድበው ይሰራሉ፡፡በተጨማሪም መንግስት በቢ.ፒ.አር.(business process reengineering) ብሎ ወደፊት ሊዘረጋ ላቀደው የሰራተኞች ማፈኛ መንገድ የራሱን ታማኝ የስለላ ሰዎች ወደመሲሪያቤቱ ያስገባል፡፡የአዲሶቹን ተመዳቢዎች አመጣጥ ተከተሎ በመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የፍረሃት ድባብ ተፈጠረ፡፡እነሱ ሰራተኞችን ወደሚጭነው ሰርቪስ ሲገቡ አንድም ሰው ትንፍሽ አይልም፡፡የአውቶቡሱ ሰው ሁሉ በጸጥታ ይዋጣል፡፡ጆሮ ጆሮ እያሉ ያንሾካሽካሉ፡፡በእረፍት ሰሀት እነሱ በተቀመጡበት አካባቢ አብሮ ተቀምጦ ሻይ ቡና የሚል የለም፡፡ሲመደቡ የኮሙኒኬሽን ሰራተኞች ተብለው ሲሆን ከመስሪያቤቱ እውቅና ውጭ ከነአቶበረከት ሰምኦን ጋር በየሳምንቱ ስብሰባ እና የመረጃ ልውውጥ ያደርጋሉ፡፡ከሳይንስና ቶክኖሎጂ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ ጋር ከፈለጉ በአካል መኪና አዝዘው ካልፈለጉ በስልክ በቀጥታ መገናኘት ይችላሉ፡፡አቶ መሳይ እና ሌሎች የመስሪያቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የማያውቁት መረጃ ከነሱጋ ይገኛል፡፡በዚህ የአንድ አመት ቆያታቸው በመስሪቤቱ ደጋፊዎችን ማፍራት አልቻሉም፡፡

“ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል”!! ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) የተሰጠ መግለጫ

ታህሣሥ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.


በዓለም ላይ እስከአሁን የተከሰቱ መንግሥታት (ቅኝ ገዥዎችን ጨምሮ) ጨቋኝ (አምባገነን)፣ በዝበዥ፣ ዘራፊ (በሙስና የተዘፈቀ) … ወዘተ ሊሆኑ ይችላሉ። አሁን ኢትዮጵያን በመግዛት ላይ እንዳለው የትግሬ ዘረኛ ቡድን የሚገዛትን ሀገርና ሕዝብ የሚጠላና ሀገሩንም ለማጥፋት 24 ሰዓት የሚሠራ መንግሥት ግን እስከ አሁን በታሪክ አልታየም። ወደፊትም ከወያኔ በስተቀር የሚገዛትን ሀገር፣ ታሪኳንና ሕዝቧን የሚጠላና ሆን ብሎ ለማጥፋትም ቀን – ተሌት የሚጥር መንግሥት በምድር ላይ ይከሰታል ብለን አናምንም። ይህ የትግሬ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን መጥላቱን የሚያሳይ የድርጊቱን ሥንክሣር መዘርዘር ቢቻልም፣ በአሁኑ ሰዓት የተከሰቱ ሁለት ታላላቅ ብሔራዊ ጉዳዮችን ብቻ እንኳ ብናይ ዘረኛው ቡድን ምን ያህል የሚገዛትን ሀገርና ሕዝቧን አምርሮ እንደሚጠላ ፍንትው አድርገው ያሳያሉ፦

በሣዑዲ አረቢያ የወገኖቻችን ደም በግፍ ሲፈስስ፣ እህቶቻችን ያለርህራሄ በቡድን ሲደፈሩ፣ በ21ኛው ክ/ዘመን በሰው ልጅ ላይ የፈፀማል ተብሎ የማይታሰብ ኢሰብአዊ ግፍ ሲፈፀምባቸውና በአጠቃላይ በሀገሪቱ ላይ ብሔራዊ ውርደት ሲደርስ የትግሬው ዘረኛ ቡድን “የሣዑዲ አረቢያ መንግሥት በሀገሩ ላይ ይህንን ማድረግ መብቱ ነው” ነበር ያለው።

በዚህ ሰቅጣጭ ሐዘን ውስጥ ተውጠንና በስቃይ ላይ ያሉ ወገኖቻችንን ለመርዳት ላይ ታች በምንልበት ጊዜ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ታጥቆ የተነሳው የትግሬው ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ጠብቀው ያቆዩትን 1600 ኪ/ሜ ርዝመትና ከ20-60 ኪ/ሜ ወደ ኢትዮጵያ ጥልቆ የሚገባውን ከሱዳን የሚያዋስነውን ድንበራችንን በሕገወጥነት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ፈርሞ ለሱዳን አስረከበ። ምንም እንኳን በሚስጥር ሊይዘው ቢሞክርም የድንምበር ማካለሉ ከጥር ወር 2006 እስከ መስከረም 2007 ችካል በመቸከል እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።

ከችሎቱ ጀርባ ያለው ጥቁር ዳኛ ማነው? (ክፍል አንድ)

በስለሽ ሃጐስ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥር አስር ቀን 2004 ዓ.ም በእነ ርዕዮት አለሙ ላይ ያስተላለፈው የጥፋተኝነት ውሳኔ በችሎቱ የተሰየሙት ዳኞች በነጻ ህሊና የሰጡት ፍርድ ነው ብሎ ያመነ ሰው አልነበረም፡፡ እዚህም እዚያም ሲወራ የነበረው ውሳኔው በመንግስት ፍላጎት ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነበር፡፡ ፕሮፌሰር መስፍንን ጨምሮ በርካታ ሰወች ይህንኑ በአደባባይ ጽፈውታል፡፡ ቆየት ብሎ ግን ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ የሚገልጹና ተጨማሪ ነገር ለማወቅ የሚገፋፉ መረጃዎች ወደኔ መምጣት ጀመሩ፡፡

እርግጥ የኢትየጵያ የፍትህ ስርአት በተደጋጋሚ ተፈትኖ የወደቀና ነጻነቱ ጥያቄ ውስጥ የገባ ከመሆኑ አንጻር እንዲህ አይነት የጥርጣሬ ድምጾች መሰማታቸው በራሱ ብዙ የሚገርም አይደለም፡፡ በመሆኑም በጉዳዩ ላይ የምር እንዳስብ የሆንኩት ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ በመስማቴ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም ከዚያ በፊት በነበረው የፍርድ ሂደት ያስተዋልኳቸው ሦስት አጠራጣሪ ክስተቶቸ ናቸው እንደ ጋዜጠኛም ሆነ እንደ ርዕዮት የቅርብ ሰው ስለ ጉዳዩ ብዙ ለማወቅ እንድታትር የገፋፋኝ፡፡

የመጀመሪያው፣ ርዕዮት በማዕከላዊ ምርመራ ላይ እያለች የታዘብኩት ነው፡፡ ርዕዮት በተያዘች በማግስቱ አራዳ ፍርድ ቤት ቀርባ ፖሊስ የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሲጠይቅ አባቷና ጠበቃዋ የሆኑት አቶ አለሙ ደግሞ ቤተሰብ እንዲጠይቃትና የህግ ምክር እንድታገኝ አመለከቱ፡፡ ዳኛዋም ፖሊስ ይህንኑ እንዲፈጽም አዘውና የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሰጥተው ችሎቱ አበቃ፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ርዕዮት፣ ጠበቃም ሆነ ቤተሰብ ሳታገኝ 28ቱ ቀን አለፈ፡፡

የነበረው አማራጭ የቀጠሮው እለት ጠበቃዋ ገብተው ድጋሜ እንዲያመለክቱ ማድረግ ብቻ ነበር፡፡ እኛም ፍርድ ቤት ስትመጣ ጠብቀን ቢያንስ አይኗን ለማየት ጓጉተናል፡፡ በዕለቱ የሆነው ግን በጣም አስገራሚም አሳዛኝም ነበር፡፡

ቀጠሮው ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ነበረ፡፡ በዚያን ዕለት ጠዋት 2፡30 ቁርስ ላደርስላት ወደ ማዕከላዊ ስሄድ ከዚያን ዕለት በፊትም ሆነ በኋላ አይቻት የማላውቃት አንዲት ልጅ “ርዕዮትን በሌሊት ወደ ፍርድ ቤት ወስደዋታል ሮጠህ ድረስባት” ብላኝ ካጠገቤ ብን አለች፡፡ ለአቶ አለሙ በስልክ ይህንኑ ነግሬ ወደ ፍርድ ቤቱ አመራሁ፡፡ ቦታው ቅርብ በመሆኑ 10 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ደረስኩ፡፡ እኔ ወደ ግቢው ስገባ ርዕዮት በፒካፕ መኪና ተጭና እየወጣች ነበር፡፡

የፍርድ ቤቱ የቀጠሮ ሰዓት የተለወጠው ባጋጣሚ ወይም በስህተት ሊሆን ይችላል በሚል ይህ ለምን እንደሆነ መዝገብ ቤቱን ጠይቀን የተረዳነው ኬዙን ያየችው ዳኛ በህመም ምክኒያት ለረጅም ጊዜ ስራ የምትገባው ከሰዓት በኋላ ብቻ መሆኑንና ሁኔታው ለእነሱም እንግዳ ነገር መሆኑን ነው፡፡ ስለዚህም የቀጠሮው ሰዓት ለውጥ በፖሊስ ፍላጎት ሆን ተብሎ ተፈጽሟል ለማለት ይቻላል፡፡ ይህ ማለት በፍርድ ቤቱና በፖሊስ መሀከል ሊኖር የሚገባው መስመር ላይ ችግር አለ ማለት ነው፡፡

ሌላው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለ5 ወራት ያህል ግራና ቀኙን ሲያከራክር ሰንብቶ ታህሳስ 17 2004 ዓ.ም የመጨረሻውን ፍርድ ለመስጠት በተሰየመበት ዕለት የነበረው ሁኔታ እንዲሁ ጥርጣሬውን የሚያጠናክር ነው፡፡ ቀጠሮው ከጠዋቱ 3፡00 የነበረ ቢሆንም በዚያን ዕለት ይሰጣል የተባለውን ፍርድ ለመስማት የተገኙ ሰዎች የችሎቱን አዳራሽ የሞሉት ቀደም ብለው ነበር፡፡ ዳኞቹ 1 ሰዓት አርፍደው 4፡00 ላይ ችሎቱ ተሰየመ፡፡ ወዲያውኑ ውሳኔው ማለቁንና ይሁን እንጂ በኮምፒውተር ተጽፎ ስላላለቀ ከሰዓት በኋላ እናርገው አሉ፡፡ በዚህ ጊዜ የእነውብሸት ጠበቃ አቶ ደርበው “ከሰዓት ሌላ ቀጠሮ ስላለኝ አልችልም” ብለው ከአራት ቀን በኋላ ለታሀሳስ 21 እንዲሆን አማራጭ አቀረቡ፡፡ ዳኛው ግን አልተቀበሉትም፡፡ “እነዚህ ሰወች ያሉት በማረሚያ ቤት ነው፤ ቀጠሮው ከሚራዘም 7 ሰዓት እንገናኝና እስከ 8፡00 እንጨርሳለን” የሚል አማራጭ አቅረቡና በዚሁ ተስማሙ፡፡

“ሕወሓት ከመለስ ሞት በኋላ እየተዳከመ ያለ ድርጅት ነው” (ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ – የቀድሞ ህወሃት ታጋይ እና አመራር የነበሩ)

“ኢህአዴግ ለዘለዓለም መግዛት አለብኝ የሚል ድርጅት ነው”



ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ከህወሓት ጋር 17 ዓመታት በትግል ያሣለፉ እና ከፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች መካከል አንዷ ነበሩ፡፡ በ1993 ዓ.ም ከፓርቲው ከተሰናበቱ አባላት አንደ ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት የ“አረና” ፓርቲ አባል የሆኑት ወ/ሮ አረጋሽ በአጠቃላይ ጉዳዮች ዙሪያ ከ“ሎሚ” አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ጋ  ያደረጉትን ክፍል አንድ ቆይታ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡-


በእስር ከሚገኙ የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የተሰጠ መግለጫ

ኢትዮጵያ ከአንድ ሺህ አራት መቶ አመታት በፊት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ማህበረሰብ ካሰፈነው ፍትህ የላቀ ፍትህ ማስፈን ችላ ነበር። የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉስ በነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) አንደበት ‹‹በሐበሻ አንድም ሰው የማይበደልበት ንጉስ አለ›› ተብሎለታል። እንዲህ አይነት ፍትህ በዚህ መልኩ ለማስፈን ምን ያህል ፍትሀዊ፣ እውነተኛ እና የሰለጠነ ማህበረሰብ መገንባት እንደሚጠይቅ ግልፅ ነው። በሀገራችን የነበረው ፍትህ በጊዜው ነፃነት እና ፍትህ ፍለጋ ይዋትቱ የነበሩትን ማስጠለል የቻለ እና ዘመናትን ተሻጋሪ ነበር። ግና የዛሬው አሳዛኝ እውነታ ‹‹ሰዎች ስለ ፍትህ ግንዛቤ ባልነበራቸው በዚያ ዘመን የፍትህ ጥግ የደረሰችው አገራችን ሰዎች ሁሉ ወደ ዲሞክራሲ እና ፍትህ ፊታቸውን ሲያዞሩ ለምን ጀርባዋን ሰጠች?›› ብለን እንድንጠይቅ አስገዳጅ ሆኗል።

Read full story in PDF: …የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የተሰጠ መግለጫ..

‹‹በታማሚዎች መነገድ ስንት ያተርፋል?›› (ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ – ከቃሊቲ እስር ቤት)

በውብሸት ታዬ

“ፀሐይ በሞቀው…” የፍርድ ሂደት ራሴን ለመከላከል አቅርቤው ከነበረው የተከሳሽ የመከላከያ ቃል በኋላ ዳግም ድምጼን ለማሰማት የተመለስኩበት አጋጣሚ ለወራት ሲያሰቃየኝ ለቆየው የኩላሊት ሕመሜ የቃሊቲ ማ/ቤት “የጤና ባለሙያዎች” ምንም ሕክምና ሊሰጡኝ እንደማይችሉ መሆኑ ቅር ያሰኘኛል፡፡ ጥልቅ ፍቅር እና ክብር ላለኝ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ከመልካም ዜና ጋር ብመጣ እንዴት ደስ ባለኝ ነበር፡፡ አልሆነማ!

ጉዳዩን የበለጠ ግልፅ ለማድረግ በተደረገልኝ የኩላሊት የአልትራሳውንድ ምርመራ በተለይ በግራ ኩላሊቴ ላይ በአሳሳቢ ሁኔታ እጅግ የተከማቸ አሸዋ መኖሩ ተረጋግጧል፡፡ በግራም በቀኝም ያሉ ወገኖች ይህን በማንኛውም ጊዜ መመልከት ይችላሉ፡፡ (ለጠላትም ለወዳጅም አላልኩም፡፡ ምክንያቱም በግራና በቀኝ በተሰለፉት ውድ ኢትዮጵያውያን መካከል እየከረረ የመጣ የሀሳብና የመስመር ልዩነት እንጂ ጠብታ የጠላትነት መሰረት እንደሌለ ታሪክና እውነት ይመሰክሩልናል፡፡) ለማንኛውም የቃሊቲዎቹ ሐኪሞች ስቃዬ ሊሰማቸው አልቻለም፤ ወይም አልፈለጉም፡፡ ከቶ ለምን ይሆን?

ይህን አስደማሚ የሰቆቃ ድራማ ከጀርባ ሆኖ እየመራ ያለው ባለ እጀ ረጅሙ ማን ይሆን? ለመሆኑስ አማራጭ በሌላቸው ታማሚዎች ጤንነት መነገድ ስንት ያተርፋል? ምን ይሉት ርካታስ ያጐናፅፋል? ከእኛ ስር የበቀለው የነገይቱ ኢትዮጵያችን ተረካቢ ትውልድስ ይህን አስፀያፊ ድርጊት እንዴት ይመለከተዋል ትላላችሁ? ሁላችንንም ቸርና ፍፁም የሆነው እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

በተለይ እኔ ባለሁበት የእስርና የጤንነት ሁኔታ ላይ የሚገለፅ ሀሳብ ስሜታዊነት ሊንፀባረቅበት ቢችል ትረዱኛላችሁ ብዬ አምናለሁ፡፡ ሌሎችን ለመውቀስም፣ የጥላቻ ስሜትንም ለመግለፅ ተደርጎ እንዳይወሰድብኝም በትህትና እጠይቃለሁ፡፡ ክብርና ፍቅር የሚገባችሁ ውድ ኢትዮጵያዊያን በግሌ የእስር ቆይታዬ በነፍሴ ውስጥ እንደ ውቅያኖስ የጠለቀ ፍቅርና የእናንተን አጋርነት በማይነጥፍ አሳቢነት አገኘሁበት እንጂ ጥላቻን አልተማርኩበትም፡፡

እኛ ኢትዮጵያዊያን ነን፡፡ የታሪክ፣ የእምነት፣ የወግና የባሕል በአጠቃላይም የማንነት ፅኑ መሰረት አለን፡፡ ትናንት የመጣን ነገ የምንሔድ አይደለንም፡፡ እንኖራለን፤ ቢያንስ ትውልድ ይኖራል፡፡ ታዲያ እንዴት ህክምና በመንፈግ፣ ከቤተሰብ አርቆ በማሰር (የሁለትዮሽ እንግልት ለመፍጠር በማሰብ) ይህን ማንነት እንጣው? አይሆንም!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!

አክባሪ ወንድማችሁ ውብሸት ታዬ /ከቃሊቲ እስር ቤት/

ምንጭ፡ ኢትዬፎረም

Monday, December 23, 2013

ከአቶ አያሌው መነሳት ጀርባ የአቶ ደመቀ ሚና! "የቆየ ቁጭትና ቁርሾ ነው"

በአማራ ክልል የተካሄደውን ሹም ሽር ተከትሎ የተሰጠው ሹመትና የሹም ሽሩ አካሄድ መነጋጋሪያ ሆነ። “በቃኝ አሉ የተባሉትን ባለስልጣን አውርዶ እንደገና መሾም የተነቃበት የህወሃት የማረጋጊያ ጨዋታ ነች” ሲሉ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ተናገሩ። በሹም ሽሩ የአቶ ደመቀ መኮንን እጅ እንዳለበትና መንስዔውም “የቆየ ቁጭትና ቁርሾ” እንደሆነ ተጠቆመ።

የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው ጎበዜ ከመንበራቸው እንዲነሱ ተደርጓል። የመንግስት ልሳን መገናኛዎች እንዳመለከቱት አቶ አያሌው ከሃላፊነታቸው የተነሱት ታህሳስ 9/2006 በተጠራ አስቸኳይ የክልሉ ጉባኤ ነው። አዲስ ሹመት ያስፈለገው አቶ አያሌው ባቀረቡት “የመተካካት” ጥያቄ እንደሆነም ተመልክቷል። ምትካቸው የነበሩት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የክልሉ ፕሬዚዳንት ሆነዋል።

አቶ ገዱ ፕሬዚዳንትነታቸው በጉባኤ ተወስኖ ይፋ ከመደረጉ ጎን ለጎን ዜና የሆነው የሳቸው ሹመት ሳይሆን የአቶ አያሌው ስልጣናቸውን በፍላጎታቸው መልቀቃቸው ነው። አቶ አያሌው የ”በቃኝ” ጥያቄ ማቅረባቸው ከተሰማ ብዙ የቆየ ቢሆንም አሁን አስቸኳይ ጉባኤ ተጠርቶ የተወሰነበት ምክንያት ዜናውን አነጋጋሪ ያደረገው ጉዳይ ነው።

የአቶ አያሌው ከሃላፊነታቸው መነሳት ከግራና ቀኝ መነጋገሪያ በሆነ ማግስት ኢህአዴግ የሙሉ አምባሳደርነት ሹመት እንደሰጣቸው ይፋ መደረጉም ሌላ ግርምት ፈጥሯል። በ”መተካካት” ሰበብ ከስልጣን ተነሱ የተባሉት አቶ አያሌው “ባለሙሉ ስልጣን” አምባሳደር ሆነው መሾማቸው ደግሞ የሹም ሽር ተውኔቱን “ኮሜዲ” አሰኝቶታል ያሉና በማህበራዊ ድረገጾች መዝናኛ ያደረጉት ጥቂት አይደሉም።

Saturday, December 21, 2013

የሕወሓት አደገኛ የዘረኝነት መርዝ እና የናዚ ፍልስፍና

ከመጀመርያው ዓለም ጦርነት ማገባደጃ ቦኋላ በጀርመን ማደግ ጀምሮ የነበርው ´´የናሺናል ሶሻሊስት ፓርቲ´´ የናዚ የፖለቲካ ዘይቤን በማስፋፋት ፣ የፋሺስቶች የቀኝ ክንፍ እንቅስቃሴ በዛን ወቅት በዋናነት ይታገል ፣ ይዋጋ ነበረው አንዱ ኮሚኒስቶችን ነበር ፡፡ እነዚህን ክፍሎች ዒላማ ካደረገበት ምክንያት አንዱ ፣ በወቅቱ በዓለማችን ዙርያ እየተጠናከረ የነበረውን ፣ የኮሚኒስቶች እንቅስቃሴ ለመቋቋምና ፣ በስራቸው እየተደራጀ የነበረውን የሰራተኛውን ክፍል (working class ) ከኮሚኒስቶች ነጥሎ በናዚስቶች ስር ለማሰለፍና ነበር ፡፡

የናዚ ፍልስፍና መሰረት ፣ የ አርያን ታላቅ ዘር (Aryan master race ) ከሌሎች የሰው ፍጠረት ዘሮች ሁሉ የላቀና ፣ የተመረጠ ሕዝብ እንደሆነ ያምናሉ ፡፡ እነሱ የሚሰጡትን ገጸ-ባህሪያት የማያሟላ ፣ እንደ ሰው ካለመቁጠራችወም በላይ ``በስህተት ወይም ሳይፈለጉ ተፈጥረው ``የተገኙ ነገሮች ተደርገው ስለሚታዩ ፣ መደምሰስ ወይም መጥፋት አለባቸው ብለው ያምኑ ነበር ፡፡ በዚህም የተነሳ ታሪክ እንደመዘገበው ከነሱ ዝርያ ውጪ ናቸው ብለው ፣ በተለያየ ዘርፍ የመደብዋቸውን ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሌሎች ዜጎችን በየማጎርያ ካንፑና (concentration camp)፣ በየእስር ቤቱ እየተሰበሰቡ በሚያሰቅቅ ሁኔታ በጋዝ ጢስ ፣ በጥይት እሩምታና በተለያየ መንገድ እንደጨረሱዋቸውና ፣ ከፊሎቹንም ፣ በጣም አሰቃቂና ፣ኢ-ሰባዊ በሆነ መንገድ ፣ ሰውነታቸውን ለህክምና ምርምር ይጠቀሙባቸው ነበር ፡፡ ከዚያም አልፈው ሄደው፣ የሰውን ልጅ ክቡር ፍጡር ከእንሳት በታች አድርገው በመቁጠር ፣ ቆዳቸውን ለማስታዎሻ (souvenir) ለመብራት አንፖል ማጌጫና ፣ ለቤት ማሳመርያ ቁሳቁስ ይጠቀምባቸው እንደነበር ፣ ዛሬ ከነማስረጃው በተለያዩ የማጎርያ ካንፕ ፣ ሙዝየም ውስጥ ተቀምጠው ማየት ይቻላል ፡፡

እነዚህ ከአርያን ዘር ውጪ ያሉትን ፣ መፈጠር አይገባቸውም ነበር ብለው የመደቧቸውን ፣ ይሁዲዎችን ፣ ጂብሲዎችን ፣ የአዕምሮ ህመምተኞችን ፣ አካለ ስንኩላንን፣ ጥቁሮችን ፣ ከነሱ ሃይማኖት ውጪ ያሉትን ፣ እንደ የጆሃቫ እምነት ተከታዮችን ፣ የፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸውንና ፣ የተለየ ጾታዊ አቀራረብ እምነት የነበራቸውን ፣ ከሰባዊ ማንኛውም ፍጡር በታች አድርገው ከማየታቸውም በላይ እንደ የግል መገልገያ ቁሳቁስ አድርገው ፣ አዕምሮዋችን መገመት ከሚችለው በላይ ፣ ኢሰባዊ ድርጊት ይፈጽሙባቸው ነበር ፡፡ የፓርቲ መመሪያቸውም ከላይ የተዘረዘሩትን ከነሱ ውጭ የተፈጠሩትን ፣ የማጥፋት መብት እንዳላቸው ተደርጎ እንዲታመንበት ተቃኝቶ የተዘጋጀ ንድፈ -ሃሳብ ወይም የፖለቲካ ዘይቤ( ideology) ስለነበር ፣ አብዛኛው ሕዝባቸውን በዚህ ፍልስፍና አሳምነው ፣ አሳስተው ከጎናቸው ማሰለፍ ችለው ነበር ፡፡

አርያን የሚለውን ፣ ቃሉን መጠቀም የጀመሩት ሰዎች ፣ ለዚህ የዘረኝነት ተግባር መጠርያ ለማድረግ ሳይሆን ፣ ለአንድ አካባቢ ሕዝብ (ፖርቶ ፣ ኢንዶ አውሮፓውያን ...ወዘተ) መጠርያ ወይም መለያ ለማድረግ ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም ናዚዎች ይህንን እውነታ ቀይረው ፣ ትክክለኛ ሕዝብ ማለት በነሱ በነሱ እምነት ፣ ነጭ ፣ ሰማያዊ የዓይን ቀለም ያለውና ፣ ወርቃዊ ቀለም ጸጉር ያለውና ፣ (white, blue eyes and blond hair) የነሱን የፖለቲካ መስመር የሚከተል ...ወዘተ ብለው ያምናሉ፡፡

Friday, December 20, 2013

አጋጣሚዎችን ሁሉ ለራሳቸው ጥቅም የሚያውሉ ነውረኞች !

አበራ ሽፈራው (ከጀርመን)
 
እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጥርጥቅምትመጨረሽና  ህዳር ወር 2006 እጅግ አሳዛኝና በህይወት እስከአለን ድረስ የማንረሳው ክፉ አጋጣሚ በእህቶቻችንና በወንድሞቻችን ላይ ግድያን፣ መድፈርን፣ እስርን፣ መታረድንም፣ በመኪና እየተገጩም ጭምር መሞትንም መጀመሩን ያየንበትና የሰማንበት:: ክፉ ወር:: ብዙዎቻችን በውስጣችን ከራሳችን ጋር የተሟገትንበት፣ ምን እናድርግ? ብለን ከቅርብ ጓደኞቻችን ጋር የተነጋገርንበት:: ሌሎቻችንም ተሰባስበን በውስጣችን ያለውን ሃዘን በግልጽና በአደባባይ ዓለም ሁሉ እየሰማ የተነፈስንበት::  ሳውዲ አረቢያዎች ለዘመናት አብሮአቸው የነበረውን ጭካኔ በአይናችን የተመለከትንበት ምን አልባትም እህቶቻችንና ወንድሞቻችን ከዚህ በላይ ሲጨቆኑና ሲረገጡ መኖራቸውንም ለማየት የቻልንበት ጊዜ ይህ ይፋ ወጣ እንጂ::  
  
በእርግጥም ሳውዲዎች ጨካኞች ናቸው ስራቸውም እጅግ አሳፋሪ ነው:: ጊዜ ይለወጣል ሀብትም ይጠፋል  ነገር ግን ታሪካቸው በተለይም በወንድሞቻችን ላይ የተፈጸመው ግፍ ግን ለታሪክ ሲታወስ ይኖራል :: በሳውዲዎች ድርጊት ያላዘነ ኢትዮጵያዊ የለም እኔ እስካየሁትና እስከሰማሁት ድረስ:: ታሪክ የእኛን እንግዳ ተቀባይነትን እንደመዘገበ ሁሉ የእነሱንም ውለታ መላሽነት በእኛ ዘመን ለማየት ችለናል ይህንንም ታሪክ መዝግቦታል:: በክፉ ዘመናቸው በአገራችን ተሰደው እንደ እናት ቤት ኢትዮጵያ እንዳልተቀበለቻቸው ሁሉ ዘሬ ሰርተው ሳይሆን አምላክ በተፈጥሮ በሰጣቸው ተመክተው  የጥጋብ ዱላ በወገኞቻችን ላይ አዘነቡ የብዙ የኢትዮጵያውያን እንባ በአለም ሁሉ ፈሰሰ፣ የአምላክንም እጅ ተማጸነ፣ ብዙዎች የአምላክንም ምህረት በእንባ ለመኑ በእርግጥም አምላክ ሰምቷል መልሱም አንድ ቀን ለአገሬም ይሠጣል::
 
ላለፉት 50 ዓመታት አረቦች ለኢትዮጵያ ያላቸውን ጥላቻ በተለያየ መልኩ ለመፈጸም ሞክረዋል ዋናው መነሻቸውም በሁሉም መልኩ ለመስፋፋት ያደረጉትን እንቅስቃሴ ሁሉ እሽ ብሎ የተቀበላቸው ያለመኖሩና በአፍሪካ ቀንድ የአረቦች አስተሳሰብ ተግባራዊ ሊሆን ያለመቻሉ ሲሆን ይሁንና ሃሳቦቻቸውን ተግባራዊ ለማድረግ ግን አርፈው ተኝተዋል ማለት ግን አይደለም:: ለዚህም ይረዳቸው ዘንድ ኢትዮጵያን ለመበታተን የተጠቀሙት አንደኛው መንገድ የዛሬዎችን ዘረኛ የህወሓት/ ወያኔ ቡድን እንደ ሌሎቹ የኢትዮጵያ ጠላቶች ሁሉ አንደኛው መሳሪያ ሆኖ ያገለገላቸው እኩይ ቡድን መሆኑ ጭምር ነው::

ህወሓትን መመከት የወቅቱ ጥያቄ ነው

አበራ ሽፈራዉ /Abera Shiferaw/


የህወሓት ምስረታና ግቡ ኢትዮጵያዊነት እንዳልሆነና አብዛኞቹ የህወሓት መስራቾችም ኢትዮጵያዊነት የማይሠማቸው እንደሆኑም በተደጋጋሚ ለማየት፣ ለመስማትና ለማንበብ ችለናል።ዛሬም ይህ ማንነታቸውን የሚያሳዩ እጅግ ዘግናኝ ድርጊቶቻቸውን ለእነዚህ እውነታዎች ምስክሮች ናቸው። ህወሓቶች ግቦቻቸውን ለመተግበር ማናቸውንም ድርጊት ከመፈጸም ወደኋላ የማይሉ በዚህ ዘመን ምንም ተወዳዳሪ የሌላቸው የጭቆና ቡድኖች መሆናችውን ማንም ኢትዮጵያዊ የሚያውቀው ሀቅ ነው።

ባለፉት 22 ዓመታት ብቻ እንኳን ብንወስድ እነዚህ ዘረኛና የአገሪቷና የህዝቧ ጠላቶች በግለሰቦች ላይ፣ቡድኖች ላይ፣ በተማሩ ምሁራን ላይ፣ በሐይማኖት ተቋማትና አማኞቻቸዉ ላይ፣ በፖለቲካ ፓርቲዎችና አባሎቻቸዉ ላይ፣ በተማሪዎች ላይ፣ በልዩ ልዩ መሥሪያ ቤቶች በሚሠሩ ሠራተኞች ላይ፣በገበረየዎች ላይ፣በወታደሩና በፖሊሶችም ላይ ፣በሲቪክ ማህበራትና አባሎቻቸዉ ላይ በአጠቃላይ በአገሪቷ ሰብዓዊ ፍጥረት ላይ እስራትን ፣ግርፋትን ፣ሞት፣ ማፈናቀልን፣ ማሳደድን፣ ፈጽመዋል አሁንም ተው የሚል ሀይል በመጥፋቱ በአገሪቷና በህዝቧ ላይ ግልጽ የመንግስት ሽብር ቀጥሏል ፤ማንም የህወሓት ጥቃት ያልደረሰበት የኢትዮጵያ ክልል የለም ለማለት ያስችላል።

የአገሪቷን ንብረትና ሀብት፣ መሬት፣ የንግድ ተቋማትንና ማናቸውንም የመንግስት መዋቅር ተቆጣጥረው የብዝበዛ ግዜያቸውን እያራዘሙ ይገኛል፤ ይህን ችግር ለመቀየርና ነጻነትን ለማስመለስ እየተደረገ ያለውን ሠላማዊ ትግል ለማሳካት የሚደርጉትን ትግሎች በተደጋጋሚ ለማደናቀፍ የሚፈጥሩት ችግር ስንመለከት በርግጥም እነዚህ ሰዎች ለህዝብና ለሀገር እንዲሁም ለዲሞክራሲና ለፍትህ ምንም አይነት ፍላጎት እንደሌላቸውና ይልቁንም ዛሬ ጥቅሞቻቸዉን ላለማጣት የሚያደረጉት ርብርብ መሆኑን ከድርጊታቸው ለማየት ይቻላል። በእርግጥም ለዓመታት የፈጸሟቸው ወንጀሎች እንደሚያስጠይቋቸው የገባቸው ህወሓቶች ስልጣናቸውን በዲሞክራሲያዊ ግብዓቶች ይለቃሉ ብሎ የሚያምን ካለ ተሣሥቷል ያለፈው ታሪካቸው የሚያሳየን ይህንኑ ሃቅ ነውና።

ህወሓትን ለመታገል የትግሉ መንገድ ምንም ይሁን ምን ካልቆረጥን ይኸው መከራችን ማብቂያ እንደሌለው ማስተዋል ያለብን ይመስለኛል። ህወሓቶች በታጠቁት ትጥቅ ተመክተዋል ፤አንዳንዶችም በዘረፉት ሀብትና በአከማቹት ሃብት ተማምነዋለ፤ ድርጅቱም ቢሆን ባለዉ የታጠቀ ሰራዊት ተመክቷል ፣ የትጥቅና የወታደር ብዛትም ምንም መመለስ እንደማይችል ከታሪክ መረዳት ያልቻሉት ለምን እንደሆነ ባይገባኝም ምን አለበትም ውድቀታቸውን እያቀረቡ ይመስለኛል።

ባለፉት ቀናት በሰላማዊ የትግል መሥመር የሚንቀሳቀሱትን የፖለቲካ ፓረቲዎች ማለትም የሰማያዊ ፓርቲ ፣የአንድነትና የመድረክ ፓርቲዎችን ሠላማዊ እንቅስቃሴ ለመገደብ በአባሎቻቸውና በመሪዎቻቸው ላይ የሚያደርጉትን እስራትና ማዋከብ እንዲሁም በእስላምና እምነት ተከታዮች ላይ የሚወስዱትን ግድያ ስንመለከት እነዚህ ህወሓቶች ወደለየለት የሽብር እንቅስቃሴ ውስጥ ገብተዋል ህዝቡም በመንግስት እየተሸበረ ይገኛል።

ዛሬ ኢትዮጵያ በተደራጀና የራሳቸውን ጥቅም ከግብ ለማደረስ በተዋቀሩ የህወሓት መሪዎችና የጥቅም ተጋሪዎቻቸው ወደለየለት ችግር ውስጥ ገብታለች፤ ዛሬ የተደራጁ የመንግስት አሸባሪዎች ኢትየጰያንና ህዘቦቿን በሽብር እያተራመሷት ይገኛሉ፤ ይሁንና ይህንን ችግር ለመለወጥ መፍትሔ ያለው በእኛው በኢትዮጵያውያን እጅ ነውና ከአገር ውስጥ ጀምሮ ኢትዮጵያውያንን በአሉበት አገራትም የተቀናጀ የትግል ስልት በመደገፍ መታገል እንዳለብን አመክራለሁ። ካልሆነ ግን የኢትዮጵያ ህዘብ አሁንም መከራ እንደሚገፋ ሊገባን ይገባል አላለሁ። ህወሓትን መመከት የወቅቱ ጥያቄ ነውና እንነሳ።

ኢትዮጵያን እግዚአብሔር ይባርክ

በህወሓት/ወያኔ መቃብር ላይ ብቻ ኢትዮጵያ በሰላምና በብልጽግና ትኖራለች!

አበራ ሽፈራው/ ከጀርመን/

የኢትዮጵያ ህዝብ ማናቸውም መብቶቹ ተነፍጎ የመኖርና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ ላይ እንገኛለን:: የህዝቡ የሰብዓዊ መብቶችበየትኛውም ዓለም በማይገኝ መልኩ ይጨፈለቃል ለዚህ ያበቃን ደግሞ ትልቁ ምክንያት የህወሓት/ወያኔን የወንበዴነት ጭካኔ ለመጋፈጥ ያለመፈለጋችን ወይም የጭካኔያቸውን መጠን የሚቋቋም ትግል ባለመኖሩና መስዋዕትነትን ለመክፈል ባለመቁረጣችን የመጣብን መከራ እንጂ ህወሓት/ወያኔ ምንም ስለሆነ አይደለም::  የተቃራነውን ጎራ የልብ ትርታ የተረዳው ህወሓት/ወያኔ ሲፈልገው ይገድላል፣ያስራል፣ ያዋክባል፣መሬትንና ንብረትን በሠበብ አስባቡ ይነጥቃል፣ ከስራ ያባርራል፣ የትምህርትና ሌሎች መብቶችን ገፎ ለመከራ ይዳርጋል ካልሆነም ከአገር ማሳደድን እንደትልቅ አማራጭ ተያይዞታል::

በኢትዮጵያ የመኖር መብት እንዳለንና አገራችን መሆኑን እያወቀ መብቶቻችንን የነፈገን ህወሓት/ወያኔ በማን አለብኝነት መቀጠላቸውን ይሁን ብለን ተቀብለን እኛም መስማማታችን ለዛሬው የባሰበት ችግር አድርጎናል:: እነሱ አገራችን አይደለችም ብለው በሚበዘብዟት አገር ላይ ተንደላቀው እየኖሩ ኢትዮጵያ አገሬ የሚሏት እየተዋከቡ ለችግርና ለመከራ መዳረጋችን እጅግ ያሳዝናል:: አሁን ባለው ሁኔታ ኢትዮጵያ ለውጥ ልታመጣ የምትችለው ህወሓት/ወያኔ ይዞት ከተነሳው  አገርን የማጥፋት እኩይ ተግባሩና አስተሳሰቦቹ ጋር ወደመቃብር ሲወርድ ብቻ ነው :: ህዝቡም ጨክኖ ለዚህ እውነት ሲነሳ ብቻ ነው:: 

ከመቼውም ጊዜያት በላይ ህዝባችንና አገራችን ለከፍተኛ ውርደት የተጋለጥንበት ሁኔታ ላይ ደርሰናል:: በሃገራችን መኖር አልቻልንም፣ በሃገራችን ጉዳይ ላይ መወሰን አልቻልንም ፣በሃገራችን ላይ የበይ ተመልካች ሆነን እንገኛለን፣ በህወሓት/ወያኔ ቀኝ ገዥነት ህዝባችንና አገራችን ለከፍተኛ ብዝበዛ ተጋልጠናል፣ በከፍተኛ ሁኔታ በታጠቁ የህወሓት/ወያኔ በዝባዞች ቁጥጥር ውስጥ ወድቀናል፣ ከፍተኛ ህዝብ ከረሃብ አልፎ ለከፍተኛ ጠኔ ተጋልጦ ይገኛል፣ ይህ አልበቃ ብሎ የአገሪቷ ህዝብ ወደ ውጭ ወጥቶ እንኳን እንዳይሰራ ለከፍተኛ ውርደት ተዳርጎ ማንም እንደፈለገው የሚያደርገውና ተከላካይ የሌለው በዓለማችን ላይ የሚገኝ ህዝብ ለመሆን በቅተናል::

ህዝቡ በአገር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር ተጋልጦ ማንም እንደፈለግ የሚጫወትበት ህዝብ ከመሆኑም በላይ በየትኛውም ነገሩ ላይ ሃይማኖታዊ ጉዳዮቹን ጨምሮ በፈለገው መልኩ እንዳያከናውን መደረጉ ይታወቃል:: ከዚህም አልፎ ደግሞ የአገሪቷ መሬት በተለያዩ ጊዜያት ለተለይዩ ጎረቤት አገራትና ሃይሎች በመስጠትና በማካለል ትልቅ የታሪክ ውርደት ገጥሞናል:: ኢትዮጵያ መቼም ባልታየ መልኩ ለትልቅ ችግር ተጋልጣለች:: ይህንን ሁኔታ ለመቀየር ትልቅ መስዋእትነትን የሚጠይቅ ትግል ከፊታችን ተጋርጦብናል ይኸውም በህወሓት መቃብር ላይ አገራችንን እንደገና ለማከም የሚያስገድድ ሁኔታ ገጥሞናል:: የህዝብ መብት ጉዳይ ሲነሳ ግድያ፣እስራትና ሞት ሆኗል እጣችን የአገሪቷን ወሰን ለማስጠበቅ የተወሰደው እርምጃም ምንም ባለመሆኑ ዛሬ ኢትዮጵያ መሬቷንና የግዛት ክልሎቿን እየተነተቀጭ ትገናለች::

በአባቶቻችን ተከብረው የነበሩ ድንበሮችን አሳልፎ ለመስጠት ዛሬ ለሱዳንና ለኤርትራም ጭምር እንደፈለገ የሚደራደረው ህወሓት/ወያኔ ገና ያልጨረሳቸው ኢትዮጵያን የማጥፋት አላማዎቹ አላለቁም እና እንዲሁም ቀደምት ወራሪዎቻችን  የፈለጉትን መሬት አባቶቻችን በትግላቸው ያቆዩትን አገር በባንዳዎች በእጅ አዙር ለማግኘት እየጣሩ መሆኑና ለዚህም ተፈጻሚነት ደግሞ የህወሓት/ወያኔ የባንዳ ቡድን ሃላፊነት ወስዶ እየሰራ መሆኑን ስንመለከት ያሳዝናል::  

ከወያኔ መንደር ውጡ!!!

ዳዊት መላኩ (ከጀርመን)

አቶ አያሌው ጎበዜም እንደምንም የመምህርነት ስራቸውን ትተው የድል አጥቢያ አርበኛ በመሆን ገብተው ወይ ራሳቸውን ነፃ ሳያወጡ ወይ ህዝቡን በትክክል ሳያገለገሉ እንዲሁ እንደ ውሃ ላይ ኩበት እመሀል ላይ እንደዋለሉ የማይቀረውን ስንብታቸውን ተሰናበተዋል፡፡ወያኔ እንደ ሸንኮራ ምጥጥ አድርጎ ተፋቸው፡፡እኔ እስከማውቃቸው አቶ አያሌው ከሌሎች የወያኔ ባለስልጣናት የሚለዮት በሙስና አለመጠርጠራቸው፤ብዙ ማውራት የማይወዱ ሲናገሩም ከባህል እና ከሞራል የማያፈነግጡ፤ለሚኖሩበት ማሀበረሰብ ክብር በመስጠት ሚስታቸው ሳይቀር አብረዋቸው ከሚኖሩት እድርተኞች እኩል መሳተፋቸው ነው፡፡ አቶ አያሌው እንደአባዱላ ገመዳ ብዙ ቤት ገንብተው ለትግሉ ስላስቸገረኝ ውሰዱልኝ ሲሉ አልተደመጡም፡፡እስካሁን ባለኝ መረጃ መሰረት አቶ አያሌው ባህርዳር ከተማ ውስጥ ቀበሌ 14 አካባቢ በማህበር ተደራጅተው በወሰዱት አንድ ቦታ ቤት እንደገነቡ ነው ፡፡ ዘመድ አዝማዳቸውን ስራ በማስገባት አይታሙም ፡፡የአቶ አያሌው ልጆች እንደ ሌሎች የባለስልጣን ልጆች አሜሪካ እና አውሮፓ ወይም አዲስ አበባ ውስጥ ባሉ ውድ የግል ትምህርት ቤቶች አይደለም የሚማሩት፡፡እንደማንኛውም ደሃ ቤተሰብ ባህርዳር ውስጥ ባሉ የመንግስት ትምህርቤቶች ያስተምሩ ነበር፡፡

አቶ አያሌው እንግዲህ እነዚህ መልካም ነገር ቢኖራቸውም የተሰጣቸውን መክሊት አባክነው የክልሉ ህዝብ በየቦታው ሲፈናቀል የክልሉ መሬት እንደዳቦ እየተሸነሸነ ሲታደል የተቀመጡባትን ወንበር ላለማጣት በዝምታ ማለፍን መርጠዋል፡፡ይህ ደግሞ በምንም መልኩ ከተጠያቂነት አያድንም፡፡ከሌባ ጋር አብሮ ስርቆት ሂዶ በቅርብ ርቀት ሲሰርቁ እያዩ ዝም ማለት እና የሰረቀው አብሮኝ ያለው ሰው ነው አንጂ እኔ ነፃ ነኝ ቢሉ ከቅጣት አያመልጡም፡፡እንግዲህ እርሳቸው በስልጣን ላይ በቀዮበት ጊዜ ለጠፋው ሀይወት፤ለወደመው ንብረት፤ለተፈጠረው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ድቀት የድርሻቸውን ይወስዳሉ፡፡

መቼም በዘመኔ ወያኔ ስራና ሰራተኛ ተገናኝተው ባይውቁም እንደአማራ ክልል ባለስልጣናት በእውቀት ድርቅ የተጠቃ የለም፡፡”ሰው ሢታጣ ይመለመላል ጎባጣ” ነው ነገሩ፡፡ሰው ሲታጣ ማለቴ ለወያኔ በታማኝነት የሚያገለግል ማለቴ ነው፡፡አቶ አያሌውን የተኩት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በርቀት ትምህርት በማኔጅመት የመጀመሪያ ዲግሪ ሲኖራቸው በ1998 ዓ.ም የብአዴን ቢሮ ውስጥ ይሰሩ ነበር፡፡የተኛው የተምህርት ዝግጅት ተዛምዶ የክልሉየግብርና ቢሮ ኃላፊ ሁነው እንዲሰሩ እንዳበቃቸው የሚያውቀው ወያኔ ብቻ ነው፡፡ይባስ ብሎ ክልሉን የመምራት ሀላፊነት ለሳቸው መስጠት ከምጡ ወደ ዳጡ ነው፡፡ አቶ ገዱን የአማራ ወጣቶች ከከፍተኛ ትምህርቶች ተመርቀው የፓሪቲ አባል ካልሆኑ ስራ እንዳይሰጣቸው በክልሉ ላሉ ሁሉም ዞኖች ትእዛዝ ሲያስተላልፉ በተቃራኒው አባል ለሆኑት ስልክ ብቻ በመደወል እንዲቀበሉዋቸው ያል ምንም ውድድር እና ማስታወቂ በደብዳቤ ብቻ ሲመድቡ እንደነበር ይታወቃል፡፡በተለይ በ1998ዓ.ም የንግድ እና ኢንዱስትሪ ጽ/ቤት በወረዳዎች መከፈትን ተከትሎ በሁሉም ወረዳዎች የተመደቡ ፈላፊዎች በዚህ አይነት የተመደቡ ነበሩ፡፡አቶ ገዱ የክልል ፕሬዚዳንት ቀርቶ ለቀበሌ አመራርነት ሚያበቃ ስብእና እንደሌላቸው ሚያወቁዋቸው ሁሉ የሚስማሙበት ሀቅ ነው፡፡ግን ምን ይደረግ ወያኔ በሚመራው ሀገር ውስጥ ለሀገር የሚጠቅም ነገር በነፃነት መስራት ስለማይቻል አንዴ አዲሱ ለገሰ፤አንዴ ደመቀ መኮነን፤አንዴ ገዱ አንዳርጋቸው እተፈራረቁ በህዝቡ ትክሻ ላይ ያለከልካይ ይጫናሉ፡፡

Thursday, December 19, 2013

በሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያኑ ላይ ያነጣጠረው ዘመቻ ተጠናክሮ ቀጥሏል !

በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ አንባሳደር ዘነበ ከበደ የሚመሩት የመንግስት ሹማምንቶች ጅዳ ከተማ ውስጥ፡መሽገዋል ያሏቸው 80 ሺህ ኢትዮጵያውያን እጃቸውን በሰላም ካልሰጡ የመንፉሃው አይነት እልቂት እንደሚጠብቃቸው ሲያሞርቱ ! ሪያድ በኢትዮጵያው አንባሳደር መሃመድ ሃሰን የሚመራው ቡድን የሚያሰማው « ጅብ ከሄድ ውሻ ጮህ ጥሪ » ድብቅ አጀንዳ ያለው መሆኑ ተገለጸ !

ከ9 ሚልዮን በላይ የተለያዩ የውጭ፡ሃገር ዜጎች በጥገኝ ነት እንደሚኖሩባት የምትታወቀው ሳውዲ አረቢያ በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ የውጭ ሃገር ዜጎች የመኖሪያ ፈቃዶቻቸውን እንዲያስተካከሉ የተሰጠ የ 7 ወር የግዜ ገደብ መጠናቀቅን ተከትሎ የሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች ኢትዮጵያውያኑ ላይ ብቻ ባነጣጠረ እርምጃ እስካሁን ቁጥሩ በወል ለማይታወቅ ወገናችን አሰቃቂ ህልፈተ ህይወት ስቃይ እና መከራ ምክንያት መሆኑ ይታወቃል። በተለይ ሪያድ ከተማ በተለምዶ መንፉሃ እይተባለ የሚጠራ ሰፈር ሃገራቸው ለመግባት ጥያቄ ባቀረቡ ወገኖቻችን እና በሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች መሃከል በተነሳ ግጭት አያሌ እህቶቻችን በአረብ ጎረምሷች ተደፍረዋል እህቶቻቸውን እና ሚስቶቻቸውን ለመከላከል ጩሀታቸውን ያሰሙ ንጽሃን ወገኖች በአሰቃቂ ሁኔታ በሳንጃ እና በጓራዴ ተገድለዋል ፡፤

ይህንንም ተከትሎ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻች ከአሰቃቂው ጥቃት እርሳቸውን ለመታደግ ከዳር እስከዳር «ሆ »ብለው አደባባይ በመውጣት የሳውዲ አረቢያ አውራጎዳናዎችን በማጨናነቅ የአለምን መገናኛ ብዙን ሽፋን በማጝት በሳውዲ አረቢያ በጠራራ ፀሃይ እና በሌሊት በወገኖቻችን ላይ ሲፈጸም የነበረው ጭፍጨፋ ስቃይ እና በደል በሃገር ውስጥ እና በውጭ ሃገር የሚገኙ ወገኖቻቸውን ዘንድ ቁጣን በመቀስቀስ በሳውዲ መንግስት ላይ ባደረጉት ተጸዕኖ በማን አለብኝነት በወገኖቻችን ላይ ሲፈጸም የነረውን ኢሰባዊ ድርጊት ለግዜውም ቢሆን ጋብ እንዲል አስችሏል።

የፍርሃት ባህልን እያነገሰ ያለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ፤ አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት ወደ ኋላ

(ክፍል ሁለት)

ያሬድ ኃይለማርያም

ከብራስልስ  

ታኅሣሥ 9፣ 2006

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሂደት በኢትዮጵያዊያን ላይ እያሰፈነ ስላለው የፍርሃት ባህል ቀደም ሲል ባሰራጨሁት የዚህ ጽሑፍ የመጀመሪያ ክፍል ውስጥ ባለሙያዎች በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ ለፍርሃት ባህል መስፈን መንሰዔዎች ያሏቸውን ነጥቦች ዘርዝሬ ነበር። በክፍል አንድ ጽሑፌ መግቢያ ላይ እንደገለጽኩት ምንም እንኳን ፍርሃት የግለሰቦች ባህሪ መገለጫዎች መካከል አንዱ ቢሆንም የዚህ ጽሑፍ ትኩረት በወል የምንጋራቸውና በማኅበረሰብ ደረጃም በሚንጸባረቁት የፍርሃት ምልክቶች ላይ ብቻ ያተኮረ ነው። በመሆኑም በዚህ ክፍል ውስጥ የህሊና እና የአካል ቁስልን ባስከተሉ ትላንቶች ውስጥ ማለፍ የሚፈጥረውን የፍርሃት ቆፈንና የሚያስከትለውን መዘዝ በመቃኘት ፅሑፌን ልደምድም።

በአለማችን ታሪክ ከሰው ልጅ አዕምሮ ተፍቀው የማይወጡና እጅግ አሰቃቂ በመሆናቸው ሲታወሱ የሚኖሩ በርካታ ጦርነቶችና የእርስ በርስ እልቂቶች ተከስተዋል። የመጀመሪያውና የሁለተኛው የአለም ጦርነቶች፣ የኦሽዊትዝ ጭፍጨፋ፣ የአፓርታይድ የግፍ አገዛዝ፣ የሩዋንዳው የዘር ማጥፋት እልቂት፣ እንዲሁም በተለያዩ የአፍሪቃ እና የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ውስጥ የተከሰቱትና የሚሊዪኖችን ሕይወት የቀጠፉት እልቂቶች በዋነኝነት ተጠቃሾች ናቸው። እነኚህ በክፉ ክስተትነታቸው በታሪክ የሚወሱት አጋጣሚዎች ካስከተሉት እልቆ መሳፍርት የሌለው ሰብአዊ ቀውስ እና የንብረት ውድመት ባሻገር ከትውልድ ትውልድ የሚወራረስ ትምህርትንም አስተምረው አልፈዋል። በተለይም የምዕራቡ አለም በራሱም ሆነ በርቀት በሌሎች ላይም የተፈጸሙትን እነዚህን መሰል መጥፎ ክስተቶች በአግባቡ በመመርመር፣ መረጃዎችን ሰብስቦና አደራጅቶ በማስቀመጥ፣ በመጽሐፍ ከትቦና እና በፊልም ቀርጾ በማኖር ቀጣዩ ትውልድ እነኚህን መሰል አደጋዎችን ከሚያስከትሉ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ፣ ኃይማኖታዊና ኢኮኖሚያው ቀውሶችና ቅራኔዎች እራሱን በማራቅ ችግሮችን እጅግ በሰለጠነና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንዲፈታ ማድረግ ችለዋል። ዛሬ ላይ ያለው ትውልዳቸውም እነ ናዚ እና ሌሎች አንባገነኖች በታሪካቸው ውስጥ ያደረሱትን ሰቆቃና ግፍ እያሰብ የሚሸማቀቅ ወይም በፍርሃት የሚርድ ሳይሆን ታሪክን በታሪክነቱ ትቶ ሙሉ አቅሙንና ጊዜውን ከሳይንስና ተክኖሎጂ ጋር አዋህዶ በዚህ ምድር ላይ ያሻውን ሁሉ ለማድረግ የሚያስችል አቅም በመገንባት ላይ ይገኛል።

ወደ አገራችን ስንመለስ ኢትዮጵያም ዛሬ ያለችበትን ጂዮግራፊያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ሌሎች ገጽታዎች ለመላበስ ያበቋት እጅግ በርካታ ክፉ እና በጎ ተበለው የሚጠቀሱ የታሪክ ክስተቶችን አስተናግዳለች። ምንም እንኳን ከላይ ከተጠቀሱት የአለማችን አሰቃቂ ታሪኮች ጋር ባይወዳደርም አገራችንም ከውጭ ወራሪዎች በተሰነዘረባት ጥቃትም ሆነ በልጆቿ መካከል በተከሰቱ የእርስ በእርስ ግጭቶች በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ውድ ልጆቿን አጥታለች። ድህነትን ጠራርጎ ሊያስወግድ ይችል ከነበረው አቅም በላይ በብዙ እጥፍ የሚገመት አንጡራ ሃብቷን በጦርነቶች፣ በግጭቶችና በዘራፊዎች ተነጥቃለች። ይህ እና ሌሎች በርካታ ምክንያቶችም ተደራርበው አገሪቱን ከድሃም ድሃ ተብለው ከሚጠቀሱት አገሮች ተርታ አሰልፈዋታል። እንግዲህ ትልቁ ጥያቄ እኛስ እንደ ሌላው ዓለም ሕዝብ አገራችን ካለፈችበት የረዥም ዘመን ታሪክ እና በየወቅቱ ከተከሰቱ መጥፎና በጎ የታሪክ ክስተቶች ምን ተማርን? ተምረንስ ለዛሬ እኛነታችን ምን አተረፍን? በአያቶቻችን እና በእኛ መካከል በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ እና በፖለቲካ ተክለ አቋማችንም ሆነ አመለካከታችን ዙሪያ ለውጦች አሉ ወይ? ለውጣችን ቁልቁል ወይስ ካለፉት ወገኖቻችን የህይወት ተመክሮ ትምህርት ወስደን የደረስንበት የላቀ የአስተሳሰብና የኑሮ ደረጃ አለ? የታሪክ መዛግብቶቻችንስ ያለፉ ነገስታቶችን እና የጦር አበጋዞቻቸውን ከማወደስና ገድላቸውን ከመተረክ ባለፈ በቀጣዩ ትውልድ ሕይወት የጎላ ሚና ሊኖራቸ በሚችል መልኩ ተዘጋጅተዋል ወይ? ወይስ ‘እኔ የገሌ ዘር’ እያለ እንዲያዜምና በአያቶቹ ገድል እንዲያቅራራ ብቻ ተደርገው ነው የተዘከሩት? እንደ እኔ እምነት ከምዕራቡ አለም እኛንና ብዙዎች የአፍሪቃ አገራትን ከሚለዩን ነገሮች መካከል ጥቂቶቹ ከነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ የሚመነጩ ይመስለኛል።

የዛሬ መቶ እና ሁለት መቶ አመት በፊት የተፈጠሩ የታሪክ ክስተቶችን ፍጹም በተዛባ መልኩ እያጣቀስን ልክ የእኛ የልፋት ውጤት አስመስለን እስኪያልበን የምንፎክርና የምንጨፍር እኛ ነን። ታሪክን እና ጀግኖችን ማወደስ ተገቢ ቢሆንም የኛን ድርሻ እነሱን በማወደስ ብቻ ስንገታው አደጋ ላይ ይጥለናል። እንደ አያቶቻችን ታሪክን መስራት ሲያቅተን ታሪክ ሰሪዎችን በማውሳትና በዜማና በግጥም ማወደስ ብቻ ብንኮፈስ የዛሬውን ማንነታችንን አይሸፍነውም። ይህ በአያቶቻችን ታሪክ ውስጥ ተደብቀን ‘በኢትዮጵያዊነቴ እኮራለሁ’ እያሉ ማዜም፣ መፎከር፣ ማቅራራትና ያዙኝ ልቀቁኝ ማለት ዛሬ ከተጣቡን የድህነት፣ የፖለቲካ ጭቆና እና ማኅበራዊ ቀውስ የማያስጥለን እና ነፃ የማያወጣን እሰከ ሆነ ድረስ ኩራታችን ከድንፋታ አያልፍም። አገሬን እወዳልሁ፣ በኢትዮጵያዊነቴ እኮራለሁ እያሉ ባንዲራ ለብሶ ማቅራራት በተግባር ካልታገዘ የውሸት ወይም ባዶ ኩራት (false pride) ነው የሚሆነው። እውነተኛ ኩራት የሚመነጨው ከራስ ነው፤ የራስን ማንነትን በማወቅና በመቀበል ላይ የሚመሰረት ነው። ማንነትን አምኖ መቀበል አቅማችንንም አብረን እንድፈትሽ ይረዳል። የዛሬ ባዶነታችንን በአያቶቻችን የታሪክ ገድል እንድንሞላ ወደሚያስገድድ የሞራል ክስረት ውስጥም እንዳንገባ ይረዳናል። የዛሬ ውርደታችንን በአድዋ ድል እና በሌሎች የአያቶቻችን ተጋድሎዎች በተገኙ ስኬቶችን ልንሸፍነው ከመጣር ይልቅ ታሪክ እንድንሰራ ብርታት ይሆነናል።

የፍርሃት ባህልን (culture of fear) እያነገሰ ያለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ፤ አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት ወደ ኋላ

(ክፍል አንድ)

ያሬድ ኃይለማርያም

ከቤልጅየም፤ ብራስልስ  

ኅዳር 27/2006 ዓ.ም.

ፍርሃት የግለሰቦች ባህሪ መገለጫ ስለሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ የሚኖረውን ገጽታ እና ትርጓሜ ማስቀመጥ ያስቸግራል። አንዱ ሰው የሚፈራውን ነገር ሌላው ላይፈራው ስለሚችል ፍርሃት እንደ የግለሰቡ ባህሪ እና ጥንካሬ ወይም ስነ-ልቦናዊ ሁኔታ የተለያየ መልክ ይኖረዋል። ይሁንና በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ የሚገኙ ሰዎች የሚጋሩት ባህልና ስነ-ልቦናዊ ሁኔታ እንደመኖሩ ሁሉ የሚጋሩትም ፍርሃት ወይም ደስታ ወይም ሃዘን ወይም ድፍረት ወይም ሌሎች ባህሪያት ይኖራል። በዚህም ምክንያት አንዳንድ ሰዋዊ ባህሪያት ለአንድ ማህበረሰብ ወይም ለበርካታ ሰዎች የወል መገለጫ ተደርጎ ሲገለጽ ይስተዋላል። ‘የዚህ አካባቢ ሰዎች ጀግኖች ወይም ጸብ ፈሪዎች ወይም እሩህ ሩህዎች ወይም ጨካኞች ወይም ቂመኞች ወይም ገራገሮች ወይም ተንኮለኖች ወይም ጎጠኞች ወይም ሌላ ባህሪ ያላቸው ናቸው’ የሚል አገላለጽ የተለመደ ነው። ይህ አይነቱ አነጋገር ሳይንሳዊ መሰረት ያለው ባይሆንም በአካባቢው ላይ ጎላ ብለው በሚታዩ ሰዎች ላይ ተደጋግሞና ተዘውትረው የሚታዩ ተመሳሳይ ባህሪያት የአካባቢው ሰው ሁሉ መገለጫ ተደርገው ስለሚወሰዱ ድምዳሜው ለስህተት የተጋለጠ ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ ለመግለጽ እወዳለሁ። ከዚህ መንደርደሪያ በመነሳት በዚህ ጥልቅ ጥናት ባላካሄድኩበት ነገር ግን ደጋግሜ ሳብሰለስለው በቆየሁት የፍርሃት ባህል እና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ድባብ ዙሪያ ያለኝን ምልከታ ለአንባቢያን ለማካፈልና በጉዳዩም ላይ ለመወያየት ወሰንኩ።

በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ የፍርሃት ድባብ እንዲሰፍን እና ከዚያም አልፎ ባህል እንዲሆን ምክንያት ከሆኑት በርካታ ነገሮች መካከል የተወሰኑትን ልጥቀስና በእኛ ማኅበረሰብ ውስጥ ያላቸውን ገጽታ በመጠኑ ለመዳሰስ እሞክራለሁ። በስነ-ልቦና ጠበብቶች ከሚጠቀሱት ዋና ዋና የፍርሃት ምንጮች መካከል፤ ነፃነትን ማጣት፣ ነገ የሚሆነውን ማወቅ አለመቻል፣ የህሊና እና የአካል ቁስልን ባስከተሉ ትላንቶች ውስጥ ማለፍ፣ የማያቋርጥ ብስጭት ወይም ንዴት፣ ድህነት በሚያስከትለው ስቃይ ውስጥ መማቀቅ፣ አጋር እና አለኝታ ማጣት፣ በሌሎች ክፉኛ መነቀፍ፣ መንጓጠጥ፣ መጠላት እና መገለል፣ በሚኖሩበት ማኅበረሰብ ዘንድ ተቀባይነትን ማጣት፣ የሞት አደጋን ማሰብ፣ ሽንፈት ወይም ስኬት አልባ ሆኖ መቆየት፣ እና ሌሎችም ይገኙበታል። ከእነኝህ መክንያቶች ውስጥ የአንዱ መከሰት አንድን ሰው ወደ ፍርሃት ውስጥ ሊከት እንደሚችል ጥናቶች ይጠቁማሉ። እነኝህ ምክንያቶች ተደራርበውና በአንድ ጊዜ በአንድ ሰው ወይም በአንድ ማኅበረሰብ አባላት ላይ ሲከሰቱና ዕልባት ሳያገኙ እረዘም ላለ ጊዜ ሲቆዩ ደግሞ አደጋቸው የከፋ ነው የሚሆነው። ከዚህም በመነሳት ወደ እኛ ማህበረሰ ስንመለስ በግላችንም ሆነ በጋራ ህይወታችን ከላይ ከተጠቀሱት የፍርሃት መንሰዔዎች መካከል ስንቶቹ በህይወታችን ውስጥ ተከስተዋል፣ ስንቶቹን በአሸናፊነት አለፍናቸዋል፣ ስንቶቹስ ዛሬም ድረስ አብረውን ይኖራሉ፤ የሚሊቱን ጥያቄዎች እያንዳንዱ ሰው እራሱን እንዲጠይቅ እየተውኩ በወል በምንጋራቸው ጥቂት የፍርሃት መንሰዔዎች ላይ ላተኩር።

Wednesday, December 18, 2013

ከወያኔ ክፋትና እብሪት እንጂ ፍትህ አይጠበቅም!!!

 ወያኔ ባለፉት ሃያ ሁለት አመታት የአገራችንን የፍትህ ተቋሞች አንዴ አንደ ቂም መበቀያ ሌላ ግዜ ደግሞ እንደ ማጥቂያ መሳሪያ እየተጠቀመባቸዉ የፖለቲካ ተቀናቃኞቹንና ጥርስ የነከሰባቸዉን የህብረተሰብ አባላት እያሰረ፤ እያሳደደና እየገደለ ከርሞ ዛሬ ላይ ደርሷል። በተለይ ከግንቦት 1997ቱ ምርጫ በኋላ ወያኔ ብዕርና ወረቀት ይዘዉ በሃሳብና በአመክኖ የታገሉትን ሰላማዊ ዜጎች “ሽብርተኞች”፤ ድምጻችን ይሰማ ብለዉ የመብትና የነጻነት ጥያቄ አንግበዉ በሰላማዊ መንገድ የታገሉትን ኢትዮጵያዉያን የእስልምና እምነት ተከታዮች ደግሞ “አክራሪዎች” እያለ ፍርድ ቤት በማቅረብ በፍትህ ተቋሞች በኩል የፖለቲካ ዉሳኔ በማሳለፍ ሠላማዊ ዜጎችን ለረጂም ግዜ እስርና እንግልት ዳርጓል።

ወያኔ ለኢትዮጵያና ለዜጎቿ ደንታ የሌለዉ እና ከስህተቱ የማይማር የግብዞችና የዘረኞች ስብስብ ስለሆነ አሁንም የአገሪቱን የፍትህ ተቋሞች እንደ ማጥቂያ መሳሪያ እየተጠቀመ የኢትዮጵያን ህዝብ በፍርሃት ጨለማ ዉስጥ ሸብቦ እየገዛ ለመኖር የቆረጠ ይመስላል። ባለፈዉ ሳምንት አጋማሽ ላይ የወያኔ አገዛዝ ከአንድ አመት ተኩል በላይ እስር ቤት ዉስጥ አጉሮ ያቆያቸዉን የድምጻችን ይሰማ መሪዎች ከፊሎቹን በነፃ ተለቅቀዋል የሚል ከፊሎቹን ደግሞ ተከላከሉ የሚል ትርጉም የለሽ ብይን ሰጥቷል። በህወሀት ታጋዮች የተሞላዉ ፍርደ ገምድሉ የወያኔ ፍርድ ቤት እንኳን ተከሳሾቹ በተከሰሱበት ሽብር የመፈጸም ወንጀል ምንም አይነት ማስረጃ አልተገኘባቸዉም ሲል አገዛዙ ግን የፖለቲካ ክንዱን በመጠቀም ማስረጃ ያልተገኘባቸዉን ሠላማዊ ዜጎች የተከሰሱበትን መሰረተ ቢስ ክስ ተከላከሉ የሚል የፖለቲካ ዉሳኔ ሰጥቷል።

የወያኔ አገዛዝ የሙስሊሙን ህብረተሰብ የመፍትሄ አፈላላጊ ቡድን መሪዎች ፍርድ ቤት ያቀረባቸዉ ለምዕራባዉያን ለጋሾቹና ለአለም አቀፍ አበዳሪ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍትህ ያለ ለማስመሰል ነዉ እንጂ ወያኔ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን የፈረደባቸዉ ያሰራቸዉ ቀን ነዉ። የወያኔ የፍትህ ታሪክ በግልጽ እንደሚያሳየን ወያኔ ግለሰቦችን የሚያስረዉ ለክስ የሚያበቃ ማስረጃ አግኝቶባቸዉ አይደለም፤ ይልቁንም ወያኔ ማስረጃዎችን እየፈበረከ ለፍረድ ቤቶች የሚያቀርበዉ ግለሰቦችን ካሰረና ሰብዓዊ መብታቸዉን ከገፈፈ በኋላ ነዉ። ለምሳሌ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን አስሮ ብዙም ሳይቆይ የእነዚህን ሰላማዊ ዜጎች ተክለ ሰዉነት ጥላሸት የቀባና ግለሰቦቹን ያለ ማስረጃ ወንጀለኛ አድርጎ የፈረጀዉን “ጂሐዳዊ ሀረካት” የሚል የፈጠራ ድራማ ሰርቶ ለህዝብ አቅርቧል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሽብር በመፈጸም ወንጀል ተጠርጥረዉ የቀረቡለትን ግለሰቦች በተከሰሱበት ወንጀል ማስረጃ አላገኘሁባቸዉም ካለ በኋላ ሁሉንም በነጻ አለማሰናበቱ የሚያሳየን የወያኔ ፍርድ ቤቶች ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነጻ አለመሆናቸዉን ብቻ ሳይሆን፤ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍርድ ቤቶች የገዢዉ ፓርቲ የማጥቂያ መሳሪያዎች መሆናቸዉን ጭምር ነዉ። የወያኔን አገዛዝ ከሌሎች አምባገነኖች ለይቶ አደገኛ የሚያደርገዉና በምዕራባዉያን መንግስታትና በቀላጤዎቻቸዉ እንዲወደስ ያደረገዉም ይሄዉ አገዛዙ የሚቃወሙትን ኃይሎች የሚያጠፋቸዉ እንደሌሎቹ አምባገነኖች በግልጽ ሳይሆን በህግ ሽፋን ዉስጥ በስዉር መሆኑ ነዉ።

የወያኔዉ ፍርድ ቤት በተመሳሳይ ወንጀል ተከስሰዉ የቀረቡለትን ነገር ግን ምንም መረጃ ያላገኘባቸዉን የድምጻችን ይሰማ መሪዎች ገሚሶቹን በነፃ ለቅቆ የተቀሩትን ጥፋተኛ አለመሆናችሁን አረጋግጡ ብሎ መወሰኑ የወያኔን ሁለት እኩይ አላማዎች ያሳየናል። የመጀመሪያዉ የወያኔ አላማ በአላማቸዉ ጸንተዉ የቆሙትን የድምጻችን ይሰማ መሪዎች መከፋፈል ሲሆን፤ ሁለተኛ አላማዉ ደግሞ የኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች የቀረቡላቸዉን የክስ መዝገቦች በሚገባ አጣርተዉ ዉሳኔ የሚሰጡ መሆናቸዉን ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ ለማሳየት ነዉ።

የኢትዮጵያ ህዝብ ግን እንደዚህ አይነቶቹን የወያኔ እኩይ ተግባሮች ካወቀ ዉሎ አድሯል፤ ስለሆነም ከወያኔ ፍትህ ጠብቆ አያዉቅም፤ ወያኔ የክፋትና የበቀል ምንጭ ነዉና ለደፊትም አይጠብቅም። የድምጻችን ይሰማ መሪዎችም ሆኑ ከእነሱ በፊት በግፍ ታስረዉ መከራቸዉን የሚያዩት የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፤ ጋዜጠኞችና የሲቪክ ማህበራት መሪዎች የታሰሩት ለቆሙለት የፍትህ፤ የነጻነትና የእኩልነት አላማ እንደ አለት ጸንተዉ በመቆማቸዉ ነዉ። እነዚህ ጀግኖች የታሰሩለት አላማ የሁላችንም አላማ ነዉና ፍትህ፤ እኩልነትና ነጻነት የጠማን ኢትዮጵያዉያን ክንዳችንን አስተባብረን የችግሮቻችን ሁሉ ምንጭ በሆነዉ በወያኔ ስርዐት ላይ ክንዳችንን በጋራ እናንሳ!

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

ህወሓት/ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ብሔራዊ የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት የማስጠበቅ ጥያቄ ላይ ሊታመን አይችልም!

ታህሳስ 8፣ 2006 (ዲሰምበር 17፣ 2013)  

ያለፉት አራት አሥርት ዓመታት የህወሓት/ኢህአዴግ ታሪክ ያስገነዘበን ነገር ቢኖር ገና ከጅምሩ በጠባብ ብሔረተኝነት አጀንዳ የራሱን ጥቅምና ሥልጣን የማስከበርና የማቆየት ዓላማ እንዳለው ብቻ ነው። ይህንንም ተልዕኮውን እውን ለማድረግ የተከተላቸው ፖሊሲዎችና አካሄዶች በተለያዩ ጊዚያት የኢትዮጵያን ግዛታዊ አንድነትና ሉዓላዊነት የሚጻረሩ ሆነው እንደቆዩ እንረዳለን።    
መለስ ዜናዊና የአገዛዙ አባላት ከግልብ የፖለቲካ አመለካከት፤እንዲሁም ከገደብ የለሽ የሥልጣንና ራስ ወዳድነት የተነሳ፤ ዕኩይ ዓላማቸውን በሥራ ላይ ለማዋል ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ተቀናቃኞች ጋር ባደረጉት ድርድሮች የራሳቸውን ማንነት ከመካድ እስከ አገር መሸጥ የሚደርስ ሸፍጥ ማካሄዳችው የአደባባይ ምስጢር ነው።
  
በተለይም በዚህ ወቅት በዋንኛነት ሊጠቀስ የሚገባው ህወሓት/ኢህአዴግ ገና ቀደም ብሎ ከትጥቅ ትግል አጋሩ ከሻዕቢያና፤ ከፍተኛ ድጋፍና አሰተዋፅዖ ሲያደርግለት ከነበረው ከሱዳን መንግሥት ጋር በምስጢር ያደረጉት ስምምነት ነው።የመለስና የሕወሃት/ኢህአዴግ አመራር አባላት በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት መጠበቅ ላይ ግድ ያለመኖርና በአገሪቱ ብሔራዊ ሉዓላዊነት ላይም ባላቸው ሥር የሰደደ ጥላቻ የተነሳ፤ ገና ከጅምሩ ከማንም የበለጠ በዋነኛነት የኤርትራ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ተቆርቋሪና አራማጅ ብቻ ሳይሆን የሱዳን የድንበር መሬት ይገባኛል ጥያቄም ደጋፊና አቀንቃኝ ሆነው መቆየታቸው የሚታወስ ነው። 

ሙሉን መግለጫ ከታች የቀረበውን ሊንክ በመክፈት ያንብቡ፤ 

Tuesday, December 17, 2013

የማንዴላ መልዕክት ለኢትዮጵያውያን ወጣቶች፣ “በፍጹም እጅ እንዳትሰጡ !…”

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም | December 17th, 2013


ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

የአፍሪካው ብልህ አንበሳ እና እረፍትየለሾቹ የኢትዮጵያ አቦ ሸማኔዎች – በፍጹም እጅ እንዳትሰጡ፣ ፍቅር የነገሰበትን የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ለመገንባት ጥረታችሁን ቀጥሉ!

እ.ኤ.አ ዴሴምበር 15/2013፣ ለእኔ የዓመቱ ታላቁ የኃዘን ዕለት ነው፡፡ ኔልሰን ሮሺስላሽላ ማንዴላ በደቡብ አፍሪካ በምስራቅ ኬፕ ግዛት በምትገኘው ኩኑ በምትባል ትንሽ የገጠር የትውልድ መንደራቸው በርካታ የአገር መሪዎች በተገኙበት ግብዓተ መሬታቸው ተፈጽሟል፡፡ ማንዴላ በህጻንነት የህይወት ዘመናቸው በዚያች ትንሽ መንደር የከብት እረኛ በመሆን በርካታ የደስታ ቀናትን አሳልፈዋል፡፡ ከረዥም ዓመታት የነጻነት ትግል ጉዞ፣ ከበርካታ ዓመታት የእስር እና ረዥም ጊዚያት የህይወት ውጣ ውረድ ጉዞ በኋላ ለዘላለማዊ ማሸለብ አያት ቅድመ አያቶቻቸውን ለመቀላቀል እንደገና ወደ ትውልድ መንደራቸው ወደ ኩኑ ተመልሰዋል፡፡ ወጣቱ የኩኑ መንደር የከብት እረኛ የነበሩት ማንዴላ ከዚያ ወዲህ ደግሞ የተደነቁ፣ የተወደዱ እና የተከበሩ የህዝቦቻቸው እረኛ በመሆን ወደ ዘላለማዊ ማረፊያቸው ወደ ትውልድ መንደራቸው ወደ ኩኑ ተመልሰዋል፡፡ ደህና ይሁኑ እያልኩ እሰናበትዎታለሁ፡፡ ነብስዎ በሰላም ለዘላለም እረፍት ታግኝ፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ እ.ኤ.አ ዴሴምበር 15/2013፣ ለእኔ የዓመቱ ታላቁ የደስታ ዕለት ነው፡፡ ከዋሽንግተን ዲሲ ወጣ በማለት በአንድ ከተማ በሚገኝ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመገኘት ሰማያዊ ፓርቲን እና ወጣቱን የፓርቲውን ሊቀመንበር ይልቃል ጌትነት እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የክብር ሰላምታዬን ሳቀርብ ነበር፡፡ ጭቆናን እና የሰብአዊ መብቶች ደፍጣጮችን በሰላማዊ ትግል ለማንበርከክ ለሚታገሉት የዴሞክራሲያዊ ለውጥ ፈላጊ እና ለመንፈሰ ጠንካሮቹ የኢትዮጵያ ወጣቶች ክብር ለመስጠት፣ የማያቋርጥ እና ጽኑ ድጋፍ በቀጣይነት እንደምሰጥ ያለኝን ስሜት ለመግለጽ ነው እዚህ የተገኘሁት፡፡ በዝዚሕች ቀን የሰማያዊ ፓርቲ ምስከር አንደሆን ተጠረቼ ነው የመጣሁት::

በዚህ ዓመት የመጀመሪያ በነበረችው ትችቴ እ.ኤ.አ 2013 “የኢትዮጵያ የአቦ ሸማኔዎች (የወጣቱ ትውልድ) ዓመት” ይሆናል ብዬ ተምኘ ነበር:: ለዚህም ዕውን መሆን የኢትዮጵያን ወጣቶች በሙሉ ለመድረስ፣ ለማስተማር እና ለማሳወቅ ቃል ገብቼ ነበር። ቃሌን ጠብቄአለሁ:: እንደጠበቅሁም እቀጥላለሁ፡፡

በዛሬው ዕለት ከይልቃል ጋር እዚህ በመካከላችሁ በመገኘቴ ልዩ ክብር እና ሞገስ የተሰማኝ መሆኑን ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡ የዛሬዋን ዕለት ለነጻነት የሚደረገውን ተጋድሎ፣ ከጎሳ የዘረኝነት አለመቻቻል እና ከአንባገነንነት እንዲሁም ከጭቆና ነጻ መሆን፣ ለማለም ነጻ መሆን፣ ለማሰብ ነጻ መሆን፣ ለመናገር ነጻ መሆን፣ ለመጻፍ እና ለመስማት ነጻ መሆን፣ ለመፍጠር ነጻ መሆን፣ ለመስራት ነጻ መሆን እና ነጻ ለመሆን ነጻ መሆን በማለት ራዕያቸውን ሰንቀው የሚታገሉትን የኢትዮጵያ ወጣቶችን ቃል አቀባይ እንዳገኘሁ ያህል ይሰማኛል፡፡

የኢትዮጵያ (የአፍሪካ ማለትም ይቻላል) ዕጣ ፈንታ በሁለት ትውልዶች ትከሻ ላይ የተንጠለጠለ ነው፡፡ ጆርጅ አይቴይ በግልጽ እንዳስቀመጡት የአፍሪካ “አቦሸማኔ (ወጣቶች)ትውልድ” “አዲሱን እና ጠንካራ፣ የማይበገር፣ ብሩህ አዕምሮ ያለው እና ነገሮችን በውል የሚያጤን የአፍሪካ ፕሮፌሽናሎችን እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሩቃንን የሚያካትተው ቁጡ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ ይህ የህብረተሰብ ክፍል ግልጸኝነት፣ ተጠያቂነት፣ ሰብአዊ መብት እና መልካም አስተዳደርን በሚገባ የተረዳ እና ለተግባራዊነታቸውም በጽናት የቆመ ኃይል ነው፡፡“ በሌላ በኩል ደግሞ የአፍሪካ የጉማሬ ትውልድ (የኔ ትውልድ ማለት ነው) ጨለምተኝነት የነገሰበት፣ ምክንያታዊነት የጎደለው እና በቅኝ ግዛት የትምህርት ፖሊሲ ዘይቤ የታጠረ አመለካከት ያለው የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ ይህ የህብረተሰብ ክፍል ብሩህ ራዕይ የለውም፣ ሁሉንም የአፍሪካ ችግሮች መንግስታት መፍታት ይኖርባቸዋል በሚል እምነት ለእራሱ ተደላድሎ እና በምቾት መኖርን የሚመርጥ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ መንግስት ሊያገኝ የሚገባው ብዙ ኃይል እና በርካታ የውጭ እርዳታ ነው የሚል አስተሳሰብ ያለው የህብረተስብ ክፍል ነው፡፡”

የዛሬዋ ዕለት ታላቅ ቀን ናት፣ ምክንያቱም እኔ የጉማሬው (የቀድሞ ትውልድ) አባል ብሆንም ከኢትዮጵያ የአቦ ሸማኔው ትውልድ መሪ ከይልቃል ጋር በጋራ የቆምኩባት ዕለት ናትና፡፡

የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል የተመሰረተበትን አንደኛ አመት አስመልክቶ የተሰጠ ድርጅታዊ መግለጫ!!!

ቀን ታህሳስ 7 2006

ታህሳስ 7 2006 ዓም የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ከተመሰረተ አንድ አመት ሞላው። አንድ አመት በጭንቅና በአሳር ለተያዘች የዛሬይቱ ኢትዮጵያና ህዝቧ እጅግ ረጅም ግዜ እንደሆነ ህዝባዊ ሃይሉ በሚገባ ይገነዘባል። ባላፈው አንድ አመት ውስጥ የኢትዮጵያን ህዝብ የመከራ፣ የአሳርና የውርደት ህይወት ይበልጥ እየሰፋ፣ የሚፈጸምበት ግፍ ይበልጥ እየገዘፈ መሄዱን አይተነዋል። በሃገርና በህዝብ ላይ እየወረደ ያለውን ወያኔ ወለድ የስቃይና የፍዳ ናዳ በቅጡ ላጤነው ሃገሪቱና ህዝቧ የአዳዲስ የስቆቃና የመከራ አይነቶች መፈተኛ ቤተ ሙከራዎች እየተደረጉ ለመሆኑ ጥርጥር አይኖረውም። ለሚራበው፣ ለሚረገጠው፣ በግፍ ለታጎረው፣ በኑሮ ውድነት ለሚጠበሰው፣ ለተሰደደው ለተፈናቀለው ኢትዮጵያዊ እንድ አመት በሲኦል የቀናትና የወራት መቁጠሪያ እንደሚለካ ዘመን እጅግ የረዘመ የስቃይ ግዜ ነው።

የዋልድባ መነኩሳት ገዳማችን አትድፈሩ አታፍረሱ በማለታቸው እየተገረፉ ለዘመናት ፈጣሪያቸውን ከሚማጸኑበት ለሃገርና ለህዝብ ምልጃ ከቆሙበት ገዳም በዘር መመዘኛ እየተለዩ እንደቆ ሻሻ ተጠርገው የተባረሩበት፣ እምነታችን አትንኩ ያሉ የእስልምና እምነት ተከታዮችና መሪዎቻቸው በሃሰት ክስ ተመስርቶባቸው ወህኒ መውረዳቸው አንሶ ወንድሞቻችን ይፈቱ በማለት ሰላማዊ ጥያቄ ያቀረቡ ወገኖቻቸን በወያኔ ነፍሰ ገዳዮች በአረመኔያዊ ጭካኔ የተጨፈጨፉት በዚሁ አመት ነው። ወያኔ በህዝብ መሃከል በዘራው የዘር መርዝ የተነሳ በሽዎች የሚቆጠሩ አማሮች ከጉራ ፈርዳና ከቤንሻንጉል፣ ኦሮሞዎች ለዘመናት ከኖሩበት ምስራቅ ሃረርጌ አካባቢ እንዲፈናቀሉና በገዛ ሃገራቸው መድረሻ ቢሶች እንዲሆኑ የተደረገው በዚህ አንድ አመት ውስጥ ነው። ጋምቤላዎች ሙርሲዎች አፋሮችና ሌሎችም ብሄረሰቦችና ማህበረሰቦች የተጨፈጨፉበት፣ በልማት ስም ለመጡ የውጭ ወራሪዎችና ወያኔ ለፈጠራቸው ቱጃሮች ቦታ እንዲለቁ ተደርጎ ቀደምቶቻቸው ለዘመናት ከኖሩባቸው ቀየዎች እንዲነቀሉ ተደርገው እንደ አልባሌ ነገር የትም እንዲበተኑ የማድረጉ ሂደት ከመቼውም በላይ ተጠናክሮ የቀጠለው በዚሁ አመት ነው። በዚሁ አንድ አመት በወያኔ የሃገሪቱ ገዥዎች በህዝብ ላይ የተፈጸመው ጭካኔና ወንጀል ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም።

ይህ ወያኔ ሰራሽ ሃገር በቀል የውርደትና የስቃይ ህይወት አልበቃ ብሎ ወያኔ ከሳውዲ የጨለማ ዘመን ገዥዎች ጋር በመተባበር ወንድሞቻችን በሳውዲ አውራ ጎዳናዎች ላይ እንዲታረዱ እህቶቻችን በቡድን በተደራጁ የሳውዲ ጎረምሳዎች እንዲደፈሩ ሁኔታዎችን አመቻችቶ ለኢትዮጵያውያን ያለውን እጅግ የከረረ ጥላቻ በአደባባይ ያሳየበት አመት ነው። እንዲህ አይነቱ የጅምላ ግፍና ውርደት ከመከሰቱ በፊት ህዝባዊ ሃይሉ በአረብ ሃገር በባርነትና በስደት የሚገኙ እህትቶቻችንን ወንድሞችችን ስቃይ ስቃዩ አድርጎ በመውሰድ “ላንቺ ነው” በሚለው ድርጅታዊ መዝሙሩ “በባለጌ አረቦች መዳፍ ውድ ክብራቸው ለጎደፈው እህቶቻችን፣ በአረቦች የባርነት ቀንበር ጀርባቸው ለጎበጠው ወገኖቻችን እንደርስላችኋለን፣ የተሰባሰብነው ደማችን የሚፈሰው የመከራ ቀናችሁን ለማሳጠር ነው” የሚል ቃል ኪዳኑ ሰጥቶ ነበር። የድርጅታችንን ምስረታ አንደኛ አመት ስናከብር ልባችንን ደስታ ሳይሆን ሃዘን እንዲሞላ የሚያደርገው ይህ ቃል ኪዳናችን ለማክበር የጀመርነው ጉዞ ከድርጅት ምስረታና ከድርጅታዊ ዝግጅት አልፎ በኢትዮጵያ ህዝብ ጥላቻና ንቀት የተነፋውን የወያኔን እብሪት በማስተንፈስ የወሰዳቸው ተጨባጭ የአለኝታነት እርምጃዎች ባለመኖራቸው ነው።

ምንም እንኳን ግንቦት7 ህዝባዊ ሃይል እራሱን እንደ ድርጅት አቁሞ ኢትዮጵያውያንን አሰባስቦ መራራው ትግል የሚጠይቀውን የፖለቲካ የወታደራዊ ስልጠናና ትጥቅ አስታጥቆ በወያኔ ላይ ለመዝመት የጀመረውን ጉዞ የሚያስቆመው ምድራዊ ሃይል እንደሌለ ብናውቅም የህዝብ ስቃይ ለግዜው መቀጠሉ የህባዊ ሃይሉን አባላት ማሰቃየቱ አልቀረም። በወያኔ ግፈኛ አገዛዝ የተንገፈገፈው ወገናችን ህዝባዊ ሃይሉ የወያኔን አገዛዝ እድሜ የሚያሳጥሩ ፈጣን እርምጃዎችን እንዲወስድ በከፍተኛ ጉጉት እየተጠባበቀ እንደሆነ እናውቃለን። ህዝባዊ ሃይሉን ለመቀላቀል በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ የሃገሪቱ ዜጎች በተጠንቀቅ እንደቆሙ እናውቃለን። እነዚህ ዜጎች ከሁሉም የእምነት የቋንቋ የጾታ የእድሜ የኑሮና የማህበረሰብ ስብጥር የሚያካተቱ እንደሆኑ እናውቃለን። በሃገሪቱ ታሪክ ተሰምቶና ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የወታደር ልብሱን እየጣፈ እንዲለብስ፣ የወታደር ጫማውን መቀየሪያ አጥቶ ሸበጥ እንዲያደርግ የተገደደውን፣ የወያኔ ጀነራሎች በስልጣንና በዘረፋ ሲያብጡ በድህነት እንዲሟሽሽ የተፈረደበት የሃገሪቱ ሰራዊት በዘር በእምነት ሳይለያይ ከህዝባዊ ሃይሉ ጎን ለመቆም አሰፍስፎ የቆመ እንደሆነ እናውቃለን። ይህ ሃገራዊ እውነታ ለህዝብ የገባነውን ቃልኪዳን የለምንም ጥርጣሬ ማስከበር እንደምንችል በሙሉ ድፍረት እንድናውጅ የሚያስችለን ሃቅ ነው።

Monday, December 16, 2013

የሶማሌ ክልል የወያኔ ጦር መኮንኖች ገንዘብና ንብረት እንዲያካብቱ የሚላኩበት ቦታ መሆኑ ተሰማ

ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ባለዉለታዎቼ ናቸዉ የሚላቸዉን ትግርኛ ተናጋሪ የሆኑ ወታደራዊ መኮንኖች ወደ ሶማሌ ክልል በመላክ ከፍተኛ ህብትና ንብረት አጋብሰዎ እንዲመለሱ ሆን ብሎ መንገድ አንደሚያመቻችላቸዉ አዲስ አበባና ጅጅጋ ዉስጥ የሚገኙ ለአገዛዙ ቅርበት ያላቸዉ ዉስጥ አዋቂ ምንጮች ሀለጹ። በሙሰኝንት የተጨማለቀዉ የወያኔ አገዛዝ ከፍተኛ የመከላከያ አዛዦቹ ሶማሊ ክልል ዉስጥ እንዲመደቡ በማድረግ ከክልሉ መንግስት ጋር በመተባበር ከፍተኛ ሀብት አጋብሰው በቋሚነት ወደሚኖሩበት ቦታ እንደሚመልሳቸዉ ለማወቅ ተችሏል።ነበአሁኑ ጊዜ ተቀማጭነታቸው ጅጅጋ የሆኑት እና በክልሉ ቁጥር አንድ ሀብታም የሚባሉት /ወ/ት ሀዋ የሌተናንት ጄኔራል ዮሀንስ ገ/መስቀል ሁለተኛ ሚስትና የልጅ እናት ሲሆኑ፣ ግለሰቧ ከተራ ጫት ነጋዴነት በአንድ ጊዜ በብዙ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ሀብት ለማጋበስ የቻሉት በፍቅር ጓደናቸው አማካኝነት መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ሰራተኞች ለኢሳት ገልጸዋል።

ጄኔራል ዮሐንስ ከወ/ት ሀዋ ጋር የተዋወቁት በኮሎኔልነት ማእረግ የምእራብ ጎዴ አዛዥ በነበሩበት ወቅት ሲሆን፣ በወቅቱ ክልሉ ያወጣውን የምእራብ ጎዴን የካናል ጠረጋ የመከላከያ ሰራዊት እንዲያሸንፍ በማስደረግና የሰራዊቱ አዛዥም ስራውን ወ/ት ሀዋ ኩባንያ አቋቁመው በሰብ ኮንትራትነት እንዲሰጣቸው በማድረግ በአንድ ጊዜ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ እንዲያገኙ አድርገዋቸዋል። በጄኔራል ዮሀንስና በወ/ት ሀዋ መካከል ያለው የፍቅር ግንኙነት እየደራ ሲሄድ፣ ወ/ት ሀዋ ከፍተኛ ሀይል እየተሰማቸው ከታክስ ጋር በተያያዘ ጥያቄ የሚያቀርቡባቸውን የክልል ሰራተኞችን ሳይቀር የመከላከያን መኪኖች ይዞ በመሄድ በማስፈራራት ከግብር ራሳቸውን ነጻ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ምንጮች ይናገራሉ። ወ/ት ሀዋ ከፍቅር ጓደኛቸው ከጄ/ል ዮሐንስ ጋር በመሆን ባቋቋሙት ኩባንያ በጅጅጋ ሁለት ታላላቅ ፎቆችን የገነቡ ሲሆን፣ ከዚህም በተጨማሪ ያለምንም ጫረታ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ሀብት የፈሰሰባቸውን ፕሮጀክቶች እንዲሰሩ ተፈቅዶላቸዋል።

ከፕሮጅቶች መካከል የቀብሪ ደሀር የውሀ አቅርቦት፣ የደገሀቡር የውሀ አቅርቦት፣ ጅጅጋ መምህራን ማሰልጠኛ ማስፋፊያ፣ የክልል የትምህርት ቢሮ ፕሮጀክት፣ ጅጅጋ አየር ማረፊያ አካባቢ የሚገኘው ዘመናዊ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ግንባታና ሌሎችንም ውድ ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። ምንም እንኳ /ወ/ት ሀዋ ግንባር ቀደም ሆነው ሀብቱን ቢቆጣጠሩትም ከጀርባ ሆነው የክልሉን ፕሮጀክቶች የሚያሰሩት ጄኔራል ዮሐንስ መሆናቸውን ምንጮች ይናገራሉ።

በሌላ በኩል ደግሞ በክልሉ ውስጥ አሁን በመከላከያ አዛዥነት የሚንቀሳቀሱ አንድ የህወሀት የመከላከያ ኮሎኔል የክልሉ ፕሬዚዳንት የትውልድ ቦታ ላይ አንድ የውሀ ፕሮጀክት እንዲሰሩ የ120 ሚሊዮን ብር ተፈራርመው ስራውን ከጀመሩ በሁዋላና አስፈላጊው ክፍያ ከተፈጸመ በሁዋላ ፐሮጀክቱ አለመሳካቱን ምንጮች ገልጸዋል። ባለፈው ወር ለእኝሁ ኮሎኔል 22 ሚሊዮን ብር ከክልል መስተዳደር ወጪ ተደርጎ እንደተከፈላቸውም ምንጮች ገልጸዋል። ሰሞኑን በተከበረው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ዝግጀቶችን ከማዘጋጀት ጀምሮ የሽያጭ እቃዎችን እስከማቅርብ የሚደረሱ ስራዎችን ከህወሀት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች በኮንትራት ወስደው ከፍተኛ ትርፍ እንዳገኙበት እነዚሁ የመስተዳድሩ የአስተዳደር ሰራተኞች ገልጸዋል።

የወያኔ 40 በ 60 እና 10 በ 90 የቤት ስራ ዕቅድ ገንዝብ መዝረፊያ መንገድ መሆኑ ተረጋገጠ

የወያኔ አገዛዝ 40 በ 60 እና 10 በ 90 ብሎ የጀመረዉ የቤት ልማት ዕቅዱ በድምሩ ከአንድ ሚሊዮን በላይ አገር ዉስጥና ዉጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንን መዝግቦ ገንዘበቸዉን ከተቀበለ በኋላ ቃል የገባዉን ልማት ለማካሄድ አለመቻሉን ከአገር ቤት የሚደርሱን ዜናዎች ጠቆሙ። በውጭ አገር ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና የገንዘብ አቅሙ ላላቸው የአገር ዉስጥ ዜጎች የ40 በ60 አዲስ አበባ በአነስተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ዜጎች ደግሞ የ10 በዘጠናና የ20 በ80 የቤት ስራ ጅምሮችን ያቀፈዉ የወያኔ የቤት ልማት ዕቅድ በችግር ላይ ችግር እያጋጠመዉ ምንም ያክል ወደ ፊት መራመድ አለመቻሉ በስፋት እየተነገረ ነዉ። በዚህ የቤት ልማት ዕቅድ አገር ዉስጥ በ10/90 850 ሺ በ 20/80 ደግሞ 350 ሺ የአዲስ አበባ ነዋሪ ተመዝግቦ እድሉን በመጠባበቅ ላይ ሲሆን ከ12 ሺ በላይ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያም በ40 በ60 በሚባለው ውስጥ ታቅፈዉ እድላቸዉን እየተጠባበቁ ቢሆንም በመርሀግብሩ ዝግጅት የተሳተፉ የውስጥ ምንጮች እንደገለጹት የወያኔ አገዛዝ ይህን እቅድ ለማሳካት ከፍተኛ የሆነ ፈተና ገጥሞታል ።

በባዶ ሜዳ ላይ ዕቅድ ማዉጣት የለመደዉ የወያኔ አገዛዝ የቤት ልማት እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ ወደ 2 ሚሊዮን የሚደርሱ ቤቶች መገንባት የሚኖርበት ሲሆን ይህን ያክል ብዛት ያለዉ ቤት ለመገንባት ደግሞ ቢያንስ 30 ሺ ሄክታር ስፋት ያለው ቦታ ያስፈልጋል። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸዉ ወገኖች አስረግጠዉ እንደሚናገሩት ደግሞ አዲስ አበባ ዉስጥ ይህንን ያክል ሰፊ መሬት ማግኘት በፍጹም አይቻልም። የማዕከላዊዉ መንግስት ለአዲስ አበባ ከተማ ሰፋ ያለ የማስተር ፕላን በማዘጋጀት በማስተር ፕላኑ ውስጥ የኦሮሚያ ልዩ ዞኖች የሚባሉትን ሱሉልታን፣ ሰንዳፋንና ገላንን በማካተት በቂ የቤት መስሪያ ቦታዎችን ለማፈላለግ እቅድ ነድፎ እየተንቀሳሰ ቢሆንም ፣ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ግን ” ከእንግዲህ መሬት ለአዲስ አበባ መስተዳድር መሬት የምንሰጠው በመቃብራችን ላይ ነው” የሚል አቋም ወስዶ በአቋሙ እንደጸና ነዉ።

በኦሮሚያ ክልል አቋም አጣብቂኝ ውስጥ የገባው የፌደራሉ መንግስት ከተለያዩ መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ ባለስልጣናትን በመሰብሰብ እና አንድ ኮሚቴ በማዋቀር ወደ ክልሎች ልኳቸዋል። እነዚህ ባለስልጣኖች ወደ ተለያዩ ክልሎች በመሄድ አዲስ አበባ ዉስጥ ቤት እንዲሰራላቸዉ ገንዝብ ለከፈሉ የዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን በየክልሉ የቤት መስሪያ ቦታ እያፈላለጉ ነዉ። ክልሎች ቦታ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ ደግሞ የወያኔ ሁለተኛዉ ስራ እንደለመደዉ ወደ ዳያስፖራ በመምጣት ቤት ለማሰራት ገንዘባቸዉን የሰጡትን የዲያስፖራዉን አባላት ከአዲስ አበባ ወጣ ብለው በክልሎች ግንባታ እንዲያካሂዱ ማግባባት ሊሆን እንደሚችል ዉስጥ አዋቂ ምንጮች በእርግጠኝነት በመናገር ላይ ናቸዉ።

መንግስትን የገጠመው ሌላው ፈተና የገንዘብ እጥረት ነው። ንግድ ባንክ ለቤቶች ግንባታ የሚሆን 12 ቢሊዮን ብር ብድር መስጠት የሚኖርበት ሲሆን፣ በቅርቡ የንግድ ባንኩ ፕሬዚዳንት ከጠ/ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ጋር በተገናኙበት ወቅት ባንካቸው ማበደር የሚችለው 6 ቢሊዮን ብር ብቻ መሆኑን ገልጸውላቸዋል። አቶ ሀይለማርያምም ባንኩ ቢያንስ 10 ቢሊዮን ብር ማበደር እንዳለበት ትእዛዝ ሰጥተዋል። ባንኩም ለታዋቂዎቹ የመጠጥ አምራች ድርጅቶች ማለትም ለሀይነከንና ዲያጎ የቢራ አምራች ፋብሪካዎች ፈቅዶት የነበረውን የ3 ቢሊዮን ብር የብድር ውል በመሰረዝ፣ ድርጅቶቹ 560 ሚሊዮን ብር ብቻ እንዲበደሩ በማድረግ ቀሪውን ገንዘብ ለዚሁ ፕሮጀክት ለማዋል ተስማምቷል። ባንኩ እስካሁን 8 ቢሊዮን ብር ለማሰባሰብ የቻለ ሲሆን፣ የመንግስትን ጥያቄ ለማሙዋላት ተጨማሪ 2 ቢሊዮን ብር ከየት እንደሚያመጣ ግልጽ አልሆነም።

በሌላ በኩል ደግሞ የቤቶች መስሪያ ዋጋ መጀመሪያ ከታቀደበት መጠን እንዲከለስ ተደርጓል። በመጀመሪያ ለ3 መኝታ ቤት መስሪያ የተመደበው ገንዘብ 385 ሺ የነበረ ሲሆን በተከለሰው አዲስ ዋጋ ግን ይህ ዋጋ በእጥፍ አድጎ 779 ሺ ብር እንዲሆን ተደርጓል። ይህ ዋጋ በቅርቡ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት ግምት ውስጥ በማስገባት ወደ አንድ ሚሊዮን እንደሚጠጋ ምንጮች ገልጸዋል። ዲያስፖራው ይህን ገንዘብ ግማሹን በአንድ ጊዜ ቀሪውን ደግሞ በአንድ ወር ውስጥ እንዲከፍል ይጠበቅበታል። አስገራሚው ነገር ይላሉ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች፣ መንግስት ከሚሰራው ቤት የተሻለ ጥራት ያለው ቤት በ450 ሺ ብር ማግኘት መቻሉ ነው።

ፕሮጀክቶችን ለማስፈጸም ሌላው ችግር የሆነው ተናቦ ለመስራት አለመቻል መሆኑን የውስጥ አዋቂዎች ይገልጻሉ። ለቤቶች ግንባታ ሃላፊነት በተሰጣቸው ሚኒስትር መኩሪያ ሀይሌ፣ በአዲስ አበባው ከንቲና ድሪባ ኩማ፣ በንግድ ባንክ ፕሬዚዳንትና በውጭ ግንኙነት ሚ/ሩ ቴዎድሮስ አዳህኖም መካከል መናበብ በመጥፋቱ ፕሮጀክቱ ባለበት የቆመ ሲሆን፣በተለይም እያንዳንዱ ባለስልጣን ኢህአዴግን ከመውደቅ ያዳንኩት እኔ ነኝ ለማለት ሁሉም የራሱን እቅድ አውጥቶ ሳይናበብ እየሰራ መሆኑን ምንጮች ተናግረዋል።

ሰመጉ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ዉስጥ ወያኔ የዜጎችን ሰብአዊ መብት መርገጡን አጋለጠ

የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዉስጥ ባካሄደው ጥናት ባለፈዉ አመት ከክልሉ አማራ ናችሁ ተብለዉ በተባረሩ በብዙ ሺዎች በሚቆጠሩ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የክልሉ ባለስልጣኖችና የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች የሰብአዊ መብት ጥሰት እና አካላዊ ጉዳት ማድረሳቸዉን አረጋገጠ። በክልኩ በተለያዩ ዞንና ወረዳዎች ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ቁጥራቸው ከ10 ሺህ በላይ የሚገመቱ ዜጐች ለረዥም አመታት ይኖሩበት ከነበረው አካባቢያቸው የዚህ ክልል “ተወላጆች አይደላችሁም” በማለት በሀይልና በግዳጅ ቤት ንብረታቸውን ጥለው ከመጋቢት 15/2005 ዓ.ም ጀምሮ እንዲሰደዱ መደረጋቸውን ተቋሙ አውስቷል፡፡

የሰመጉ የጥናት ቡድን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቡለን እየተባለ በሚጠራዉ ወረዳ ባካሄደዉ ጥናት ህፃናትና ሴቶች እንዲሁም አቅመ ደካማዎች በቂ ምግብና ህክምና ባለማግኘታቸው በከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀው እንደነበር አረጋግጦ የጉዳዩን ስፋትና ተፈናቃዩች በአሁኑ ግዜ የሚገኙበትን አጠቃላይ ሁኔታ ለማጣራት መቻሉንም ገልጿል።ተፈናቃዮቹ አሁን የሚገኙበት ሁኔታ አስቸጋሪ ነው ያለው የጥናቱ ሪፖርቱ፤ በአንዳድ አካባቢዎች ለምሳሌ በካማሼ ዞን ተፈናቃዮቹ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ የተደረገ ቢሆንም ከተመለሱ በኃላ ንብረታቸው በመወሰዱና በመጥፋቱ ለመቋቋምና ወደ ነበሩበት የኑሮ ሁኔታ ለመመለስ አልቻሉም ። በተለይ ተፈናቃዮቹ ለእርሻ ግብዓት የሚሆኑ እንደ ዘር ፣ማዳበሪያ የመሳሰሉትን ለመግዛት ወይም ብድርም ለመውሰድ በሞከሩባቸዉ አማራ በመሆናቸዉ ብቻ አድሎ እንደተደረገባቸዉ ለማወቅ ተችሏል።

በጥናቱ ወቅት ተፈናቃዮቹ ለሰመጉ እንዳስረዱት የደረሰባቸውን ከፍተኛ በደልና እንግልት በተለያዩ የሀገር ውስጥ ጋዜጦችና የውጭ ሚዲያ በመናገራቸው ምክንያት እስራት ዛቻና ክትትል እየተፈፀመባቸው እንደሆነና በከፍተኛ ስጋት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ተፋናቃዮቹ ለረዥም አመታት ያፈሩትን ንብረትና የእርሻ መሬታቸውን በአካባቢው ባለስልጣናትና በሌሎች ብሔረሰብ አባላት መነጠቃቸውን፣ የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶቻቸውን እንዳያዙበት መደረጋቸውን፣ መታወቂያ ካርድ እንዳያወጡ መከልከላቸውንና፣ ልጆቻችው በትምህርት ቤቶች ውስጥ ገብተው እንዳይማሩ መደረጉን ተናግረዉ “የዚህ ክልል ተወላጅ አይደላችሁም” እየተባሉ ዛቻ፣ ድብደባ፣ ንብረት ነጠቃና ለእሰራት ጭምር እንደተጋለጡ የተፈናቃይ ተወካዮች ለሰመጉ በፃፉት ማመልከቻ ተናግረዋል።

የባሩዳ ቀበሌ ተፈናቃዮች “ በአካባቢው አስተዳደር አካላትና በሌሎች የክልሉ ብሄረሰብ አባላት የተነጠቁትን የተለያዩ ንብረቶች ተመላሽ አለመደረጉን ፣በአሁኑ ወቅት ከሌሎች ብሄረሰቦች እየተለዩ ማስፈራሪያና ድብደባ እየተፈፀመባቸው መሆኑ፣ ምንም አይነት እገዛና ማቋቋሚያ አለመደረጉ፣ የእርሻ ግብዓትን እንደ ዘር ማዳበሪያ ያሉ ግብዓቶችን “እናንነተ የዚህ (ብሄር) አባላት ናችሁ” በማለት እየተከለከሉ ነገር ግን ለሌሎች እየተሰጠ እንደሚገኝና በፌዴራል መንግስት አማካኝነት ቢመለሱም የዞንና የቀበሌ አስተዳደር አካላት “እናንተ ከዚህ ክልል ውጪ ናችሁ” በማለት ልዩ ልዩ አድልዎና መገለል እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝ ለሰመጉ አመልክተዋል፡፡ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የአማራ ተወላጆች ለረዥም አመታት ይኖሩበት ከነበረው ቦታ “ የዚህ አካባቢ ሰዎች አይደላችሁም” በማለት ከተፈናቀሉ በኋላ ወደ ነበሩበት ቦታ ይመለሱ እንጂ ምንም አይነት እገዛ ከመንግስት እንዳልተደረገላቸውና ይባስ ብሎም እንግልትና የተለያዩ አስተዳደራዊ በደሎች እየተፈፀመባቸው እንዳለ ዘጋቢያችን ሪፖርቱን ተከትሎ ባደረገው ማጣራት ለማረጋገጥ መቻሉን ገልጿል።

የወያኔዉ ጋጠወጥ ፍርድ ቤት የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን ባልፈጸሙት ወንጀል ተከላከሉ ብሎ በየነ

የሰብዓዊ መብታቸዉ አንዱ አካል የሆነዉ የማምለክ መብታቸዉ እንዲከበር በመጠየቃቸዉ ብቻ በወያኔ የጸጥታ ኃይሎች ታድነዉ ከአንድ አመት በላይ በግፍ ታስረዉ የቆዩት የድምጻችን ይሰማ መሪዎች ዜጎችን ለማጥቃት ሆን ተብሎ የተፈጠረዉ የወያኔ ፍርድ ቤት ተከላከሉ ብሎ እንደበየነባቸዉ ጠበቃ ተማም አባ ቡልጉ ተናገሩ። የየስሙላ ፍርድ ቤቱ አስር ሁለት እስረኞችን በነጻ የለቀቀ ሲሆን እነ አቶ አቡበከር አህመድና ሌሎች ደግሞ የተመሰረተባቸዉን ሽብር አነሳስታችኋል የሚል ክስ እንዲካለከሉ ብይን ሰጥቷል። አንደ ተከሳሾቹ ጠበቃ እንደ አቶ ተማም አባ ቡልጎ አባባል ሙራድ ሹኩር ጀማል፣ ኑሩ ቱርኪ ኑሩ፣ ሼህ ባህሩ ኡመር ሸኩር እና ጋዜጠኛ የሱፍ ጌታቸው ሽብርን በመርዳት በሚለው ሀግ አንቀጽ ሰባት ተጠቅሶባቸዉ ክሱን ተከላከሉ የተባሉ ሲሆን ተከሳሾች መከላከያቸውን ከጥር 22 እስከ 27 እንዲያቀርቡ ፍርድ ቤቱ አዟል።

ውሳኔውን በተመለከተ አስተያየታቸውን ለኢሳት ቴሌቪዥንና ሬድዮ ቃለ መጠይቅ የሰጡት የተከሳሾቹ ጠበቃ አቶ ተማም አባ ቡሉጎ፣ ምንም እንኳ ተከላከሉ የተባሉት አንቀጽ የቅጣት መጠኑን ቢቀንሰውም፣ የእሳቸዉ አላማና ፍላጎት ግለሰቦቹ በነጻ ተለቅቀዉ ወደ ቤተሰቦቻቸዉ እንዲመለሱ ማድረግ ነዉ ብለዋል። የወያኔ አገዛዝ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን መጀመሪያ ላይ የከሰሳቸዉ የሽብር ጥቃት ፈጽማችኋላ በሚል ጠንከር ያለ ክስ ቢሆንም ይህንን መሰረተ ቢስ ክስ የሚደግፍ መረጃ እንዳልተገኘ ጠበቃ ተማም አባ ቡልጎ ተናግረዋል።ብይኑ ሲሰጥ በእስረኞች ቆጠሩ ንጽበኩል ምንም አይነት የመደናገጥ ወይም የመረበሽ ምልክት አለማየታቸውን የተናገሩት ጠበቃው፣ የእኛ ደንበኞች ለምን እንደታሰሩ የሚያውቁ የሀይማኖት መምህራን እና ለእኛ ጽናትን የሚያስተምሩ ናቸው ብለዋል

የወያኔዉ የይስሙል ፍርድ ቤት የተመሰረተባቸውን ክስ ተከላከሉ የበየነዉ አቡበከር አህመድ፣ አህመዲን ጀበል መሃመድ፣ ያሲን ኑሩ ኢሳአሊ፣ ከሚል ሸምሱ ሲራጅ ፣ በድሩ ሁሴን ኑር ሁሴን፣ ሼህ መከተ ሙሄ መኮንን፣ ሳቢር ይርጉ ማንደፍሮ፤ መሃመድ አባተ ተሰማ፣ አህመድ ሙስጠፋ ሃቢብ፣ አቡበከር አለሙ ሙሄ፣ ሙኒር ሁሴን ሃሰን ፣ ሼህ ስኢድ አሊ ጁሃር፣ ሙባረክ አደም ጌቱ አሊዬ እና ካሊድ ኢብራሂም ባልቻን ሲሆን በነጻ ያሰናበተዉ ደግሞ ሃሰን አሊ ሹራባ፣ ሼህ ሱልጣን ሃጂ አማን፣ ሼህ ጀማል ያሲን ራጁኡ፣ ሼህ ጣሂር አብዱልቃድር፣ ሃሰን አቢ ሰኢድ፣ አሊ መኪ በድሩ፣ ሼህ ሃጂ ኢብራሂም ቱሃፊ፣ ሼህ አብዱራህማን ኡስማን ከሊል፣ ወይዘሮ ሃቢባ መሃመድንና ዶክተር ከማል ሃጂ ገለቱን ነዉ።

ነጋሪቱም ተጎስሟል፤ፋኖም ተሠማርቷል !!!

ዛሬ ኢትዮጵያዊያን እያዩ ያሉት ውርደት ቃል የሚገልፀው አልሆነም። ኢትዮጵያ በታሪኳ ዛሬ እየደረሰ ያለ ዓይነት ውርደት ደርሶባት እንደሆነ በታሪክ የተመዘገበ ነገርም ተፈልጎ አልተገኘም። ይሄ ለኢትዮጵያዊያን የጨለማ ዘመን ነው። በኢትዮጵያ እንዲህ ስደትና እንግልት፤ ሃዘንና ዋይታ የበዛበት ዘመን ታይቶ አይታወቅም።

በዚህ ግዜ በኢትዮጵያችን መንግስት ነኝ እያለ ራሱን የሚጠራ ቡድን አለ።ይሄ ቡድን አገሪቷን ከተቆጣጠረ ዘመን ጀምሮ ኢትዮጵያ የገባችበት የውርደት አዘቅት ከባድ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ በህወሃቶች አዝማችነት ተስምቶ የማይታወቅ ጆሮን ጭው የሚያደርግ ግፍ በዜጎች ላይ ይፈፀማል። የተለየ የፖለቲካ አመለካከት ያላቸውን ሰዎች ይዘው ግብረ ሶዶም እንዲፈፀምባቸው ያደርጋሉ፤ ሴቶች ልጆችን በጋራ ሁነው ይደፍራሉ፤ በተቀደሱ ስፍራዎች ገብተው ቅዱሱን ስፍራ ያረክሳሉ፤ ዜጎችን ከእርሻ ማሳቸው አፈናቅለው በገዛ አገራቸው መፃተኛ ያደርጓቸዋል። በአጠቃላይ ዜጎች በአገራቸው ተስፋ አጥተው ሃዘንተኛ እንዲሆኑ ያደርጋሉ። ተስፋ የቆረጡ ዜጎች ኢትዮጵያ ውስጥ ከምኖር ሂጄ ብሞት ይሻለኛል ብለው እግራቸው በመራቸው መንገድ ይሰደዳሉ። በእንዲህ ሁኔታ ከኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ250ሺህ በላይ ወጣቶች ይሰደዳሉ።ገሚሱ በየበርሃው በውሃ ጥማት ወድቆ ይቀራል፤ ገሚሱም የባህር አዞ ቀለብ ሁኖ ዱካው ይጠፋል። ከሞት ተርፈው በየአርብ አገራቱ የደረሱ ዜጎች በሰው ልጆች ላይ ሊደርስ የማይገባ ወንጀል ይፈፀምባቸዋል።ባንዲራቸውን በአንገታቸው እንደጠመጠሙ ሬሳቸው ሜዳ ላይ ተጥሎ የአርብ መሳቂያ መሳለቂያ ይሆናሉ። በዚህ ሰሞን በሳውዲ ዓረቢያ እየተፈፀመ ያለው ግፍ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ብሄራዊ ውርደት ሁኗል።

ይሄ በእንዲህ እንዳለ “መንግስት ነኝ “ እያለ ራሱን የሚጠራው ህወሃት በዜጎቹ ሲቃና መከራ እየቀለደ ይገኛል።አንድ ግዜ ዜጎቼን እያወጣሁ ነው ይላል፤ ሌላ ግዜ ደግሞ የሥራ ፈቃድ የሌላቸው ስለሆኑ አላውቃቸውም ይላል። ህወሃቶች በዚህ ብቻ አላበቁም በኢትዮጵያዊያኑ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ ለማስቆም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ እምባሲ ፊት ለፊት ሠላማዊ ሠልፍ እንዳይደረግ መከልከል ብቻ ሳይሆን ለሠላማዊ ሰልፍ የወጡ ዜጎችን የቻሉትን ያክል ወደ እስር ቤት አግዘዋል፤ ያገኙትን ሁሉ በቆመጥ እንዲደበደቡ አድርገዋል። የአካል ጉዳትም አድርሰዋል። ይሄን ሁሉ ግፍ የሚታደግ፤የህዝቡንም ሮሮ የሚሳማ መንግስታዊ አካል አልተገኘም። ዓለምም ፊቷን ያዞረችብን የሚመስል ሁኔታ ታይቷል።

ኢትዮጵያዊያን ቀና ብለን በኩራት በአርብ አገራት ጎዳናዎች ላይ የምንመላለስ ዜግች ነበርን። ስማችን ያማረ፤ ማንነታችን የተከበርን ዜጎች ነበርን። አረብ የሚያከብረን እንጂ እንዲህ የሚንቀንና የሚያዋርደን ዜጎች አልነበርንም። በዘመነ ህወሃት ግን ያ ሁሉ ክብራችን ተዋርዶ ዜጎቻችን እንደ ሌጦና ቆዳ በገንዘብ የሚሸጡ ሆኑ። በኢትዮጵያችን ላይ የነበሩ የቀድሞው ገዥዎች ምንም እንኳ ጨቋኞች ቢሆኑም ዜጎቻቸው በሌላ በማንም እጅ እንዲገላቱና እንዲዋረዱ የሚፈቅዱ አልነበሩም።በአንድ ወቅት አፄ ኃ/ስላሴን” ሠራተኛ ይላኩልኝ” ብለው የሳውዲው ንጉስ ሲጠይቋቸው “ለመሆኑ ምንድ ነው የምትፈልጉት መሃንዲስ ነው ወይስ ሃኪም “ብለው ይጠይቋቸዋል። አይ “እኛ የምንፈልገው በቤት ሠራተኛነት የሚያገለግሉንን ነው” ይላሉ አረቦቹ።አይ “እኛ ለቤት ሠራተኛ የሚሆን ዜጋ የለንም” ብለው መለስውላቸዋል።ለራሱም ሆነ ለወገኑ ክብር ያለው መሪ መልሱ እንዲህ እንጂ ሳውዲ ድረስ ሂዶ ዜጎቹን ለባርነት ለመሸጥ ሲዋዋል አይገኝም።

ደሳለኝ ኃ/ማሪያም ከስድስት ወር በፊት ሳውዲ ድረስ ገስግሶ ሂዶ የቤት ሠራተኞችን ለአረቦቹ ለመላክ ተዋውሎ መመለሱ የሚታወስ ነው። ይሄን ውል ሲዋዋል ግን ስለ ክፍያ፤ ስለ ዕረፍት ግዜ፤ በህመም ግዜ ምን ይሆናል የሚሉ መሠረታዊ ቁም ነገሮች በውሉ ውስጥ አልተካተቱም። በእነዚህ ነገሮች ምክንያት የኢንዶኔዥያ እና የፊሊፕልንስ መንግስታት ግን ምንም እንኳ ድሃ ብንሆንም ዜጎቻችንን የምንሰደው የታወቀ የክፍያ መጠን፤ የእረፍት ግዜ፤ የህመም ፈቃድ እነዚህንና ሌሎችን መሠረዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ የተሟላ የህግ ድንጋጌ ሲኖራችሁ ነው። ይህን ህግ እስከምታበጁ ዜጎቻችን የእናንተ መጫወቻ እንዲሆኑ አንልክም ብለው እምቢ ማለታቸው ይታወቃል። ህወሃት መራሹ መንግስት ግን ስለውጪ አገር አኗኗር ምንም ዓይነት ግንዛቤ የሌላቸውን ወጣት ልጆችን ያለ ምንም ህግ ከለላ አሳልፎ ለባእዳን ይሰጣል። ወጣት ሴቶችንና ወንዶችን ለግርድናና ለአሸከርነት የመላኩ የድለላ ሥራም ህወሃቶች ባቋቋማቸው ድርጅቶች ተካሂዶ ከዚህ ንግድ በተገኘው ገንዘብ ህውሃቶች ብዙ ገንዘብ አፈሱ። ወገኖቻችን ግን በአረቦች እጅ እንባቸውን በመዳፋቸው የሚሰፍሩ ሆነው ቀሩ።

ለዚህ ሁሉ መከራ እና ውርደት ያበቃን ምንድ ነው የሚል ርዕስም የሰሞኑ የመወያያ ርዕስ ሆኗል። የመከራውና የውርደቱ ምንጭ ፈርጀ ብዙ ቢሆንም ህወሃት ዋነኛው የችግሩ ምንጭ ስለመሆኑ ብዙ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። በአጠቃላይ ግን ህወሃት መንግስት ነኝ ብሎ ሲያበቃ ዜጎችን ለመታደግ ምንም ዓይነት ተግባራዊ እንቅስቃሴ አለማድረጉ ብቻ ሳይሆን ዜጎች በሰላማዊ ሰልፍ እንኳ ቁጣቸውን እንዳይገልጹ መከልከሉ ማንነቱን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።ለዚህ ብሄራዊ ውርደትና መከራ በመጀመሪያ ደረጃ ሊጠየቅ የሚገባው ህወሃት እንጂ ሌላ ማንም አይደለም። ህወሃት የኢትዮጵያዊያን ጠላት መሆንን የመረጠ የጠባብ ዘረኞች ቡድን ነው። ዜጎቻቸን እንዲህ ላለው ጉስቁልናና ውርደት እንዲጋለጡ ያደረጋቸው ህወሃት መሆኑን መያዝ ለነፃነት ለሚደረገው ትግል አንዱ አካል ነው።

የተከበራችሁ ወገኖቻችን፤

በሳውዲ አረቢያ የሚሰቃዩ ዜጎችን በተመለከተ ህወሃቶች ምንም ተቆርቋሪነት ያሳዩበት ሁኔታ እንዳልታየ ታውቃላችሁ።ለወገን ተቆርቋሪነት ከህወሃቶች የሚጠበቅ ስላልሆነ እኛ አንደነቅም። አስቀድመው በገንዘብ አሳልፈው ለሸጧቸው ዜጎች ይቆረቆራሉ ብሎ መጠበቅ የህወሃቶችን ባህሪይ ካለመረዳት የሚመነጭ ብቻ ሳይሆን ህወሃቶች ዜጎች ማኩረፊያ አገር እንኳን እንዳይኖሯቸው የሚያሴሩትን ሴራ ለመረዳት ካለመፈለግ የሚመነጭም ጭምር ነው። ወደ አረብ አገር የተሰደዱም ሆኑ በሌሎች አገር በስደት ላይ ያሉ ዜጎች በከፋቸው ግዜ ተመልሰው የሚገቡበት ሥፍራ አላቸው ለማለት የሚያስደፍር ሁኔታ በኢትዮጵያ የለም። ጉራፈርዳ እና ቤንሻንጉል አገርህ አይደለም ተብሎ የተባረረ ወጣት መግቢያው የት ነው ? ከዚህ ሥፍራ ወደ ሳውዲ የተሰደደ ወጣት መመለሻው ወደየት ነው ? በዚያች አገር ድንጋይ ለመፍለጥ እንኳ የኢሕአዴግ አባል እንዲሆን በሚገደድበት አገር ምን አገር አለኝ ብሎ ነው የከፋው ወደ ኢትዮጵያ የሚመለሰው? አዎን ኢትዮጵያዊያን ማኩረፊያ አገር የሌለን ከርታታ ዜጎች እንድንሆን ተደርገናል።አገር ያሳጡንም ህወሃቶች ናቸው እንጂ ሌላ ማንም አይደለም።

እንግዲህ ምን ይደረግ?

ይሄ ጥያቄ ግልጽና ቀላል መልስ አለው።አምርሮ መነሳት። ህወሃቶች በአዲስ አበባ ላይ ወንድ ልጅን አስገድደው ግብረ ሶዶም እንዲፈፀምበት ሲያደርጉ ሰምቶ “እነዚህ ምን ዓይነት አረመኔዎች ናቸው” ማለት ብቻ በቂ አይደለም።ለአረመኔ የሚገባውን ቅጣት ለመስጠት የአያቶቻችንን ጋሻና ጦር ማንሳት ግዜው የሚጠይቀው ታሪካዊ ግዴታ ነው። በሳውዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ የቆየውን ውርደት እንምባ ብቻ የሚያስቆመው አይሆንም። እንዲህ የአረብ መቀለጃ የሆነውን ማንነታችንና ክብራችንን አስመልሰን አንገታችንን ቀና አድርገን በአርብ ጎዳናዎች ላይ እንደቀድሞው ዘመን በኩራት እንድንመላለስ የአያቶቻችንን ትጥቅ ከተሰቀለበት አውርደን መታጠቅ ግዴታችን ሁኗል።

ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ውስጥ ያለን ኢትዮጵያዊያን በወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለው ውርደት ብሄራዊ ውርደት ነው እንላለን። ከዚህ በላይ ሌላ ብሄራዊ ውርደት የለም። ለዚህ ውርደት ያደረሰንም ህውሃት ነው። ህወሃት እስካለ ድረስ ብሄራዊ ውርደታችን ይቀጥላል እንጂ አይሻሻልም። እኛ የሚደርስብንን ውርደት ለማስቆም አምርረን ተነስተናል። እኛ እንዲህ ተዋርደን መኖርን ከቅድሞዎቹ ኩሩዎች አያቶቻችን አልተማርንም።እኛን ባንዳዎችና የባንዳ ልጆች ህወሃቶች አንገታችንን አስደፍተው አዋርደው አይገዙንም። አያቶቻችን ለነፃነታቸው እና ለአገራቸው ክብር ሲሉ በቆሙበት በጀግኖች ሥፍራ ለመቆም መንገዱን ጀምረናል። ከእንግዲህ ወዲያ ከዚህ ጉዞ የሚያቆመን ምንም ዓይነት ምድራዊ ኃይል የለም። ለእኛ ነጋሪት ከተጎሰመ ቆይቷል እኛ የነጋሪቱን ድምፅ በሰማን ግዜ ሳናቅማማ ተነስተናል።

እናንተስ ሳትቅማሙ ለመነሳት የነጋሪቱን ድምፅ ሰምታችኋል ? ከወደ ሳውዲ የተሰማው ያ የሲቃ ጩኸት፤ ያ ሮሮ፤ ያ እንምባ አስደንጋጩ የነጋሪት ድምፅ ነው። ከዚህ ድምፅ በኋላ ፋኖ ይሠማራል እንጂ አያለቅስም።ማልቀስ የናቁንና ያዋረዱን እንዲያከብሩን አያደርግም። ነጋሪቱ ከተጎሰመ በኋላ አገሬን፤ ክብሬን የሚል ተነስቶ ያያቶቹን ጋሻና ጦር ያነሳል እንጂ እንዲያው ዝም ብሎ አያጉረመርምም።አገር ተዋርዳ፤ ህዝብ ተበደሎ ዝም ብሎ ተንጋሎ የሚተኛ ካለ ይህን ብሄራዊ ውርደት ካመጡ ቡድኖች በምን እንደሚለይ ራሱን ይጠይቅ። አበቃን።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!!

Sunday, December 15, 2013

አቶ ልደቱ ወደ ፖለቲካ ተመለሱ

ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ቢሆንም ግን ፈተናውን ወድቋል የሚሉት አቶ ልደቱ አያሌው፤ የኢኮኖሚ እድገቱን መካድ ስህተት ነው፤ እድገቱ ዘላቂነት እንደሌለው አለመገንዘብም ስህተት ነው በማለት የኢዴፓ “ሦስተኛ አማራጭ” የተሰኘ የኢዴፓ አቋምን ይተነትናሉ፡፡ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች መዳከም አንዱ ምክንያት የመንግስት ተጽእኖ እንደሆነ አቶ ልደቱ ገልፀው፤ ነገር ግን ህዝቡን አሰባስቦ በመታገል የመንግስትን ተጽእኖ ማስቆምና ለውጥ ማምጣት ይቻላል፡፡ ይልቅስ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ራሳቸውን ለመፈተሽና ስህተታቸውን ለማረም አለመዘጋጀታቸው ትልቅ እንቅፋት ሆኗል ይላሉ፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ፣ በጭፍን ድጋፍና በጭፍን ተቃውሞ ለሁለት ስሜታዊ ጽንፎች ፖለቲካ እንደሰፈነ ጠቅሰው፤ ስር የሰደደውን የተሳሳተ የጽንፍ አስተሳሰብ በምክንያታዊ አስተሳሰብ በመተካት ሦስተኛ አማራጭ መያዙ ለአገሪቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ይላሉ፡፡ ከ1997 ወዲህ የአገሪቱ ፖለቲካ ቁልቁል እየተንሸራተተ በ15 አመት ወደኋላ መመለሱን ሲያስረዱ፤ አሁንም ከደጡ ወደ ማጡ እንዳይሰምጥ፣ ከዚያም ወደፊት እንዲራመድ ቁልፍ ያለው በገዢው ፓርቲ፣ በተቃዋሚ ፓርቲዎችና በህዝቡ ዘንድ ነው ብለዋል አቶ ልደቱ፡፡ አቶ ልደቱ እነዚሁ 3 ቁልፍ አካላት ካሁን በፊት ምን ስህተት እንደሰሩና ወደፊት ምን እንደሚጠበቅባቸው ከመተንተን በተጨማሪ፤ ለበርካታ ጉዳዮች ላይ የሰነዘሩትን ሃሳብ በዚህ ቃለ ምልልስ እናቀርባለን፡፡

አቶ ልደቱ ለረጅም ጊዜ ጠፍተዋል..ከፓለቲካውም ከሃገሪቱም.. ከመገናኛ ብዙሃን ትንሽ ራቅ ስላልኩ የጠፋሁ ይመስላል፡፡ ላለፉት ሁለት ዓመታት ለትምህርት ከኢትዮጵያ ውጪ ነው የነበርኩት፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ከሃያ አምስቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት አንዱ ብሆንም፣ በጠቅላላ ጉባኤ ከሊቀመንበርነት ስለወረድኩ የፓርቲው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ አልመራም፡፡ በነዚህ ምክንያቶች ከመገናኛ ብዙሃን ርቄያለሁ፡፡ ከኢትዮጵያ ፓለቲካ ግን አልራቅኩም፡፡ አሁን ትምህርቴን አጠናቅቄ እዚሁ አገሬ እየኖርኩ ነው፡፡ የነበሩበት ትምህርት ቤት ምንድን ነበር የሚባለው… ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ኦፍ ለንደን ውስጥ፤ ስኩል ኦፍ ኦሬንታል ኤንድ አፍሪካን ስቴዲስ የሚባል አለ፡፡ እዚያ ነው ዲቨሎፕመንት ስተዲስ ያጠናሁት፡፡ ከ1997 ዓ.ም. ምርጫ በኋላ ኢዴፓ ‹‹ሶስተኛ አማራጭ›› የሚል ሃሳብ ይዟል፡፡ ይሄ ሃሳባችሁ ከምን አደረሳችሁ? ‹‹ሶስተኛ አማራጭ›› የምንለውን ነገር በአግባቡ ያለመረዳት ነገር አለ፡፡ እኛም በበቂ ሁኔታ አላስረዳን ሊሆን ይችላል፡፡

ሶስተኛ አማራጭ ሲባል፣ ልዩ የርዕዮተ አለም መስመርን ለመግለጽ ሳይሆን፣ የአቀራረብና የስልት ጉዳይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ፓለቲካ፣ እስከ አሁን ድረስ ሁለት ፅንፍ የያዘ ነው። ሁለትም ነገር መደገፍ ወይም ሁሉንም ነገር መቃወም፡፡ የገዥው ፓርቲ አባል ከተሆነ፤ ተቃዋሚ የሚሰራውን ነገር ሙሉ በሙሉ ማጥላላት፤ የተቃዋሚ አባል ከተሆነ ደግሞ መንግስት የሚሠራውን ነገር ሁሉ መቃወም፡፡ እንዲህ ሁለት ጫፍ የያዘ አሰላለፍ፤ ለአገራችን ፖለቲካ አልጠቀመም፡፡ ከመቻቻል ከመደማመጥ አርቆናል፡፡ ለዚህም ነው፤ ከሁለቱ ጽንፎች የተለየ አማራጭና የተለያየ አቀራረብ ያስፈልጋል የሚል አስተሳሰብ ይዘን የመጣነው፡፡ በመንግስትም ሆነ በተቃዋሚ የተሠራ ነገር ለአገርና ለህዝብ የሚጠቅም ከሆነ ልንደግፈው ይገባል፡፡ የማይጠቅምና የሚጐዳ ከሆነ ደግሞ በተጨባጭ መረጃ መቃወምና እንዲቀየር መታገል ያስፈልጋል፡፡ በስሜታዊ ጽንፍ ሳይሆን በምክንያታዊ አስተሳሰብ ነው ፖለቲካው ሊመራ የሚገባው፡፡ አለበለዚያ፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ወደ ዲሞክራሲያዊ የመቻቻል ባህል ሊቀየር አይችልም። ሁለት ስሜታዊ ፅንፎችን ይዞ፣ ብሔራዊ መግባባት ለማምጣት በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ፣ ምክንያታዊ አስተሳሰብ ነው የሚያዋጣን ብለን ሶስተኛ አማራጭ ይዘናል፡፡ ይሄንን አቀራረብ ይዘን ስንመጣ ፈተናዎች ገጥመውናል፡፡

ሁለቱ ጽንፎች ለረዥም ጊዜ ስር የሰደዱና የከረሩ ስለነበሩ፣ ብዙ ሰዎች የእኛን አስተሳሰብ ለመቀበል በጣም አስቸግራቸዋል፡፡ ደግሞም አያስገርምም፡፡ ሰዎች በቀላሉ ይሄን አስተሳሰብ የሚቀበሉ ከሆነ፤ ከመነሻው የአገራችን ፖለቲካ ከባድ ችግር የለበትም ማለት ነው፡፡ የአገራችን ፖለቲካ ግን ለረዥም ጊዜ የዘለቀ ትልቅ ችግር አለበት፡፡ ስለሆነም፤ ሦስተኛ አማራጭ ብለን ያቀረብነው የምክንያታዊ አስተሳሰብ አቅጣጫችንን ብዙ ሰዎች በቀላሉ ሊቀበሉት አልቻሉም። “ተቃዋሚ ከሆንክ በቃ ማንኛውንም ነገር ትቃወማለህ፡፡ ኢህአዴግም ከሆንክ ማንኛውንም ነገር ትደግፋለህ፤ ሌላ ሦስተኛ አማራጭ የለም” የሚል የተዛባ አመለካከት ይሰነዘርብን ነበር፡፡ “እንዲያውም ሦስተኛው አማራጭ የምትሉት ነገር ወላዋይነት ነው” በማለት ውዥንብር የመፍጠር ነገርም ነበር። በሂደት ግን፣ ብዙ ሰው ጉዳዩን እያብላላው፣ እያጤነውና እየተገነዘበው እንደሆነ አይተናል፡፡ እኛ በምንፈልገው ፍጥነት ህብረተሰቡ ተረድቶታል የሚል እምነት የለንም፡፡ ገና ብዙ ይቀራል፡፡ የኢትዮጵያ ፖለቲካ እስከአሁን በመጣበት የጽንፈኝነት መንገድ የትም ሊያደርሰን እንደማይችል ብዙዎች እየገባቸው ነው፡፡ ሁለቱ ጽንፎች የሚፈጥሩት ቅራኔና ውጥረት፣ ከዴሞክራሲ እያራቀን እንጂ ወደ መቻቻል እያመጣን እንዳልሆነ ሰው እየተገነዘበው ነው፡፡

Saturday, December 14, 2013

ሁለገብ-ገብ ትግል – ከኔልሰን ማንዴላ ጋር የምንጋራው የትግል ስትራቴጂ

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄም በኔልሰን ማንዴላ ዜና እረፍት የተሰማውን ሐዘን በመግለጽ መግለጫ ያወጣ ቢሆንም የትግል ተሞክሯቸው ለአገራችን ስላለው ጠቀሜታ ተጨማሪ ቁም ነገሮችን ማንሳት አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል።

ኔልሰን ማንዴላንና የትግል ጓዶቻቸው መሣሪያ እስከማንሳት ያደረሳቸው የደቡብ አፍሪቃ አፓርታይድ አገዛዝ ዋነኛው መገለጫው የባንቱስታን ሕግ ነበር። በዚህ ህግ መሠረት ደቡብ አፍሪቃ ዘርን መሠረት ያደረጉ አስር “ባንቱስታ” የተሰኙ “ራስ ገዝ” ግዛቶች ተቋቁመው ነበር። ያኔ በደቡብ አፍሪቃ አገዛዝ ሥር በነበሩ የደቡብ ምዕራብ ግዛቶች ደግሞ ሌላ አስር ባንቱስታዎች ነበሯቸው። በእያንዳንዱ ደቡብ አፍሪቃዊ መታወቂያ ባንቱስታው እንዲገልጽ ህጉ ያስገድዳል። የአንዱ ባንቱስታ ነዋሪ ያለልዩ ፈቃድ ወደሌላው ባንቱስታ መሄድ አይችልም። ከዚህም ሌላ ለነጮች ብቻ በተከለሉ ቦታዎች ጥቁሮች ለሥራ ካልሆነ በስተቀር ለሌላ ማናቸው ተግባር እንዳይገኙ ህጉ ያዛል። አፓርታይድ የደቡብ አፍሪቃ ዜጎችን በየዘር ክልሎቻው ውስጥ አጉሮ አገራቸውን እስር ቤታቸው እንዲሆን አደረገው። ይህንን ለመቃወም ኔልሰን ማንዴላ እና የወቅቱ ታጋዮች በመጀመሪያ ሰላማዊ ትግልን ሞከሩ፤ ያ አላዋጣ ሲል መሣሪያ አነሱ።

በአሁኑ ሰዓት ባንቱስታን መሰል የክልል አስተዳደር ያለው በአገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው። ልክ በአፓርታይድ ደቡብ አፍሪቃ እንደነበረው ሁሉ የኛም መታወቂያዎች ዘራችንና ክልላችንን ይገልፃል። በአፓርታይድ ደቡብ አፍሪቃ እንደነበረው ሁሉ እኛም ከክልላችን ውጭ ተንቀሳቅሰን መሥራትና መኖር አንችልም። ከቤንሻንጉል-ጉሙዝ እና ከደቡብ ክልሎች ተፈናቅለው ለጎዳና ኑሮ የተዳረጉት የአማራ አርሶ አደሮች የዚህ ፓሊሲ ሰለባዎች ናቸው።

ኔልሰን ማንዴላ እና ድርጅቱ ኤ. ኤን. ሲ. በሰላማዊ ትግል ብቻ አፓርታይድን ማስወገድ እንደማይቻል የተገነዘቡት ከስዊቶ እልቂት ነው። በስዊቶ እልቂት 176 ዜጎች እንደተገደሉ ይነገራል። እኛ አገር ብዙ ስዌቶዎች አሉ። በበደኖ፣ በአዋሳ፣ በሀረር፣ በጋምቤላ፣ በጎንደር፣ በኦጋዴን፣ በአዲስ አበባ እና በሶማሊያ የደረሱት እልቂቶች እያንዳንዳቸው የስዌቶን እልቂት ያክላሉ። በዚህም ላይ በሰቲትና በሁመራ የተደረገው ስልታዊ የዘር ማጥራት፤ የወጣቶች ያላባራ ስደት የዚሁ ፓሊሲ አስከፊ ውጤቶች ናቸው።

ሰላማዊ ትግል ብቻውን የደቡብ አፍሪቃ ዘረኛ አገዛዝን ማስወገድ አልቻለም። ሰላማዊ ትግል ብቻውን ወያኔ በአገራችን ላይ የጫነብን ዘረኛ አገዛዝ እንዲያበቃ ማድረግ ይችላል ብሎ ማመን አዳጋች ነው። ስለዚህም ነው ማንዴላ እንዳደረገው ሁሉ ግንቦት 7 ም ሁለገብ ትግልን እንደ ትግል ስትራቴጄ ለመያዝ የተገደደው።

ሁለገብ ትግል ሕዝባዊ አመጽ እና ሕዝባዊ እምቢተኝነትን አጣምሮ መያዝ ይጠይቃል። ሁለገብ ትግል መጨከንን ያም ሆኖ ለእርቅ አንድነት ለሀገር እና ለወገን የጋራ ጥቅም መሥራትን ይጠይቃል። ሁለገብ ትግል ዘረኝነትን በጽናት የመታገል ሆኖም ግን ይቅር ባይ መሆንን ይጠይቃል።

ግንቦት7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሁለገብ የትግል ስትራቴጂን በአማራጭነት ሲወስድ ከወያኔ ዘረኛ አገዛዝ ጋር ተመሳሳይ የሆነውን የደቡብ አፍሪቃ አፓርታይድ ሥርዓትን ለመለወጥ የነበረውን ፍቱንነት በጥልቀት በማጤን ነው።

ዘላለማዊ እረፍት ለኔልሰን ማንዴላ

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Thursday, December 12, 2013

እምዬ ምኒልክ፡ የጥቁር ሕዝብ ኩራት! ከነሐሴ 11 ቀን 1836 ዓ.ም. --

ዛሬ ታህሳስ 3ቀን የሚከበረው የዳግማዊ አጼ ምኒልክ 100ኛ የዕረፍት ዓመት “እምዬ ምኒልክ ምን ዓይነት ውርስ ትተውልን ሄዱ?” ብለን እንድንጠይቅ የሚያደርገን ነው፡፡ በመሆኑም ወደ ጦርነት ለመግባት ሳይፈልጉ “በግድ” ወደሄዱበት የጣሊያን ጦርነት መለስ ብለን የሆነውን እንድናስብ ወደድን፡፡

ክተት፡-

“እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላትን አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ፡፡ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ፡፡ እንግዲህ ብሞትም ሞት ለሁሉ ነውና ስለ እኔ ሞት አላዝንም፤ ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም፤ እንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም፡፡ አሁንም አገር የሚያጠፋ፣ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚአብሔር የወሰነልንን የባሕር በር አልፎ መጥቷልና እኔም ያገሬ ከብት ማለቁንና የሰዉን መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፡፡ አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም፡፡ ያገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም፤ አንተም እስካሁን አላስቀየምከኝም፡፡ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ፡፡ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፣ ለምሽትህ፣ ለሃይማኖትህ ስትል በሐዘን እርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ፡፡ አልተውህም ማርያምን፤ ለዚህ አማላጅ የለኝም፡፡ ዘመቻዬ በጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረኢሉ ከትተህ ላግኝህ፡፡”

ከድል በኋላ፡-

“(ጥልያኖች) በጥጋባቸው አድዋ ላይ ተዋግተው ድል ሆኑ፡፡ እኔ በድንቁርናቸው ብዛት የእነዚያን ሁሉ ክርስቲን ደም በከንቱ መፍሰሱን እያየሁ “ድል አደረኩዋቸው” ብዬ ደስ አይለኝም” መጋቢት 23፤ 1888 ምኒልክ ለአውሮጳዊው ዲፕሎማት ሙሴ ሸፍኔ ከላኩት፡፡

ምርኮኞችን ሲመልሱ፡-

“… በእጄ ጨብጫቸው፤ በእግሬ ረግጫቸው የነበሩትን እኒህን ምርኮኞች ሳልነካቸው የሰደድኩልህ … በሞኝነት አይደለም፡፡ … ብትታረቁ ድንቅ፤ ጦርነትም ከከጀላችሁ እነዚህንም ጨምራችሁ ኑ፡፡”
ስለዚህ የምኒልክን ውርስ እያስታወስን እንዲህ እንላለን:-

ምኒልክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ አበሻ።
በሠራው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ
ተፈጠመ ጣሊያን አበሻ እንዳይደርስ።

 ምንጭ: ጎልጉል ጋዜጣ

Saturday, December 7, 2013

የችግሮቻችን የመፍትሔ ቁልፍ – ወያኔን አስወግዶ ፍትህን ማስፈን

አሁንም በሳውዲ አረቢያ እና አካባቢው አገሮች የሚገኙ ወገኖቻችን የድረሱን ጥሪዎች እያሰሙ ነው። የወገኖቻችን ዋይታና ሰቆቃ አልበረደም። ዛሬም እህቶቻን እየተደፈሩ፣ እየተዋረዱ፣ እየተገደሉ ናቸው። በጥጋብ አገር ውስጥ ሆነው ኢትዮጵያዊያን ሕፃናት በረሀብና በጥም እየሞቱ ነው። በርካታ ኢትዮጵያዊያን ለከፋ የአዕምሮ ህመም እየተዳረጉ ነው።

በተለያዩ የዓለም አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኙ ወገኖቻቸውን ሕመም እየታመሙ፤ ስቃያቸውን እየተሰቃዩ ይገኛሉ። አስቸኳይ እርዳታ ለማድረስም አቅማቸው የቻለውን ሁሉ ለማድረግ በመረባረብ ላይ ናቸው።

ባለፉት ጥቂት ሣምንታት ኢትዮጵያዊያን ባደረጓቸው ብርቱ ጥረቶች ጥቂት አበረታች ውጤቶች ተገኝተዋል። ከደረሰባቸው የመብት ረገጣ ጋር ፈጽሞ ተመጣጣኝ ባይሆንም ቢቢሲን ጨምሮ አንዳንድ የዓለም ዓቀፍ የዜና አውታሮች በወገኖቻችን ላይ ስለሚደርሰው በደል እንዲዘግቡ ማድረግ ተችሏል። እስካሁን ምን ያህል ወገኖቻችን እድሉን እንዳገኙ ማረጋገጥ ባይቻልም የሳውዲ መንግሥት ሙሉ የትራንስፓርት ወጪ ችሎ ወገኖቻችን ማጓጓዝ ጀምሯል። ዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅቶች ለኢትዮጵያዊያን መብት መከራከር ጀምረዋል።

በአንፃሩ ግን አሁንም ሕሊናን የሚረብሹ ነገሮች እየተሰሙ ነው።

1. ከሳውዲ እየታፈሱ የመን ድንበር ላይ የተጣሉ፤ የደረሱበት የማይታወቁ ኢትዮጵያን ቁጥር በየእለቱ እየጨመረ ነው። እነዚህ ወገኖቻችን በየመን በረሀ ላይ የሚደርስባቸው ሰቆቃ ሳውዲ ውስጥ ከነበረው የባሰ ነው።

2. አሁንም በሳውዲ ተደብቀው የሚገኙ፤ “እጃቸውን ለመንግሥት ሰጥተው” እንደ ወንጀለኛ በእስር ቤቶች የሚማቅቁ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሉ። እነዚህ ወገኖቻችን ያሉበት ሁኔታ ሕሊና ሊሸከመው ከሚችል በላይ ነው።
ከዚህ ሁሉ በላይ ኢትዮጵያዊያንን እየረበሸ ያለው የወያኔ ባህርይ ነው።

ወያኔ በእንዲህ ዓይነት የመከራ ወቅትም በወገኖቻችን ላይ ዘርፈ ብዙ ንግድ እያጧጧፈ ነው። በሳውዲ አረቢያ መንግሥት ወጪ የተመለሰሉትን ወገኖቻችን ለምርጫ ቅሰቀሳ ፕሮፖጋንዳ ሥራ እየተጠቀሙባቸው መሆኑ ሳያንስ ለእለት ጉርስ የሚሰጣቸው የእርዳታ ገንዘብ በወያኔ እየተዘረፉ ነው። ገንዘብ ባለበት ሁሉ ወያኔ አለ። ወያኔ ለተመላሽ ስደተኞች የእለት ጉርስ የተሰጠውንም እርዳታ እየቀማ የሚበላ እኩይ ኃይል ነው።

ድሆች ኢትዮጵያዊያን ወደ አረብ አገራት ሲሰደዱ ለወያኔ ድርጅቶች ገንዘብ ከፍለው ነው። እዚያ በነበሩበት ጊዜም ለወያኔ ገንዘብ እንዲከፍሉ ይደረግ ነበር። በግፍ ተፈናቅለው፤ ሀብታቸው ተዘርፎ ባዶ እጃቸውን ሲመለሱም ለወያኔ የእርዳታ ገንዘብ መለመኛ ሆነዋል። ወያኔ በድሆች ኢትዮጵያዊያን ድህነት የሚከብር በታሪካችን ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ስግብግብ ነው። ወያኔ ኢትዮጵያዊያን ፈጽሞ ሊጠየፉት የሚገባ ነው ስብስብ ነው።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በችግር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን ከመርዳት ጎን ዓይኖቻችንን ከወያኔ እንዳንነቅል በአጽንዖት ያሳስባል። ወያኔ ከሥልጣን ሳይወገድ ችግሮቻችንን መፍታት አንችልም። የኢትዮጵያዊያን ችግሮች ለወያኔ የገቢ ምንጮች ናቸና ወያኔ እስካለ ድረስ ችግሮችን መፍጠሩና ማስፋፋቱ አይቀርም።

የኛ የኢትዮጵያዊያን ችግሮች የመፍትሔ ቁልፍ ያለው ወያኔን በማስወገድ ፍትሀዊ አመራር ማስፈን ላይ በመሆኑ የጋራ ትኩረታችን እዚያ ላይ እንዲሆን ግንቦት 7 ያሳስባል።

 ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ኔልሰን ማንዴላ በሕይወት ቢለዩንም በመንፈስ አብረውን ይቆያሉ

በአፓርታይድ የደቡብ አፍሪቃ መንግሥት ብቻ ሳይሆን በዩ. ኤስ. አሜሪካ ጭምር ሽብርተኛ ተብለው ሲሳደዱ፣ ሲታሰሩና ሲሰቃዩ የሕይወታቸውን አጋማሽ የጨረሱ፤ በመሣሪያ የታገዘ አመጽንና ሕዝባዊ እምቢተኝነትን አጣምሮ የያዘ ሁለ-ገብ ትግል በመምራት ለአፓርታይድ አገዛዝ ማብቃት ከፍተኛ ድርሻ ያለው የትግል አስተዋጽዖ ያደረጉ፤ ለመላው ዓለም የነፃነት ታጋዮች አርአያ የሆኑት ኔልሰን ማንዴላ አረፉ።

ኔልሰን ማንዴላ የነፃነት ትግልን በግንባር በመሰለፍ መርተዋል። ኢትዮጵያ ድረስ በመምጣት ወታደራዊ ሥልጠና ወስደው ዘረኛዉን የፕሪቶሪያ አገዛዝ በመሣሪያ ታግለዋል። የእሳቸው ጠመንጃ ማንሳት ለበርካታ ወጣት ታጋዮች አርዓያ ሆኗል። እስር ቤት በቆዩባቸው 27 ዓመታት ደግሞ የድርጅታቸውንና የትግሉን አመራሩ ለጓዶቻቸው በመተው እርሳቸው ለነፃነትና ለእኩልነት በመታሰርና ስቃይን በመቀበል ትግሉን መርተዋል። በዚህም ምክንያት በትግል ሜዳም በእስር ቤትም መሪ እንደሆኑ የዘለቁ ታላቅ አፍሪቃዊ ናቸው።

ከነፃነት በኋላ ደግሞ ኔልሰን ማንዴላ በሕዝብ ነፃ ፈቃድ የተመረጡ የአዲሲቷ ደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያ ፕሬዚዳንትነት ሆነዋል። በየምርጫው ተወዳድሬ አሸንፌ በፕሬዚዳንትነት ልቀጥል ሳይሉ በአፍሪቃ ባልተለመደ ሁኔታም አንድ ዙር ብቻ አገልግለው ደግመው ላለመወዳደር ወስነው በጊዜ ሥልጣናቸውን በመልቀቅ መርተዋል። በመሆኑም ኔልሰን ማንዴላ ሥልጣን ላይ ሆነውም ሥልጣን ለቅቀውም መሪ መሆን የቻሉ ድንቅ አፍሪቃዊ ናቸው።

ኔልሰን ማንዴላ ታላቅ የነፃነት አርበኛ፣ ታላቅ የለውጥ አራማጅ፣ ታላቅ መምህር እና ታላቅ የእርቅ ሰው ነበሩ። ዛሬ ዓለም እኚህን ታላቅ አፍሪቃዊ አጣች።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በኔልሰን ማንዴላ ሕልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ይገልፃል። ከእንግዲህ ማንዴላን የምናስባቸው ከእሳቸው ተሞክሮ የምንማረው ሲኖር ነው። በዘረኝነት እየተጠቃን ላለነው ኢትዮጵያዊያን የማንዴላ ትምህርት ሕያው ሊሆን ይገባል።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ዘረኝነትን በጽናት የመታገል ሆኖም ግን ይቅር ባይ የመሆንን እሴቶች ተግባራዊ በማድረግ ማንዴላ በሕይወት ቢለዩንም በመንፈስ ሁሌም አብረውን እንዲኖሩ እናድርግ ይላል።

የግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ህዝብ ግንኙነት

Thursday, December 5, 2013

የካርቱም ድራማ

በኣብርሃ ደስታ

(ከካርቱም የተላከልኝ መረጃ ነው፤ እንዳለ ለጥፌዋለሁ።)

ትላንት ማክሰኞ (ህዳር 24, 2006 ዓም) በኢትዮጵያ ስዓት አቖጣጠር ልክ ከ10:00ጀምሮ ለተለያዩ የማህበራት አመራሮችና እድሮች ዛሬ ሮብ ለሚደረግ ስብሰባ ሰዉ እንዲጠሩ መልዕኽት ተላለፈ። መልዕክቱ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለች የሚመሩትና ሌሎች ሚንስትሮች የሚገኙበት በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ5:00 የሚጀመር ስብሰባስላል ከየማህብራችሁ 200 ሰዉ እንድትጋብዙ የሚል በስልክ መደወል ተጀመረ።

በተሰጠዉ መምሪያ መሰረት ሁሉም አመራሮች ወደ አባሎቻቸዉ መደወል ያዙ። በአካል ያገኙትም ለሌላዉ እንዲናገር ወሬው ድፍን ካርቱም እንዲዳረስ አደረጉ። የሚገርመዉ ከሃይለማሪያም ደሳለኝ ውጭ ሌሎች ሚኒስትሮች ከባለፈዉ ዓርብ ጀምሮ መግባት ጀምረዋል። እስከ ትላንትና ቀን ሁሉም በየመጡበት ፊና የተለያዩ ስራዎች ሲያከናዉኑ ቆይተዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደግሞ ትላንት ማክሰኞ ምሽት ላይ ካርቱም ገቡ። አይነጋ የለ ለሊቱ ነጋ። በካርቱም የሚገኙው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ስትገባ የመጀመሪያዉ በር ስታልፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ/ማህበረሰብ/ ሬስቶራንት አለ ከዛ አልፎ ሌላ ሁለተኛ በር ልዩ ፍተሻ የሚደረግበት አልፎ ኤምባሲዉ ትገባለህ።

በዚህ መስረት ስብሰባዉ ዛሬ ሮብ ይደረጋል ተብሎ የኮሚኒቲዉ ሰራተኞች ሁሉም ከጥዋቱ 2:00 ስራ ገብተዉ ግቢዉን ሲያፀዱ ዉለዉ ረፋድ ላይ በኢትዮጵያ ስዓት አቆጣጠር 6:00 ዛሬ ስራ ስለሌለ ወደ ቤታችሁ ሂዱ ተባሉ። ጊዜዉ እየገፋ ነዉ ስዓቱ እየተቃረበ ነዉ። ስብሰባዉ በማህበረሰቡ ውስጥ በሚገኙዉ መናፈሻ ይደረጋል ተብሎ ሲጠበቅ ነበር። ምክንያቱ ሁሌም የተለያዩ ፖለቲካዊ ና ሃይማኖታዊ በዓላት የሚደረጉት በዚሁ አከባቢ ነበር። ዛሬ ግን ሌላ ነገር ተደረገ። ለታዳሚዉ የሚሆኑ ወንበሮች በኤምባሲው ግቢ ዉስጥ በለችሁ ትንሽ ሚዳና ዛፎች ስር ተደረደሩ። ስዓቱ ገፋ ኤምባሲዉ ውስጥ የሚገኙ ሰራተኞ ከዉትረዉ ለየት ባለ አለባበስ ግማሾች ሱፍ በከራቫታ ግማሾቹ ደግሞ ነጭ ቲሸርት በክራቫታ ለብሰዉ ውር ውር ማለት ጀመሩ። የደህንነት ሰዎች ግቢዉን ሁሉ መመርመር ጀመሩ። የተወሰኑ የፀጥታ ሰዎች ከተመደቡ በኋላ ልክ በኢትዮጵያ ስዓት አቆጣጠር 10:30 ወደ ውስጥ መግባት ተጀመረ። ህዝቡ ቀስ ያለ መምጣት ጀመረ።

ኤምባሲዉም ሆነ የኮሚኒቲ ሬስቶራንቱ በሱዳን ፖሊሶች ተከቧል። የመጀመሪያዉ በር ፍተሻ ላይ ሰዉ በማህበሩ ወይ በእድሩ እየተጠየቀ ሞቫይሉን በትልቅ ፌስታል ዉስጥ በማስቀመጥ ተፈትሾ ባዶ እጁን ወደ ግቢዉን ይገባል። ከዛም በተጨማሪ የኤምባሲዉ መግቢያ ሁለተኛ በር ጋር ድጋሜ ተፈትሾ ወደ ውስጥ ይገባል። በስተግራ ወደ ተዘጋጁት ወንበሮች ሁሉ ገብቶ ቦታ ቦታዉን መያዝ ይጀምራል። እንድህ እንዲህ እየተባለ እስከ 12:00 በኢትዮጵያ አቆጣጠር ሁሉም ገብቶ ቁጭ ይላል። ሌላዉ የሚገርመዉ ትዕይንት ደግሞ የገዛ ኢምባሲያችን ህንፃ ላይ ታራ ፖሊሶች ወጥተዉ አከባቢዉን እየቃኙ ጠበቃዉን ተያይዘዉታል። በተጨማሪም በኤምባሲዉ ዙርያ በሚገኙት ህንፃዎች የተለያዩ ፖሊሶች ተመደቡ። በተለይ ከኤምባሲዉ አጠገቢ በሚገኝ ሲንድያን ሆቴል አከባቢ ትንሽ እንግዶች በመስኮት ወጣ ገባ ሲሉ በፖሊሶች አርፈዉ እንዲቀመጡ ተነገራቸዉና ተደበቁ።

Wednesday, December 4, 2013

Ethiopia urged to release jailed journalist

Rights group launches a global appeal for the release of journalist sentenced to 18 years on terrorism charges.


Rights group Amnesty International has issued a global appeal for the release from prison of an award-winning journalist in Ethiopia.

Amnesty on Wednesday said it was trying to raise awareness of the case of Eskinder Nega as part of a campaign called "Write for Rights."

Eskinder, in prison since 2011, is serving an 18-year sentence on terrorism charges.

Amnesty says the journalist was a "thorn in
the side of the Ethiopian authorities" for making speeches and writing articles critical of the government.

Eskinder's wife, Serkalem Fasil, who was arrested with him but later released, and who now lives in the US, said her husband was arrested for being a journalist and for repeatedly criticising the government.

Ethiopian government spokesman, Shimelis Kemal, said Eskinder was not convicted for his criticism of the government but because he was running a clandestine 'terrorist' organisation.


According to the Committee to Protect Journalists, Ethiopia has the second highest number of journalists imprisoned in Africa and is the eighth biggest jailer of journalists in the world.

Source: http://www.aljazeera.com

Monday, December 2, 2013

የወያኔ አገዛዝ በመልዕክተኞቹ በኩል ላቀረበው የ“እንደራደር” ጥያቄ ከግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ምላሽ

ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ የገነባዉ ሥርዓት በከፍተኛ ችግሮች የተወጠረ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የመሪው ሞት በወያኔ መሀል ያስከተለው ቀውስ፤ የሕዝብ ሁለገብ ትግል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበት መሄድ የፈጠረበት ስጋት እና ምርጫ በደረሰ ቁጥር የሚደርስበት ጭንቀት መጨመር ተደማምረው ውጥረቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ እያደረሱት መሆኑን የሚያሳዩ በቂ ምልክቶች አሉ። የእስካሁኑ ተሞክሮዓችን እንደሚያሳየው ወያኔ ውጥረት ሲበዛበትና መዉጪያና መግቢያዉ ሲጠፋዉ ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶችን “እንወያይ፣ እንደራደር” በማለት ለውጥረት ማስተንፈሻ ጊዜ የሚገዛ መሆኑን ነው። ሰሞኑን በወያኔ አገዛዝ መልዕክተኞች በኩል የደረሰንን “የእንደራደር” ጥያቄ ንቅናቄያችን በዋናነት ያየው ወያኔ እንደለመደው ድርድርን ለውጥረት ማስተንፈሻነት ለመጠቀም እየሞከረ መሆኑን ነው።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚመኘው ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በሰላማዊ መንገድ በሚደረግ ትግልና በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረጉ ዉይይቶች ቢመጣ የግንቦት 7 ምርጫ መሆኑን ንቅናቄያችን በተደጋጋሚ ግልጽ አድርጓል። ግንቦት 7ን ሁለገብ ትግል ውስጥ እንዲገባ ያስገደደው የወያኔ እምቢተኝነትና እብሪት ብቻ ነው።

የግንቦት 7 ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የሰሞኑ የወያኔ የእንደራደር መልዕክት እንደደረሰው በጉዳዩ ዙሪያ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያን ሕዝብ ባጠቃላይ እንጂ ግንቦት 7ን ብቻ የሚመለከት ጉዳይ እንዳልሆነ ከድምዳሜ ላይ ደርሷል። ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ከሚያደርገው ትግልና እየከፈለ ካለው መስዕዋትነት ጋር በቀጥታ ግንኙነት አለው። በመሆኑም፤ ለቀረበልን ጥያቄ ግልጽ መልስና፤ ድርድር ስለሚባለው ጉዳይም ያለንን አቋም ጉዳዩ በቀጥታ ለሚመለከተው የኢትዮጵያ ሕዝብና የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ሁሉ ለማቅረብ የሚያስችል ተጨማሪ አጋጣሚ አድርገን ወስደነዋል። በዚህም መሠረት ለቀረበልን ጥያቄ የሰጠነዉን መልስና አቋማችንን በድርጅታችን ድረ ገጽ ላይና በሌሎች መገናኛ ብዙሀን በኩል በይፋ ለመግለጽ ወስነናል።

በድርድር ስለሚመጣ ለውጥ ያለን የመርህ አመለካከት:

ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ እንዳደረግነው ድርጅታችን ከምሥረታው ጀምሮ የትግል ስልቱን ሲወስን እምነቱ አድርጎ የተነሳው ዴሞክራሲያዊ ለውጥ በሀገራችን በሰላማዊ መንገድና በድርድር ቢመጣ በእጅጉ የሚፈልገውና የሚመኘው መሆኑን ነው:: ድርጅታችንን ወደ ሁለንተናዊ ትግል የገፋው በመግቢያው ላይ እንደገለጽነው የወያኔ እብሪት ብቻ ነው:: የቀረበልን ምርጫ በባርነትና በውርደት መኖር ወይም ለነፃነት እየታገልን መሞት ቢሆን ኖሮ ንቅናቄያችን የሚመረጠው ምን ግዜም ለነፃነትና ለአገር አንድነት ታግሎ በክብር መሞት መሆኑን በተደጋጋሚ ለሕዝብ ግልጽ አድርገናል። ይህ የማይናወጥ አቋማችን ደግሞ ለይምሰል የተቀመጠ አቋም ሳይሆን ከልባችን የምናምንበትና ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ አባላቶቻችንን ያሰባሰብንበት አቋም ነው። ዛሬ በትግሉ ግንባር የምንንቀሳቀሰውና ወደ ግባችን የሚወስደንን ተጨባጭ እርምጃዎች እየወሰድን ያለነውም በዚሁ አቋማችን ዙሪያ ነዉ።

ይህ አቋማችንና እምነታችን በአንድ ላይ ጎን ለጎን የሚሄዱ ሁለት መርሆችን አጣምሮ የያዘ ነዉ። አንደኛው፣ ሂደትን በሚመለከት ሁሌም ለድርድር ክፍት መሆኑን የሚያመለክት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ፣ ይህ የድርድር ሂደት እንዲያው ለለበጣ የሚደረግ ሳይሆን ወደሚፈለገው ነጻነት በአነስተኛ መስዕዋትነት ሊያደርስ ይችል ከሆነ በሩን ላለመዝጋት እንጂ፣ በምንም አይነት ዋና ውጤቱን፤ ማለትም ኢትዮጵያን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሀገር ማድረግን፤ የሚቀይር ወይንም ከዚያ ያነሰ ውጤትን ለመቀበል መፍቀድን ፈጽሞ የማያመለክት መሆኑን ነው::

Sunday, December 1, 2013

‹‹ድኅረ ምርጫ 97 በኢትዮጵያ ያለው ዲሞክራሲያዊ ምህዳር ጠቧል›› አና ጐሜዝ፣ የአውሮፓ ኅብረት የፓርላማ አባል

ምርጫ 97ን ተከትሎ የአውሮፓ ኅብረትን የምርጫ ታዛቢ ቡድንን የመሩት አና ጐሜዝ ምርጫውን ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ በኢትዮጵያ መንግሥትና በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ላይ የሰላ ትችትና ወቀሳ በመሰንዘር ይታወቃሉ፡፡

ከዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ በ26ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያን፣ ፓስፊክ እና የአውሮፓ ኅብረት የጋራ የፓርላማ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ የመጡትን አና ጐሜዝን በዴሞክራሲ፣ በእስረኞች አያያዝ፣ በሰብአዊ መብት አጠባበቅ እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ነአምን አሸናፊ አነጋግሯቸዋል፡፡

ሪፖርተር፡- ምርጫ 97ን ተከትሎ በእርስዎና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ያለው ግንኙነት ጥሩ የማይባል ነው፡፡ በዚህ የተነሳ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ያቀረቡት የቪዛ ጥያቄ እንዴት ነበር? ቪዛ መስጠት ያለመፈለግ አልያም ሌላ ነገር አጋጥሞዎታል? 

አና ጐሜዝ፡- በፍጹም፡፡ ምንም ዓይነት ክልከላ ወይም እምቢታ አላስተናገድኩም፡፡ ለነገሩ የአውሮፓ ኅብረት የሰብአዊ መብተት ንኡስ ኮሚቴ ባለፈው ሐምሌ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ነበር፡፡ በዚያን ወቅት በአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ አምባሳደር እኔም መሄድ እፈልግ እንደሆን ጥያቄ አቀረበልኝ፡፡ እኔም መሄድ ብፈልግም ባልፈልግም ቪዛ አትሰጡኝ ምን ያደርጋል አልኩት፡፡ እርሱ ግን የለም እንሰጥሻለን አለኝ፡፡ እሺ ለአሁን የሥራ ባልደረቦቼ ይጓዙ የእኔ ጊዜው ሲደርስ አመለክታለሁ አልኩ፡፡ ስለዚህ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የአፍሪካ ፓስፊክ ካሪቢያንና የአውሮፓ ኅብረት ጥምር ስብሰባ ላይ ለመካፈል የቪዛ ጥያቄ አቀረብኩ፤ እነርሱም ያለምንም ቅድመ ሁኔታና ያለምንም ችግር ቪዛውን ሰጥተውኛል፡፡ በዚህም በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር በማለፋቸው የተለየ የፖለቲካ አተያይ እየተፈጠረ እንደሆነ የሚያሳይ ነገር ነው፡፡ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ለውጥ ለማምጣት ጥረት እያደረጉ እንደሆነም ተረድቻለሁ፡፡ በተለይ ሙስናን በመዋጋት የጀመሩት ዕርምጃ ከፍተኛ የሥርዓቱን ባለሥልጣናት ሳይቀር ወደ እስር ቤት አስገብዋል፡፡ ይህም መልካም ጅምር ነው፡፡

ነገር ግን በኢትዮጵያ ከፍ ያለ ለውጥ ማየት እሻለሁ፡፡ ይህ የእኔ ብቻ ፍላጐት አይደለም፣ የኢትዮጵያውያንም ጭምር እንጂ፡፡ እዚህ በመምጣቴ ከስብሰባው ጐን ለጐን ሌሎች ሰዎችን በማናገር ለውጡ በእንዴት ያለ ሒደት ላይ እንዳለ ለመመልከትም እሞክራለሁ፡፡

ሪፖርተር፡- የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድንን በመምራት በ1997 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ውስጥ ስለነበሩ የአገሪቱን የምርጫ የዲሞክራሲና ሰብአዊ መብትንና የመሳሰሉ ጉዳዮችን ያውቋቸዋል፡፡ አገሪቱ አሁን ያለችበትን ሁኔታ እንዴት ይገመግሙታል? 

አና ጐሜዝ፡- እንደሚመስለኝ ድኅረ ምርጫ 97 በኢትዮጵያ ያለው ዲሞክራሲያዊ  ምህዳር ጠቧል፡፡  ከምርጫ 97 በፊት ከነበረበት ገጽታ አንፃር ብሶበታል፡፡ ምርጫውን ተከትሎ እልቂቶችን አይተናል፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሲታሠሩ አይተናል፣ ለሲቪል ማኅበራት ምህዳሩ ሲጠብ አይተናል፡፡ እንደሚመስለኝ በበጐ አድራጐት ማኅበራት ላይ የወጣው ሕግ አሉታዊ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ አላግባብ ጥቅም ላይ ሲውል አስተውለናል፡፡ ሕጉ እጅግ የተለጠጠ ትርጓሜ እየተሰጠው የተለየ ሐሳብ ያላቸውንና የሚቃወሙ ግለሰቦችን ለማጥቃት አገልግሎት ላይ ለማዋል እየሞከረ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ የተነሳ ሁኔታው የባሰበት ነው፡፡