Saturday, November 28, 2015

ወያኔ ሰራሽ የርስበርስ ግጭት ደግሶችን እናምክን!!!

የወያኔ ስርዓት ኢትዮጵያ የተዋቀረችው በህዝብ ታሪካዊ አብሮነትና ተዛምዶ ላይ ሳይሆን የብሔር ብሔረሰብ ልዩነቶችን በማጥበቅና ልዩነትንም የርስበርስ ጥርጣሬና ግጭት ምንጭ እንዲሆን በማለም ነው። ልዩነት የግጭትና የጠብ ምንጭ እንዲሆን ተደርጎ ነው የተዋቀረውና ብፖለቲካ ደረጃ የተገፋው። አንዱ ብሔረሰብ ሌላው ብሔረሰብ ክልል ውስጥ ሲሆን ባዕድነት እንዲሰማውና እንዲሰጋ አንዱ አንዱን በጥርጣሬ እንዲመለከተው ተደርጎ ነው ሀያ አራት አመት ሙሉ የተገፋውና እየተገፋ ያለው።

ይህም ሆኖ በዘመነ ወያኔ በየቦታው የተከሰቱ የብሔር ሌብሔርሰብ ግጭቶች በሙሉ የተቀሰቀሱት በራሱ በመንግስት ባለስልጣኖች እንጂ መቼም ህዝብ ለሕዝብ ሆኖ አያውቅም። በተለያዩ የደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች አማሮችን ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ለማባረር የተወሰዱት ርምጃዎች ራሳቸው ሰለባዎቹ እንደሚናገሩት ለስቃይ የዳረጋቸው ነዋሪው ሕዝብ ሳይሆን ባለስልጣናቱ መሆናቸውን በግልጽ ሲናገሩ ሰምተናል።

በቤኒሻጉልና ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሰሞኑን ይፋ መሆኑ የተነገረው በአስቃቂ ሁኔታ ተገድለው ተቀብረው የተገኙ አማሮች አስከሬን መገኘቱ ታውቋል። ይህም ወያኔ ባስለጠናቸውና ባዘዛቸው ካድሬዎችና ባለስልጣኖች የተከወነ እንጂ በሕዝብ ተነሳሽነት የተፈጸመ አለመሆኑ የታወቀ ነው። ቀደም ሲል በመንግስት ደረጃ የተቀነባበረ አማሮችን የማፈናቀል ዘመቻ ተከታይ ስራ መሆኑን ለማወቅ ብዙ አዳጋች አይደለም። በወገኖቻችን ላይ በሚዘገንን መንገድ የተፈጸመው ግፍ ዘልቆ ይሰማናል:: ሊሰማንም የገባል። ቁጭታችንና ሀዘናችን ግን ወያኔ ወደሚፈልገው የሕዝብ ለሕዝብ ግጭት ምክንያት እንዳይሆን ከፍተኛ ትዕግስትና ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል።
ሰሞኑን በታሪክ ሊዘገብ ከሚችል ልዩነት ውጭ ባኗኗር በባህልና ቋንቋ የማይለያዩትን የሰሜን ኢትዮጵያ ህዝቦች ቅማንትና አማራ በሚል ለማጋጨት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ይህ ሰይጣናዊ አካሔድ በወያኔ የፖለቲካ ተንኮል እየተመራ እንዳለ የሚያሳዩ ብዙ መረጃዎች አሉ። የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ሁሉም ካላንዳች መድሎና ልዩነት ሀገሪቱ ላይ መብታቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ ሁሉም በየበኩላቸው የሚያደርጉትን ጥረትና ትግል እንደግፋለን። በህዝባችን መካከል ያሉት ግንኙነቶች ሊሆን የሚችለው እንዱ አንዱን የማገዝ እንጂ ርስበርስ የመጋጨትም ሆነ የመናቆር አይደለም።

ኢትዮጵያውያን ብሄርና ዘር ሳንለይ ይህንን የወያኔ ተንኮል ችግሩ ወደባሰ ደረጃ ሳይሄድ መቋቋምና ማክሸፍ ይጠበቅብናል። ይህ ታሪክነታችንና ታላቅ ሕዝብነታችንን የማይመጥን አሳፋሪ የወያኔ ፖለቲካ እንደሀገር እንዳያጠፋን ሁላችንም በንቃትና በቁርጠኝነት መቋቋም ይኖርብናል።

Wednesday, November 25, 2015

Famine in Ethiopia: Due to bad weather or policy Failure?

By: Asnake Demena

Twenty four years ago Meles Zenawi, the late Prime Minister of EPRDF was asked about his vision for Ethiopia and its people when he assumed power as head of the state after seventeen years of civil war. Meles declared that if his government remains in power, in ten years every Ethiopians will have at least three meals a day. He also anticipated that if his government remains in power from then onwards for twenty years, Ethiopians not only have three meals a day but also will have the luxury of choosing what to eat. More recently in 2011, the same Meles Zenawi said that “We have devised a plan which will enable us to produce surplus and be able to feed ourselves by 2015 without the need for food aid.”

A young boy waiting in front of his tukul for his mother as she arrives with a body of his 4-year old dead sister who died of malnutrition in Shashemene, Ethiopia: Source: NBC: & .Creeping famine-is-back-to-Ethiopia

Here we are now, after twenty four years of power monopoly by the EPRDF regime and five years later after the implementation of the so-called Growth and Transformation Plan, more than 11.3 million Ethiopians have nothing to eat let alone to choose what to eat. Arsi, Hararghe, Afar, Borena and Somali are the hardest hit areas of the latest famine in the country. Children are dying in the hands of their parents and suffering from famine related diseases. Nevertheless, the EPRDF regime has been blaming on bad weather particularly the El Niño for the recent brutal famine.

Even if the El Niño is partly attributed for drought in general, the famine we are witnessing toady, in Ethiopia is not the result of seasonal crop failure due to bad weather or natural calamity as the EPRDF regime would like us to believe. As a matter of fact, drought, climate variability and other natural calamities occur not only in Ethiopia, but also in any part of the world. However, drought does not necessarily result in famine. This implies that droughts are a normal component of Ethiopian life making famines inevitable unless the proper preventive measures are adopted. Hence, in examining the current famine in Ethiopia, I will stress the structural links between food shortage and the lack of good governance in general and the failure of policies and strategies in particular.

Fifty years ago, famine was simply understood as the result of food shortage due to seasonal crop failure or natural disasters. At that time, it was not difficult to understand the reasons for famine when poor technology and static economic systems hampered human beings from getting access to food, especially in the face of regional natural disasters. But today, natural forces and other climatic conditions cannot be responsible for famine causation as was the dominant mode of thinking five decades ago. So that it is logical to ask why famine is persist in Ethiopia in the ear of global surplus, high-technology early warning systems and “vibrant economic growth” in the country. Answering this question requires looking beyond technical factors, towards political explanations. This means that the real causes of famine in Ethiopia deeply rooted in the country’s history of civil war and repression. Therefore, analysis of the past and present famines in Ethiopia should focus on root causes of the problem, instead of seasonal symptoms.

“ረሃቡና ኢህአዴጋዊ እውነታዎች!” (ኤርሚያስ ለገሰ)

ህወሃት መራሹ መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ ረሃብ በተከሰተ ቁጥር የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ “የአየር ንብረት መዛባት” በሚል ውጫዊ ምክንያት ማላከኩ የተለመደ ሆኗል። ለአብነት ያህል የዛሬ ዘጠኝ አመት በኢትዮጵያ ረሃብ በተነሳ ወቅት “የሰሞኑ የረሃብ ፖለቲካ” በሚል ረዕስ የውስጥ ድርጀት ሰነድ ተዘጋጅቶ ነበር ደራሲው ጓድ መለስ ዜናዊ ነበሩ። በማስከተልም የፓርቲው ከፍተኛ ካድሬዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት ውይይት እንዲያደርጉበት ተደረገ። በዚህ ሰነድ ገፅ 6 ላይ የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ እንደሚከተለው ይገልጻል።

“ረሃቡ ከምን እንደሚመነጭ በትክክል ማስቀመጥ መፍትሄውን ለማስቀመጥ ወሳኝ ነው። የረሃቡ ቀጥተኛ ምንጭ ከአየር ንብረት መዛባት ጋር ተያይዞ የተከሰተው ድርቅ ነው። የአየር ንብረቱ መዛባትና ድርቁ እኛ ያልፈጠርነው ልናስተካክለው የማንችለው ነባራዊ ሃቅ ነው። በዚህ ነባራዊ ሁኔታ ማዕቀፍ ድርቁን ተቋቁመን ረሃቡን ለማስወገድ ያስቀመጥነው ስትራቴጂ ተዓምር ሰሪነቱ በንድፈ ሃሳብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በተግባር ተረጋግጧል። የረሃቡ ዋነና ምንጭም የአየር ንብረት መዛባትና ድርቅ ነባራዊ ሁኔታን መቋቋም ረሃብን ለማጥፋት የቀየስነው ስትራቴጂ በሚፈለገው ፍጥነት በሁሉም አካባቢዎችን ስላልተፈጸመ ነው” ይላል።

እስኪ ይታያችሁ! ከዛሬ ዘጠኝ አመት በፊት (በ 1999 ዓም) የድርቁ መንስዔ የአየር ንብረት መዛባት እንደሆነ ተነገረን። ከዚያ በፊትም ምንጩ ተመሳሳይ ነበር። አሁንማ ልማድ ሆኖብን በኢትዮጵያ ምድር በየሁለት አመቱ ረሃብ የሚከሰት ሲሆን ምንጩ የአየር ንብረት ለውጥ ሆኗል። በነገራችን ላይ በሃገራችን ላይ በተጠቀሰው አመት ድርቁ ወደረሃብ በመቀየሩ ምክንያት በርካታ ህጻናት እና እናቶች ሞተዋል። በአራቱም ማዕዘናት ዜጎች ቀዬአቸውን ለቀው ተሰደዋል። የተፈጠረው አስደንጋጭ ሁኔታ ከህሊና የሚጠፋ አልነበረም።

በዛን ወቅት “በምጥቁ መሪ!” አብዮታዊ አመራር ሰጪነት የተሰራው ወንጀል ዘመን ተሻጋሪና ነገ ከነገ ወዲያ ተጠያቂነትን የሚያመጣ ነው።

እንዲህ ነበር የሆነው፥

በኢትዮጵያ አዲስ ሚሊኒየም ዋዜማ የተከሰተው ድርቅ ወደረሃብ መሸገገሩን የሚያሳይ ረፖርቶች ከመላው ሃገሪቱ መሰማት ጀመሩ። የኢህአዴግ የፕሮፓጋንዳ ማሽን ከዛ አመት በፊት በነበሩት አራት አመታት ኢኮኖሚያችን በሁለት አህዝ አድጓል፥ ሚሊየነር አርሶ አደሮች መፍጠር ችለናል በሚል ቅኝት የሚመራ ስለነበረ ይህን መርዶ ለመቀበል አስቸጋሪ ሆነ። ረሃብን አስወግደናል ብለን ባወጅን ማግስት በረሃብ ተጠቅተን መገኘት በእርግጥም አሳፋሪ ነበር። የአመራርና የማስፈፀም አቅማችን፣ ምርጥ ልምዶች የማስፋት ስትራቴጂያችን ለአለም ተምሳሌት ሆኗል ባልን ጥቂት ቀናት ህዝቡ ረሃቡን መቋቋም አቅቶት እየተሰደደ መሆኑ መመልከት ፕሮፓጋንዳችን “ቢወቅጡት እምቦጭ” እንደሆነ የሚያመላክት ሆነ።

እንደ ተፈራው በዕልፍ አመቱ ዋዜማ የሰው ህይወት በየቦታው መውደቅ ጀመረ፥ ረሃቡን መቋቋም የማንችልበት ሁኔታ ግልፅ ሆኖ ወጣ። የመጀመሪያ ሰሞን እውነታውን አውገርግሮ ከማቅረብ ይልቅ ትክክለኛው መረጃ ተሰብስቦ ወደኢህእዴግ ቢሮ እንዲመጣ ልዩ ውሳኔ ተላለፈ። ለማመን በሚቸግር ሁኔታ የረሃቡ ዋነኛ ሰለባ ከሆኑት አካባቢዎች የሚመጣው መረጃ እጅግ አስፈሪና አስደንጋጭ ሆነ። ከሶማሊያ ጫፍ እስከ አብርሃ አጽብሃ የሚባል የትግራይ ቀበሌ ድረስ ህዝቡ የሚላስ የሚቀመስ ማጣቱ ታወቀ። የከፋ ረሃብ ያጋጠማቸው አካባቢዎች ልጆቻቸውን እየቀበሩ ቀዬአቸውን እየለቀቁ መሰደድ መጀመራቸው እሙን ሆነ።

በሚሊኒየሙ ዋዜማ የችጋሩ ዋነኛ ተጠቂ ከሆኑት አካባቢዎች የመጀመሪያው የሱማሌ ክልል ነበር። የሱማሌ ክልል ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ ጀምሮ ለስርዓቱ ተገዢ እንዳልሆነ በገሃድ የሚታወቅ እውነታ ነው። በዛ ላይ አካባቢው በጦርነት የሚታመስ መሆኑ የረሃብ አደጋው በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አደረገው። በወቅቱ የተፈጠረው ረሃብ በ10ሺዎች የሚጠጉ የቀንድ እና የጋማ ከብቶች መሞታቸው ታወቀ። ከ80 -100 የሚሆኑ ህጻናት በረሃቡ ምክንያት ህይወታቸው እንዳለፈ የሚያሳይ መረጃ የስም ዝርዝር ረፖርት ቀረበ።

ይህንን የሱማሊያ የረሃብ ሁኔታ የተቀበለው ጓድ በረከት ከ “ባለራዕዩ መሪ!” ጋር በመነጋገር አንድ ጠንካራ ትዕዛዝ ሰጠ። ጥብቁ ትዕዛዝ “ማንኛውም የሃገር ውስጥም ሆነ የውጭ ጋዜጠኛ፣ በመንግስት ክትትል የማይደረግበት በጎ አድርጎት ድርጀት (NGO) ወደሶማሊያ ዝር እንዳይል!” የሚል ነበር። እነሆ ላለፉት 10 አመታት የትኛውም የነጻ ፕሬስ ሆነ የውጭ ጋዜጠኛ ወደሶማሊያ ክልል ልሂድ ብሎ ጥያቄ ቢያቀርብ ኣይፈቀድለትም። ከጓድ በረከት ጋር የቅርብ ወዳጅነት የመሰረቱትም ቢሆን ፍቃድ አያገኙም። የተለያዩ ምክንያቶች እየተሰጣቸው ጥያቄዎች እንዲጥሉ ይደረጋል። በዚህ ምክንያት በሱማሊያ በረሃቡ የሞቱት ህጻናት ከሪፖርቱ ውጪ እንዲሆኑ ተደረገ። እስከ 100 የሚደርሱት ህውየታቸው ያለፉት ህጻናት ማህደር በኢህአዴግ ቢሮ ተቆለፈበት።

Sunday, November 22, 2015

CPJ Awards Zone9 Bloggers of Ethiopia: International Press Freedom Award

In April 2014, Ethiopian authorities arrested six bloggers affiliated with the Zone 9 collective. The bloggers–Abel Wabella, Atnaf Berhane, Mahlet Fantahun, Natnail Feleke, Zelalem Kibret, and Befekadu Hailu–were charged with terrorism.

The Zone 9 blogging collective was formed in May 2012 in response to the evisceration of the independent press and the narrowing of space for free expression. The name, “Zone 9,” is derived from the zones in Kality Prison, the main jail where Ethiopia’s political prisoners, including several journalists, are held. While Kality Prison is organized into eight different zones, the bloggers refer to the entire country as “Zone 9” because of Ethiopia’s lack of democratic freedoms, one of the bloggers told CPJ.

The collective is made up of nine bloggers–the six named above, and Soleyana S Gebremichael, Endalk Chala, and Jomanex Kasaye, all of whom are in exile. Soleyana has been charged in absentia.
In July 2015, weeks before U.S. President Barack Obama visited the country, Ethiopian authorities released Mahlet and Zelalem.

The Zone 9 bloggers were arrested along with three other journalists–editor Asmamaw Hailegeorgis and freelancers Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye, who were later released. The initial charges against the group included working with international human rights organizations and taking part in email encryption and digital security training. The group was subsequently charged with terrorism.
Since 2009, when Ethiopia’s anti-terror law was implemented, the government has used the sweeping legislation to imprison more than a dozen critical journalists, according to CPJ research. In 2012, blogger Eskinder Nega was sentenced to 18 years in prison and Woubshet Taye to 14 years, both on terrorism charges. CPJ’s 2014 prison census found that Ethiopia was the fourth worst jailer of journalists in the world, with at least 17 journalists behind bars. Ethiopia also ranked fourth on CPJ’s 2015 list of the 10 Most Censored Countries.

ፖለቲካ በደም አይጋባም – አርበኞች ግንቦት7 (ኢዲቶርያል)

ህዝባዊ ተቀባይነቱን ያጣው ወያኔ በሽፍትነት ዘመኑ ትግራይ ውስጥ ሲያደርግ እንደረነበረው ሁሉ፣ መንግስታዊ ስልጣኑን ከያዘም በሁዋላ መሰልጠን አቅቶትና እንደመንግስት ማሰብ ተስኖት፣ አገዛዜን ይቃወማሉ ብሎ የሚጠረጥራቸውን ዜጎች የቅርብ ቤተሰቦችና የሩቅ ዘመዶች ሳይቀር ማሰቃየት መጀመሩን ከአራቱም የአገራችን ማዕዘናት በየቀኑ የሚደርሱን ሪፖርቶች ያመለክታሉ።

በቅርቡ በአርባ ምንጭ ከተማ ለአገራቸው ነጻነት በገዛ ፈቃዳቸው ተነሳስተው ታሪካዊ ግዴታቸውን ለመወጣት በሞከሩ ወጣቶች ላይ የስርዓቱ ታማኝ ጥቂት የደህንነት ሃይሎች የወሰዱት እርምጃ ዘግናኝና ልብ የሚያቆስል ነው። ይህም አልበቃ ብሎ የተፈላጊ ወጣቶች መኖሪያ ቤቶች በታጠቁ የደህንነት ሃይሎች ተወረው ፍተሻ ተካሂዶባቸዋል:: እናቶች ህጻናት ልጆቻቸው ፊት “የተደበቁ ልጆቻችሁን አምጡ ” ተብለው መሳሪያ ተደቅኖባቸው፣ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ተፈጽሞባቸዋል።

በአገዛዙ ዘረኛና የተጨማለቀ ፖሊሲ ተማረው ተቃውሞአቸውን ለመግለጽ እርምጃ መውሰድ የጀመሩ የቴፒ ወጣቶችን ለማደን የተደረገው ሙከራ መክሸፉን ተከትሎ የፈደራል ፖሊስና መከላኪያ ሠራዊት በወላጆች ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ወስደዋል። ወጣት ሴቶች እና እናቶች ርህራሄ በጎደላቸው የስርዓቱ ታማኝ ወታደሮች ተደብድበዋል፣ ተደፍረዋል፣ ታስረዋል። በሰሜን ጎንደርም እንዲሁ መብታችን ይከበር ብለው በተነሱ ወጣት ቤተሰቦች ላይ የገዢው ሃይል ታማኞች ፣ ግድያና አስገድዶ መድፈር ፈጽመዋል። እህትማማች ሴቶች መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ እንዳሉ ተገድለዋል። በወታደሮች የተደፈሩ ሴቶች ቅስማቸው ተሰብሮ ወደ አደባባይ ለመውጣት እንኳ የማይችሉበት ደረጃ ደርሰዋል።

በመርአዊ ከተማ መኳንንት ጸጋዬ የተባሉ በሰላማዊ ትግል ስርዓቱን የሚቃወሙ ግለሰብ፣ በልጆቻቸውና በባለቤታቸው ፊት አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ተደብድበዋል፤ የልጆችን ስነልቦና በሚነካ መልኩም ሰዋዊ ክብራቸው እንዲዋረድ ተደርጓል።

በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ ድንበር የለውም፤ የወያኔን የበቀል ዱላ ያልቀመሰ፣ ማንነቱና ክብሩ ያልተዋረደ ህዝብ ማግኘት አይቻልም። በገዳዩ ስርዓት እየደረሰ ያለው ግፍ አንድ ጊዜ በሰሜን፣ ሌላ ጊዜ በደቡብ፣ ሌላ ጊዜ በምስራቅ እያለ ቀጥሎአል። የዚህ ፍጹማዊ የአፈና አገዛዝ ህልውና እንዲቀጥል እስከተፈቀደለት ድረስ ጭቆናው፣ መዋረዱ፣ መታሰሩና መሞቱ አይቆምም። የአገዛዙ ባህሪ እነዚህን ሰይጣናዊ ድርጊቶች ለመፈጸም እንጅ መልካም ነገር ለመፈጸም አያስችለውም።

ለነጻነት የሚደረገው ትግል በመሬት ላይ አድማሱን እያሰፋ በመጣ ቁጥር የጥቃቱ አይነትና መጠንም እየጨመረ እንደሚመጣ ስናስብ፣ ይህን ጥቃት የምናስቆምበት ወይም የምንቀንስበትን መንገድም መሻት ተገቢ ነው። ወያኔ በነጻነት ታጋይ ቤተሰቦች ላይ ጥቃቱን ሲፈጽም ከሚጠቅሳቸው ምክንያቶች መካከል አንዱ “ልጅህ ወይም ወንድምህ መንግሥታችንን ለመናድ ሌት ተቀን እየሰራ አንተ በሠላም ልትኖር አትችልም” የሚል ነው። ይህ ሁዋላ ቀር አስተሳሰብ ወያኔን ከሚመሩ ሰዎች የሚጠበቅ ቢሆንም፣ ፖለቲካ ወይም የነጻነት ጉዳይ በደም የሚወረስ ሳይሆን ከግለሰቦች ማንነት ጋር ተያያዞ የሚመጣ መሆኑን፣ ቀድም ብለው በሁለት ጎራ ለይተው ሲፋለሙ የነበሩ ወጣቶችን ታሪክ ማስታወስ በቂ ነው። ከአንድ ማህጸን የወጡ የአንድ እናት ልጆች የተለያዬ የፖለቲካ አመለካከት እንደሚይዙ ታሪካችን ብቻ ሳይሆን፣ የወያኔ ታሪክ ራሱ ምስክር ነው።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ በጅምላ በቤተሰብ ላይ የሚደርሰው ጥቃት፣ ከሁዋላ ቀርነትና ከግንዛቤ ማነስ የመጣ ነው ተብሎ የሚመጣ ብቻ ሳይሆን፣ ድርጊቱን ከሚፈጽሙት ሰዎች ስነልቦና ቀውስና የሁዋላ ታሪክ ጋር የሚያያዝ ነው። በንጹህ ዜጎች ላይ ጭካኔና ግፍ የሚፈጽሙ ሰዎች፣ የሰው ማንነት የሌላቸው፣ ከአስተዳደጋቸው ጀምሮ የተበላሹና ማህበረሰቡ “አይመጥኑም” ብሎ የተፋቸው ናቸው። አሁን በስልጣን ላይ ያሉና በህዝባችን ላይ የጭካኔ ዱላቸውን የሚያሳርፉ ገዢዎች የሁዋላ ታሪክ ቢጠና ከዚህ የተለየ እውነታ አይኖረውም።

ሌላው የወያኔ ስልት ደግሞ በአገር ውስጥ ያሉትን ብቻ ሳይሆን ከአገር ውጭ የሚንቀሳቀሱ የነጻነት ታጋዮችን ቤተሰቦችና ዘመዶች እየተከታተሉ ” እባካችሁ ዘመዶቻችሁ ከፖለቲካው እንዲርቁ አድርጉ፣ እንዲህ ካደረጋችሁ የምትፈልጉትን ነገር እናድርግላችሁዋለን፣ ለእነሱም የፈለጉትን ነገር እናደርግላችሁዋለን” በማለት ለመደለል መሞከራቸው ነው።

Sunday, November 15, 2015

በረሀብ ለተጠቁ ወገኖቻችን እንድረስላቸው !!!

በወቅታዊ ሁኔታ ላይ የአርበኞች ግንቦት 7 የአቋም መግለጫ


የኢትዮጵያ ሕዝብ ዳግም ለአስከፊ ረሀብና ችጋር ተጋልጧል፤ ስፋት ጥልቀቱ በ70ዎቹና 80ዎቹ ከነበሩት ጋር ይስተካከላል ተብሎ ተፈርቷል። ከአሁኑ ሰው በረሀብ መሞት መጀመሩ ከአራትና አምስት ወራት በኋላ የሚመጣውን አደጋ ከባድነት መገመት ያስችላል።
ለአስር ተከታታይ ዓመታት ከአስር በመቶ በላይ ዓመታዊ የኢኮኖሚ እድገት በማምጣት ዓለምን እየመራን ነው የሚለው ዓይን ያወጣ ውሸት፤ “ድህነትን ተረት እናደርጋለን” የሚለው ጉረኛ መፈክር፤ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ራድዮ “የህዳሴ ብስራቶች”፣ የአባይ ግድብና የከተማ ባቡር ግንባታ ዜናዎች ለኢትዮጵያዊው አርሶ አደር ቁርስ፣ ምሳና እራት አልሆኑም።

“አድገናል”፣ “ተመንድገናል”፣ “በምግብ ራሳችንን ችለናል” ሲል የከረመው የህወሓት አገዛዝ የረሀቡ ዜና አፈትልኮ ሲወጣ እና የዓለም መገናኛ ብዙሀን መነጋገሪያ ሲሆን የተራበውን ወገናችንን ለማብላት ከመሯሯጥ ይልቅ ተፈጥሮ ላይ ማላከኩን ተያይዞታል። ከዚህ አልፎ ዓመታዊ ድግሶቹ እና ለባለሥልጣናቱ የሚሰጡ ጥቅማጥቅሞች ጉዳይ ከረሀብ በላይ አሳሳቢ በመሆኑ 15 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ በሞት አፋፍ ላይ እያለ የአገሪቱ ሀብት ለድግስና ፈንጠዚያ እንዲሁም ለእያንዳንዱ ባለሥልጣን ቤተመንግሥት አከል መኖሪያ ቤት ማሠሪያ እየዋለ ነው። መቀሌ ላይ ህወሃት 40ኛ ልደቱን ለማክበር ወደ ግማሽ ቢልዮን ብር ባወጣ ማግስት በአማራ ስም ለወያኔ ባርነት የገባው ብአዴን 300 ሚሊዮን ወጪ በማድረግ በረሃብተኛው ሕዝብ አናት ላይ እየጨፈረ ነው:: ይህ የኢትዮጵያን ሕዝብ መናቅ ብቻ ሳይሆን ደግሞ ደጋግሞ ከመግደል የሚቆጠር ወንጀል ነው።

ለመሆኑ የአየር ንብረት መዛባት እየተደጋገመ ለሚመጣ ችጋርና ቸነፈር በቂ ምክንያት ሆኖ ያውቃልን? ለምንድነው ፍትህና ነፃነት በሰፈነባቸው አገሮች ውስጥ ዝናብ ጠፍቶ የእርሻ ምርት ቢቀንስ እንኳን ሰው በረሀብ የማይሞተው? አስከፊ የረሀብ ዜናዎች የሚሰማባቸው አገሮች በሙሉ ነፃነት የታፈነባቸው አገሮች መሆናቸውስ የአጋጣሚ ጉዳይ ነው? ለምንድነው ተደጋግሞ ከሚመጣ የረሀብ አዙሪት መውጣት ያቃተን?

የእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልስ አጭርና ቀጥተኛ ነው። ለችግሮች መፍትሄ መሻት የሚቻለው በነፃነት ማሰብ የሚችል ጭንቅላት ሲኖር ነው። በባርነት ጨለማ ውስጥ ያለ ጭንቅላት ለችግሮች መፍትሄ የማፍለቅ አቅም የለውም። እንዲያውም እንዲህ ዓይነቱ ድኩም ጭንቅላት ችግሮችን ማሸነፍ ሳይሆን ተሸናፊነትን ተቀብሎ ከችግሮች ጋር ተስማምቶና ተወዳጅቶ መኖርን ይመርጣል። ለዚህም ነው የአስተዳደር በደልና ረሀብ ምክንያትና ውጤት ብቻ ሳይሆን እጅና ጓንትም ጭምር የሆኑት።

ነፃነት ያለው ሕዝብ ረሀብን እንደሚያሸነፍ ተደጋግሞ የታየ ጉዳይ ነው። ለዚህም ነው ረሀብን የተፈጥሮ ሚዛን መዛባት ውጤት ብቻ አድርጎ ማቅረብ እውነትን መሸፈጥ የሚሆነው። ረሀብ የብልሹ አስተዳደር ውጤት መሆኑ ያፈጠጠ፣ ያገጠጠ ሀቅ ነው። ከረሀብ መገላገያ መንገድም የተበላሸ አስተዳደር ተወግዶ ኃላፊነት የሚሰማው፣ የዜጎች የማሰብ ነፃነት የሚያረጋግጥ ሕዝባዊ አስተዳደር ሲኖር ነው።

አገራችን ኢትዮጵያን የረሀብ ቀጠና ካደረጉ የ24 ዓመታት የወያኔ “የዘርፈህ ብላ” የኢኮኖሚ ፓሊሲ ውጤቶች መካከል አንዳንዱን ለአብነት ያህል መዘርዘር ይቻላል።

1. ገበሬና መሬት ተለያይተዋል። ኢትዮጵያዊያን አርሶ አደሮች መሬት አልባ ሆነዋል። ለም መሬቶች በኢንቨስትመንት ስም ለህወሓት ጉልተኞችና ምስለኔዎቻቸው ታድሏል፤ እነሱ ደግሞ በተራቸው ለባዕዳን ሽጠውታል። ኢትዮጵያዊው አርሶ አደር በሀገሩ ጭሰኝነት እንኳን አጥቶ ለቀን ሠራተኝነትና ልመና ተዳርጓል። በዚህም ምክንያት ገበሬው እንኳንስ ትልቁን የአየር መዛባት ትንሿንም የዋጋ ንረት መቋቋም እስከማይችልበት ደረጃ ተዳክሟል።

ረሃብና ፖለቲካ (የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)

አገራችን ኢትዮጵያ ምንም እንኳን ዛሬ በምጣኔ ሀብቷ፣ በፖለቲካዊና ማህበራዊ እድገቷ ከዓለም አገሮች በጠቅላላ ወደ ኋላ የቀረች ብትሆንም ቅሉ ጀማሪና ልዩ የሚያደርጓት ብዙ ታሪካዊ እሴቶችና የተፈጥሮ ችሮታዎች አሏት፡፡ የሰው ዘር መገኛና ነፃነቷን ጠብቃ የቆየች መሆኗ ልዩ ከሚያደርጓት ታሪካዊ እሴቶቿ መካከል ጎልተው የሚጠቀሱና ዓለም ሁሉ የሚያውቃቸው ናቸው፡፡ ቀደምት ህዝቧ ትቶት ያለፈው የኪነ-ህንፃ ረቂቅ ጥበብ እትም አሻራም ስሟን በውዳሴ እያስጠራ ዘመናትን አሻግሯታል፡፡

ኢትዮጵያ የናይል ሸለቆ ስልጣኔን ቀድማ በመጀመርና ለሌሎች በማስፋፋት የምጥቀትን ጮራ ለዓለም የፈነጠቀች የራሷ የቀን አቆጣጠር ያላት ብቸኛዋ አገር ናት፡፡ የተለያየ ቋንቋ ኃይማኖት፣ ወግና ልማድ ያለው ህዝቧ ተቻችሎና አንድነቱን ጠብቆ የሚኖርባት ጥበብ ምስጢርም በዓለም ህዝብ ዘንድ የሚያስወድሳት ነው፡፡ የአየር ንብረቷ ለሰዎች ኑሮና ለእፅዋት እድገት እጅግ ተስማሚ፤ መሬቷ ለምና ሰፊ፤ ጅረቶቿ ዕልፍና ረጃጅም፤ ሀይቆቿ ታላላቆች ናቸው፡፡

ነገር ግን ኢትዮጵያ ከኒጀር ቀጥላ ሁለተኛዋ የዓለማችን መናጢ ድሃ አገር በመሆን ስሟ በጥቁሩ የጉስቁልና እና የውርደት መዝገብ ላይ ሰፍሮ ይገኛል፡፡ ህዝቧ ደሙን አፍስሶ፣ አጥንቱን ከስክሶ፣ ዳር ድንበሯን ጠብቆና ሉአላዊነቷን አስከብሮ የአፍሪካ የነፃነት ፋና ወጊ፣ የጥቁር ህዝቦች አርነት ተምሳሌት ቢያደርጋትም እስካሁን ድረስ ውስጣዊ ነፃነቱን ሊጎናፀፍ ሳይችል ቀርቶ በገዛ ወገኞቹ እንደባሪያ ተቀጥቅጦ እየተገዛ ይገኛል፡፡

በተለይም ደግሞ ከ1983 ዓ.ም ወዲህ የህዝቧን ተቻችሎ የመኖር ጥበብ የሚሰልብ የአንድነት ቀበኛ የሆነ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን ከምድረ ገፅ ለማጥፋት በእጭር ታጥቆ ቀን ከሌሊት የሚተጋ አገዛዝ ጥሎባታል፡፡ ይህ ኢትዮጵያን ለረጅም ጊዚያት የተጣባት የፖለቲካ አደገኛ ደዌ ከዘመን ዘመን እየተሸጋገረ መጥቶ ዛሬ ላይ ህመሙ ጠንቶባት የአልጋ ቁራኛ አድርጓታል፡፡ ኢትዮጵያና ህዝቦቿ የገቡበት የፖለቲካ አዙሪት የእድቷ ዋነኛ ማነቆ ሆኖ አገሪቱ ከኮንጎ ቀጥላ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣ እየተገኘችና "የአፍሪካ የውሃ ማማ" ተብላ እየተጠራች በተደጋጋሚ ድርቅ ተመትታ ህዝቧ እንደ ቅጠል እንዲረግፍና የዓለማችን የችጋር ምሳሌና የለየላት ለማኝ እንድትሆን ጋብዟታል፡፡

ከብዙ ሺህ ዓመታት በፊት የተጀመረው በሰውና እንስሳት ጉልበት የሚካሄደው ኋላ ቀር የአስተራረስ ብሎም የማዝመርና የማምረት ባህል እስካሁን ድረስ ምንም ሳይቀየር ወይንም ሳይሻሻል ሙሉ በሙሉ እንዳለ በመቀጠል ዛሬ ላይ የደረሰው በአገሪቱ ብልሹ ፖለቲካ ደንዳና ጀርባ ታዝሎ ነው፡፡ አገሩ የአፍሪካ የውሃ ማማ እየተባለች የምትጠራው የኢትዮጵያ ገበሬ ለዘመናት ሰማይ ሰማዩን እያንጋጠጠ ሲያይ መኖሩ ህልውናው በደመና ላይ መመስረቱና ጠብታ ዝናብ እስትንፋሱ መሆኑ ደግሞ በዓለም አደባባይ ቅስማችንን እየሰበረ የሚገኝ ሌላኛው የብልሹው ፖለቲካ መጥፎ ገፅታ ነው፡፡

ኢትዮጵያ በዝናብ እጥረት በተደጋጋሚ ድርቅ ተደቁሳ ህዝቧ በረሃብ ሲረግፍ ግብፅ ከኢትዮጵያ እምብርት ፈልቆ የሚሄደውን የአባይ ውሃ ከኢትዮጵያ ድንግል መሬት እየተጠረገ የሚጓዘውን የለም አፈር ደለል እየተጠቀመች በምግብ ራሷን ከመቻል አልፋ መበልፀግ መቻሏ የብልሹ ፖለቲካው እንጂ የአገራችን ገበሬ ድክመት አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ገበሬማ ከቁራሽ መሬቱ ላይ የዕለት ጉርሱን ለማምረት ለዓንድ ዓመት ብቻ የሚያፈሰው የትየለሌ ጉልበት በዘመናዊ የእርሻ ቴክኖሎጂና ዕውቀት ቢደገፍ የትና የት በደረስን ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ገበሬ የውሃ ችግር የለበትም፤ የኢትዮጵያ ገበሬ የእርሻ መሬት ጥበት የለበትም፤ የኢትዮጵያ ገበሬ ዕውቀት ያለመቀበል የአቅም ችግር የለበትም፤ የኢትዮጵያ ገበሬ ኋላ ቀር ሆኖ አልተፈጠረም፣ የኢትዮጵያ ገበሬ ዘመናዊነትን አልሻም አላለም፤ የኢትዮጵያ ገበሬ ዘመናዊ የእርሻ ቴክኖሎጂን አልጠቀምም አላለም ወይንም ለመጠቀም የሚያስችል አቅም አያንሰውም፤ እሱማ ተፈጥሮ የሚባል የማይጋፋው ክፉ ባላጋራ ጥሎበት በረሃብ ይሞታል፣ እትብቱ ከተቀበረበት ቀዬው ተፈናቅሎ ይሰደዳል እንጂ ከአባቶቹ በወረሳት ባለችው ባህላዊ ዕውቀት አርሶ አንደፋርሶ ነጭና ቀይ አምርቶ እየጫነ ብቻውን ኢትዮጵያን እስከ ዛሬ ድረስ አቆይቷታል፡፡ የአሳ ግማቱ ከአናቱ እንዲሉ ችግሩ ያለው ከላይ ከመሪዎቹ ከብልሹው ፖለቲካ ዘዋሪዎቹ ከአንጋቾቹ ነው፡፡
ዘዋሪዎች ወይንም አንጋቾች ብልሹውን ፖለቲካ ችግር አስወልደው ችግሩ የፈጠረውንና የብልሹው ፖለቲካ የልጅ ልጅ የሆነውን ድርቅና ረሃብ መልሰው ለፖለቲካ ማምረቻ ፋብሪካቸው በግብአትነት ይጠቀሙበታል፡፡ በረሃቡ የረገፈውን ህዝብ ሬሳ በመቀጣጠል እንደመሰላል ተጠቅመው የስልጣን ማማ ላይ ቁብ ይላሉ፡፡ ለዚህ ሁለቱ አንጋቾች ደርግና ህወሓት ጥሩ አብነቶች ናቸው፡፡
1965 እና 66 ዓ.ም የሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል በድርቅ ወጀብ ክፉኛ ተመትቶ ልክ እንደ ዛሬው ህዝብ በረሃብ የተሸመደመደበት ክፉ ዘመን ነበር፡፡ በእርግጥ በተራበው ህዝብ ቁጥር ደረጃ ከተመለከትነው የዛሬው ይልቃል፡፡ በመሆኑም 4ኛ ክፍለ ጦር ግቢ ውስጥ ተወልዶ በእነ ሻለቃ አጥናፉ አባተና ሻለቃ መንግስቱ ኃይለ ማርያም የሚመራውና ራሱን ደርግ ብሎ የጠራው ሻለቃና ከሻለቃ በታች የሆኑ ዝቅተኛ መኮንኖች የተሰባሰቡበት የወታደሮች ቡድን ወይንም ኮሚቴ ስልጣን ላይ ለመውጣት አድፍጦ እያደባ የሚገኝበት ወቅት ስለነበር አጋጣሚውን ተጠቀመበት፡፡ በወቅቱ 225ኛው የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት የነበሩትን ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴን በቁጥጥሩ ስር አውሎ በጆናታን ድምቢልቢ ተቀርፆ የተቀነባበረውን በረሃብ እያለቀ የሚገኘውን ህዝብ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል የዘመን መለወጫ ዋዜማ ዕለት ምሽት በአገሪቱ የቴሌቪዥን ጣቢያ ለህዝብ አሰራጨው፡፡ የ1967 ዓመተ ምህረትን አዲስ ዓመት በአዲስ ተስፋ ለመቀበል ሽርጉድ ይል የነበረው መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ድንገት በቴሌቪዥን መስኮት በተመለከተው የወገኖቹ አሳዛኝ ዕልቂትና መከራ ልቡ ተሰብሮ ለአፍታ ተስፋው ካጠገቡ ሸሸው፡፡ ንጉሰ ነገስቱንም አምርሮ ጠልቷቸው ዓይናቸውን ለአፈር አላቸው፡፡ ለሺህዎች ዓመታት የዘለቀው የዘውድ ስርዓት በ225ኛው ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ስላሴ ተደምድሞ ዳግመኛ ላናየው ግብአተ መሬቱ ተፈፀመ፡፡

1977 ዓ.ም አንጋቾች ዙፋን ላይ ከወጡ ከ10 እና ከ11 ዓመታት በኋላ ድርቁና ረሃቡ አድማሱን አስፍቶ በአደገኛ ሁኔታ ተመልሶ መጣ፡፡ ይህ ዘመን ኢትዮጵያ ከአራቱም ማዕዘን በተቀሰቀሰ የእርስበርስ ጦርነት እየታመሰችና ምጣኔ ሀብቷ ክፉኛ እየተሽመደመደ የሚገኝበት ስለነበር ድርቁንና ረሃቡን ፈፅሞ ትከሻዋ መሸከም ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሳ ነበር፡፡

Tuesday, November 10, 2015

They can jail the journalist but not journalism

On November 7, 2015, journalist Serkalem Fasil posted a Facebook reminder. It was her husband’s birthday. “Four years and two months have passed since we physically separated,” she wrote.
“No matter how long it takes, I will persevere and will never give up hope with the help of Almighty God,’” she promised to her husband. Sentenced to 18 years in jail on trumped-up terrorism charges in Ethiopia, Eskinder Nega cannot read the note from his beloved wife.

The couple have been through hell together that she certainly feels his presence and unbreakable spirit is with her at all times.

When Serkalem met Eskinder nearly two decades ago, she could not have predicted the trials and tribulations awaiting them along their ways.

Eskinder is now serving 18 years behind bars for using pen and paper and sharing powerful stories and his thoughts with his people.


Theirs is a touching story of true love that has endured constant threats, attacks, prison, torture and exile spanning almost two decades. Serkalem leads a challenging life as an exiled “single mom” in Alexandria, Virginia, with their nine-year old son Nafkot, who was condemned to be born in jail.
Her husband is languishing in Kaliti jail, which he referred to as “Gulag” in a New York Times op-ed that he penned two years ago. After that article was published and exposed the harsh realities behind bars, he has been banned from having access to his lethal weapons, pen and paper. He is not allowed to read anything–even his Bible, which was confiscated by prison guards.

Charged with treason and “genocide”, Serkalem and Eskinder were among a group of journalists falsely accused of causing turmoil during the 2005 national election. Unprepared to accept any electoral defeats , the late Meles Zenawi declared a state of emergency and took personal control of the armed forces. Security forces massacred hundreds of unarmed peaceful protesters and injured almost 800 others. Scores of opposition leaders, journalists, human rights activists and civic leaders, along with some 30 thousand suspected supporters of opposition parties, were also jailed.
They languished in vermin-ridden jails, where their son Nafkot was born. Serkalem was denied prenatal care in prison under the orders of Meles Zenawi. The couple were released after 18 months behind bars with the condition that they “never write, never publish and never speak out against injustice”.

Thursday, November 5, 2015

ረሃብ የመንግሰት ፖሊሲ ብልሹነት እንጂ የዝናብ እጥረት ዉጤት አይደለም!

ኤፍሬም ማዴቦ- ከአርበኞች መንደር !!

ደርግ የቀዳማዊ ኃ/ሥላሤን ስርዐት ከደመሰሰ በኋላ ወሎ፤ ትግራይና ሰሜን ሸዋ ዉስጥ ህዝብ እንደ ቅጠል ሲረግፍ እሳቸዉ የልደት በዐላቸዉን ለማክበር ከዉጭ አገር ኬክ ያስመጣሉ ብሎ ነበር ንጉሰ ነገስቱንና ስርዐታቸዉን የከሰሰዉ። በአስራ ሰባቱ የደርግ ዘመን ሁለት ግዜ ከባድ ረሃብ ተነስቶ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻችን አልቀዋል። በተለይ በ1977 ዓም ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ የተከሰተዉና የአለምን ህዝብ ያስደነገጠዉ ረሃብ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያንን እንደ ቅጠል ሲያረግፍ ደርግ የስብሰባ አዳራሽ ለመስራትና የኢሠፓን ምስረታ ለማክበር ብዙ ሚሊዮን ዶላር እንዳባከነ ይታወሳል። ህወሃት የደርግን ስርዐት ሲዋጋ የኢትዮጵያን ህዘብ ከጎኑ ለማሰለፍ ከተጠቀመባቸዉ ዋና ዋና የፕሮፓጋንዳ ስራዎች ዉስጥ አንዱ ይህንኑ ረሃብ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻቸንን ሲገድል ደርግና ባለሟሎቹ የፓርቲ ምስረታ ለማክበርና አዳራሽ ለማሰራት በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ያባክናሉ የሚል ፕሮፓጋንዳ ነበር። ከዚህ በተጨማሪ በአገሪቱ ዉስጥ ለደረሰዉ ረሃብ ዋናዉ ምክንያት የዝናብ እጥረት ሳይሆን የደርግ የተበላሸ የኤኮኖሚና የፖለቲካ ፖሊሲ ነዉ ብሎ ደጋግሞ ደርግን መክሰሱ አይረሳም። ህወሃት ኢትዮጵያን በመራባቸዉ ባለፉት ሃያ አራት አመታት ዉስጥ የዘንድሮዉን ጨምሮ የኢትዮጵያ ህዝብ ሦስት ግዜ ለረሃብ አደጋ ተጋልጧል። የዘንድሮዉ ረሃብ ደግሞ ስፋቱና ጥልቀቱ እጅግ በጣም አደገኛ መሆኑ በአለም አቀፍ የመገናኛ አዉታሮች እየተነገረ ነዉ።

ዛሬ ኢትዮጵያ በየአመቱ ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ የዉጭ ዕርዳታ ታገኛለች፤ በየአመቱ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ትበደራለች፤ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የዉጭ ምንዛሪ በዉጭ አገር ከሚገኙ ዜጎቿ ታገኛለች። ኢትዮጵያ ዉስጥ ከፍተኛ የልማት ሰራዎች እንደሚሰሩ ይነገራል። ግድቦች፤ መንገዶች፤ ህንጻዎችና የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ይገነባሉ እየተባለ ይነገራል። የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ በአመት ከ10% በላይ እንደሚያድግ ይነገራል። ይህ ሁሉ ሆኖ ረሃብ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያንን ህይወት አደጋ ላይ ጥሏል። ለምን? ከህወሃት በፊት የነበሩት ሁለት መንግስታት በስልጣን ላይ በነበሩበት ግዜ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለደረሰዉ ረሃብና በረሃብ ላለቁ ወገኖቻችን ተጠያቂዎች ነበሩ። ደርግና የቀዳማዊ ኃ/ሥላሤ ስርዐት የተከተሏቸዉ ብልሹ የሆኑ የኤኮኖሚ ፖሊሲዎችና ጎታች የመሬት ይዞታ አስተዳደር በሁለቱ ስርዐቶች ዉስጥ ለደረሰዉ ረሃብ አይነተኛ ምክንያቶች ነበሩ። ዛሬስ የሃያ ሚሊዮን ወገኖቻችንን ህይወት አደጋ ላይ ለጣለዉ ረሃብ ምክንያቱ ምንድነዉ? ተጠያቂዉስ ማነዉ? በነገራችን ላይ ህወሃት ሠላም አነገስኩባት በሚለዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ ረሃብተኛ ቁጥር ላለፉት አምስት አመታት በእርስ በርስ ጦርነት በምትታመሰዉ ሦሪያ ዉስጥ ካለዉ ረሃብተኛ ቁጥር ይበልጣል።

የቀድሞዉ የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስቴር አቶ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ህዝብ በአጭር ግዜ ዉስጥ በቀን ሦስት ግዜ የመብላት ዋስትና ይኖረዋል ብለዉ ባዶ ተስፋ ከቀለቡን በኋላ የዘንድሮዉን አመት ጨምሮ እኛ ትዮጵያዉያን ሦስት ግዜ የረሃብ አደጋ ላይ ወድቀናል። ለመሆኑ ምን ይሆን ባለ ራዕዩ መሪ ያዩልን ራዕይ? በቀን ሦስት ግዜ መብላታችንን ወይስ ረሃብ ሦስት ግዜ እንደሚጎበኘን? ከአንድ አመት በፊት ክረምቱ መገባደጃ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኢትዮጵያ ዉስጥ 6.5 ሚሊዮን ህዝብ የረሃብ አደጋ ይጠብቀዋል ብሎ ባስጠነቀቀ ማግስት ጠ/ሚ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ኢትዮጵያ በምግብ ምርት እራሷን የቻለች አገር ሆናለች ብለዉ ለአለም አወጁ። እንደ ፈረንጆቹ ዘመን አቆጣጠር በሰኔ 2015 ዓም እኚሁ ሰዉ ኢትዮጵያ ረሃብን በግማሽ እንደምትቀንስና በአመቱ ማለቂያ ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረሃብ የሚጋለጠዉ ህዝብ ከ5% በታች እንደሚሆን አረጋገጡ። በተመድና በብዙ ለጋሽ አገሮች ጥናት መሠረት በ2015 ማለቂያ ላይ ከኢትዮጵያ ህዝብ 21% የሚሆነዉ አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ካላገኘ ከፍተኛ አደጋ ይጠብቀዋል። ለምንድነዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ መሪ ነን ተብዬዎች የኢትዮጵያን ህዝብ የማይጨበጥ ባዶ ተስፋ የሚቀልቡት? ለምንድነዉ ፈጣኑና ታዳጊዉ የአፍሪካ ኤኮኖሚ ለዜጎቹ የስራ ዕድል መፍጠር ተስኖት ወጣት ኢትዮጵያዉያን አገራቸዉን እየጣሉ የሚሰደዱት? ለምንድነዉ በቀን ሦስቴ ትበላላችሁ ተብለን አንዱም ያረረብን? ለምንድነዉ በምግብ እህል እራሳችንን ችለናል ተብሎ ተነግሮን መንፈቅ ሳይሞላ ረሃብ የሚጨፈጭፈን? ለምንድነዉ? . . . ለምንድነዉ? . . . ለምንድነዉ?

በቅርቡ CNN እና ኒዮርክ ታይምስን ጨምሮ አያሌ ታዋቂ የአለማችን መገናኛ አዉታሮች ኢትዮጵያ ዉስጥ እየመጣ ያለዉን አስፈሪ የድርቅ አደጋ መዘገብ ሲጀምሩ ጠ/ሚ ኃ/ማርያም ደሳለኝ ድርቅ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አዉስትራሊያንና አሜሪካንን ጭምር እንዳስቸገረ ገልጸዉ ነበር። ይባስ ብለዉም “ኤልኒኖ” የተባለዉን የተፈጥሮ ክስተት ኢትዮጵያ ዉስጥ ለተከሰተዉ ድርቅ ተጠያቂ አድርገዋል። የሚገርመዉ ጠ/ሚ ኃ/ማሪያም ደሳለኝና መንግስታቸዉ ዛሬ ምግብ ካልሰጣችሁን በረሃብ ልናልቅ ነዉ እያሉ የሚወተዉቱት እንደ ኢትዮጵያ እነሱንም ድርቅ መቷቸዋል ያሉትን አሜሪካንና አዉስትራሊያን ነዉ። በነገራችን ላይ ጠ/ሚ ኃ/ማርያም ደሳለኝ ትክክል ናቸዉ – ድርቅ ኢትዮጵያ ዉስጥ እንደገባ ሁሉ አሜሪካና አዉስትራሊያ ዉስጥም ገብቷል፤ ኤልኒኖም ኢትዮጵያ ዉስጥ በተከሰተዉ የአየር ጸባይ መዛባት ላይ ተፅዕኖ ነበረዉ። ሆኖም እሳቸዉ ስራ ስለሚበዛባቸዉ ረስተዉ ሳይጠቅሱት ቀረ እንጂ ድርቅ ጎረቤት አገር ኬንያ፤ ሱዳንና ኤርትራ ዉስጥም ገብቷል። ጠ/ሚኒስትሩ የኮነኑት ኤልኒኖም ቢሆን ኤርትራንና ኬንያን ዘልሎ ኢትዮጵያ ዉስጥ ብቻ አልመጣም። ድርቅ ማለት ደግሞ ሌላ ትርጉም ካልተሰጠዉ በቀር የዝናብ እጥረት ማለት ነዉ። ዝናብ በተከታታይ ካልዘነበ ዬትም አገር ዉስጥ ድርቅ ይከሰታል። ነገር ግን ድርቅ ሁሉም አገር ዉስጥ ወደ ረሃብ አይለወጥም። ድርቅን አስመልክቶ በአገሮች መካከል ያለዉ ትልቁ ልዩነትም እዚህ ላይ ነዉ። አንዳንድ አገሮች ድርቅን በሩቁ ያዩና ዝግጅት አድርገዉ ረሃብን ይከላከላሉ፤ እንደ ኢትዮጵያ አይነቶቹ በልመና የተካኑ አገሮች ደግሞ ድርቁ ወደ ረሃብ እስኪለወጥ እጃቸዉን አጣጥፈዉ ይጠብቁና ህዝቡ ሲራብ አለም አቀፉን ህብረተሰብ “ስለ ማሪያም” ማለት ይጀምራሉ።

Tuesday, November 3, 2015

Berhanu Nega: The Quest for Change in Ethiopia

By: Laura Secorun Palet, Ozy

It was the spring of 2001 and 43-year-old Berhanu Nega was optimistic. His homeland, Ethiopia, was recovering from decades of conflict, he had just given a speech to university students about academic freedom, and now he had landed at Charles de Gaulle Airport for a business conference in Paris.

Then he turned on his phone. The students he’d spoken to hours earlier had staged a peaceful protest that the police answered with brute force and live ammunition, leaving 40 people dead. A week later, Nega was back in Ethiopia, behind bars.

So began a 14-year-long ordeal that has seen Nega, one of Ethiopia’s leading activists, arrested and jailed twice — once for almost two years — exiled to the United States and finally, condemned to death, in absentia. These days, the would-be mayor of Addis Ababa (he was detained right after he won the election) is an associate professor of economics at Bucknell University. But Nega remains a prominent opposition leader: He is the co-founder of Ginbot 7, an outlawed political party that he leads from the sleepy Pennsylvania campus town of Lewisburg.

Of late, Ethiopia has been a darling of Western powers. The landlocked country is considered an island of stability in the otherwise turbulent Horn of Africa. Yes, its name was once synonymous with starving children and charity concerts, but today, Ethiopia posts GDP growth numbers in the double digits. In the past year, foreign investment has skyrocketed. The country is also a valuable partner against the threat of Islamist terrorism — here, in the incarnation of al-Shabab in Somalia, which killed 148 students in April at a Kenyan university.

that’s why the the U.S. donated $340 million to a country with such a horrible human rights record. Under Meles Zenawi, who ruled from 1991 until his death in 2012, the government ostracized the opposition and imposed a system of ethnic-based federalism, which enhanced divisions and was useful for repressing certain ethnic groups. Zenawi’s successor, Hailemariam Desalegn, has carried on his legacy of media muffling, extrajudicial executions and torturing dissidents. Nega says protecting a regime that most citizens resent will backfire in the long run: “Ethiopia is ready to explode, it just needs a little match to light it up,” he says. “The West is not going to give Africans democracy, Africans have to fight for it.”

Malnutrition hits record high in Ethiopia

By: Katy Migiro

NAIROBI, Nov 2 (Thomson Reuters Foundation) – Donors are not responding fast enough to urgent calls for more aid to drought-stricken Ethiopia where record-breaking numbers of children are suffering malnutrition, the United Nations said on Monday.

Ethiopia is experiencing its worst drought in decades, after low and erratic rainfall during the spring and summer, leaving more than eight million people in need of food aid.

“The El Niño-caused drought emergency is worsening and is worryingly underfunded despite repeated calls by the Ethiopian government and humanitarian partners for additional funds,” the U.N.’s Office for the Coordination of Humanitarian Affairs said.

The El Niño weather phenomenon, caused by Pacific Ocean warming, is causing droughts and floods across eastern Africa.

The number of children admitted to hospitals with severe acute malnutrition, meaning they are likely to die without therapeutic feeding, has hit record levels, the U.N. said.

In September, there were more than 35,000 new admissions, bringing the number of children under 5 years old treated for SAM this year to more than 250,000, the U.N. said.

Children are falling critically ill because of the failed rains along with shortages of food aid, particularly supplementary nutrition given to the most vulnerable members of the population, it said.
Women and girls are travelling up to 30km (18.6 miles) a day in search of water, their burden increased by the death of their livestock.

“They are now carrying loads, which otherwise would have been carried by their donkeys,” it said.
The number of hungry people in the region is expected to almost double to 22 million in early 2016, from 12 million a year earlier, the U.N. said.