Tuesday, December 30, 2014

አፋጣኝ ፍትህ የማግኘት መብት ከወዴት አለ?

በላይ ማናዬ

 በታላቁ መጽሐፍ የተጠቀሰ አንድ ታሪክ ላይ አንዲት እናት ልጇን በጓደኛዋ ስለመሰረቋ እናነባለን፡፡ ይህቺ እናት ልጄን ተሰረቅኩ ብላ ወደ ጠቢቡ ሰለሞን አቤት ትላለች፡፡ ጠቢቡ ሰለሞንም ሁለቱን ሴቶች ተሰረቀ ከተባለው ህጻን ጋር ተያይዘው እንዲቀርቡ ያደርጋል፡፡ ጠቢቡ ንጉስ ሰለሞን እውነተኛ እናት የትኛዋ እንደሆነች ለማወቅም የራሱን የምርመራ ዘዴ ሲጠቀም እናስተውላለን፡፡ በዚህም ሁለቱ ሴቶች የተካሰሱበትን ጉዳይ ሰለሞን በጥበብ ትክክለኛ ዳኝነት ሰጥቶ ያሰናብታቸዋል፡፡ ህጻኑም እውነተኛ እናቱን ያገኛል፡፡ ይህ ፍትህ የተሰጠው ከብዙ መመላለስ በኋላ አልነበረም፤ አፋጣኝና ትክክለኛ ፍርድ ነበር የተሰጠው፡፡

እንደ ጠቢቡ ሰለሞን በአንድ ጀንበር በጥበብ ተከሳሽንና ከሳሽን ሰምቶ ትክክለኛ ውሳኔ የሚሰጥ የዳኝነት አካል እንዲኖረን በባዶ የምመኝ ሰው አይደለሁም፡፡ ነገር ግን ማነኛውም ተከሳሽ የተከሰሰበት ጉዳይ ተጣርቶ በፍጥነት ውሳኔ እንዲሰጠው፣ ፍትህ እንዲያገኝ እፈልጋለሁ፡፡ የዘገየ ፍትህ እንደተነፈገ ይቆጠራል ይባላል፡፡ ትክክለኛ አገላለጽ ነው፡፡ እውነትም በሀገራችን በዚህ አገላለጽ መሰረት ውሳኔ ተጓትቶባቸው፣ ፍትህ የተነፈጉ ብዙዎች ናቸው፡፡

ማክሰኞ ጥቅምት 4 ቀን 2007 ዓ.ም በእነ እስማኤል ኑርሑሴን የክስ መዝገብ ከ1 አመት ከ6 ወር በላይ በእስር ሲሰቃዩ የቆዩ 12 ተማሪዎች እና 1 መምህር በመጨረሻ ብይናቸው ሲሰማ የሆነው ‹‹የዘገየ ፍትህ እንደተነጠቀ ይቆጠራል›› የሚለውን አባባል ያስረገጠ ነበር፡፡ ምክንያቱም ተከሳሾቹ ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የተበየነው የ6 ወር እስር ብቻ ነበር፤ በእስር የቆዩት ግን 1 አመት ከ6 ወር ነበር፡፡ ይህ የሚያሳየን ተከሳሾቹ አፋጣኝ ፍትህ ባለማግኘታቸው ብቻ ተጨማሪ አንድ አመት እስርን በግፍ አሳልፈዋል ማለት ነው፡፡ በእነ እስማኤል ኑርሑሴን የክስ መዝገብ ያለአግባብ ከተፈረደባቸው ጊዜ በላይ በእስር ያሳለፉት ሰዎች ከጅግጅጋ፣ ከሲቪል ሰርቪስ፣ ከባህር ዳር፣ ከጅማ፣ ከደሴ፣ ከሐዋሳና ከደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲዎች ተለቅመው የታሰሩ 12 ሙስሊም ተማሪዎችና 1 አስተማሪን የተካተቱበት ነበር፡፡ በአጠቃላይ የተጓተተው ክስ ሂደት ብይን ለማግኘት 18 ወራትን ወስዷል፡፡ በዚህ ሁሉ ጊዜ ደግሞ ተከሳሾቹ በእስር ላይ ነበሩ፡፡ በግንቦት 2005 ዓ.ም ክስ የተመሰረተባቸው እነዚሁ ተማሪዎች በተለያዩ ሰበባ-ሰበቦች ምክንያት ችሎቱ እየተጓተተ በመቆየቱና የፍትህ ስርዓቱ የዜጎችን መብት ማስከበር በማይችልበት ደረጃ በመኮላሸቱ ጥፋተኛ ሆነው ቢገኙ እንኳ ክሳቸው ከሚያስፈርድባቸው በላይ በእስር እየቆዩ መሆኑን የህግ ባለሙያዎች ሲያሳስቡ ቆይተው ነበር፡፡ ሆኖም ግን ሰሚ ጆሮ አላገኙም ነበር፡፡ እነዚህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ለረጂም ጊዜ ተስተጓጉለዋል፡፡ ሊሰሩት የሚችሉት ነገር ሁሉ ተደናቅፎ መቆየቱም እሙን ነው፡፡ ታዲያ እነዚህ ሰዎች ፍትህ አገኙ ወይስ ተነፈጉ?

Monday, December 29, 2014

የባህር ዳር መስዋዕትነት የማይቀረዉ ድል ዋስትና ነዉ!

ወያኔ በየአመቱ ህዳር ወር መጨረሻ ላይ የኢትዮጵያን ብሄር ብረሰቦች ሰብስቦ ዘፈን የሚያስዘፍንበትን በዐል ሲያከብር በተደጋጋሚ ከሚያሳማቸዉ መፈክሮች አንዱ የብሄር ብሄረሰቦች መብትና እኩልነት በህገመንግስታችን ተከበረ የሚል እጅግ በጣም አሳሳች የሆነ መፈክር ነዉ። በእርግጥም ወያኔ ለይስሙላ ወረቀት ላይ ያሰፈረዉ ህገ መንግስት መግቢያዉ ላይ “እኛ የኢትዮጵያ ብሄሮች፤ ብህረሰቦች፤ ህዝቦች በነጻ ፍላጎታችን የህግ የበላይነትና በራሳችን ፍላጎት ላይ የተመሰረተ አንድ የፖለቲካ ማህበረሰብ በጋራ ለመገንባት ቆርጠን ተነስተናል” ይላል። መቼም ይህ ምንም በማያሻማ መልኩ ቁልጭ ብሎ የተቀመጠ ህገ መንግስታዊ አንቀጽ ሌላ ትርጉም ካልሰጡት በቀር የአማራንም ህዝብ ያጠቃልላል የሚል ሙሉ እምነት አለን። በዚህ ደግሞ የአማራን ክልል የማስተዳድረዉ እኔ ነኝ ባዩ ባዕዴንም የሚስማማ ይመስለናል። በተግባር ሲታይ ግን ይህ የወያኔ ህገ መንግስት ላይ ህዝብና መንግስት የሚተዳደሩበት ህግ ቀርቶ ህገ አራዊት እንኳን አይመስልም። ምክንያቱም በህገ አራዊት አሰራር ተመሳሳይ ዝሪያ ያላቸዉና በአ ያላቸዉ የዱር አራዊት ይከባበራሉ እንጂ አንዱ ሌላዉን አያጠፋም። ለምሳሌ አንበሳና አንበሳ ይረዳዳሉ ወይም አብረዉ አደን ይወጣሉ እንጂ እርስ በርስ አይተላለቁም፤ ነብርና አንበሳም ቢሆኑ በተገናኙ ቁጥር ተከባብረዉ ይተላለፋሉ እንጂ አንደ ወያኔ ብጤያቸዉን ባዩ ቁጥር አያጠቁም ወይም አይገድሉም።

ወረቀት ላይ የሰፈረዉን የወያኔ ህገ መንግስት የተመለከተ ሰዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዜጎች መብታቸዉና ነጻነታቸዉ ተከብሮ የሚኖሩ ሊመስለዉ ይችላል። በእርግጥም ይመስላል። ምክንያቱም የወያኔ ህገ መንግስት ችግሩ አጻጻፉ ላይ ወይም ይዘቱ ላይ ሳይሆን በተግባር አተራጓጎሙ ላይ ነዉ። በ1987 ዓም የፀደቀዉ የወያኔ ህገ መንግስት በተግባር ሲታይ ብሄሮች፤ ብህረሰቦችና ህዝቦች የሚለዉ ቦታ ደብዛዉ ጠፍቶ ሁሉም ነገር ወያኔ ወይም ህወሓት በሚለዉ ቃል ተተክቷል፤ ወይም ሁሉም የአገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ተጨፍለቀዉ የትግራይ ልህቃን ወይም የህወሓት ሎሌዎችና ተላላኪዎች ሆነዋል። ለዚህ ነዉ አገራችን ኢትዮጵያ ወያኔ ያሰኘዉን የሚያዝባት የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ አንገቱን ደፍቶ የሚታዘዝባት አገር የሆነችዉ።

ሌላዉ ወያኔ ህገ መንግስቱ ዉስጥ አስፍሮ በየቀኑ እንደቤቱ ዉስጥ ምንጣፍ ከሚረግጣቸዉ ህገ መንግስታዊ አንቀጾች ዉስጥ አንዱ አንቀጽ 30 ንዑስ አንቀጽ አንድ ነዉ። ይህ አንቀጽ ማንኛዉም ሰዉ ከሌሎች ጋር በመሆን መሳሪያ ሳይዝ በሠላም የመሰብሰብና ሠላማዊ ሠልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ ሙሉ መብት አለዉ ይላል። ሆኖም የዚህን አንቀጽ ሙሉ ቃል ከወያኔ የየቀኑ አረመኔነት ጋር ስናነጻጽር አንቀጹ የተጻፈበትን ወረቀት ያክል እንኳን ክብደት የለዉም። ይህንን ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ሠላማዊ ሠልፍ ባደረገባቸዉ ቦታዎች ሁሉ ወያኔ በተከታታይ በወሰዳቸዉ አረመኔያዊ እርምጃዎችና በፈጸማቸዉ ሰቆቃዎች ተመልክተናል። ለምሳሌ ባለፈዉ አመት አምቦ ዉስጥ አሁን ከሰሞኑ ደግሞ ባህርዳር ዉስጥ ህገ መንግስታዊ መብታቸዉን ተጠቅመዉ ጥያቀያቸዉን ሠላማዊ ሰልፍ በማድረግ ያቀረቡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ህፃናት፤ ወጣቶች፤ አዋቅዎች ወንዶችና ሴቶች በአግዓዚ ነብሰ ገዳዮች ጥይት ተጨፍጭፈዋል።

ወያኔ በተደጋጋሚ ሠላም … ሠላም እያለ በአፉ ይናገር አንጂ ወያኔን ከሰላም ጋር የሚያገናኘዉም ሆነ ወያኔ ስለ ሰለም የሚያዉቀዉ ምንም ነገር የለም። እዉነቱን ለመናገር ኢትዮጵያ ዉስጥ ሠላማዊ ሠልፈኞችን የሚገድል፤ ሠላለማዊ ዜጋን አስሮ የሚደበድብና የሠላም መንገዶችን ሁሉ ቅርቅር አድረጎ የዘጋዉ ወያኔ ብቻ ነዉ። ሌላዉ ቀርቶ ወያኔ የሚያስበዉ፤ የሚያቅደዉና ዕቅዱን ወደ ተግባር የሚለዉጠዉ ከህዝብ ፈቃድና ፍላጎት ዉጭ ስለሆነ ልማት ብሎ የሚጀምራቸዉ ፕሮጀክቶች እንኳን የህዝብን ሠላም የሚያናጉና የሠላማዊ ዜጎችን ህይወት የሚቀጥፉ ጅምሮች ናቸዉ። ከሰሞኑ ደግሞ ባህር ዳር ዉስጥ እየታየ ያለዉ ህዝባዊ ቁጣ የዚሁ ወያኔ ልማት እያለ የቀሰቀሰዉ ህዝባዊ እሳት ዉጤት ነዉ።

Friday, December 26, 2014

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩን ይፋ አደረገ


  • በ15 ከተሞች በተመሳሳይ ሰዓት ሰልፎች ይደረጋሉ

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ያወጣውን ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩን ዛሬ ታህሳስ 17 ቀን 2007 ዓ.ም ይፋ አድርጓል፡፡ ትብብሩ የመጀመሪያ ዙር መርሃ ግብሩን በህዳር ወር በተለያዩ እንቅስቃሴዎች ማከናወኑ የሚታወስ ሲሆን፣ ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩ ደግሞ ለ2 ወራት የሚቆይ እንደሚሆን ተገልጹዋል፡፡

የትብብሩ አመራሮች በሰማያዊ ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት በሁለተኛ ዙር የትብብሩ መርሃ ግብር መሰረት የካቲት 15 ቀን 2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት በ15 የሀገሪቱ ትላልቅ ከተሞች ላይ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፎች ይደረጋሉ፤ በአዲስ አበባ፣ በሀዋሳ፣ በባህር ዳርና በአዳማ ደግሞ ህዝባዊ ስብሰባዎች እንደሚደረጉ የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ይልቃል ጌትነት (ኢ/ር) በመግለጫው ወቅት ተናግረዋል፡፡

‹‹የመግባቢያ ሰነዳችንና የጥናት ሪፖርታችንን እንዲሁም ከመጀመሪያው ዙር ያገኘውን ተሞክሮ በሠረት በማድረግ ይህን የሁለተኛ ዙር የሁለት ወር ዕቅድ (ከታህሳስ 16 እስከ የካቲት 15 /2007) አውጥቶ በቀዳሚነት ለዋነኛ ባለቤቶቹና ፈጻሚዎቹ ኢትዮጵያዊያን ሲያቀርብ እንደመጀመሪያው ዙር ከጎኑ እንደሚቆሙ ሙሉ እምነት በማሳደር ነው›› ያለው መግለጫው፣ በትብብሩ በኩል በአመራር ከፊት ቆመው ትግሉን ለመምራት ዝግጁነትና ቁርጠኝነት መኖሩን አስረድተዋል፡፡

‹‹የያዝነው የትግል መንገድ ሠላማዊና ህገ-መንግሥታዊ ብቻና ብቻ፣ መጓጓዣችን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ፣ መድረሻችን መድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት፣ እንዲሁም በጉዞኣችን ላይ የቱንም ያህል አረመኔያዊ የኃይል እርምጃ ይወሰድብን፣ ትግሉ የቱንም ዓይነት ዋጋና መስዋዕትነት ይጠይቅ ከጅምሩ ያለመስዋዕትነት ድል የለም ብለን ተነስተናልና ከያዝነው ዓላማ ኢንች የማናፈገፍግና ለቃላችን በጽናት የምንቆም መሆኑን ዳግም እናረጋግጣለን›› ብሏል ትብብሩ በመግለጫው፡፡

እቅዱ የመጀመሪያው ዙር ቀጣይ መሆኑን ያተተው የትብብሩ መግለጫ፣ ‹‹ዓላማችን የምርጫ ሁኔታዎች ባልተሟሉበትና የመራጩ ህዝብ ነጻነት በሌለበት ስለምርጫ መናገር አስቸጋሪ ነው፣ እነዚህ በሌሉበት አማራጭ የምርጫ ኃሳቦች በህዝብ ውስጥ ሊንሸራሸሩም ሆነ አማራጭ ኃሳባችንን ከህዝብ ማድረስ አይቻልም፣ ሚናችንም የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታው አማራጭ ሆኖ መቅረብ ሣይሆን የህወኃት/ኢህአዴግ አጃቢነትና የሀገር ሃብት በአላስፈላጊ መንገድ የማባከን ሥራ ተባባሪነት የዘለለ አይሆንም ከሚል የመነጨ ነው›› ሲል አቋሙን አሳውቋል፡፡ ነጻነት በሌለበት ተጨባጭ ሁኔታ ምርጫ ቧልት ነው ሲልም አክሏል መግለጫው፡፡

ከታህሳስ 10 ቀን 2007 የአዲስ አበባና ባህርዳር አመጾች ምን እንማራለን?

ዓርብ ታህሳስ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. አዲስ አበባ እና ባህርዳር በዓይነታቸው ልዩ የሆኑ ሕዝባዊ ተቃውሞዎችን አስተናግደዋል። በአዲስ አበባ ሙስሊም ወገኖቻችን ከህወሓት ሰላዮች እይታ ውጭ በተደራጀ መንገድ በኑር መስኪድ ያደረጉት ተቃውሞ ቢያንስ ሶስት ቁም ነገሮችን አስገንዝቧል። እነዚህ ሶስት ነገሮች፣ (1ኛ) ምላሽ እስካላገኘ ድረስ የመብት ማስከበር ትግል በአፈና ተዳፍኖ እንደማይጠፋ፣ (2ኛ) ጽናት ካለ የወያኔ አፈናን የሚቋቋም ድርጅትና ተግባቦት መፍጠር እንደሚቻል፣ እና (3ኛ) ሙስሊሙን በተመለከተ የህወሓት አንድ-ለአምስት አደረጃጀት መፍረሱ ናቸው። ይህ ድል የሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆን ሙስሊም ያልሆኑ ኢትዮጵያዊያንም የሚጋሩት የጋራ ድል ነው። በተለይም የወያኔ አንድ-ለአምስት አደረጃጀት የሚናድ መሆኑ በተግባር ማሳየታቸው እና የህወሓት ሰላዮች ሳይሰሙ ተቃውሞዓቸውን አደራጅተው ተግባራዊ ማድረጋቸው የሚደነቅ ነው።

በዚሁ ዕለት በባህርዳር የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ከሕዝብ ጋር ሳይመክር በልማት ስም ያሻውን የሚያደርገውን እብሪተኛን ለመቃወም በአጭር ጊዜና በፍጥነት ተሰባስበው ቁጣቸው ማሰማት ችለዋል። በባህር ዳር ሕዝብ ልብ ውስጥ ለዓመታት ሲብሰለሰል የቆየውን የበደል ስሜት በዚህ አጋጣሚ ገንፍሎ ወጥቷል። በተለይም የወያኔ “ምርጥ ባርያ” መሆኑ የሚስፈነጥዘው ብአዴን በአማራ ሕዝብ ምን ያህል የተጠላና የተናቀ መሆኑ እንዲያውቅ ተደርጓል። ሆኖም ግን፣ ማናቸውንም ዓይነት ተቃውሞ የማያስተናዱት ህወሓትና ባርያው ብአዴን በባዶ እጁ ለተቃውሞ በወጣው ሕዝብ ላይ የጥይት ናዳ እንዲያወርድ ሠራዊታቸውን በማዘዛቸው እና ይህን ዘግኛኝ ትዕዛዝ የሚያስፈጽም ሠራዊት ያለ በመሆኑ ብዙ አዛውንት፣ ጎልማሶችና ወጣቶችን ለሞትና ለአካል ጉዳት ተዳርገዋል። የህወሓትና የብአዴን ሠራዊት ከዱላና ከገዳይ ጥይት ሌላ አንዳችም የአድማ መበተን እውቀት የሌለው መሆኑን የሚያሳዝን ነው፤ በሰላማዊ ሕዝብ ላይ እንዲተኩስ ሲታዘዝ የሚተኩስ መሆኑም የሚያሳፍር ነው። በባህርዳር ከተፈፀመውም የኢትዮጵያ ሕዝብ (1ኛ) ሕዝባዊ አብዮት እንዲህ በደንብ ሳይታሰብበትም ሊቀሰቀስ የሚችል መሆኑ፣ (2ኛ)ህወሓት ሕዝብ አምርሮ ሲነሳበበት የሚደነግጥና የሚርበተበት ፈሪ መሆኑ፣ እና (3ኛ) በፈሪነቱ ምክንያትም በባዶ እጃቸው በወጡ አዛውንትና ህፃናት ጭምር የተኩስ እሩምታ ከመክፈት የማይመለስ መሆኑን አስተውሏል ብለን እናምናለን።

ህወሓትንና አገልጋዮቹን ከስልጣን ለማባረር በአዲስ አበባ እና ባህርዳር የተደረጉትን ማቀናጀት ግዴታ ነው። በሌላ አነጋገር የባህር ዳሩ ሕዝባዊ አመጽ አዲስ አበባ ኑር መስጊድ በታየው ዓይነት ብልሃት፣ ድርጅት እና ዲሲፕሊን ተመርቶ ቢሆን ኖሮ በባህር ዳር የተጫረው የነፃነት እሳት በመላው አገሪቷ ተቀጣጥሎ ዛሬ የምንገኝበት ሁኔታ ከታህሳስ 10 ከነበረው ፈጽሞ የተለየ በሆነ ነበር። ለወደፊቱም ማድረግ የሚኖርብን ይህ ነው። ሙስሊምና ክርስቲያኑ ተደጋግፎ አንዱ ዘንድ የጎደለው በሌላው አካክሶ የሁላችንም ጠላት የሆነውን ህወሓትን ከነ አገልጋዮቹ ከሥልጣን ማስወገድ የሁላችንም የጋራ ግዴታ ነው። ጠመንጃው የፍርሃቱ መሸሸጊያ ያደረገው ህወሓትም ጠመንጃውን የሚያስጥል መላ እና ዱላ መዘጋጀት ይኖርበታል። ህወሓትንና አጫፋሪዎቹን ከሥልጣን ለማባረር በጠንካራ ድርጅት፣ ዲሲፕሊንና ብልሃት የሚመራ ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አመጽ ቅንጅት ሊኖር እንደሚገባ የታህሳስ 10 ቀን 2007 ትልቁ ትምህርት ነው። በዚህ ዕለት የህወሓትን ወደ ጠመንጃ የመሮጥ ወራዳ ባህርይን የሚያስቆም ኃይል የማደራጀት አስፈላጊነትም ጉልህ ሆኖ ወጥቷል። ዓርብ ታህሳስ 10 ቀን 2007 ዓም አዲስ አበባና ባህርዳር የተፈፀሙትን አገናኝቶ ያነበበ ማንኛውም ሰው የሁለገብ ትግል ስልት ምንነትና አዋጭነት በገሃድ ይረዳል፤ ወደዚያ እያመራን መሆኑንም ይገነዛባል።

Tuesday, December 23, 2014

ግፍና አፈና ዐመጽን ይወልዳሉ!

የዐመጸኛ አፍ ጥልቅ ጉድጓድ ነው (መ. ምሳሌ ም. 22፣  ቁ. 14)

ከያሬድ ኃይለማርያም ብራስልስ፣ ቤልጂየም ታኅሣሥ 10፣ 2007

ሰብአዊ መበቶችን በመጣስ፣ ግፍ በመፈጸምና አፈናን በማጠናከር እደሜ የሚሸምት የአገዛዝ ሥርዓት የእያንዳንዱን ሰው መንፈሳዊና አካላዉ ጥንካሬ የማዳከም፣ ቅስምን የመስበርና ፍርሃትን የማንገስ ከፍተኛ አቅም እንዳለው ሁሉ በብሶት የሚወለዱ፣ እምቢኝ ለግፈኞች፣ እምቢኝ ለአንባገነኖች፣ እምቢኝ ለነጻነቴ የሚሉ መንፈሰ ጠንካራ ጀግኖችንና ታጋዮችንም ይወልዳል:: የአለማችን ስመ ጥርና ዘመን የማይረሳቸው የነጻነት ታጋዮች እነ ማህተመ ጋንዲ፣ ማርቲን ሉተር ኪነግ፣ ማንዴላ፣ ኡንግ ሳን ሱ ኪ እና ሌሎችም ብዙዎች የፈለቁት በብሶት ከተሞላ፣ ጭቆና ካንገሸገሸውና በአፋኝ ሥርዓት ከታመቀ ማኅበረሰቡ ጉያ ነው:: አንድን ማኅበረሰብ በአፈሙዝ፣ በሕግና በገንዘብ ኃይል ጭፍሎቆና አፍኖ ማቆየት የሚቻለውም ለተወሰነ ጊዜ ብቻ መሆኑን የእነዚህ ታጋዮች ገድልና የአለም ታሪክም ይመሰክራል:: አንድ ሕዝብ በላዩ ላይ ገዢዎች እየተፈራረቁበት ረዘም ላለ ጊዜ በአገዛዝ ሥርዓት ሥር ሊቆይ ይችል:: ይሁንና እድሜ ልክ የገዛ አፋኛ ሥርዓት ግን የለም:: ሥርዓቱም እንደ ድርጅት፣ ሹማምንቱም እንደ ሰው የጉብዝና እድሜያቸው የተወሰነ ነው:: የአፈናን ስልት በመለዋወጥና ሸምቀቆውን በማጥበቅም እድሜን ማራዘም የሚቻል ቢመስልም በተቃራኒዉ ውድቀትንም ያፋጥናል:: ግፉ እየበረታና የመብት ጥሰቱም መረን እየለቀቀ በሄደ ቁጥር የሕዝብ ትእግስት ይሟጠጣል:: ሕዝብ መቆጣት ከጀመረና ቁጣውም ወደ አደባባይ አመጽ በተቀየረ ጊዜ የግፍ አገዛዝ ወደ መቃብር፣ ግፈኞቹም ወደ ዘብጥያ እንደሚወርዱ እርቀን ሳንሄድ ባለፉት አምስትና አሥርት አመታት ውስጥ በአለም የታዩ ሕዝባዊ ነውጦችንና ያስከተሉትን መዘዝ ማጤን በቂ ነው::

ትልቁ ጥያቄ በግፍ አገዛዝ ውስጥ ያለ ሕዝብ መቼ እና ብሶቱስ ምን ደረጃ ላይ ሲደርስ ነው የሚቆጣው? መቼ ነው ቁጣውንስ በየመንደሩ ከማጉረምረም አልፎ ባደባባይ የሚገልጸው? ቁጣውስ ወደ አመጽ ሊያመራው የሚችለው በምን ሁኔታ ነው? የሚለው ነው:: የሕዝብ ቁጣ ወደ አመጽ የሚለወጥበት ጊዜና ደረጃው የሚለካው በተለየ ሳይንሳዊ ቀመር ስላልሆነ መቼና በምን ሁኔታ ሊከሰት እንደሚችል እርግጠኛ ሆኖ መናገር ይቸግራል:: ይህ አይነቱ ሁኔታ በእያንዳንዱ ማኅበረሰቡ ባህላዊ፣ ኃይማኖታዊና ማኅበራዊ አመለካከቶችና የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ላይ ይወሰናል:: በትንሽ በትልቁ አደባባ እየወጣና በሚሊዮን የሚገመት የመንግሥትና የሕዝብ ንብረትን እያወደመ ተቃውሞውን የሚገልጽ ሕዝብ አለ:: በሌላ መልኩም አገሩን ቢሸጡበት፣ መሬቱን ቢነጥቁት፣ ሚስቱን ቢያስጥሉት፣ ልጆቹን ቢደፍሩበት፣ ቢገድሉበት፣ ቢያስሩበትና ቢያፍኑበት፣ ቤቱን በላዩ ላይ ቢያፈርሱበት፣ ቀየውን ለቱጃሮች ሰጥተው ቢያፈናቅሉት፣ ግብር እየከፈለ ያስተማራቸውን ልጆቹንና አመራቹን ኃይል እያዋከቡ ከአገር ቢያሰድዱበትና ለባርነት ቢዳርጉት፣ ከሰው ተራ አውርደው በየጎዳናው ቢጥሉትም ‘አዬ ጉድ፣ አዬ ጉድ’ ከማለት ባለፈ ቁጣውን የማያሳይም ሕዝብ አለ:: በከፋ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ታዋቂ የነበሩት ሟቹ ጠ/ሚ መለስ ያረፉ ወቅት አስከሬናቸውን ይሳለሙ ከነበሩ ሰዎች በኑሮው እጅግ የተጎዳና የተጎሳቆለ አንድ የጎዳና ተዳዳሪ በመንግሥት የቴሌቪዥን ማሰራጫ ሃዘኑን የገለጸበት መንገድ ጥሩ ማሳያ ሊሆን ይችላል:: የአዞ እንባውን እያነባ “እኔ እኮ እሳቸውን ተማምኜ ነው ጎዳና ላይ የማድረው” ነበር ያለው::

በሳንቲም ደረጃ የዋጋ ጭማሪ ተደረገብኝ ብሎ ወደ አደባባይ እየደጋገመ የሚወጣውን የኬኒያን ሕዝብ ቁጣ ለማየት በሚያዚያ ወር 2011 (እ.ኤ.አ) የነዳጅ ዋጋ ማሻቀብን ተከትሎ የተከሰተውን የኑሮ ውድነት በመቃወም በናይኖቢ የተካሄደውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ማየት ይቻላል:: እኛ ዘንድ የነዳጅ ዋጋ ስንት ጊዜ አሻቀበ? በእያንዳንዱ የእለት ተዕለት መገልገያ ቁሳቁሶች ላይ በምን ያህል መጠንና ስንት ጊዜ የዋጋ ንረት ታየ? የቤት ኪራይ፣ የትራንስፖርት፣ የጤና አገልግሎት፣ የመድሃኒቶች እና ሌሎች መሰረታዊ አቅርቦቶች ዋጋስ በስንት እጥፍ ናረ? እኛስ ስንት ጊዜ ቁጣችንን ገለጽን? በኑሮ መማረራችንንስ በምን መልኩ ለገዢዎቻችን አሳየን? ከኑሮ ዋስትና ማጣት ባሻግር የሹመኞች ከሕግ በላይ መሆን የዜጎችን በሕገ-መንግሥቱ የተደነገጉ መሰረታዊ የፖለቲካና የሲቪል መብቶችንና ነጻነቶችንም ትርጉም አልባ ሲያደርጋቸው እያየን ምን አደረግን? ለዚህም ነው የሕዝብ ብሶትና ምሬት የት ደረጃ ላይ ሲደርስ ቁጣ ወደተቀላቀለበት ተቃውሞ ሊያመራ እንደሚችል ሳይንሳዊ በሆነ ቀመር ማረጋገጥ ወይም መገመት የማይቻለው:: ምክንያቱም ግፍና በደሉን የተሸከመው ሕዝብ ያለው የታጋሽነት ልክ፣ ሆደ ሰፊነቱ፣ አርቆ አሰተዋይነቱ፣ የተዋጠበት የፍርሃት ጥልቀት ወይም ሌሎች ስነ-ልቦናዊ ሁኔታዎች ናቸው ይህን የሚወስኑት:: በዛሬዎቹም ሆነ በትላንት ገዢዎቹ ጭካኔና የማስተዳደር ብቃት ማነስ የተነሳ ለከፋ ድህነት የተጋለጠውና በልቶ ማደር ፈተና የሆነበት የኢትዮጵያ ሕዝብ ምሬቱንም ሆነ ተማጽኖውን የሚያሰማው ለፈጣሪው ብቻ ነው:: ሲመረውም ‘ምነው ዝም አልክ? ወይ ፍረድ ወይ ውረደ’ እያለ ካምላኩ ጋር መሟገት ይቀለዋል:: ትንሽ ሲደሰትም ‘ተመስጌን ይችን አትንሳኝ’ እያለ የነገን እጣፈንታውን እያሰላሰለ ፈጣሪውን ያመሰግናል:: ስለዚህ መንግሥት በሕዝብ ላይ ያሻውን ቢያደርግም ሕዝብ የልቡን የሚወያየውም ሆነ ይግባኝ የሚለውም ከመንግስት ዘንድ ሳይሆን ከፈጣሪው ጋር ነው:: ይህ አይነቱ የኅብረተሰብ ምላሽ ገዢዎችን ያማግጣል፣ ያሻቸውን እንዲያደርጉም ያበረታታል፣ ሕዝብን እንዲንቁና እራሳቸውንም ከሕግ በላይ አድርገው እንዲያስቡ ያደርጋል::

በዚህ አይነት ማኅበረሰብ ውስጥ ትልቁ ቀውስና ፖለቲካዊ ነውጥ የሚጀምረው የገዢዎቹ መረን መልቀቅ እየበረታ፣ የሕዝቡም ክፌት እየገነፈለ ሕዝብ የሚጠብቀው የፈጣሪው ምላሽ ግን የዘገየ ዕለት ነው:: ያኔ የሕዝብ ትግስት ይሟጠጣል፣ ሰፊውም ሆድም በቂም፣ በክፌትና በጥላቻ ይሞላል፣ አርቆ አሰተዋይነቱም ወደ ግብታዊነትና ንዴት ይለወጣል፣ ፍርሃቱም ተስፋ መቁረጥ ወደሚያሰከትለው ጨለምተኝነትና ጀብደኝነት ይቀየራል:: እዛ ደረጃ ከተደረሰ በኋላ የሚሆነውን መገመት አይከብድም:: በቅርቡ በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች በተለይም በቱኒዚያ፣ በግበጽ፣ በሊቢያ፣ በዩክሬንና ሌሎች አገሮች የተከሰቱት የሕዝብ ቁጣዎች ለዚህ ጥሩ ማሳያዎች ናቸው:: ባለፉት አራት አመታት ውስጥ በሕዝብ ቁጣና አመጽ ሲናወጡ የከረሙትን፣ በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመቶችን ያሰተናገዱትንና የመንግሥታትም ለዉጥ የታየባቸውን የአረብ አገራት መለስ ብለን የተመለከትን እንደሆነ አብዛኛዎቹ በቡዙ መልኩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሚገኝበት ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ሁኔታዎች እጅግ በተሻለ ደረጃ ላይ የሚገኙ ናቸው:: ጥሩ የነፍስ ወከፍ ገቢ ያላቸው፣ ሕዝብ በምግብ አጦት የተነሳ በርሃብ የማይሰቃየባቸውና የማይሞትባቸው፣ እጅግ የተሻለ የእሌክትሪክ፣ የውሃ፣ የነዳጅ፣ የጤና፣ የትምህርት፣ የኢንተርኔትና ልሎችም መሰረታዊ አቀርቦቶች የተሟሉባቸው አገሮች ናቸው:: ከፖለቲካ ነጻነቱም አንጻር ብዙዎቹ ከኢትዮጵያ በተሻለ ሃሳብን የመግለጽ፣ የመደራጀት፣ ባደባባይ የመሰብሰብና ተቃውሞንም የመግለጽ ነጻነትም የሚታይባቸው ናቸው:: ይሁንና በእነዚህ አገራት ውስጥ ሕዝብ ሙሉ በሙሉ የሥልጣን ባለቤት ባለመሆኑና ብለሹ በሆኑት የፖለቲካ ሥርዓቶች እጅግ ተከፍቶ የቆየ ስለነበር በቀላሉ ወደ አመጽ ሊያመራ ችሏል:: አንዳንዶቹም ዘላቂ ለሆነ ቀውስ መዳረጋቸው ይታወቃል::

ትግሉን ወደፊት ከመግፋት ውጭ አማራጭ የለም!

በፋሲል የኔያለም (የኢሳት ጋዜጠኛ)

ባለፉት 6 ወራት ብቻ 11 አብራሪዎች አገዛዙን ጥለው ጠፍተዋል። አንድን አብራሪ ለማሰልጠን ረጅም ጊዜ ይወስዳል፤ አብራሪዎች የጤና ሰራዊት፣ የልማት ሰራዊት እየተባሉ በሳምንት ውስጥ እንደሚፈለፈሉት ካድሬዎች አይደሉም። ለምሳሌ ሻለቃ አክሊሉ መዘነ አየር ሃይልን ጥሎ ከመጥፋቱ በፊት ለ15 አመታት በአየር ላይ በሯል። ሌሎችም እንዲሁ ከ7-15 ዓመታት የበረራ ልምድ ነበራቸው ። እነዚህን ሰዎች ማጣት ባገዛዙ ላይ የሚፈጥረው ተጽዕኖ ቀላል አይደለም። እውነተኛው ትግል ሲጀመር አብራሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ጄኔራሎችም እስከነ ወታደሮቻቸው የነጻነት ትግሉን እንደሚቀላቀሉ የሚጠራጠር ካለ ኢህአዴግ ውስጥ ስላለው ትርምስ በቂ መረጃ የሌለው ሰው ብቻ ነው።

ትግሉን ሞቦቱ ሴሴሴኮ በወረደበት ፍጥነት ማጠናቀቅ እንደማይቻል አምናለሁ። ነገር ግን በምድር ላይ ያሉትን ነባራዊ ሁኔታዎች ማለትም የህዝቡን የለውጥ ፍላጎትና የስርአቱን መበስበስ ግምት ውስጥ ስናስገባ፣ ህወሃት ደርግን ለመጣል የወሰደበትን ሩብ ያክል ጊዜ ላይወስድ እንደሚችልም እገምታለሁ። ገና ብዙ ስራዎች ይቀራሉ ። ብዙ መጥራት ያሉባቸው ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች አሉ። ህዝቡን በአንድ ልብ እንዳይነሳ የሚያደርጉትን ስጋቶች መርምሮ በቶሎ እልባት መስጠት ለነገ የሚተው ስራ አይደለም፤ ለውጡ ኢትዮጵያዊ እንዲሆን በፖለቲካውና በዲፕሎማሲው መስክ መሰራት ያሉባቸው በርካታ ስራዎች ከለውጡ በፊት ቀድመው ማለቅ አለባቸው። ዞሮ ዞሮ የትግሉ አላማ እጅግ ነጻ የሆነ የፖለቲካ ስርዓት መገንባት ነውና ዜጎች ለነጻነታቸው መረጋገጥ እንቅፋት ይሆናሉ ብለው የሚሰጉባቸውን ጉቶዎች ለይቶ በመንቀል፣ መንገዱ አስጊ አለመሆኑን ማሳየት ግንባር ቀደም ሆነው ከተሰለፉት የፖለቲካ ድርጅቶች ይጠበቃል። በተለይ በሃይል መንግስትን ለማስወገድ የሚታገሉ ሃይሎች፣ የሃይል አማራጭን ሆነ ሃይሉ የሚመጣበትን በሃይልም ይሁን በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ሃይሎች፣ የመጨረሻ ግባቸው ለራሳቸው ስልጣን ለመያዝ አለመሆኑን፣ አገዛዙን ጥለው የሚመሰርቱት የሽግግር መንግስትም ሁሉንም በእኩል የሚያስተናግድ መሆኑን ቃል ከመግባት ባሻገር በተግባር ማረጋገጥ አለባቸው።

ከፖለቲካ ድርጅቶች ተጽኖ ነጻ የሆኑ የሲቪክ ተቋማት በብዛት ቢመሰረቱ በሁዋላ ላይ ለሚመሰረተው ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የጀርባ አጥንት ይሆናሉ። የሲቪክ ተቋማቱ ነጻነትንና ዲሞክራሲን የተመለከቱ ማቴሬያሎችን በማዘጋጀት፣ ለነጻነት ለሚፋለሙ ሃይሎች መሬት ድረስ በመውረድ በማስተማር ለነጻነት የሚደረገው ትግል ፈሩን እንዳይስት ሊያግዙ ይችላሉ። የፖለቲካ ድርጅቶችም ቢሆኑ ግልጽ የሆነ ስርዓተ ትምህርት አዘጋጅተው ለሚመጡ የሲቪክ ተቋማት በራቸውን ክፍት አድርገው ታጋዮቻቸውን እንዲያስተምሩ ሊፈቅዱላቸው ይገባል። ሚዲያውም በተመሳሳይ ታጋዩ የሚታገልለለትን አላማ በውል እንዲገነዘብ በየጊዜው የማስተማር ሃላፊነት

ሞትን ሸሽቶ ተራ ሞት ከመሞት ከገዳዮች ጋር ተፋልሞ በክብር መሞት የኢትዮጵያዊነት ምልክት ነዉ

ወጣቱ ትዉልድ በየትኛዉም አገር ወይም ህብረተሰብ ዉስጥ በአገር ልማት’፤ በመሰረታዊ ተቋሞች ግንባታና አገርን በመከላከል ስራዎች ላይ የተሸከመዉ ኃላፊነት ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የበለጠ ነዉ። እንደ ኢትዮጵያ አይነት ዘረኛ አምባገነኖች በነገሱበት አገር ደግሞ ከላይ ከተጠቀሱት አገራዊ አደራና ሀላፊነቶች በተጨማሪ ወጣቱ ትዉልድ እራሱንና ወገኖቹን ከዘረተኝነትና ከአምባገነንነት አላቅቆ በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ዲሞክራሲያዊ ስርዐት የመገነባት ተጨማሪ ሀላፊነት አለበት። ወጣቱ ትዉልድ የኢትዮጵያን አገራዊ ራዕይ የተሸከመ ደከመኝን የማያዉቅ ተከታታይነት ያለዉ የማይነጥፍ የህይወት ምንጭ ነዉ። በእርግጥም ወጣትነት የህይወት ህልምና ፊቺዉ አብረዉ የሚገለጹበት የእድሜ ክልል ነዉ። ወጣቱ ደግሞ ራዕይ ተሸካሚ ብቻ ሳይሆን የተሸከመዉን ራዕይ እዉን ሆኖ ለማየትና ለማሳየት ብቃቱ፤ ችሎታዉና ፍላጎቱ ያለዉ መበአካሉም በመንፈሱን ጠንካራ የሆነ የህብረተሰብ ክፍል ነዉ።

አገራችን ኢትዮጵያ በአለም ታሪክ ዉስጥ እንደ አገር ተመዝግባ በኖረችባቸዉ ረጂም አመታት ዉስጥ የየዘመኑ ወጣት ለእናት አገሩ ሠላም፤ ብልጽግናና የግዛት አንድነት መከበር ይህ ነዉ ተብሎ በቃላት ሊነገር የማይችል ትልቅ መስዋዕትነት ከፍሏል ዛሬም እየከፈለ ነዉ። ትናንት በአባቶቻችን ዘመን የአገራቸዉን ዳር ድንበር በጠላት አናስደፍርም ብለዉ ጫካዉንና ዱሩን ቤታቸዉ ያደረጉ በላይ ዘለቀን፤ አብዲሳ አጋንና ጃገማ ኬሎን የመሳሰሉ ወጣቶች ነበሩን። በ1970ዎቹ ደግሞ ሰዉ በላዉን የደርግ ስርዐት ፊት ለፊት ተጋፍጠዉ ለእናት አገራቸዉ ኢትዮጵያ የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ነበሩ። ዛሬም ዘረኛዉን የወያኔ ስርዐት ለማስወገድና አገራቸዉ ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር ለማድረግ በየቀኑ የአካልና የሕይወት መስዋዕትነት የሚከፍሉ ኢትዮጵያዉያን ወጣቶች ቁጥር በቀላሉ የሚገመት አይደለም። ለምሳሌ በ1997 ዓም የህዝብ ድምጽ ይከበር ብለዉ በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ያቀረቡ ከሁለት መቶ በላይ ወጣቶች የጦር ሜዳ መሳሪያ ከታጠቁ አግዓዚ ነብሰ ገዳዮች ጋር ባዶ እጃቸዉን ተጋፍጠዉ በክብር ተሰዉተዋል።

ከላይ ከፍ ሲል አጽንኦት ሰጠተን እንደገለጽነዉ ወጣቱ ትዉልድ የህብረተሰብ አንቀሳቃሽ ሞተር ነዉ። ሀኖም ሞተር ከራሱ ዉጭ ሌሎችን ማንቀሳቀስ የሚችለዉ መጀመሪያ እሱ እራሱ መንቀሳቀስ ሲችል ነዉ። የኢትዮጵያም ሆነ የማንኛዉም አገር ወጣት ሞተር ሆኖ የሚኖርበትን ህብረተሰብ ማንቀሳቀስ እንዲችል ከፍተኛ የመንግስትና የሁሉም ህብረተሰብ ያላሰለሰ ድጋፍ ያስፈልገዋል። ከሁሉም በላይ ደግሞ ወጣቱ በነጻነት መንቀሳቀስ የሚችልበት የፖለቲካ፤የማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ ድባብ ያስፈልገዋል። እዚህ ላይ አንድ እጅግ በጣም የሚያሳዝነንና የሚያሳስበን ጉዳይ አለ፤ እሱም የኢትዮጵያ ወጣት የእድገት ሞተር ሆኖ አገሩን የሚያንቀሳቅስበት ቀርቶ እሱ እራሱም የነጻነት አየር የተነፈሰበት አንድም የታሪክ አጋጣሚ የለም። በተለይ በወያኔ ስርዐት ዉስጥ ከልጅነት ወደ ወጣትነት የተሸጋገረዉ ኢትዮጵያዊ ሁሉ አገር፤ አንድነትና ኢትዮጵያዊነት ከሚባሉ ትልላቅ ብሄራዊ እሴቶች ጋር እንዳይተዋወቅ ተደርጎ ያደገ ወጣት ነዉ።

የዛሬዉ ዘመን ኢትዮጵያዊ ወጣት በጻፈ ቁጥር የሚደበደብ፤ ባነበበ ቁጥር የሚጋዝ፤ ተናግሮ ሀሳቡን በገለጸ ቁጥር ደግሞ ከየመንገዱ እየተለቀመ የት እንደደረሰ እንኳን ሳይታወቅ ደብዛዉ የሚጠፋ ቀን የጨለመበት ወጣት ነዉ። ባጠቃላይ ወያኔ ስልጣን ይዞ በቆየባቸዉ ባለፉት ሃያ ሦስት አመታት ዉስጥ የኢትዮጵያ ወጣት የአባቶቹን ታሪክ እንዳያዉቅና ከዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂ ጋር ሳይተዋወቅ ድቅድቅ ጨለማ ዉስጥ እንዲኖር ተደርጓል። የኢትዮጵያ ወጣት ከመረጃ ቴክኖሎጂ ጋር ተዋዉቆ እራሱን ካደራጀና ከጓደኞቹ ጋር ባሰኘዉ ግዜ ሁሉ ከተገናኘ በአገሩ የፖለተካና ማህበራዊ መድረኮች ላይ የሚጫወተዉን ሚና ወያኔ ስለሚረዳ የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም ከወሰዳቸዉ እርምጃዎች አንዱና ዋነኛዉ ወጣቱ ህብረተሰብ ከመረጃ ቴክኖሎጂ ጋር ያለዉን የቅርብ ግኑኝነት መስበር ነዉ። ይህ ፀረ አገርና ፀረ ዕድገት እርምጃ ደግሞ ወጣቱን ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ አገራችን ኢትዮጵያ በመረጃ ቴክኖሎጂ ዕድገትና ስርጭት የአለማችን የመጨረሻዋ ጭራ አገር እንድትሆን አድርጓታል። ይህ ደግሞ የኢትዮጵያን ወጣት አማራጭ አሳጥቶ ከዚህ ቀደም ታይቶም ተሰምቶም በማያዉቅ ፍጥነትና ብዛት አገሩን እየጣለ እንዲሰደድ አድርጎታል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ሌሎችም አለም አቀፍና አህጉራዊ ድርጅቶች ያደረጉት ጥናት በግልጽ እንደሚያመለክተዉ ምሁሩና ወጣቱ ትዉልድ በከፍተኛ ቁጥር ከሚሰደድባቸዉ አገሮች ዉስጥ ኢትዮጵያ በዓለዉ ዉስጥ ቀዳሚዉን ቦታ የያዘች አገር ናት። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን አኮኖሚ የአፍሪካ የዕድገት ምልክት አድርገነዋል እያሉ ቢፏልሉም ይህ አሳደግነዉ የሚሉት ኤኮኖሚ ስራ አልባ ኤኮኖሚ በመሆኑ የራሱን አገር መገንባት የነበረበት ኢትዮጵያዊ ወጣት ወንድ ሴት ሳይል እጅግ በጣም በሚያስፈራ ፍጥነት አገሩን እየለቀቀ በመዉጣት ላይ ነዉ።

ዛሬ በዘለም ዙሪያ ከደቡብ ኮሪያ እስከ አዉስትራሊያ፤ ከሳዑዲ አረቢያ እስከ ካናዳ በየአህጉሩ፤ በየአገሩና በየደሴቱ ላይ ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች የሌሉበት አገር የለም። በ1970ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ የደርግን ጭፍጨፋ እየሸሸ ከአገሩ መሰደድ የጀመረዉ ኢትዮጵያዊ ወጣት ዛሬም ከ37 አመታት በኋላ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ አገዛዝ የለየለት ነብሰ ገዳይ አገፈዛዝ በመሆኑ የኢትዮጵያ ወጣት አሁንም አገሩን እየለቀቀ በመዉጣት ላይ ነዉ። የስደት ጉዞ ብርድና ቁር፤ ሀሩርና ንዳድ፤ እንዲሁም ህመም፤ ቁስልና ሞት የተቀላቀሉት ለወገንም ለባዳም የማይመኙት እጅግ በጣም አደገኛ ጉዞ ነዉ። ስደት ጉዞዉ ብቻ ሳይሆን ስደተኞች በስደት የሚኖሩበት አገርም ቢሆን ለአካልም ለመንፈስም የማይመች ቦታ ነዉ። ሴቶች እህቶቸቻችን በየቀኑ ወደ አረብ አገር የሚጎርፉት አካለቸዉ ላይ የፈላ ዉኃ እንደሚደፋ፤ ከፎቅ ላይ እንደሚወረወሩና በአረብ ጎረምሳ በየቀኑ እንደሚደፈሩ እያወቁ ነዉ ከወያኔ ጋር ከመኖር ስደት ይሻላል ብለዉ አገራቸዉን ለቅቀዉ የሚሰደዱት። ወንዶች ወንድሞፐቻችንም ቢሆኑ የሰሃራን በረሃና የቀይ ባህርን የመከራ ጉዞ ቆርጠዉ የሚገበቡበት ከቀዳዳ ይሻላል ጨምዳዳ ብለዉ ነዉ እንጂ በየበረሃዉና በየባህሩ ላይ እንደወጣ የቀረዉ ኢትዮጵያዊ ቁጥር እጅግ በጣም ብዙ እንደሆነ ሳያዉቁት ቀርተዉ አይለደም። ለመሆኑ ኢትዮጵያዉያን ይህንነ ሁሉ ቸግርና ጣጣ እያወቁ ወነድ፤ሴት፤ ወጣት አዛዉንት፤ ሳራተኛና ገበሬ ሳይል ሁሉም በጅምላ እትብታቸዉ የተቀበረበትን አገር እየለቀቁ የሚሰደዱት ለምንድነዉ?

ኢትዮጵያዉያን የሚሰደዱት ወያኔን እየጠሉ ነዉ ወይም የወየኔ ዘረኝነት፤ ከፋትና ጥላቻ እንገፍግፏቸዉ ነዉ ብለዉ የሚገምቱ ብዙ ኢትዮጵያዉያን ሰዎች ሊኖሩ ይቻላል። በጥቅሉ ሲታይ ግምታቸዉ ትክክለኛ ግምት ነዉ፤ የወያኔ ዘረኝነትና ፀረ ኢትዮጵያ አቋም ብዙ ኢትዮጵዉያንን አንገፍግፏል፤ አበሳጭቷል ወይም አስቆጥቷል። ሆኖም ሰዎች ስለተቆጡና ስለተንገፈገፉ ብቻ እንደ ምፅአት አገራቸዉን እየለቀቁ አይወጡም። ኢትዮጵያዉያን አገራቸዉን እየለቀቁ የሚወጡት ከወያኔ እስር፤ ድብደባና ግድያ ለማምለጥ ነዉ ብለን መገመትም እንችላለን። ትክክለለኛ ግምት ነዉ። ግን ስንቱ ኢትዮጵያዊ ነዉ ኬንያ፤ ማላዊ፤ ሞዛምቢክ፤ ግብፅ’ የመንና ሊቢያ ድረስ ሲንከራተት በየመንገዱ እየሞተ ለቀብር እንኳን የማይበቃዉ? ደግሞም የሰዉ ልጅ ባህሪይ የሚያሳድደዉንና የሚገድለዉን እየገደለ መሞት ነዉ እንጂ ሞትን እየሸሰ ጣረ ሞት ዉስጥ መግባት አይደለም። እዉነቱን ለመናገር የኢትዮጵያ ወጣት አገሩን በገፍ እየለቀቀ የሚሰደደዉ የወያኔ ዘረኞች ተስፋዉን ስለገደሉበትና የወደፊቱን ስላጨለሙበት ነዉ።

ተስፋ የሰዉ ልጆች የመኖር ዋስትና ነዉ። እኛ ሰዎች እየከፋንም ቢሆን ደስ እንዳለዉ ሰዉ የምንኖረዉ ይኖረናል፤ ይመቸናል ወይም ክፉዉ ቀን አልፎ መልካም ቀን ይመጣል በሚል ተስፋ ነዉ።ተስፋ የሞተ ቀን ለምን እንደምንኖር ስለማናዉቅ አገር ጥለን መሰደድ ብቻ ሳይሆን ከዚህም የከፋ ብዙ ነገር ማድረግ እንችላለን። ወያኔ ስልጣን ይዞ የቆየባቸዉን ያለፉት ሓያ ሦስት አመታትን ትተን ከ2000 እስከ 2007 ያሉትን ሰባት አመታት ብቻ ስንመለከት ማላዊ ሀይቅ ወስጥ፤ ሰሃራ በረሃ ዉስጥ፤ ኤደን ባህረ ሰላጠና ባቢኤል መንደብ ዉስጥ እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ኢትዮጵያዊ የአዉሬ ስራት ሆኖ ቀርቷል። ነፃነትና የተሻለ ኑሮ እናገኛለን ብለዉ በኮንቴነር ተጭነዉ ወደ ደቡብ አፍሪካ ይጓዙ የኘበሩ ከ50 በላይ ኢትዮጵያዉያን በእግራቸዉ እየተራመዱ ከገቡበት ኮነቴነር እሬሳቸዉ እየተጎተተ ወጥቷል።

ስደትንና እየተሰደደ ደብዛዉ የሚጠፋዉን ኢትዮጵያዊ በተመለከተ የኢትዮጵያ ህዝብ ብዙ ለጆሮ የሚከብዱ ዜናዎችን ሰምቷል። ባፈዉ ህዳር ወር ማለቂያ ላይ ከወደ የመን የተሰማዉ ዜና ግን ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ብቻ ሳይሆን ለምን ኢትዮጵያዊ ሆኜ ተፈጠርኩ የሚያሰኝ ነዉ። አገራቸዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ ተስፋቸዉን ያጨለመባቸዉ አያሌ ኢትዮጵያዉያን እንደ ዜጋ የሚመለከታቸዉና የት ገቡ ወይም የት ደረሱ የሚል መንግስት ስለሌላቸዉ ለቀበር እንኳን ሳይበቁ ቀይ ባህር ዉጧቸዉ ቀርቷል። ለወትሮዉ ለኢትዮጵያዉያን ስደተኞች ብዙም ግድ የሌለዉ የየመን መንግስት እንኳን ሰብዓዊነት ቆርቁሮት ቀይ ባህር እንደዋጠ ያስቀራችዉን ኢትዮጵያዉያን አስከሬን ፍለጋ ጀልባና መርከብ ሲያሰማራ፤ 99 በመቶ ኢትዮጵያዉያን መረጡኝ የሚለዉ የወያኔ አገዛዝ ግን የራሱ ዜጎች ሞት የተመቸዉ ይመስል ሰምቶ እንዳልሰማ ተመልካች መሆኑ አልበቃ ብሎት በተላላኪዉ ጠ/ሚኒስተር በኃ/ማሪያም ደሳለኝ አማካይነት ጭራሽ በአለም ዙሪያ የሚገኙ ስደተኞችን ሲዘልፍና ሲያጥላላ ከርሟል። አሜሪካ፤ አዉሮፓና መካከለኛዉ ምስራቅ ዉስጥ በየጋዜጣዉ በየቴሌቪዥኑና በማህበራዉ ሜድያዉ የአንድ ሳምንት የመወያያ አርዕስት ሆኖ የከረመዉ የኢትዮጵያዉያኑ እልቀት አገራቸዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ግን ለይስሙላ እንኳን ስማቸዉ አልተነሳም።

አዎ እኛ ኢትዮጵያዉያን የትም እንኑር የት በህይወታችን ቆመንም ሆነ ሞተን ዜጎቼ ብሎ የሚቆረቆረልንና ለወገንና ለአገር ልጅ የሚደረገዉን ልዩ እንክብካቤ የሚየደርግልን መነሰግስ/ት የለንም። አልፎ አልፎ የወያኔ ባለስልጣኖች አዉሮፓና አሜሪካ ሲመጡ በየኤምባሲዉና በሚስጢር በሚያዙ ሆቴሎች ለዉይይት የሚጋብዙት ታማኝ ሎሌዎቻቸዉንና የአንድ አካባቢ ተወላጅ የሆኑ ሰዎችን ነዉ እንጂ ብዛት ያለዉን ሌላዉን ኢትዮጵያዊ የት ወደቀ ብለዉ እንኳን አይጠይቁም። እንዲያዉም ከቅርብ ግዜ ወዲህ ከጠ/ሚ ኃ/ማሪያም ደሳለኝን ጨምሮ ሁሉም የወያኔ ባለስልጣኖች በዉጭ አገሮች የሚኖረዉን ኢትዮጵያዊ እንደ ባዕድ መመልከና መዝለፍ ጀምረዋል። ይህ ሁሉ የሚያሳየን አገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ አገሮች እኛ ኢትዮጵያዉያን ተገናኝተን እርስ በርስ ካልመከርንና ችግሮቻችንን በጋራ እኛዉ ካልፋታን እንደ ዜጋ የሚንከባከብልን ቀርቶ እንደ ሰብዓዊ ፍጡር የሚመለከተንም እንደሌለን ነዉ። ይህንን ደግሞ ባለፈዉ አመት ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ አሁን በቀርቡ ደግሞ የመን ዉስጥ በግልጽ አይተናል። ወገኖፐቻችን የሆኑ ኢትዮጵያዉያን የመን እንገባለን ብለዉ ቀይ ባህር ዉስጥ የአሳ ሲሳይ ሆነዉ ሲቀሩ በጠ/ሚኒስቴርነት ስም የወያኔ ተላላኪ የሆነዉ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ጭራሽ በአለም ዙሪያ የሱን እርግጫ፤ እስርና የጅምላ ግድያ ሸሽተዉ የተሰደዱ ሲትዮጵያዉያንን እጅግ በጣም አስነዋሪና አስጸያፊ በሆነ መለኩ ሲዘልፋቸዉ ተሰምቷል። የሚገርመዉ ባለፈዉ ህዳር ወር ማለቂያ ላይ ቀይ ባህር ዉስጥ ሰጥመዉ ካለቁት ከሰባ በላይ ወገኖቻችን ዉስጥ ገሚሶቹ ባለፈዉ አመት ከሳዑዲ ተባርረዉ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱና እነ ቴዎድሮስ አድሃኖም ኢትዮጵያ ለዜጎቿ የማታደርጉወ ምንም ነገር የለም ብለዉ የተናገሩላቸዉ ሰዎች ናቸዉ።

ባጠቃላይ እኛ ኢትዮጵያዉያን አገራችን ዉስጥ ተዋርደናል፤ በስደት በምንኖርባቸዉ አገሮች ዉስጥም ተዋርደናል። አገር ዉስጥ ወያኔ እንዳሻዉ ያስረናል፤ ይደበድበናል ይገድለናል። ይህንን ጠልተን ከአገራችን ስንሰደድ ደግሞ በየበረሃዉና በየባህሩ ላይ ክብርና ወግ ላለዉ ቀብር እንኳን ሳንበቃ እንደወጣን እንቀራል። ካሁን በኋላ እንደ ህዝብ መብታችንና ነጻነታችን ተከብሮ አንደ አገር ደግሞ አንድነታችንና ዳር ድንበራችን ተጠብቆ ለመኖር የምንፈልግ ከሆነ አማራጩ አገራችንን አንደ ምጽዐት ለቅቀን መዉጣት ሳይሆን ለዚህ ሁሉ ዉርደትና መከራ ከዳረጉን ዘረኞች ጋር ፊት ለፊት መግጠምና ይለየለት ማለት ብቻ ነዉ። ወያኔ የሚፈጽምብን ሰቆቃ እንዲቆም፤ አስርና ግድያዉ አክትሞ ስደት እንዲያበቃ ብቸኛዉ አማራጭ እነዚህ ነገሮች ሲፈጸሙ መግለጫ ማዉጣትና ከንፈር መምጠጥ ብቻ ሳይሆን የችግሮቻችንን ምንጭ ማድረቅ ነዉ፤ ወይም ዘረኛዉን የወያኔ አገዛዝና እሱ የገነባዉን ዘረኛ ስርዐት ነቃቅለን ማስወገድ ብቻ ነዉ። በዜግነታችን ተከብረንና በገዛ አገራችን ኮርተን መኖር የምንችለዉ ይህንን ስናደርግ ብቻ ነዉ።

የወደፊቱ የተሻለ የህይወት ተስፋ ያለው ወያኔ መቃብር ላይ ነው!!

ወያኔ በሀገራችን የዘረጋው ማህበራዊ ፖለቲካዊና የኢኮኖሚ ስርአት ለጠቅላላ ህዝባችን፣ በተለይ ለወደፊቱ ሀገር ተረካቢ ወጣት ሲኦል መሆኑ ቅጥሏል። በሀገሬ ውስጥ፣ ሰርቸ የተሻለ ህይወት እኖራለሁ ብሎ ማለም ቅዠት ሆኗል። ከዚህ ይልቅ ያብዛኛውን ወጣት ተስፋ ሀገር ጥሎ በገፍ መሰደድ ከሆነ ውሎ አድሯል።

በእጅጉ በሚዘገንን ሁኔታ በግፍ ተሰቃይተው ከሳውዲ አረቢያ ወደሀገራቸው ከተመለሱት ከ160 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ግማሽ ያህሉ ተመልሰው መሰደዳቸውን በቅርቡ የወጣ ጥናት አረጋግጦል። በዚህ ሁኔታ ከተሰደዱ ወገኖቻችን ውስጥ ቁጥራቸው ከ70 በላይ የሚሆኑት ቀይ ባህር ላይ የነበሩበት ጀልባ ሰምጦ አልቀዋል። እነዚህ ወገኖቻችን ጉዞቸው በሞትና ህይወት መሃል መሆኑን አስቀድመው ያውቃሉ። ይህንን ያስመረጣቸው ግን የወያኔ ስርአት ነው። የወያኔ ስርአት የተመቻቸው ለስርአቱ ሹመኞችና ለዘመድ አዝማድ ከዚያ ከተረፈ ለጎሳ ተወላጆቻቸው ብቻ ነው። ሀገሪቱ ውስጥ ተገኘ የሚባል የኢኮኖሚ እድገት ካለም ከዚሁ ከጠባብ ቡድን ጥቅም አልፎ መከረኛውን ህዝብ የሚጠግን አልሆነም።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ከተስፋ ቆራጪነትና ሞትና ህይወትን ከሚያስመርጥ አስከፊ ህይወት ያለፈ ምርጫ አለ። ዋናው ምርጫቸውም ይህ ሊሆን ይገባል፤ ምርጫው ለዚህ መከራና ሀዘን ውርደት የዳረገንን ጨካኝ የወያኔ ስርአት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማስወገድ ነው።

ወያኔ የህዝቡ ጉስቁልናና ስቃይ ጉዳዩ አለመሆኑን ባለፉት ሳምንታት ከ70 በላይ ወገኖቻችን ቀይ ባህር ውስጥ ሰምጠው: አለም በሀዘን በሚመለከተንና መንግስት አለ ብሎ የሀዘን መግለጫ በሚልክበት ሰአት የብሄረሰብ ቀን በሚባል የቦልት በአል የወያኔ ሹሞች ብዙ ሚሊዮን ብር አውጥተው በውስኪ እየተራጩ ይጨፍሩ ነበር።

ይህ አልበቃ ብሎ አሻንጉሊቱ ሃይለማርያም ደሳለኝ በስደተኛው ላይ ለሰሚ የሚቀፍ የወረደ አሉባልታና ስድብ ሲያወርድ ሰምተናል፣ ራሱን ያወረደ ተረት ተረትም ተናገረ። በሥልጣን የመባለግ ዝንባሌያቸው ሳይውል ሳያድር በሚጠቀሙት የባለገ አዋራጅ ቃላት የመጠቀም ርሃባቸው አሳየን።

የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፦ በምድረ ኢትዮጵያ የተስፋ መቁረጥና ለወያኔ ሎሌዎቹ መሳለቂያ እንድንሆን ያበቃን ይህ የነቀዘ ዘራፊ የወያኔ ስርአት ብቻ ነው። ይህ ሁሉ ስቃይና ውርደት የሚቆመው ወያኔ ሲወገድ ብቻ መሆኑን ሁላችንም ጠንቅቀን ልንረዳ ይገባል። በቅርቡ ዱላውንና ግፉን ሁሉ ለመቀበል ቆርጠው ወያኔን ከተጋፈጡት የሰማያዊ ፓርቲ አባልና ደጋፊ ወጣቶች ብዙ ልንማር ይገባል። እንደእባብ በጭካኔ መቀጥቀጣቸው አጠነከራቸው እንጂ አላዳከማቸውም።

Sunday, December 21, 2014

" ኦ ባህር ዳር ! "

ሀገር ይዘን ፣ ሀገር አጥተን
ሰው ሞልቶ ፣ ሰው ጠፍቶብን
ባህር ወደን ፣ ባህር አጥተን
ባህር ይዘን ፣ ውሃ ጠምቶን
እውንት ይዘን ፣ ውሸት ተብለን
ድህነትን አቅፈን ፣ አድገት እያልን
ሰብዕናውን ሳናስቀድም ትተን
በእድገታችን ልማት ተመጻድቀን
የመናገር መጻፍ ፣ መቃወሙን
ፈጣሪ የሰጠንን መበት ተነፍጎን
ፈጣሪ አያለ ፣ ሰው አምልከን
ሹም እያለ ፣ ፍትህ ርቆን
የባህር ዳሩ ማህበል አይሎብን
ሰው ተጎዳ ፣ ሀዘን ጎዳን ...

እናማ!

አዝነን ከፍቶን፣ ጊዜ ጎድሎብን
የሞተ ቀባሪ ፣ ከንፈር መጣጭ ሆነን
ጨንቆን ጠቦን ፣ ፍርሃት አዋርዶን
የቁርጥ ቀን ልጆችን ግንባር እያስመታን
የቆሙለትን ፍትህ ጥያቄ እያጥላላን !
እዚህ ደርሰን እንዲህ ሆንን ...

ለሆዳችን አድረን ፣ሰብዕናን አስረግጠን
እውነትን በገሃድ መጋፈጥ ገዶን
ውሸትን የመቃወም ወኔ ተሰልበን
በአንቶ ፈንቶ በብርቅርቅ ህይወት ተታለልን !

ዛዲያማ ...

ራሳችን ሳንሆን ፣ ሳናዳምጠው ውስጣችን
መሄጃ መድረሻ ፣ ጠፍቶን መንገዳችን
ለፍትህ ሳንተጋ ፣ ለመመጻደቁ ተግተን
ፈጣሪን ሰው አድርገን ፣ ሰውን እያመለክን
የማይጨበጥ የማይሆነውን እያወራን
በማይዳሰስ ተስፋ ፣ አመታትን ገፋን !

የኢትዮጵያ መንግሥት (ገመና ክፍል 2)


ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (ከዝዋይ እስር ቤት)

በዚህ አውድ ለማቅረብ የተገደድኩበትን ዘግናኝ ታሪክ፣ ወደር በሌለው አስከፊነቱ የተነሳ ለንባብ ባላበቃው በወደድኩ ነበር፡፡ ግና! ይህ መንግስታዊ የጭካኔ ተግባር፣ ዛሬም በምስኪን ዜጎች ላይ እየተፈፀመና ብዙዎችን ሰለባ እያደረገ በመሆኑ ህዝቡ ይህን ሊሸሸግ እየተሞከረ ያለውን መከራ ተረድቶ ሥርዓቱን በአደባባይ ዓመፅ “ሃይ!” ይል ዘንድ ትርክቴን ለማጠናቀር ተገድጄያለሁ፡፡ ለእስር ያበቃኝ የጋዜጠኝነት ሙያዬም ተጨማሪ ዕዳ ጭኖብኛል፡፡

“ጄል-ኦጋዴን”

ጄል ኦጋዴን በሱማሌ ክልል ርዕሰ-መዲና የሚገኝ፤ ለ800 እስረኞች ታቅዶ በ1992 ዓ.ም የተገነባ እስር ቤት ነው፡፡ የግቢውን ዙሪያ ከከበበው አጥር በግምት 15 ሜትር ፈንጠር ብሎ ሌላ ተደራቢ የድንጋይ አጥር ተበጅቶለታል፡፡ እስከ ሚያዝያ 24 1999 ዓ.ም ድረስ እስር ቤቱ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ካሉ መሰል ማጎሪያዎች ብዙም የተለየ አልነበረም፡፡ በዚህ በተጠቀሰው ቀን የኦጋዴን ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) ታጣቂዎች፣ አቦሌ እና ሰንደሬ ወታደራዊ ካምፖችን ጨምሮ፣ በነዳጅ ዘይት ፍለጋ ላይ የተሰማሩ ቻይናውያን ባለሙያዎች መኖሪያ ሰፈር ላይ የሰነዘሩትን ከባድ ጥቃት ተከትሎ የፖለቲካ እስረኞች ብቻ የሚታጎሩበት እስር ቤት ከሆነ ወዲህ ግን በዋይታ የሚናወፅና በደም ጅረት የሚጥለቀለቅ ምድራዊ ሲኦል ለመሆን በቅቷል፡፡ መንግስት በጥቃቱ ከዘጠኙ ቻይናውያን ጋር 74 ሲቪል ዜጎችና ወታደሮች መገደላቸውን ቢያምንም፤ የአካባቢው የአይን እማኞች ከሰራዊቱ ብቻ እስከ 300 እንደተሰዉ ይናገራሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ኦብነግ እንደ አል-ቃይዳ እና አል-ሸባብ የአባላቱን አስከሬን ትቶ የመሸሽ ልምድ ስለሌለው በቡድኑ ላይ የደረሰውን ጉዳት በትክክል ለማወቅ አዳጋች እንደሆነ ቀጥሏል፡፡

የሆነው ሆኖ ከዚህ ጥቃት በኋላ በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ የሚመራ አምስት ከፍተኛ ባለስልጣናትን ያካተተ የደህንነትና (ጄነራል ሳሞራ የኑስ እና ጌታቸው አሰፋ ያሉበት) የፀጥታ ኮሚቴ ተቋቁሞ የሚከተሉትን (ዛሬም ድረስ እየተተገበሩ ያሉ) አስቸኳይ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡ ‹‹ከጅጅጋ ውጭ ባሉ በክልሉ ማንኛውም የመንግስትም ሆነ የግል ተሽከርካሪ እንዳይንቀሳቀስ፣ ትዕዛዙን ጥሶ የተገኘ ከነጭነቱም ሆነ ተሳፋሪዎቹ በከባድ መሳሪያ እንዲመታ፤ አብዛኛውን ህዝብ በፍጥነት ከመኖሪያ ቀዬው በማፈናቀል ለቁጥጥር ወደሚያመቹ ከተሞች ማስፈር (በ2006 ዓ.ም መጀመሪያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ካሳ ተክለብርሃን 2300 መንደሮችን ወደ ተመረጠ ቦታ ማስፈሩ እንደተሳካ መናገሩን ልብ ይሏል)፤ ወታደራዊ መኪና ላይ ምንም አይነት የደፈጣ ጥቃት ከደረሰ በአቅራቢያው የሚገኝ መንደርን ያለርህራሄ ማውደም (ለማሳያ ያህልም ፍልቼ፣ ቃሙዳ፣ ሳስባኒ፣ ሁለሌ፣ ለንካይርተ፣ ቻለሌን… የመሳሰሉ ከተሞች ወደ ፍርስራሽነት መቀየራቸውን መጥቀስ ይቻላል) እና ከአንድ ሻምበል ያነሰ ኃይል ለአስቸኳይ ጉዳይም ቢሆን ከቦታ ቦታ እንዳይንቀሳቀስ›› የሚል እንደነበር ይታወሳል፡፡ ከዚህ በኋላም ኤታማዦር ሹሙ ጄነራል ሳሞራ የኑስ በክልሉ የሚገኘውን የደቡብ ምስራቅ ዕዝ ወታደራዊ አዛዦችን በቪዲዮ ኮንፈረንስ ሰብስቦ ማብራሪያ ሰጥቶ ሲያበቃ ውሳኔውን ያለምንም ማቅማማት ተግባራዊ እንዲያደርጉት በጥብቅ አሳስቧል፡፡

ደቡብ ምስራቅ ዕዝ ከኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት (ከ1993 ዓ.ም) በኋላ በምስራቅ ኢትዮጵያ የሰፈረ ሲሆን እስከ ታህሳስ 1999 ዓ.ም ድረስ በሜ/ጀነራል ባጫ ደበሌ ሲመራ ቆይቷል፡፡ ከታህሳስ 1999 እስከ 2000 ዓ.ም ደግሞ ብርጋዴር ጄነራል ስዩም አስተዳድሮታል፤ በዚሁ ዓመት ከጥቅምት እስከ ሚያዚያ ድረስ ባሉት ጊዜያትም በብ/ጄነራል ሙሉጌታ በርሄ ስር የቆየ ሲሆን፤ ከሚያዚያ 2000 ዓ.ም አንስቶ አሁን ድረስ እየተመራ የሚገኘው በሌ/ጄነራል አብርሃም ወ/ማርያም (ቅፅል ስሙ ‹‹ኳርተር››) እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ዕዝ ውስጥ በዋናነት ሶስት ክፍለ ጦሮች (12ኛ፣ 13ኛ እና 32ኛ) ክልሉን ሶማሊያ ድንበር ድረስ እንዲቆጣጠሩት ተመድበዋል፡፡ ሰፈራቸውን ነገሌ ቦረና ያደረጉት 43ኛ እና 44ኛ ክፍለ ጦሮችም፣ ኦጋዴን ድረስ እንዲንቀሳቀሱ ትዕዛዝ ተሰጥቷቸዋል፡፡ በአናቱም የአግአዚ ኃይል በቀድሞ ምክትል አዛዡ ብ/ጄኔራል ገ/መድህን ፈቀደ (‹‹ወዲ ነጮ››) ስር ሆኖ አልፎ አልፎ በተደራቢነት እየተላከ በነዋሪዎቹ ላይ በደረሰው ጅምላ ጭፍጨፋ እና ዘግናኝ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የተሳተፈ ስለመሆኑ ከወታደራዊ መረጃ ምንጮቼ ሰምቻለሁ፡፡ ይህም ሆኖ ለደረሱ እልቂቶችና ጭፍለቃዎች በግንባር ቀደምትነት ተጠያቂ ተደርገው የሚጠቀሱት ከጄነራል ሳሞራ፣ ከጀኔራል ‹‹ኳርተር›› እና ከክልሉ ፕሬዝዳንት በተጨማሪ በብ/ጄነራል በየነ ገ/እግዚአብሔር (‹‹ወዲ አንጥር››) የተመራው 12ኛ ክ/ጦር እና በብ/ጄነራል ፀጋዬ ገ/ጨርቆስ (‹‹ጀብጀብ››) ዕዝ ስር የነበረው 13ኛ ክ/ጦር እንደሆነ ይነገራል፡፡ ኦብነግ በስፋት ይንቀሳቀስባቸዋል ተብለው የሚታሰቡት፡- ደገሃቡር፣ ቀብሪደሃር፣ ዋርደር፣ ጎዴ እና ቪቅ ከተሞች መደበኛ የጦር ቀጠናዎች ከሆኑ 15 አመት ያለፋቸው በመሆኑ፣ ከሌሎች የክልሉ አውራጃዎች በተለየ ሁኔታ የችግሩ ቀጥተኛ ተጠቂ ሆነዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትም የሚፈፅማቸውን ኢ-ህገ መንግስታዊ ድርጊቶች ለመሸፈን እንደ ቀይ መስቀል፣ ዓለም-አቀፍ ሚዲያዎች፣ ግብረሰናይ ድርጅቶችና መሰል ተቋማት ከጅጅጋ ውጪ እንዳይንቀሳቀሱ በኃይል አግዷል፡፡ ይህ ኩነትም በ ዙ-23 እና በሌሎች ከባድ መሳሪያዎች ተደብድበው ከምድረ-ገፅ የጠፉ መንደር ነዋሪዎች፣ የቤት እንስሳት እና ቁሳዊ ንብረቶች በአንድነት ተቃጥለው መውደማቸውን ዛሬም ድረስ በምስጢርነት ሸሽጎ ለማቆየት አስችሎታል፡፡

Saturday, December 20, 2014

የኦባንግ ጉዞና ለዲያስፖራው ፖለቲካ ያለው አስተዋጽኦ!

በሽመልስ ወርቅነህ

 ቅርቡ በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ በአቶ ኦባንግ ሜቶ በተጠራው ስብስባ ላይ የመገኘት እድል አጋጥሞኝ ነበር:: በስብሰባው ላይ ከተለያዩ የአለም ክፍሎችና ከአሜሪካ ግዛቶች የተሰባሰቡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል::

የስብሰባው መሪ ሀሳብ “ስለ እያንዳንዳችን ከመናገር እያንዳንዳችን እንነጋገር” የሚል ድፍረትን፣ ግልፅነትን፣ መከባበርን፣ መነጋገር መቻልን ሃላፊነት በተሞላበት ስሜት ይቀርቡ በነበሩት አስተያየቶች የሚያረጋግጡ ከመሆናቸውም በላይ የተለየዩ የፖለቲካ አመለካከት፣ እምነት እንዲሁም የተለየዩ ብሄረሰቦች ዉሁድ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጠረጴዛ ዙርያ ተቀምጠው ያነሱዋቸው የነበሩት ሃሳቦች በጥንታዊት ኢትዮጵያና በአዲሲቱ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ገመድ ጉተታ ግራ ለተጋቡ ጥሩ አስተማሪ መድረክ ነበር::

ኢትዮጵያ የምትባል ጥንታዊት ሃገርን የሲኦል መገለጫ አድርገው ለሚስሉዋት የህወሃት ኢሃዴግ ደጋፊዎችና ተመሳሳይ አመለካከት ያላቸው የፖለቲካ ሰአሊዎች ወይም ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ያላቸውን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቁርኝት በፖለቲካ ብሩሽ ለማጥፋት የሚንደፋደፉ ያሉትን ያህል አዲሲቱን ኢትዮጵያን በጎሪጥና በሃሳባቸው የተለየ ቅርፅ ሰጥተው ለሚባንኑትም ሁለቱም አካሄዳቸው ሃገራችንን መጉዳቱን የስብሰባው ተሳታፊዎች አማካይ መንገድ እንዳለ በማሳየት ለዚህም ብቸኛ መንገዱ እውነትን መጋፈጥና መነጋገር ብቻ እንደሆነ ያሰመሩበት ጉዳይ ነው::

ስለ ዲሞክራሲ ማውራትና በዲሞክራሲ ህይወት ውስጥ መኖር ያለውን ልዩነት በተሳታፊዎቹ አቀራረብና በመድረኩ አመራር ያለው የዳበረ የፖለቲካ ግንነት አመላካች ነበር::

ይህ ወቅቱ የጠየቀውና አብዛኛው መድረክ ያጣና የታፈነ ኢትዮጵያዊ ድምፅ በመሆኑ ወንድማችን ኦባንግና ሶሊዳሪቲ ይህን መድረክ በመክፈታቸው ከፍተኛ ምስጋናና ድጋፍ ሊደረግላቸው ይገባል:: ከተለያዩ ክፍለ አለማትና ከአሜሪካ ስቴቶች በስፍራው ተገኝታችሁ አሁን በሀገራችን የሚታየውን ችግር ለመፍታት የሚያስችሉ የበሰሉ ሃሳቦችን ላቀረባችሁ ምሁራን የሃይማኖት አባቶችና እናቶች ታላቅ አክብሮትና ምስጋና ይድረሳችሁ::

 ኢትዮጵያውያን ዝርዝር ሂደቱን ክፍል 1፣ ክፍል 2 እና ክፍል 3 ከዚህ ማግኘት ትችላላችሁ::


በተለይም በዲያስፖራው የሚታየው ጫፍና ጫፍ ቆሞ በስልጣን ላይ ካለው አምባገነን የህወሃት ኢሃዴግ መንግስት ባልተናነሰ ሁኔታ ባለፉት አመታት ኢትዮጵያውያንን እየከፋፈሉ ያሉት ጥቂት የፖለቲካ ሃይሎችና በስመ ደጋፊነት የተሰለፍን ወገኖች አካሄድ ትግሉን ወደ ሁዋላ ከማስኬድ በስተቀር ያስገኘው ፋይዳ እንደሌለውና አሁንም መፍትሄው ድፍረትና የመቻቻል ፖለቲካ ብቻ እንደሆነ ከምንም በፊት ለእውነት እራስን ም ማስገዛት ተቀዳሚ ተግባር ና የፖለቲካው ወሳነ ሃይል ህዝብን ማእከል ያደረገ ትግል ብቻ መ ሆኑን ከዚህ ስብሰባ መገንዘብ ይቻላል::

ዲያስፖራው የኢትዮጵያን ፖለቲካ በአብዛኛው የሚገመግምበት መድረኩ የፓልቶክ ክፍሎች በመሆናቸው በአካል ተገናኝቶ በመነጋገርና በኮምፒዩተር ጀርባ ሃሳብንም ሆነ ልዩነትን ማስተናገድ ያላቸውን ልዩነት በመገንዘብ ለአካላዊ ግንኙነት ትኩረት በመስጠት መሰባሰቡ ያለውን ፋይዳ መገንዘቡ የወቅቱ ጥያቄ ይመስለኛል::

ኢህአዴግ በባህር ዳር ግድያ ፈጸመ! በባህርዳር ዋይታ ሆነ!


 በእምነት ቦታ ይገባኛል ነዋሪዎች ባሰሙት ጥያቄ ኢህአዴግ የጥይት መልስ ሰጠ፡፡ ድርጊቱን በምስል በማያያዝ በተለያዩ ማኅበራዊ ገጾች ያሰራጩት ክፍሎች አዛውንትና መነኮሳት ሳይቀሩ መደብደባቸውንና መቁሰላቸውን በምስል አስደግፈው አመልክተዋል፡፡
አኻዙ በትክክለኛው ባይታወቅም አምስት የሚደርሱ ሰዎች ሕይወታቸው እንዳለፈ በማኅበራዊ ገጾች የተበተኑት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ አንዳንድ የድረገጽ ዜናዎችም በአኻዝ ከመለያየት በስተቀር የግድያውንና የድብደባውን መጠን በመግለጽ ዜናቸውን አስፍረዋል፡፡

ድርጊቱን የፈጸመው ኢህአዴግ ስለሞቱትና ስለተደበደቡት መነኮሳትና አዛውንት እንዲሁም ሌሎች ወገኖች ይህንን መረጃ እስካጠናቀርንበት ጊዜ ድረስ ይፋዊ ማስተባበያ አልሰጠም፡፡ ይልቁንም ከሁለት ሳምንት በፊት ኢህአዴግ የፌዴራል ምክት ሚ/ሩን በፖሊስ ፕሮግራም በማቅረብ የፌስቡክ ዜናዎችን አትመኑ በማለት ማሳሰቢያ ሲሰጥ ነበር፡፡
“ነገረ ኢትዮጵያ” የተሰኘው የፌስቡክ ገጽ ቀበሌ፣ ወሰንና የምክርቤት ስም ጠቅሶ የተፈጠረውን ሁኔታ ከዚህ እንደሚከተለው አስፍሮታል፡፡

“የአማራ ክልል አስተዳደር የቤተ ክርስቲያን ንብረት የሆነውን የታቦት ማደሪያ ለመንገድና ለጥቃቅንና አነስተኛ ሱቆች መስሪያ እንዲነጠቅ ማዘዙን ተከትሎ በቤተ ክርስቲያን የተጠራው ተቃውሞ አሁንም ድረስ እንደቀጠለ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ከታቦት ማደሪያው 9 ሜትር ገብቶ መንገድ እንዲሰራ እንዲሁም ቀሪው ለጥቃቅንና አነስተኛ ሱቆች እንዲሰጥ አስተዳደሩ ማዘዙን ተከትሎ ታቦት ማደሪያውን ከነገ ህዳር 10/2007 ዓ.ም ጀምሮ ሊፈርስ እንደነበር መረጃው የደረሳት ቤተ ክርስቲያን ለህዝበ ክርስቲያኑ አስቸኳይ ጥሪ ማስተላለፏ ታውቋል፡፡ ህዝቡም “በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተገናኝተን በእግዚያብሄር ስም በአስቸኳይ ጠርተንዎታል” በሚል በቀረበለት ጥሪ መሰረት ዛሬ ጠዋት ተቃውሞውን የጀመረ ሲሆን አሁንም ድረስ እንደቀጠለ ተገልጾአል፡፡ ህዝቡ ቀበሌ 10 በሚገኘው አዲሱ ምክር ቤት እንዲሁም በዚሁ ቀበሌ በሚገኘው የቀድሞው ምክር ቤት በመገኘት ተቃውሞውን እየገለጸ ይገኛል፡፡ በተለይ በአዲሱ ምክር ቤት ተገኝቶ ተቃውሞውን እያሰማ የሚገኘውን ህዝብ በኃይል ለመበተን ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡”

Wednesday, December 17, 2014

I’m longing for you, comrades

By Zelalem Kibret

From Kilinto prison, Addis Ababa Ethiopia 

O! The mighty reminiscence! Of all the thoughts nothing is more haunting than reminiscence. When I read, walk; sleep — in all of my daily routines I recall yesterday. Yesterday as if it is painted by one of the renaissance realist painters. Those yesterdays are here facing me virtually, if Raphael and Titan meets for a team work and puts those yester times in a big canvas.

How you doing comrades? You might be confused by my word choice of comrade. I got you Yes, our (me and you) formal relationship was a ‘Master’ pupil, ‘teacher – Student’, ‘Boss – Subordinate ‘ relationship. I am not comfortable with such hierarchical dichotomy. Rather, we were friends. I think we are still friends but, from afar and I hope our friendship will blossom by tomorrow. Hence, our bond of relationship is the rationale behind my choice, comrade (with all its political connotations) instead of something else.

Comrades, since my departure from the scene that is common for both of us, I know some of you are done with your formal schooling and I know that some of you are still counting your orders in the main dish, please consider my humble wishes.  For those who are done with your time in school, I wish a good time of preparation for the sequel. For those who are still struggling in school, have a wonderful fight.

The ‘departed’

Friends, if you remember we used to have a term of relationship, which put us in a promise to get together in the classroom. Regrettably, I am the one who fails to fulfill my promise but, forgivably. I say, forgivably. Because it is not I rather tyranny that should take the blame. Dictatorship is the hurdle that set us apart. It is the state which is the sinner. I fail to keep my words of promise because of a force majeure called despotism.

A short summery of what happens to me may give you the excuses to forgive me for my incompliance with terms of our promise.

የነጻነት ታጋዮች መልዕክት ከቃሊቲ እና ቂሊንጦ

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

‹‹በሰላማዊ ሰልፈኛ ላይ ዱላ መሰንዘር ሽንፈት ነው›› እስክንድር ነጋ

ሰማያዊ ፓርቲ እና ሌሎች በትብብሩ ውስጥ የታቀፉ ፓርቲዎች በጠሩት የአዳር ሰልፍ ላይ የወጡ ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የተወሰደውን አሳፋሪ እርምጃ ሰምቻለሁ፡፡ እርምጃው ሁለት ነገሮችን በጉልህ ያሳዬ ነበር፡፡ አንደኛ የኢህአዴግ መራሹ መንግስት ሽንፍትን ያሳየ ነው፤ ሁለተኛው ደግሞ ሰላማዊ ትግሉ እየተጠናከረ መምጣቱን ያመላከተ ነው፡፡

አንተ ባዶ እጅህን መብትህን ለመጠየቅ ስትንቀሳቀስ፣ መሳሪያ ወደታጠቀ አካል በሰላም ስትገሰግስ ባለመሳሪያው ዱላውን ከሰነዘረብህ አሸናፊው አንተ ሰላማዊው ታጋይ ነህ፡፡ በትብብሩ ሰልፍ ላይ የሆነው ይኸው ነው፡፡ አሁን ሰላማዊ ትግሉ ፍጹም ሰላማዊነቱን እንደጠበቀ መጠናከር ነው ያለበት፡፡ ሰላማዊ ትግል ላይ ልብ ማለት ያለብን ነገር አለ፤ እሱም ሰላማዊ ሆኖ መዝለቅ የሚለው ጉዳይ ነው፡፡

ሰላማዊ ታጋይ ይሰደባል፣ ይደበደባል፣ ይሞታልም፡፡ ግን ደግሞ ሰላማዊ ታጋይ አይሳደብም፣ አይደባደብም፣ አይገድልም፡፡ ይህ ከሆነ ሰላማዊ ትግል ያሸንፋል፡፡ አምባገነኖች ሰላማዊ ታጋዮችን በተለያየ መንገድ ከሰላማዊነታቸው እንዲወጡ ሊገፋፏቸው ይሞክራሉ፤ ስሜት ውስጥ በመክተትም የኃይል በትራቸውን ለማሳረፍ ይቋምጣሉ፡፡ ይህ ሴራ ሰላማዊ ታጋዮችን ሊያዘናጋቸው አይገባም፡፡

በቀደም በተደረገው ሰልፍ ላይ ድብደባው በሰላማዊ ሰዎች ላይ መፈጸሙ ለተደብዳቢዎቹ ሳይሆን ሽንፈቱ ለደብዳቢዎቹ ነው፡፡ በደረሰው ድብደባ ባፍርም፣ ባዝንም በውጤቱ ግን ደስተኛ ነኝ፤ ምክንያቱም ሰላማዊ ሰልፈኞች ሰላማዊነታቸውን አሳይተዋልና! በሰልፉ ወቅት ድብዳባ እና እስር የደረሰባቸውን የመብት ጠያቂዎች ሁሉ በርቱ ልላቸው እፈልጋለሁ፡፡ ባደረጉት ሰላማዊ እንቅስቃሴ በጣም ኮርቻለሁ፡፡ ሰላማዊና ህጋዊ ትግላችሁን ቀጥሉ ማለትም እፈልጋለሁ!

Sunday, December 14, 2014

የፈሪ ዱላ ነፃነትን አያስቀርም !

ህወሃቶች ኢትዮጵያን “ለመምራት” ያላቸው አቅም ተሟጦ አልቋል። ፍርሃት አቅላቸውን አስቷቸዋል። ፍርሃታቸው ጭካኔን ወልዷል። ይህ ጭካኔያቸው ወሰን አጥቷል። ልጥ ባዩ ግዜ እባብ እየመሰላቸው ልጡን በቆመጥ ሲደበድቡ ውለው ያድራሉ። ፍርሃት ያ ደካማ ማሰቢያቸውን ጥርቅም አድርጎ ዘግቶታል። የፈሪ ዓይን ማየት እንደማይችል፤ ጆሮውም መስማት እንደተሳነው ከህወሃቶች ተርድተናል።

እኛ ግን እንዲህ እንላለን ህወሃቶች ዓይናችው እያየ፤ ጆሮዋቸውም እየሰማ የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነቱን ይቀዳጃል። እውነት እውነት እንላችኋለን የነፃነቱ ግዜ እሩቅ አይደለም። ህወሃቶች ከነፍርሃታቸው ወደ መረጡት መቃብራቸው መውረዳቸው እንደማይቀር ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ የለንም።

የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫ ነፃነት ነው።ይህን ነፃነት ከህወሃቶች እጅ ለምነን የምናገኘው አይደለም። ነፃነታችንን ታግለንና አሸነፈን የምንቀዳጀው ንፁህ ሃብታችን ነው። ይህን ንፁህ ሃብታችንን በቀማኞች አስነጥቀን ዝም ብንል እርግማን ይሁንብን ያሉ ኢትዮጵያዊያን እያደረጉ ያሉት ትግል ተስፋ ሰጪ ነው። በተለይም ወጣቶች እምቢ ለክብሬ፤ እምቢ ለነፃነቴ እምቢ ለማያውቁን ህወሃቶች ማለታቸውን ስናይ ተስፋችን ከመቸውም ግዜ በላይ ለምልሟል።

ህወሃቶች ኃላፊነት የሚሰማቸው ቢሆኑ ኑሮ “በሃሳባችሁ ባንስማም ልዩነታችሁን መግለፅ የምትችሉበትን መብት ለማስከበር እሰከ ሞት ድረስ እንቆማለን” ይሉ ነበር። አለመታደል ሁኖ ህወሃቶች አገር፤ ህዝብ፤ ወገን የሚባል ቋንቋ በውስጣቸው የለም። ኢትዮጵያም አገራቸው አትመስላቸውም፤ ህዝቡም ወገናቸው እንደሆነ አይሰማቸውም። ህወሃቶች በወንድምና እህቶቻቸው አጥንት ላይ ቁመው ለኢትዮጵያና ለህዝቧ ጠላት መሆንን መርጠዋል። ለነፃነት ብለው በትግል ሜዳ የተሰው ጓዶቻቸውን ሞትም ከንቱ ሞት አድርገው አስቀርተውታል። ይሄ እርግማን ነው።ይሄ እርግማን ደግሞ አሁን ባሉት ህወሃቶች ብቻ የሚቆም ሳይሆን ወደ ልጅ ልጆቻቸው እንደሚሸጋገር ህወሃቶች ለማሰብ አቅቷቸዋል።

ህወሃት የስለጠነ ፖለቲካ አያውቅም። የነፃነትንም ትርጉም ሳያውቅ ነፃ አውጪ ነኝ ይላል። በአገሪቷ ጫንቃ ላይ መቆየት ብቻ የህልውናየ መሠረት ነው ብሎ ካመነም ቆይቷል። ይህን የህልውናየን መሠረት የሚነካ ሁኔታ ከተፈጠረም ጠመንጃየ መመኪያ ጉልበቴ ነው የሚል የማይናወፅ አቋምም ይዟል። ይህ አቋሙ አገሪቷ ከተጋረጡባት አደጋዎች መካከል አንዱ ሁኖ ይታየናል። የዚህ አቋም መዘዙ አሁን ባለው ትውልድ ብቻ የሚያበቃ አይደለም። ወደ ቀጣዩ ትውልድ ተሸጋግሮ የአገሪቷ ዜጎች በሠላም አብረው የሚኖሩበትን እድል እንደሚያበላሸው ህወሃቶች አያውቁም ማለት አይቻልም። ተደጋግሞ እንደተነገረው በህወሃቶች ዘንድ ትውልድ የሚባል ቋንቋ እንዲጠፋ በመደረጉ ለመጪው ትውልድ የሚተርፍ ቂም ትተው ለማለፍ ሳያቅማሙ እየሰሩ ይገኛሉ።

Friday, December 12, 2014

የቅሊንጦ አንበሶች!

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

ከአዲስ አበባ በስተደቡብ ቅሊንጦ የሚባል ጫካ አለ እዚያ ጫካ ውስጥ በርካታ ጥቁር አንበሶች አሉ፡፡ ለጥቂት ቀናት እዚያ ጫካ ውስጥ ከትቸ ነበር፡፡ በገባሁ በዐሥረኛ ቀኔ ትቻቸው ወጣሁ፡፡ እዚያ በነበርኩበት ወቅት ካገኘኋቸው አናብስት የሁለቱን ታሪክ ብቻ በአጭር በጭሩ ላጫውታቹህ፡፡

አንደኛው አበበ ካሴ ይባላል፡፡ ተወልዶ ያደገው ጎንደር ነው፡፡ አምና 2006ዓ.ም. ጥር 12 ቀን ነበር የተያዘው፡፡ ወደዚህ ጫካ ከመምጣቱ በፊት በተለያዩ ሀገሪቱ ውስጥ ባሉ የማሰቃያ ቦታዎች ሰቆቃ ሲፈጸምበት ቆይቶ በመጨረሻ ነው እዚህ ጫካ ውስጥ የታሰረው፡፡ አበበ ካሴ የግንቦት 7 ቆራጥ ታጋይ ነው፡፡ ከዚያ በፊት ከ1981-1993ዓ.ም. ድረስ የቀድሞው ኢሕዴን የአሁኑ ብአዴን ታጋይ ሆኖ ለ12 ዓመታት አገልግሏል፡፡ ከዚያ በኋላ እሱና ጓዶቹ ታግለው ለዚህ ያበቋቸው መሪዎቹ ከዚህ በስተቀር የማይባል ሁለንተናዊ ድጋፍ እየሰጠ ባበቃቸው ሕዝብ ላይ የሚፈጽሙት ገደብ የለሽ ግፍና በደል አንጀቱን ሲቆርጥበት፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ የፍትሕ ጥያቄ የመመለስ ብቃቱ ወኔው ፍላጎቱ ጽናቱ እንደሌላቸው ባረጋገጠ ጊዜ ጥሏቸው በረሀ ገባ፡፡ በረሀ ሆኖ ለሦስት ዓመታት ያህል በግሉ ሲንቀሳቀስ ቆይቶ በኋላ እንደሱ የከፋቸው ቢጤዎቹህ ተቀላቀለ ከዚያም ወደ ግንቦት 7 ተቀላቅሎ ድርጅቱ ላዘዘው ተልእኮ አምና ጎንደር ላይ እስከተያዘበት ቀን ድረስ ለ9 ዓመታት ያህል ነፍጥ አንሥተው ከሚታገሉ ወገኖች ጋራ ሲታገል ቆይቷል፡፡

ለአበበ ካሴ አምና ጥር 12 ገደኛ ቀን አልነበረችም፡፡ ያች ቀን የተሰጠውን ወታደራዊ ተልእኮ (mission) በዚህ አገዛዝ ባለሥልጣናት ላይ የሚፈጽምባት ቀን ነበረች፡፡ ለዚህ ለሚወስደው እርምጃ ከአጋሩ ጋራ ቅድመ ዝግጅት በሚያደርጉበት ሰዓት በጥቆማ ተያዙ፡፡

አበበ ጎንደር ከመግባቱ በፊት ከሁለት ጓዶቹ ጋራ ሆኖ ሙሉ ትጥቃቸውን እንደያዙ ከኤርትራ ተነሥተው የሱዳንን በረሀ ለ13 ቀናት በእግራቸው ተጉዘዋል፡፡ ወደ ሀገራቸው ምድር ገብተው እየገሰገሱ እንዳሉ ከወያኔ ካምፕ በቅርብ ርቀት ላይ በሆኑበት ሰዓት ከሁለቱ ጓዶቹ አንደኛው መሬት ላይ በመቀመጥ እንደደከመውና መንቀሳቀስ እንደማይችል ተናገረ፡፡ አበበም እንደ አለቃነቱ ያሉበት ቦታ ከወያኔ ወታደሮች ካምፕ ቅርብ ርቀት በመሆኑ አደገኛ መሆኑን አስገንዝቦ እንደምንም ተጠናክሮ ቦታውን ከመልቀቅ ውጭ ምንም አማራጭ እንደሌለውና እንዲነሣ አዘዘው፡፡ ጓዱ ግን ጨርሶ መንቀሳቀስ እንደማይችል ተናገረ፡፡ ይሄኔ ነበር አበበ ይህ ባልደረባው በእርግጥም የወያኔ ሰላይ እንደነበረ አልነሣም ያለውም ስለደከመው ሳይሆን ሆን ብሎ እንደነበር ያረጋገጠው፡፡

አበበ በዚህ ልጅ ላይ ጥርጣሬ አድሮበት የነበረው ሱዳን በረሀ ላይ እንዳሉ ያሉበትን ሁሌታ ለአለቆቹ ለማስታወቅ ከሁለቱም ነጠል ብሎ ስልክ ለመደወል በሚሞክርበት ሰዓት ድንገት ወደጓዶቹ ዞር ሲል ይህ አሁን ተቀምጦ አልንቀሳቀስም ያለው ጓዱ መሣሪያውን የማቀባበል እንቅስቃሴ ሲያደርግ ያየው ይመስለውና ስልኩን አቋርጦ ይመለስና መሣሪያውን ተቀብሎ ሲመለከተው በእርግጥም ተቀባብሎ አገኘው፡፡ ማን አዞት ለምን እንዳቀባበለው ሲጠይቀው “ሰው ከርቀት ያየሁ መስሎኝ ነው” ይለዋል ከዚያ በኋላ አበበ ይሄንን ልጅ በጥርጣሬና በጥንቃቄ ነበር የሚመለከተው፡፡ ሁኔታውን ለአለቆቹ ለማሳወቅ ስልክ ለመደወል በተደጋጋሚ ሞክሮ ሊሳካለት አልቻለም በግሉ ወስኖም ርምጃ መውሰድ አልፈለገም፡፡ ይህ ልጅ መሣሪያውን ያቀባበለው የነበረው እነ አበበን ለመግደል አስቦ ነበር፡፡

አበበ ይህ ጓዱ አልነሣም እንዳለው መሣሪያውን ይቀበለውና ሰላይነቱን እንዳወቀበትና ሊያደርግ የሚፈልገውንም ነገር ማድረግ እንዲችል ወደፈለገበት ቦታ እንዲሄድ ይፈቅድለታል፡፡ ይሄኔ ልጁ ይደናገጥና እንዲገለው አበበን ይጠይቀዋል፡፡ አበበም “እኔም ሆንኩ ድርጅቴ ሰው የመግደል ዓላማ የለንም አንተን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ፍትሕና ነጻነት እራሳችንን መሥዋዕት ማድረግ እንጅ” የሚል መልስ ይሰጠውና ልጁን እንዲሔድ ያዘዋል ልጁ ከአሁን አሁን ተኩሶ ገደለኝ በሚል ጥርጣሬ ዐሥሬ እየዞረ በመመልከት ወደ ካምፑ አቅጣጫ ተጓዘ፡፡ አበበ እነኝህ አብረውት ያሉት ሁለቱ ጓዶቹ የተሰጣቸው ወታደራዊ ተልእኮና የትና ምን እንደሆነም ስለማያውቁ የዚህ ልጅ ከእነሱ መለየትና ሔዶ ለወያኔ ስለነሱ መናገሩ አላሳሰበውም፡፡ አበበና አንዱ ጓዱም በተቻለ ፍጥነት አካባቢውን ከለቀቁ በኋላ ሌሊት ሌሊት እየተጓዙ ጎንደር ከተማ ገቡ፡፡ ጎንደር እንደገቡም ሰዓቱ ሲደርስ ለጓዱ የሚወስዱት እርምጃ ምን እንደሆነና በማን ላይ እንደሆነም ከነገረው በኋላ በቦታው ላይ ቅድመ ዝግጅት በሚያደርጉበት ሰዓት ይሄ ከአበበ ጋር ያለው ጓዱ ቀደም ሲል ኤርትራ እያሉ አብሯቸው ለመታገል ግንቦት ሰባትን ተቀላቅሎ ከነበረ በኋላ ግን ድንገት ከተሰወረ ሰው ጋር ፊት ለፊት ዐይን ለዐይን ይጋጠማሉ፡፡ ይህ ሰው የሬዲዮ መገናኛ ይዟል ልጁ ተደናገጠ መለስ በማለት ቀጥ ብሎ አበበ ወዳለበት ቦታ ሔደ ይሄንን ሁኔታ ለአበበ እየነገረ ባለበት ቅጽበት አካባቢው በሦስት ካሚዮኖች በመጣ የፌዴራል ፖሊስ ተወረረ እነ አበበም በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

Thursday, December 11, 2014

የኢትዮጵያ መንግሥት ገመና (ተመስገን ደሳለኝ – ከዝዋይ እስር ቤት)

መሐሙድ የሱፍ የተወለደው በ1980ዓ.ም ከሶማሌ ክልል ርእሰ-መዲና ጅጅጋ 500 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውዶሀን ከተማ ነው፡፡ ለቤተሰቡ ሰባተኛ ልጅ ሲሆን፤ አምስት እህቶችእና ሦስት ወንድሞች አሉት፡፡ በጅጅጋ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ አስረኛ ክፍል ድረስ መዝለቁቢሳካለትም፤ ከዚህ በላይ ግን ሊቀጥል አልተቻለውም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የኢትዮጵያመንግስት የደህንነት ሠራተኞች የ1999ዓ.ም የግንቦት ሃያ በዓል በጅጅጋ ከተማ ስታዲዬም በተከበረበት ዕለት፣ የኦጋዴን ነፃአውጪ ግንባር (ኦብነግ) በሰነዘረው የቦንብ ጥቃት ተሳትፈሃል በሚል ለእስር በመዳረጉነው፡፡

ይህንን ተከትሎምከምድራችን አስከፊ ማሰቃያዎች መካከል ግንባር ቀደም በሆነውና የክልሉ ነዋሪ “ጄል-አዳብ” (የገሃነም እስር ቤት) እያለ በሚጠራው ማጎሪያ ውስጥ እጅግ በጣም የከፋ ምድራዊ መከራ እንደተቀበለሀዘን በተጫነው ድምፅ ይናገራል፡፡ በሠውነቱ የተለያዩ ክፍሎች ላይ እንደ ፍም ቀልተው የሚታዩት ጠባሳዎቹም ያሳለፈውንሥቃይ አፍ አውጥተው ይመሰክራሉ፡፡ ለአራት ወራት ያህል አንድ ክፍል ውስጥ ለብቻው ተቆልፎበት፤ ሃያ አራት ሠዓታትሙሉ እጆቹ በካቴና ተቀፍድደው፣በቀን ከአምስት ጊዜ በላይ ለምርመራ እየተጠራ ያለዕረፍት ከባድ ስቅየት (ቶርቸር)ሲፈፀምበት ቆይቷል:፡ በመጨረሻም ለአንዲትም ቀን የፍርድ ቤት ደጅ ሳይረግጥ፣ ለኦብነግ አባላት አንድ ፓኬት ሲጋራሲያቀብል እጀ-ከፈንጅ ተይዟል በሚል ክስ የጅጅጋ ዞን ፍርድ ቤት በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን እዛው እስር ቤት ሆኖከኢትዮጵያ ሬዲዮ የዜና እወጃ እና ከቪኦኤ ሶማሊኛ ፕሮግራም ሠምቷል፡፡

ከፍርዱ በኋላም በተመሳሳይ ወንጀል ከተከሰሰ አንድ እስረኛ ጋር በካቴና ተጠፍሮ በቀን አንድ እንጀራ ለሁለት ተካፍሎእንዲበላ እንደ ውሻ እየተወረወረለት 60 ቀናትን አሳልፏል፡፡ መሐሙድ በተለይም በእንቅልፍ ወቅት እርሱ ወይምየሰንሰለት ደባሉ የተገላበጠ እንደሆነ ካቴናው የሚያደርስበትን የመለብለብ ቃጠሎ ሲያስታውስ ዓይኖቹ በእንባ ይሞላሉ፡፡በአሁኑ ወቅት በዝዋይ ማጎሪያ ከባድ ጥበቃ ለሚደረግባቸው ብቻ በተመደበ ‹‹ዘጠነኛ ቤት›› ውስጥ አስራ አንድ ሶማሊኛተናጋሪዎችን ጨምሮ በድምሩ ሰላሳ አራት ሰዎች ጋር ከዛሬ ነገ የግፍ ፍርዱ ተፈጻሚ ሊሆንብኝ ይችላል በሚል ሰቀቀንእየባነነ በስጋት ተጠፍንጎ መኖር ከጀመረ እነሆ ሰባት ዓመት ሊደፍን ሦስት ወራት ብቻ ቀርተውታል፡፡

የተዋረደው የፍትሕ ሥርዓት!. . .

ርግጥ ነው ይህ በጨረፍታ ያቀረብኩት አሳዛኝ ታሪክ የመሐሙድ የሱፍ ብቻ አይደለም፡፡ ሌሎች ሰባት ‹‹አባሪዎቹ››ስቃዩንም ሆነ የሞት ፍርዱን ይጋሩታል (በነገራችን ላይ በአንድ መዝገብ የተወነጀሉት እነዚህ ስምንት የሞት ፍርደኞች፡-መሐድ ኢብራሂም፣ አረብ ሰዋኔ ዱልባንቲ፣ ሐሰን መሐመድ ዑስማን፣ ሐሰን መሐመድ ዓሊ፣ ሙክታር መሐመድ ዓብዱላሂ፣ከድር ሽኩር ሙሳ እና ካሚል ዓብዱልናስር እንኳን በጋራ መንግሥት ላይ ሊያሴሩ ቀርቶ እርስ በርስም የተዋወቁት እስር ቤትውስጥ ነው፡፡ ከጅጅጋ ወደ ዝዋይ ‹‹ዘጠነኛ ቤት›› ተዘዋውረው በርካታ ዓመታትን ያሳለፉትም በጭካኔው ወደርእንደማይገኝለት የሚነገረው የክልሉ ፕሬዚዳንት አብዲ በአደራ እንዲቀመጡ በመተላለፋቸው መሆኑን ነግረውኛል፡፡) እንደ መሐሙድ ሁሉ እነርሱም ፍርድ ቤት ቀርበውአያውቁም፤ ምንም ዓይነት የሰውም ሆነ የሰነድ ማስረጃ አልተቆጠረባቸውም፡፡ እዚህ ጋ የማነሳው አሳዛኝ ገጠመኝከመካከላቸው አንዳቸውም ራዲዮ ስላልነበራቸው የተጣለባቸውን የሞት ፍርድ ውሳኔ የሠሙት፣ ዜናው ከተላለፈ ከበርካታቀናት በኋላ ሬዲዮ ካላቸው እስረኞች መሆኑ ነው፡፡ ይህ እጅግ አሳፋሪና አስደንጋጭ መንግሥታዊ ውንብድና በደንብ ይብራራ ዘንድ ለተከሳሶቹ ከተሰጣቸው ባለ አንድገፅ የክስ ቻርጅ የሁለቱን ብቻ በአዲስ መስመር እጠቅሳለሁ፡-‹‹በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ አቃቤ ሕግና ፍትሕቢሮ በሶማሌ ክልላዊ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት

Tuesday, December 9, 2014

በሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላይ የደረሰውን ጥቃት እናወግዛለን !!!

በአብዛኛው በወጣት ወንዶችና ሴቶች የተገነባው ሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነበት የዘጠኝ ፓርቲዎች ኅበረት፣ “ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የተሰኘ የአንድ ወር መርሀ ግብር አውጥቶ፤ ችግሮችን ተጋፍጦ አብዛኛውን ተግባራዊ አድርጓል። የመርሀ ግብሩ አቢይ አካል የነበረውና በህዳር 27 እና 28 ሊከናወን ታድቆ የነበረው የ24 ሰዓት የአደባባይ ተቃውሞ ግን በአገዛዙ የኃይል እርምጃ ምክንያት በታቀደው መንገድ ሊከናውን አልቻለም። የህወሓት ቅልብ የሆኑት ሲቪል የለበሱ ሰላዮችና የፌደራል ፓሊስ በተቃውሞው ተሳታፊዎች ላይ ኢሰብዓዊ የሆነ ጥቃት ፈጽመዋል።

ከጅምሩ፣ የፓርቲዎቹ ኅበረት የተቃውሞ ማሳወቂያ ደብዳቤውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለማስገባት የገጠመው ችግር የህወሓት አገዛዝ የመንግሥትን መዋቅር ለፓርቲ ሥራ፤ የመንግሥት ተቀጣሪዎችን ደግሞ እንደ ህወሓት አገልጋዮች የሚጠቀምባቸው መሆኑ አንዱ ማሳያ ሆኗል። ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ማሳወቅ የፈለጉት ፓርቲዎች ህወሓት የዘረጋውን አፋኝ ሥርዓት የሚታገሉ በመሆናቸው ብቻ ደብዳቤዓቸውን የሚቀበል እንኳን አጥተው ተጉላልተዋል። ለሰልፉ ቅስቀሳ ማድረግም በራሱ እንደ ወንጀል ተቆጥሮ ወጣቶች ተንገላተዋል፣ ተደብድበዋል፣ ታስረዋል። ያም ሆኖ ውጣ ውረዶች ታልፈው ቅዳሜ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ. ም. ደረሰ።

የኅበረቱ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ጥሪውን የሰማ ሕዝብ ወደ መስቀል አደባባይ ማምራት ሲጀምር ሲቪል የለበሱ የአገዛዙ ታጣቂዎች እና ፌደራል ፓሊሶች ከሰንደቅ ዓላማዎችና መፈክሮች ባለፈ አንዳች ነገር ያልያዙትን እድሜያቸው ከሃያዎች ያልዘለሉ ውድ የኢትዮጵያ ልጆችን ደብድበዋል፤ ብዙዎቹም አፍነው በአሰቃቂ ሁኔታ እያንገላቱ ወደ እስር ቤቶች ወስደዋል። ወጣቶች ተወልደው ባደጉበት አገር፤ ስሜታቸውን በነፃነት ለመግለጽ በመድፈራቸው ብቻ በጭካኔ ተረግጠዋል፤ ተፈንክተዋል፤ እጅና እግሮቻቸው ተሰብሯል።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህ የህወሓትን ፋሺስታዊ እርምጃ አጥብቆ ይቃወማል። ግንቦት 7፣ ህወሓት ከስልጣን እስካልተወገደ ድረስ እንዲህ ዓይነቱን ፋሺስታዊ ተግባር መፈፀሙን የማይተው እኩይ ኃይል እንደሆነ ያውቃል፤ በዚህም ምክንያት የትግላችን ግብ ህወሓትን ማስወገድና በምትኩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይሁንታ ያገኘ መንግሥት መመሥረት መሆን ይኖርበታል ብሎ ያምናል፤ ለዚህም ይታገላል።

ግንቦት 7፣ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ.ም. “መብቶቻችንን በህወሓት ዘረኛ አምባገነኖች አናስነጥቅም” በማለት አደባባይ የወጡ ወጣቶችን ጽናት ያደንቃል። ህወሓት የሚለውን ሳይሆን የይስሙላ ህጉ የፈቀደላቸውን ለማድረግ በመድፈራቸው በህወሓት የህግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ የሚደረገውን ትግል አንድ እርምጃ ወደፊት አራምደውታል።

Sunday, December 7, 2014

ብሄራዊ ብድር የዕድገታችን ምንጭ እንጂ የደኅንነታችን ስጋት ሊሆን አይገባም

እኛ ሰዎች ሁሌም ከምንፈራዉና ከምንጠላዉ አንዴ ከገባንበት ደግሞ የቱንም ያክል ብንጠላዉና ብንፈራዉ እየደጋገምን የምንዘፈቅበትና በቀላሉ የማንወጣዉ አዘቅት ቢኖር ብድር ወይም የብድር ልጅ የሆነዉ ዕዳ ነዉ። ብድር ግለሰቦች ብቻ ሳይሆኑ የንግድ ድርጅቶች፤ ማዘጋጃ ቤቶች፤ ትላልቅ ኮርፓሬሺኖችና አገሮች በአጭርና በሪጂም ግዜ የሚያጋጥማቸዉን የገንዘብ እጥረት የሚሸፍኑበት መንገድ ነዉ። ወይም ቀለል ባለ አማርኛ ብድር ወደፊት በምናገኘዉ ገቢ ዛሬን መኖር ማለት ነዉ። ብድር ግለሰቦች፤ ድርጅቶች ወይም አገሮች የመከፈል አቅማቸዉን እያዩ ቢበደሩና የተበደሩትን ገንዝብ ዉጤታማ በሆነ መንገድ ከተጠቀሙበት የእድገትና የብልጽግና መንገድ የሚከፍት አለዚያም የምንበደረዉ ብድር ከአቅም በላይ ከሆነና ዉጤታማ ባልሆነ መልኩ ከተጠቀምንበት ደግሞ በቀላሉ የማንወጣዉ መቀመቅ ዉስጥ ይዞን የሚገባና ጫናዉ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ የሚተላለፍ ዕዳ ነዉ። ዕዳ ደግሞ በተለይ አገሮች የሚገቡበት ዕዳ ተከፍሎ ካላለቀ ወይም በምህረት ካልተሻረ በቀር ወለዱ ወለድ እየወለደ በተበዳሪ አገሮች የኤኮኖሚ እድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያደርግ የዕድገትና የብልፅግና ጠላት ነዉ። ዛሬ ሰፋ አድርገን የምንመለከተዉ ብድርና ዕዳን ቢሆንም ዋናዉ ትኩረታችን ግን አገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በታዳጊ አገሮች የኤኮኖሚ ዕድገት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ የሚያደርገዉን ብሄራዊ ብድርና ዕዳ ነዉ። ሁላችንም እንደምናዉቀዉ አገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት ሃያ አመታት በብድር ላይ ብድር እየተበደረች አንዱንም ሳትከፍል በድጋሚ እየተበደረች ከድጡ ወደማጡ እየገባች ነዉ።

የኢትዮጵያ መንግስት መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ የዉጭ አገር ምንጮች ብድር መበደር ከጀመረ ብዙ አመታት ተቆጥረዋል።ከቀዳማዊ ሚኒልክ በኋላ ኢትዮጵያን ለረጂም አመታት የመሩት ሦስቱ መንግስታት የብድር ጥማት ከፍተኛ ቢሆንም በብድር መጠኑም ሆነ በተከማቸ የዕዳ መጠኑ ዛሬ በስልጣን ላይ አንዳለዉ እንደ ወያኔ አገዛዝ የአገራችንን ብሄራዊ ደህንነት ለአደጋ ባጋለጠ መልኩ ብድር የተበደረና ዕዳ ዉስጥ የተዘፈቀ አገዛዝ ኢትዮጵያ አይታ አታዉቅም። የወያኔ አገዛዝ አገር ዉስጥ ቦንድ እየሸጠና ብሔራዊ ባንክን እያስገደ በተለያየ መልኩ የሚወስደዉ ብድር ከአለም ባንክ፤ ከአለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት፤ ከዉጭ አገር ባንኮችና አበዳሪ አገሮች በየአመቱ ከሚበደረዉ ብድር ጋር ተደምሮ የዛሬዉን ኢትዮጵያዊ ብቻ ሳይሆን የዛሬዉን ኢትዮጵያዊ የልጅ ልጆች ጭምር ባለዕዳ አድርጓቸዋል።

የወያኔ አገዛዝ ለህዳሴዉ ግድብና ለእድገትና ትራንስፎርሜሺን ዕቅድ ማስፈጸሚያ በሚል የአገሪቱን አመታዊ ገቢና የመክፈል አቅም በላገናዘበ መልኩ እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ገንዝብ ከተለያዩ የአገር ዉስጥና የዉጭ አገር ምንጮች እየተበደረ ነዉ። ይህ መጠነ ሰፊ ብድር በረጂም አመት የሚከፈልና ከፍተኛ ወለድ የተሸከመ ሲሆን ወያኔ ይህ ብዙ ኢትዮጵያዉያንን ያሰጨነቀ ብሄራዊ ዕዳ አልበቃ ብሎት ከአቅም ዉጭ የጀመራቸዉን ፕሮጀክቶች ለማስጨረስ ነዉ በሚል ሰበብ አሁንም አገራችን ኢትዮጵያን ከዕዳ ወደ ዕዳ እየከተታት ይገኛል። በተለይ ወያኔ አበዳሪ አገሮች፤ የአለም ባንክና ወዳጆቹ የሆኑ መንግስታት ጭምር ተዉ ይቅርብህ ብለዉ እየመከሩት አልሰማ ብሎ በዚህ አመት ለመሸጥ ያሰበዉ ሉዓላዊ ቦንድ ወይም ፈረንጆቹ ሶቨርን ቦንድ ብለዉ የሚጠሩት ቦንድ ሽያጭ የጉዳዩ አሳሳቢነት የገባቸዉን ኢትዮጵያዉያንንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ከወዲሁ እያሰጨነቀ ነዉ። በእርግጥም ሉዓላዊ ቦንድ ሽያጭ የሚያስጨንቅ ብቻ ሳይሆን አንደ ኢትዮጵያ አይነቶቹን ቀድሞዉኑም ዕዳ ዉስጥ የተዘፈቁ ደሃ አገሮች ህልዉና አደጋ ዉስጥ የሚከት የኤኮኖሚ ዕድገትን ብቻ ሳይሆን የአገር ደህንነትን ጭምር የሚፈታተን አደገኛ ጅምር ነዉ። ለመሆኑ ሉዓላዊ ቦንድ ምንድነዉ? አደገኛነቱስ ምኑ ላይ ነዉ?

የህወሃት ምርጫ የህዝብ መከራ!

ህወሃቶች እኛ ከሌለን ይህችን አገር እንበትናታለን፤ ይህችን አገር የምንሰብር እኛ የምንጠግን እኛ እያሉ እንደሚያሟርቱ ሰምተናል። እኛ የቀረፅነው ፖሊስ ከሚቀየር ሞታችንን እንመርጣለን እያሉ ማቅራራታቸውም ከህዝብ የተሰወረ ነገር አይደለም። የህወሃት ፖሊሲ የሚቀየረው በመቃብርችን ላይ ነው የሚል የማይናወፅ አቋማቸው መቼም ቢሆን በሠለጠነ መንገድ በውይይትና በድርድር እንደማይቀየር ደጋግመው አሳይተውናል። ህወሃቶችን በሠለጠነ መንገድ ተደራድሮ እና ሰጥቶ በመቀበል መርህ ለለውጥ አዘጋጃለሁ ማለት ከእባብ የእርግብ እንቁላል እንደመመኘት ያህል ነው። ከእባብ የእርግብን ዘር የሚጠብቅ ማን ነው?

እንግዲህ ህወሃቶች ይህን የመሰለ የከረረ አቋም ይዘው ምርጫ ለምን ያደርጋሉ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ይሆናል። ይሄ ህወሃቶች ለኢትዮጵያና ለህዝቧ ራዕይ የሌላቸው ከመሆን የሚመነጭ ነው። ድርጅቱ ራዕይ አልባ የሆነው ደግሞ በህወሃት ውስጥ የተሰባሰቡ ግለሰቦች ራዕይ አልባ በመሆናቸው ነው። ህወሃቶች የሚኖሩለትም ሆነ የሚሞቱለት ቁም ነገር ከመብልና መጠጥ የዘለለ አይደለም። ህወሃቶች ራዕይ ቢኖራቸው ኑሮ በታሪክ የሚያስወቅሳቸውንና የህዝቡን ፍቅር የሚያሳጣቸውን እኩይ ተግባራት ባልፈፀሙ ነበር። ራዕይ የሌላቸው በመሆኑ ለሚፈፅሙት ወንጀል ሁሉ ገደብ እንዳይኖራቸው ሆኑ። ራዕይ ያለው ሰውም ሆነ ድርጅት እኔ ብቻ አይልም። ራዕይ የሰነቀ ድርጅትም ሆነ ሰው ከራሱ ክበብ አልፎ ሌላው እንደምን ሁኖ በሠላም እና በደስታ እንደሚኖር ያስባል እንጂ ዕለት ዕለት ደም በማፍሰስ አይኖርም።

ህወሃት በምርጫ ስልጣኑን እንደማይለቅ ለራሱ የማለ ድርጅት ነው። እዚህ መሃላ ላይ ያደረሰው ደግሞ እስከ ዛሬ የፈፀማቸው ወንጀሎቹ ናቸው።የጨበጠውን ስልጣን በምርጫ ቢለቅ ነገ የሚከተለውን ጠንቅቆ ያውቃል። ትላንት ያፈሰሱት የንፁሃን ደም ከኢትዮጵያ ምድር ላይ እየጮኸ ነው። ዘርፈው የገነቡት ህንፃ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ቆመው ሌብነታቸውን እየመሰከሩባቸው ነው። በልማት ሥም ከኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ተዘርፎ የተደራጀው የንግድ ተቋም በኢትዮጵያ ህዝብ ወዝና ደም ታጥኖ እንዳማረበት አለ። ህወሃት የኢትዮጵያ የህዝብ ጠላት ሆኖ ራሱን ያቆመ ቡድን በመሆኑ በሰላማዊ እና በሰለጠን መንገድ የያዘውን ሥልጣን ለህዝብ አይለቅም።

እንግዲህ ምን ይሻላል ?

ህወሃቶች ኑና እንወዳደር ብለዋል። እነዚህ ቡድኖች ኑና እንወዳደር ሲሉ እነርሱ የብረት ቦክስ ጨብጠው፤ ሌሎቹ ደግሞ ሌጣቸውን ሁነው ያለ በቂ ታዛቢ እንዲፎካከሯቸው ወስነው ነው። እንዲህ ባለ ሁኔታ ውስጥ ሁነንም ቢሆን የምንወዳደረው ለነፃነት መሆን ይኖርበታል። ከነፃነት በመለስ ያለው ማንኛውም ዓይነት የምርጫ ውጤት በአገራችን እየተካሄደ ያለውን ዝሪፊያ፤ ዘረኝነት፤ እሥራት እና ግድያ ያስቆማል የሚል ዕምነት በማንም ዘንድ ያለ አይመስለንም። በምርጫ ውድድር የምናተርፈው የህግ የበላይነት፤ እኩልነት እና ነፃነት ካልሆነ ተጎጂው ሰፊው ህዝብ ይሆናል።

አሁንስ ሰዎቹ ጫካ የነበሩም አልመስልህ አለኝ።ጫካ የነበረ እኮ ከአራዊቱም ከእፅዋቱም ሕግ ይማራል

ሕግ ሕግ ሕግ!!! ቅንጣት ታክል ሕግ የማያከብሩ ለማክበርም ፍላጎት የሌላቸው ሰዎች ተሰብስበው መንግስት መሆናቸው እየቆየ ይብሱን የሚያንገበግብ ጉዳይ እየሆነ ነው።የኢትዮጵያ ሕዝብ ኢህአዴግ/ወያኔዎች የዛሬ 20 ዓመት አፀደቅነው ያሉትን ሕግ እየጠቀሰ ሲሞግታቸው እና ሕግ አክብሩ ሲላቸው ዓመታትን አስቆጠረ።በሕግ ስልጣን ባትይዙም በሕግ ስልጣን  ለሕዝብ አስረክቡ ቢባሉም አልሰሙም።ከሽግግሩ ጊዜ ጀምሮ ብዙዎች ብዙ ሊመክሩ ሞክረዋል። በ''ዞን 9'' ጦማርያን፣በፖለቲከኞቹ አንዱዓለም አራጌ፣በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ቀደም ብሎም በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ዳኛ ብርቱካን ደሜቅሳ እና ሌሎችም ስማቸውን ያልተጠቀሰው ሁሉ ሕግ የማክበርን 'ሀሁ' ለማስተማር ቢጥሩም ሰሚ አጡ።ሁሉም ስለ የሕግ የበላይነት ተናግረዋል፣ፅፈዋል።ሰሚ የለም።ይብሱኑ ከአመት ዓመት ትዕቢት ቤቷን እየሰራች በልቦናቸው ላይ እንደ ሸረሪት ድር እያደራች የሚናገሩት እሬት እሬት የሚል የሚሰሩት የውድቀታቸውን ጥልቀት የሚያሳይ ሆነ።

ሕግን ከመከራ  

ሰሞኑን በያዝነው በኅዳር ወር መጨረሻ ''የሕገ መንግስቱ ሰነድ የፀደቀበት'' እያሉ በሚወተውቱን ሰሞን የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 30 ''የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት'' በሚለው ርዕስ ስር ቁጥር 1 ስር ''ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና፣ አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው'' የሚለውን መሰረት አድርገው ሃሳባቸውን በሰላማዊ መንገድ ሊገልጡ የተነሱትን የሰማያዊ ፓርቲን ጨምሮ 'የዘጠኙ ጥምረት' በመባል የሚታወቁት ዛሬ ህዳር 27/2007 ዓም ሰልፍ መውጣታቸው እና ከፍተኛ ድብደባ እና እስር እንደተፈፀመባቸው ይታወቃል።ፓርቲዎቹለሰልፉ  ያነሳሳቸው ዋናው ጉዳይ ሕግ የማያውቀውን ግን የህገ መንግስቱን  ሃያኛ  ዓመት ''ልደት'' ለማክበር ሽር ጉድ እያልኩ ነው የሚለውን ስርዓት ሕግ ለማስተማር ነበር።መማር አንድ ከማስተዋል አልያም ከመከራ ነው እና ኢህአዲግ/ወያኔ ከማስተዋል ሕግ እንደማይማር በተግባር አሳይቷል።ከመከራ ግን እንደሚማር ለማወቅ ግን ነቢይ መሆን አይጠይቅም።

ሕግ ካላወቅህ ለምን እንደመለስከውም አትናገርም 

ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ሐሙስ ህዳር 25/2007 ዓም ወደ አውሮፓ የነበረው ጉዞ እገዳ ምክንያት እስካሁን አልታወቀም። ዛሬ ቅዳሜ ህዳር 27/2007 ዓም  በሸገር ''ታድያስ አዲስ'' ፕሮግራም ላይም የቴዲ ጉዞ ለምን እንደታገደ አለመታወቁን ተወስቷል። ተመልከቱ! አንድ ኢትዮጵያዊ ያውም በሕዝብ የሚታወቅ ከያኒ አየር መንገድ ደርሶ ''ተመለስ መውጣት አትችልም'' ሲባል ለምን እንደሆነ አይነገረውም።''ለምን?'' ብሎ መጠየቅም አይችልም።ሕዝብም  አንድ ታዋቂ የኪነት ሰው ለምን ከሀገር መውጣት አትችልም እንደተባለ የማወቅ መብት የለውም።ምን ሕዝቡ ብቻ ጉዳዩ ስለ ኪነት ሰው ቢሆንም ጋዜጠኞችም ስለጉዳዩ መጠየቅ አይችሉም።ተመልከቱ! የትዕቢትን መጠን።ተመልከቱ የመጥገብን ልክ።ሌላው ቢቀር የአንድ አየር መንገድ ኢሚግሬሽን ሰራተኛ ሊሰጠው ከሚገባው አገልግሎት አንፃር ትንሹ አንድን ተገልጋይ እንደ ሰው ቆጥሮ ''እንዳትሄድ የተደረገው በእዚህ ምክንያት ነው'' ብሎ መናገር የአገልግሎት አሰጣጡ የሚጠይቀው ትንሹ የደንበኛ የማስተናገድ ክህሎት ነው።ለእዚህም ግን ትዕቢታቸው 'ስቅ ስቅ' እያለች ወጣጠረቻቸው።''ወደ ቤት ሂድ'' አሉት።ሃገሩ የግላቸው ነዋ! ሕግ አይገዛቸውም።ጥቂቶች ተጠራርተው በአንድ ወቅት ግንባራቸውን ለሞት በሰጡ ኢትዮጵያውያን አጥንት ተረማምደው ስልጣን ይዘዋላ! ማን ይናገራቸው? ሕዝብ ሕግ ምን እንደሆነ የሚያስተምርበት ቀን እሩቅ አይሆንም።

በአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ትግላችን አይቆምም!

ከ 9 ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ባለፈው አንድ ወር ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል መርሃ ግብር ቀርጸን ስንቀሳቀስ ዋናው አላማችን የስርዓቱን አረመኔያዊነት ለህዝብ በማጋለጥ የኢትዮጵያ ህዝብ በትግሉ እንዲሳተፍ ማድረግ ነው፡፡ እንደጠበቅነው ገና ከጅምሩ የህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ትግላችንን በጭካኔ ለማስቆም ጥሯል፡፡ ህዳር 7/2007 ዓ.ም የመጀመሪውን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በጠራንበት ወቅት ስብሰባውን በኃይል በትኗል፡፡

ትብብራችን ከመቸውም ጊዜ በላይ ያሰጋው ህወሓት/ኢህአዴግ በተለይ የህዳር 27/28 2007 ዓ.ም የአደባባይ አዳር ሰልፍን እንዳይካሄድ የትብብሩን አመራሮችና አባላቶቻችን በማዋከብ፣ በመደብደብና በማሰር ተጠምዶ ሰንብቷል፡፡ በተለይ በትናንትናው ዕለት ሰልፍ በወጣንበት ወቅት ስርዓቱ አመራሮችንን፣ አባላቶቻችንን፣ ተሳታፊዎችንን እንዲሁም አልፎ ተርፎ መንገደኛውን ህዝብ በጭካኔ ደብድቧል፡፡ አፍሶ አስሯል፡፡ ሙስሊም እህትና ወንድሞቻችን በየጎዳናው ታፍሰው የአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ሰለባዎች ሆነዋል፡፡ በርካቶችም በእየ እስር ቤቶቹ ታጉረዋል፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ ከ300 በላይ የትብብሩ አመራሮችና አባላት የታሰሩ ሲሆን የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ድርሶባቸዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆነው አቤል ኤፍሬም ራሱን እስኪስት ተደብድቧል፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ የተገኙ ሴት አመራርና አባላት አንድ አገርን እየመራሁ ነው ከሚል አካል በማይጠበቅ መንገድ በጭካኔ ተደብድዋል፡፡ እነዚህ በጭካኔ የተደበደቡ አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ህክምና እንዳያገኙ ተከልክለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በጥበቃ ሰራተኝነት የሚሰሩ የ72 አመቱ አቶ ቀኖ አባጆቢር ከስራ ሲወጡ በደህንነት ኃይሎች ታፍነው የተወሰዱና እስካሁን የት እንደደረሱ ያልታወቀ ሲሆን ይህም አገዛዙ የመጨረሻው የአረመኔነት ደረጃ ላይ እንደደረሰና ይህን የስርዓቱ ውንብድና ለማስቆም ጊዜ የማይሰጠው ተግባር መሆኑን በግልጽ የተገነዘብንበት ነው፡፡

አገዛዙ በትናንትናው ዕለት በፍጹም ሰላማዊ ሰዎች ላይ የወሰደው የውንብድና እና አረመኔያዊ እርምጃ በትግሉ ውስጥ የምንጠብቀውና ስርዓቱ ለኢትዮጵያ የማይበጅ መሆኑን ዳግመኛ ያያረጋገጠበት ነው፡፡ የትናንትናው ትላችን አገዛዙ ለይስሙላ እከተለዋለሁ ከሚለው ‹‹ህጋዊ ሰርዓት›› ይልቅ ስልጣኑን በኃይል ለማስጠበቅ ቆርጦ መነሳቱን እና በህገ መንግስት ስም ህዝብን የሚበድልበትን የአረመኔያዊነት ጭንብል ገልጠን ለዓለም ያሳየንበት የትግላችን ውጤት ነው፡፡

Saturday, December 6, 2014

በእርግጠኝነት አደባባዩ ጋ እንደርሳለን!


ጌታቸው ሺፈራው


ትናንት ለሰላማዊ ሰልፉ ዝግጅት ሙሉ ሌሊቱን ነው ስንሰራ ያደርነው፡፡ በተለይ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬና ሳሙኤል አበበ ሌሊቱን ሲለቀቁ ቢሮው ይበልጡን ሞቅ ደመቅ ብሎ አመሸ፡፡ ቢሮ ውስጥ የነበሩት ወጣቶች እስከ አፍንጫቸው አውተማቲክ መሳሪያ የታጠቁ የገዥው ፓርቲ ደህንነትና ፖሊሶች ቢሮውን እንደከበቡት ረስተው ስራቸው ላይ ተጠምደዋል፡፡ ደህንነት ይሁን ፖሊስ ከምንም አይቆጥሩትም፡፡ አቤል፣ ብርሃኑ፣ ወይንሸት፣ እያስፔድ፣ ምኞት፣ በላይ፣ ሜሮን፣ ኃይለማሪያም፣ ሳሙኤል፣ እየሩስ፣ ወሮታው፣ ይልቃል...... ፖሊስ፣ ደህንነት፣ መሳሪያ ቅብጥርጥስ ብሎ የማያስፈራቸው ፍጥረቶች ናቸው፡፡

በሌላ በኩል ከሰማያዊ ፅ/ቤት ውጭ ሰላማዊ ሰልፉን ለመጀመር ሌሎች ደፋር ወጣቶች ተሰማርተዋል፡፡ ቆራጡ ጌታነህ ባልቻ አንዱን ክፍን ይመራዋል፡፡ እየደወሉ አንዳንድ ነገሮችን ይጠይቁናል፡፡ እነሱም እንዲሁ በትንንሽ ሜትሮች ፖሊስና ደህንነት የሚበገርባት አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ አይመስሉም፡፡ ኢህአዴግ አፍነዋለሁ በሚለው ሰላማዊ ሰልፍ ማሰቃያው ማዕከላዊ እስር ቤት ጀርባ ሳይቀር ሌሊቱን ወረቀት እየተለጠፈ እንደሆነ ሲሰሙ የራሳቸውን ቆራጥነት ረስተው ሌሎቹን ያሞካሻሉ፡፡ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በፓልቶክና በመሳሰሉት ድጋፋቸውን ሲሰጡ ሲሰሙ ስራቸውን በደስታ ነበር የሚሰሩት፡፡ የሁሉም ትኩረት በተቻለው ሰላማዊ መንገድ ሁሉ መስቀል አደባባይ መድረስ ነው፡፡ ለዛም ጊዜው የረዘመባቸው ይመስላል፡፡ ደግሞ በበርካታ ስራዎች ተጠምደዋል፡፡

ወጣቶቹ ጠዋት ተነስተው ሌሎች አካባቢዎች የሚገኙት ጓዶቻቸው ምን ደረጃ ላይ እንደደረሱ፣ መቼ እንደሚጀመር ለማወቅ ቋምጠዋል፡፡ እስከዛው ደግሞ ፌደራልና ደህንነቶች የቆሙበት ድረስ እየሄዱ ፎቶ ግራፍ እያነሱ ያመጣሉ፡፡ የደህንነቶችን ስራ በማህበራዊ ሚዲያዎቸ ያጋልጣሉ፡፡ ብዙዎቹ ምግብ አልቀመሱም፡፡ የእነሱ ትኩረት ወደ መስቀል አደባባይ ማቅናት፣ ከዛም ለኢትዮጵያውያን መብት መጮህ ነው!

እናም ያ ጊዜ ደረሰ፡፡ የተወሰኑ ሰዎች ቢሮ መቅረት ነበረባቸው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞም አብዮት አደባባይ ላይ ሰልፍ ለመውጣት (ያውም የአዳር ሰልፍ) ሲሞከር ከስርዓቱ የሚመጣው ምላሽ ምን ሊሆን እንደሚችል ለወጣቶቹ ግልጽ ነው፡፡ ስርዓቱ ሊደባደብ፣ ሊያስር፣ ከዚህም ሲያልፍ ሊገድል እንደሚችል ያውቃሉ፡፡ ግን ፍርሃትን አላሰቡትም፡፡ እንዲያውም ‹‹ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት አገራችን ነጻ እናውጣ›› የሚሉት ወጣቶቹ ራሳቸውን ከፍርሃት ነጻ አውጥተዋል፡፡ እነሱ የሚታገሉት ሌሎች ከፍርሃታቸው ነጻ ይወጡ ዘንድ ነው፡፡ እናም ፍርሃትን አላሰቡትም፡፡ እነሱ ያሰቡት መስቀል አደባባይ ስለመድረስ ብቻ ነው፡፡ ከዛ ውጭ ያለው መስዋዕትነት የትግሉ አካል ነው፡፡ ስለሆነም ‹‹እኔ ብሄድ ይሻላል፡፡ እንትና ይቀር›› የሚሉት በዙ፡፡ ቢሮ መቅረትን የሚፈልግ ሰው የለም፡፡

Thursday, December 4, 2014

Ethiopia issues unfamiliar investor warning over war and famine (The Financial Times)

Javier Blas, Africa Editor

Every country tapping the global sovereign bond market details the dangers investors face in its prospectus, often in a boilerplate section enumerating possible problems – such as fiscal deficits or taxation issues – that is largely ignored.

But the document sent by Ethiopia to international investors ahead of its foray into the global sovereign bond market is somewhat different. Far from a boilerplate, it includes a list of unfamiliar hazards, such as famine, political tension and war.

The document, seen by the Financial Times, is a sobering reminder of the risk of investing in one of Africa’s less developed nations. With gross domestic product per capita at less than $550 per year, Ethiopia is the poorest country yet to issue global bonds.

In the 108-page prospectus, issued ahead of its expected $1bn bond, Ethiopia tells investors they need to consider the potential resumption of the Eritrea-Ethiopia war, which ended in 2000, although it “does not anticipate future conflict”.

There is also the risk of famine, the “high level of poverty” and strained public finances, as well as the possible, if unlikely, blocking of the country’s only access to the sea through neighbouring Djibouti should relations between the two countries sour.

Addis Ababa, Ethiopia’s capital, also warns that it is ranked close to the bottom of the UN Human Development Index – 173rd out of 187 nations – and cautions about the possibility of political turmoil. “The next general election is due to take place in May 2015 and while the government expects these elections to be peaceful, there is a risk that political tension and unrest . . . may occur.”
But the long list of risks is not deterring investors, as ultra-low interest rates in the US, the UK, eurozone and Japan push sovereign wealth funds and pension funds into riskier countries in search of higher-yielding bonds.

''ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች!'' ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት (የጉዳያችን ማስታወሻ)

''ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት እና ብዙ ትላልቅ ሰዎች የተሰዉባት ሀገር ነች'' ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ሰሞኑን ፓርቲው እና ዘጠኙ አጋር ፓርቲዎች በጋራ በጠሩት በመጪው ቅዳሜ እና ዕሁድ (ህዳር 26 እና 27/2007 ዓም) በአዲስ አበባ የተጠራውን የ 24 ሰዓት የተቃውሞ ሰልፍ አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የተናገሩት ንግግር ነው።
ይህ ንግግር አሁን ላለው ትውልድም ሆነ በኢትዮጵያዊነቱ ለሚያምነው ሁሉ ከሰማይ የገዘፈ፣ ሲያስቡት በትንሿ አእምሯችን ልንሸከመው የሚከብድ ግን ከእውነትም በላይ የሆነ እውነት ነው።

ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ካቆሟት ነገሮች ውስጥ አንዱ ለዘመናት የኖረው ሕግ ነው።ዓለም እንደ ዛሬው ስለ ሕግ ብዙ ሳይናገር በቤተ መንግስቱ እና በሕዝቡ መካከል የሚያገናኙ ሕጎች ነበሩ።የተበደለ ፍትህ የሚያገኝበት፣አቤት የሚልበት ቦታ ነበረው።በዳኝነት የተቀመጠውም ህሊናውን እና አምላኩን የሚፈራበት መመዘኛ ነበረው።ፍፁምነት በእራሱ ከሰው ልጅ ባይጠበቅም እንደ ማህበረሰብ፣እንደ ሕዝብ እና እንደ መንግስት ኢትዮጵያ እና ህዝቧ ለሺህ ዓመታት ሲዳኝ የኖረው ከፈረንሳይ ሀገር በመጣ ወይንም ከእንግሊዝ በመጣ ሕግ አይደለም። ሃይማኖታዊ መሰረቱን በያዘ፣ህሊናን እና ህዝብን ታሳቢ ያደረገ ሕግ እና ፍርድ ለዘመናት አኑረውናል።

ይህንን ሕግ እና በነፃነት የመኖር ፀጋን አባቶቻችን በነፃ አላገኙትም።ወጥተው እና ወርደው ደምተው እና ቆስለው ያቆዩት እኛነታችን ነው።ለእዚህ ነው ዛሬ ላይ ሆነን ለነገ ለማስተካከልም ሆነ የምናወራው ስለ ምን ዓይነቷ ኢትዮጵያ እንደሆነ ለማስታወስ ኢትዮጵያ ብዙ የተደከመባት ሀገር መሆኗን ለአፍታም አለመርሳቱ ተገቢ የሚያደርገው።ብዙ የተደከመባት ብቻ አይደለም ብዙ ታላልቅ ሰዎች የተሰዉላት ሀገር ነች።ኢንጅነር ይልቃል ያስታወሱን እኔም በአምሮዬ ሲመላለስ የከረመው አረፍተነገር ይህ ነው።

Wednesday, December 3, 2014

የወቅቱ የኢትዮጵያ ወጣት እና ህወሓትን የማስወገድ ትግል

በዶ/ር ታደሰ ብሩ (የግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር)

መግቢያ

አገራችን ኢትዮጵያ በሕዝብ ብዛት ከአፍሪቃ ሁለተኛ ስትሆን በተባበሩት መንግሥታት መመዘኛ “ወጣት” ተብሎ በሚጠራው የኅብረተሰብ ክፍል ብዛት ግን አንደኛ ነች። እርግጥ ነው ወጣነት በእድሜ ብቻ የሚገለጽ የኅብረተሰብ ክፍል አይደለም። የሚከተለው የወጣት ትርጉም ሰፋ ያለ ተቀባይነት ያለው ይመስለኛል።

ወጣት፣ በማኅበረሰቡ አንኳር ጉዳዮች ላይ እየወሰነ ባለው “አዋቂ” ተብሎ በሚጠራው የኅብረሰተሰብ ክፍል እና ማኅበራዊ ፋይዳ ያላቸውን ውሳኔዎች ለመስጠት ገና ባልተዘጋጀው ሕፃን መካከል ያለ የኅበረተሰብ ክፍል ነው።

በዚህ ትርጓሜ መሠረት ወጣትነት የማኅበራዊ ግኑኝነት መገለጫ ጽንሰ ሀሳብ ነው። ይህ ማኅበራዊ ግኑኝነት ወደ እድሜ እንመዝረው ስንል ችግር ውስጥ እንገባለን፤ ምክንያቱም ወጣቱ ወደ አዋቂነት የሚሸጋገርበት ጊዜ እንደየአገሩ ባህሉና እንደ እድገቱ ይለያያል። በዚህም ምክንያት ነው የወጣትነት የህግ ትርጓሜዎች በየአገሩና ባህል የተለያዩ የሆኑት። ለምሳሌ፣ የተባበሩት መንግሥታት ወጣት ማለት “እድሜው 15 እስከ 24 ዓመታት ድረስ ያለው ሰው ነው” ሲል ይተረጉማል፤ ይሁን እንጂ የራሱ አካል የሆነው UN Habitat “ወጣት ማለት እድሜው 15-32 ዓመት ያለው ሰው ነው” ይላል። በአገሮች ትርጓሜ መካከል ያለው ልዩነት ደግሞ በጣም የተዘበራረቀ ነው። ዩጋንዳ ውስጥ እድሜው 12-30 የሆነ ዜጋ ወጣት ሲሰኝ ጎረቤትዋ ኬንያ ውስጥ 18-35 ነው። ስለዚህም አንድ የ16 ዓመት ወጣት ዩጋንዳዊ ድንበር ተሻግሮ ኬኒያ ሲገባ ሕፃን ይሆናል፤ አንድ የ 32 ዓመት ኬንያዊ ወጣት ዩጋንዳ ሲሻገር ጎልማሳ ይሆናል። ከአፍሪቃ ዝብርቅርቅ የወጣት ትርጓሜዎች ለአብነት ጥቂቶቹን ላንሳ: ሞውሪሸስ 14-29፣ ደቡብ አፍሪቃ 14-29፣ ናይጄሪያ 18-35፣ ጂቡቲ 16-30፣ ኬኒያ 18-35።

በ2004 ዓም የወጣው የኢትዮጵያ መንግሥት የወጣቶች ፓሊሲ ከ15 -29 ዓመታት ውስጥ የሚገኝን ኢትዮጵያዊን ዜጋን ወጣት ብሎ ይተረጉመዋል። በወጉ የሚያስተናግደው አላገኘም እንጂ ይህ ፓሊሲ በወጣበት ወቅት የኢትዮጵያ የወጣት ትርጓሜ እንደ ኬኒያና ናይጄሪያ 18- 35 መሆን ይገባዋል የሚል ሀሳብ ቀርቦ ነበር። የወጣቱ ከፓለቲካና ማኅበራዊ ውሳኔዎች መገለል መብዛትን በማጤን የላይኛው ጣራ እስከ 39 ከፍ ማለት አለበት የሚል ክርክርም ነበር። በበኩሌ ሥራአጥነትና ዘረኛ የህወሓት ፓሊሲ ያስፋፋው መድልዎና መገለል የወጣት የእድሜ ማዕቀፍ እንዲሰፋ አድርጓል ብዬ አምናለሁ። አርባ ዓመት አልፏቸው ከወላጆቻቸው ጥገኝነት ያልወጡ “ወጣቶች” ቁጥር በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ ነው። እኔ በዚህ አጭር ጽሁፍ ውስጥ ስለወጣት ስናገር እድሜው በ 18 እና 39 ዓመታት መካከል ያለውን ዜጋ እያሰብኩ ነው።

የዘመናችን ወጣት

የዘመናችንን ወጣት የሚተቹ በርካታ ጽሁፎች የወጡ ቢሆንም እኔ ብዙዎቹ ትችቶች አግባብ መስለው አይታዩኝም። በአንድ በኩል ወጣቱ የማኅበረሰቡ አካል በመሆኑ በወጣቱ ውስጥ የሚታየው ክፉም ሆነ ደግ ከማኅበረሰቡ የወረሰው ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ነገሮች ሁሉ ወጣቱ ላይ ይጎላሉ። በሌላው ዓለም ያለው የመብቶች መከበር እና የኑሮ ሁኔታ ከራሱ እውነታ ጋር ሲያመዛዝን የአንዳንዱ ወጣት ልብ በረሀ ለማቋረጥ፣ ባህር ለመሻገር እንዲደፍር ያደርገዋል፤ የአንዳንዱ ወጣት ልብ ደግሞ የማዕከላዊ እስር ቤትና በውስጡ ያለውን ቶርቸር እንዳይፈራ ያፀናዋል። የዘመናችን ወጣት ሊወደስባቸው የሚገቡ በርካታ ነጥቦች ቢኖሩም የሚከተሉት ግንባር ቀደም ናቸው ብዬ አምናለሁ።

Monday, December 1, 2014

ለሀገር ነጻነት የወጣቱ ተሳትፎ ቀጣይነት ይኑረው!

ከ1997 ምርጫ ማግስት ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወጣቶችና በሁሉም የእድሜ ክልል የሚገኙ ዜጎች ለሀገራቸው የዲሞክራሲ መብት መከበር እያደረጉት ያለው አስተዋጽኦ ላቅ እያለ መምጣቱ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። ይህን ተከትሎ ዛሬ ወጣቱ የወላጆቻችን ደምጽ ይከበር፣ ኢትዮጵያዊነት በዘረኝነት አይፈተንም! ነጻነት ዳቦ አይደለም! እስራትና ግድያ በኢትዮጵያ ይቁም! የወያኔ አገዛዝ በቃን! በሚሉ በበርካታ ወጣቶች ጩኸት የወያኔ ሹማምንትና አገልጋዮቹ ላይ የፈጠረው ድንጋጤ ወጣቱን ሽብርተኛ አስደርጎታል።

ወጣቶች ህዝብን አስተባብረው ለተቃውሞ በማሳደም የወያኔን ዘረኝነት በመቃወም ረገድ የተለያዩ ዘዴዎችን ከሌሎች የነጻነት አቢዎት እንቅስቃሴ በመማር እምቢተኝነትን በማሳየት ጅማሮ ላይ ናቸው። ሰሞኑን በባህርዳር ከተማ የተጀመረው የእምቢተኝነት ዘመቻ በሚቀጥለው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል ይቀጣጠል ዘንድ ወጣቱ ሃላፊነት አለበት። ሀገራችን መስቀለኛ መንገድ ላይ ነች። ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው መራራ ትግል ውስጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ ይኖርበታል። አባቶቻችን የውጪ ሀገራትን ወራሪዎች ወራራ ለመመከት ሁሉም ሰው የሚችለውን ሁሉ እንዲያደርግ ያደረጉት ጥሪ አሁንም ላይ ይሰራል።

ለራሳችን ክብር፣ አንድነት፣ ለሀገር ነጻነትና ህልውና መከበር ኢትዮጵያዊ እምቢተኝነት የሚጀምረው ከትንሽ ነው። ህወሃት በጠላትነት የፈረጃችሁ የዛሬ ወጣቶች የሆናችሁ ዘመን በሚፈቅድላችሁ ቴክኖሎጂ በመጠቀም በመላው ሀገሪቱ ወረቀት ከመበትን አንስቶ ሌሎች ይትግል ስልቶችን ተጠቀሙ። ኢትዮጵያ ሀገራችሁ በአንድ ጠባብ ዘረኛ ቡድን መዳፍ ውስጥ ማልቀስ ከጀመረች ሰነባብታለች። ዜጎቿ የግለሰብም ሆነ የቡድን መብታቸው ተረግጦ በባርነት እየተገዙ ነው። ጉልበታቸውና ሀብታቸው እየተመዘበረ ሲሆን፤ ለነጻነት፣ ለዲምክራሲና ለፍትህ የጮኹ ሁሉ ሽብርተኛ ተብለው ወደ ማጎሪያ እየተወረወሩ ነው።

ስለዚህ ስለ ሀገራችን፣ ስለራሳችን የግልም ሆነ የቡድን ጥቅም ስንል በሀገሪቱ የትኛውም ከፍል የተጀመረውን የእምቢ አልገዛም ባይነት እንቅስቃሴ እንደግፍ፣ እንሳተፍ! በባህርዳር የተጀመረውን የወጣቶች እንቅስቃሴን አድንቀን ይህ ተነሳሽነት በሌላውም የሀገሪቱ ክፍል መቀጠል ያለበት ነው።

ይህን በማድረግ ወደ ትግሉ በመቀላቀል ካልተሳተፍን በስተቀር ትግላችን አንድ እርምጃ ወደፊት ፈቀቅ ማድረግ እንደማንችል ግንቦት 7 ያምናል። ስለሆነም ሁሉም አካላት በያለበት በየሚኖርበት፣ በሚችለው አቅሙ ሁሉ ወደትግሉ በንቃት ተሳተፍ! አብረን ታግለን ነጻነታችንን እናረጋግጥ! ለኢትዮጵያ ትንሳኤ፣ የነጻነት አዋጆች ነጋሪ፣ አብሳሪ ትውልዶች እንሆን ዘንድ ሳንታክት እንታገል ዘንድ ወቅቱ የሚጠይቀው ጥሪ ነው።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

Friday, November 28, 2014

የእስክንድር ነጋ ያገባኛል ባይነት!

በላይ ማናዬ

‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››

ይህን ያለው ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ነው፡፡ እስክንድር ነጋን ካወኩት ወዲህ እንደዛሬ በኃይለ ቃል ሲናገር ሰምቼው አላውቅም፤ ወይም ትዝ አይለኝም፡፡ ዛሬ (ህዳር 19/2007 ዓ.ም) እኩለ ቀን ላይ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሆኖም ሁኔታው ሁሉ እንደማንኛውም ቀን አልነበረም፡፡ በር ላይ ስደርስ በርከት ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት ሰሞኑን እያካሄዱት ያለውን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማስመልከት እስክንድር ነጋን፣ አንዱዓለም አራጌን እና ሌሎችንም ሊጠይቁ በቦታው ተገኝተው ነበር፡፡

በጠዋት ቂሊንጦ የሚገኙ ወዳጆቼን ጠይቄ አብረውኝ ከነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ነበር ወደ ቃሊቲ ያመራሁት፡፡ ቃሊቲ የተገኘው ሰው ሁሉ መጠየቅ የሚፈልገውን ሰው እና ሙሉ አድራሻውን እያስመዘገበ ሳለ በመሐል እኔም እስክንድርን መጠየቅ እንደምፈልግ ነግሬ ተመዘገብኩ፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ግን ስማችሁ ከዚህ ቀደም ያልተመዘገባችሁ አሁን መግባት አትችሉም መባሉን መዝጋቢ ፖሊሱ አረዳን፡፡ እኔ እና ትንሽ ሰዎች መግባት ስንችል አብዛኛው ሰው ግን መግባት እንደማይችል ተነገረን፡፡

በዚህ ሁኔታ እስክንድር ጋር ደርሰን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ አንድ የአንድነት ፓርቲ አባል ሰሞኑን ፓርቲያቸው እስረኞችን በተመለከተ በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ ለእስክንድር ያብራራለት ጀመር፡፡ እስክንድር በተለመደ ጥሞናው ሲያዳምጠው ቆይቶ፣ በግሉ የተሰማውን እና መሆን ቢችል ያለውን ነጥብ ተናገረ፡፡ በመሐል ወጣቱ የአንድነት አባል ወደ እስክንድር ጠጋ ብሎ ሌሎች ተጨማሪ ጉዳዮችን ሲነግረው ድንገት አንድ የፖሊስ አዛዥ ጨዋታቸውን እንዲያቆሙና እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እንዲገባ፣ ወጣቱ የአንድነት አባል ደግሞ ወደ ውጪ እንዲወጣ በትዕዛዝ ማጣደፍ ያዘ፡፡

ይህኔ እስክንድር ለስለስ ባለ አነጋገር ምንም እንዳላጠፋን በመግለጽ ፖሊሱ መረጋጋት እንዳለበት አስረዳ፡፡ የፖሊስ አዛዡ ግን ጭራሽ ብሶበት ወጣቱ በቶሎ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ‹ፖለቲካ ማውራት አቁሙ› የሚል ሆነ፡፡ ይህን ተከትሎ እስክንድር ድንገት በኃይለ ቃል ተናገረ፡፡ ‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው!›› አለ እስክንድር በስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡

Thursday, November 27, 2014

ተማሪዎች፣ መምህራን እና የተቋማት ፕሬዚዳንቶች ለአመጽ ተነሱ!

ዘረኛውና አምባገነኑ የህወሓት አገዛዝ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ከካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከላትነት ለይቶ የማያይ ስለመሆኑ በተቋማቱ ውስጥ የሚደረጉ ተግባራት ማረጋገጫዎች ናቸው። ለዚህ ተግባሩ በሰነድ ደረጃ መቅረብ ከሚችሉት የቅርብ ጊዜ ማስረጃዎች ዋነኛው በህዳር 2007 ዓ.ም. በሥራ ላይ የዋለው “የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢህአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጀት ማንዋል” የተሰኘው በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላለፈው ሰነድ ነው። ይህ ሰነድ፣ የህወሓት አሳፋሪ የትምህርት ፓሊሲ ባፈጠጠ መልኩ የተገለፀበት፤ የኢፌዴሪ መንግሥት ተብሎ በሚጠራው የህወሓት አገዛዝ ተቋም እና በህወሓት/ኢህአዴግ ፓርቲ መካከል ለይምሰል እንኳን ልዩነት አለመኖሩ በግላጭ የሚታይበት ሰነድ በመሆኑ በዚህ ርዕሰ አንቀሳችን በስፋት ልንዳስሰው ወስነናል።

ሰነዱ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ መርዙን መርጨት የሚጀምረው ገና በመግቢያው ስለማንዋሉ አስፈላጊነት ሲገልጽ ነው። ማንዋሉ “ከምንም በላይ የብጥብጥና የሁከት መንስኤ የሆነውን ተማሪ በኢህአዴግ አመራር አባላት እየታገዙ ለመያዝ የሚያስችል ነው” በማለት ህወሓት ተማሪውን የሚመለከተው “ከምንም በላይ በብጥብጥ መንስኤነት” መሆኑ፤ ለዚህ መድሀኒቱ ደግሞ ተማሪውን በኢህአዴግ አመራር አባላት “መያዝ” መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ይገልፃል። ቀጥሎም “በምርጫው ሊፈጠር የሚችለውን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሁከትና ብጥብጥ ለማስቆም በማደራጀት መረጃ ለመጥለፍ አመችነቱ የላቀ እንደሚሆን ታምኖበታል” በማለት መረጃ መጥለፍ የዩኒቨርስቲዎችና የትምህርት ሚኒስቴር ሥራ እንደሆነ አድርጎ ያቀርባል።

የማንዋሉን ዓላማዎች በሚገልፀው ክፍል ደግም “… የከፍተኛ ትምህርት የትምህርት የልማት ሰራዊት ግንባታን ወይም የፓለቲካ ሰራዊት ግንባታ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተደራጀና በተናቀጀ ሁኔታ በማቀጣጠልና በማስቀጠል … ምርጫ 2007 ውጤታማ ለማድረግ እና የኢህአዴግን አሸናፊነት ለማረጋገጥ ነው” በማለት ተቋማቱን የኢህአዴግ የምርጫ መሣሪያ መሆናቸውን፤ ግባቸውም የኢህአዴግ አሸናፊነትን ማረጋገጥ መሆኑ ይገልፃል።

በገጽ 3 ላይ ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች “በኢህአዴግ ላይ ያላቸው አቋም የወረደ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በማንኛውም ተቃውሞ ድምፅ ከተጠሩ፤ ሰልፍ የሚያደምቁ፤ ተቃውሞን ከግብ ለማድረስ ሁነኛ መሳሪያ ናቸው። ተማሪዎች በየትኛውም ሐገር እንደታየው አደባባይን የመያዝ ህዝብን አስተባብረው ለተቃውሞ የማሳደም እድላቸው የሰፋ በመሆኑ ከዚህም ሲያልፍ፤ የኢህአዴግ ምከታን በመቃወም ለጠላት ጎራ ተሰልፈው የመታጠቅ እድላቸው ከፍተኛ ነው” ሲል “በወጣቱ እጠላለሁ” የሚለው የህወሓት/ኢህአዴግን ስጋት አፍረጥርጦ ያወጣል። ትንሽ ወረድ ብሎ ደግሞ “በተለይ በአሁኑ ሰዓት ፈተና ላይ የጣለን የምርጫ ጉዳይ እንደምናሸንፍ ቃል የተያዘለት ቢሆንም፤ ፈተናዎች የሚፈጠሩት በህዝብ እና በራሱ ታማኝ ባልሆኑ ሃይሎች ማለትም በመንግስት ክንፍ አይቀለበስም ብሎ ማሰብ አይቻልም። በዚህም ቀድሞ መዘጋጀት ያለበት እና ለሁከት እና ለብጥብጥ መሳሪያ ሊሆን የሚችለው የህዝብ ክንፍ የተማረው ሃይል ሊሆን ስለሚችል ሊታሰብበት ይገባል” ሲል በተማረው ወጣትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሠራተኞች ላይ ያለው ጥርጣሬና ፍርሃት ምን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ይገልፃል።

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለአዳሩ ሰልፍ የእውቅና ደብዳቤ አስገባ


• ቦታው መስቀል አደባባይ እንዲሆን ወስኗል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ከህዳር 27/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28/2007 ዓ.ም ለሚደረገው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ለአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የእውቅና ደብዳቤ አስገባ፡፡

ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የገባው ደብዳቤ በሰማያዊ፣ መኢዴፓ እና ኢብአፓ ተፈርሞ የገባ ሲሆን የእውቅና ደብዳቤውንም ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ ሊቀመንበር፣ የከንባታ ህዝቦች ሊቀመንበርና የትብብብሩ ም/ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርጌሎ፣ አቶ ግርማ በቀለ ከኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና የትብብሩ ፀኃፊ እና የመኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ ገንዘብ ያዥ አቶ ኑሪ ሙደሲር አስገብተዋል፡፡

የትብብሩ አመራሮች ወደ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍሉ በሄዱበት ወቅት የአቶ ማርቆስ ተወካይ ለሆኑት አቶ ፈለቀ አበበ ደብዳቤውን ለመስጠት ጥረት ቢያደርጉም ተወካዩ ‹‹የከንቲባ ጉዳዮች ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው የለም፡፡ እሱ ካልመራበት መቀበል አንችልም›› በሚል ደብዳቤውን አልቀበልም እንዳሏቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ ወደ አቶ አሰግድ ቢሮ ቢያቀኑም እንዳላገኙዋቸው ጨምረው ገልጸዋል፡፡

Wednesday, November 26, 2014

ማስፈራራትና አፈና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችንና ሠላማዊ ሕዝባዊ የለውጥ ንቅናቄዎችን አይቀለብስም !!

ከ9ኙ ፓርዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ

የኢተፖፓ ትብብር አባላት በደረስንበት ስምምነት መሠረት የአጭር ጊዜ የጋራ ዓላማችንን ማስፈጸሚያ ተግባራት የመጀመሪያ ዙር ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል መርህ የአንድ ወር ዕቅድ አውጥተን ወደ ሥራ እንደገባን በገዢው ፓርቲ/መንግሥት ለ07/03/07 በታቀደው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ የዕውቅና ጥያቄ ሂደትና በዕለቱ የተፈጸመውን ሴራ በሚመለከት ‹‹በቢሮክራሲያዊ ሴራ የዜጎችን ህገመንግሥታዊ መብት ማፈን ሠላማዊ ትግሉን አያቆመውም //›› በሚል ርዕስ ሕዳር 08 ቀን 2007 ዓ.ም. ባወጣነው መግለጫ የድርጊቱን ህገወጥነትና ኢህገመንግሥታዊነት አሳይተን ለባለድርሻ አካላት አፍራሽ አካሄዱ እንዲስተካከልና ለዚህ ከምናደርገው ሠላማዊ ትግል ጎን እንዲቆሙ ጥሪያችንን ማስተላለፋችን ይታወሳል፡፡ በመቀጠልም ዕቅዳችንን በመከለስ የቀጣይ ተግባራት ዝግጅታችንን ጀምረናል፡፡ በዚሁ መሰረት ለ21/03/07 ላቀድነው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በ10/03/07 በአባል ድርጅታችን የመላው ኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ/መኢዴፓ/ አማካኝነት የዕውቅና ጥያቄ ደብዳቤ ይዘን በአካል ብንቀርብም ሁለት ቀን አመላልሰውን በመጨረሻ የአዲስ አበባ መስተዳድር የከንቲባ ጽ/ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው ይመኑ ደብዳቤኣችንን ለመቀበል ፈቃደኛ ያለመሆናቸውን ከመግለጽ አልፈው ‹‹የአብዬን እከክ ወደ እምዬ…››እንዲሉ ቢሮኣቸው ደብዳቤውን አስቀምጠን ስንወጣ ወንጀል ነው በማለት ለማስፈራራት ሞክረዋል፡፡

ባለፈው ሣምንት በተፈጸመብን ሴራ ያለመንበርከካችንን ከቀረበው ደብዳቤ የተረዱ የሚመስሉት እኚሁ ባለሥልጣን በቀጣዩ ቀን(12/03/07 ዓ.ም) የባለፈውን የአደባባይ ስብሰባ እንዲያስተባብር ኃላፊነት በሰጠነው ሰማያዊ ፓርቲ ላይ ‹‹ማስጠንቀቂያ›› በሚል ለተጨማሪ ማስፈራሪያ ደብዳቤ ጽፈዋል፡፡ይህ ዛሬ በወህኒ የሚገኙ በሽብርተኝነትና ህገመንግሥት በመጣስ በሚል የታሰሩ የፓርቲ አመራሮችና አባላት፣የኃይማኖት መሪዎች፣ጋዜጠኞች ፣ብሎጌሮች፣ከገዢው ፓርቲ የተለየ አመለካከት ያላቸውን ዜጎች በመፈረጅ ለማሰር፣ ማሰቃት… የተከደበትን ስልት፣ዛሬም በእኛም ሆነ ሌሎች ላይ እየተሞከረ ያለውን የማስፈራራትና የማሸማቀቅ ሙከራ ከሚያስተውሰን በቀር በህጋዊና ሠላማዊ ትግላችን የሚፈለገውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ስለተዘጋጀን የሚፈራ አልተገኘም፣ ከቁብ አልቆጠርነውም፡፡

በዚያው ዕለት(12/03/07 ዓ.ም) በአካል ተገኝተን አንቀበልም የተባልነውን ደብዳቤ በመንግሥታዊው የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በፈጣን መልዕክት አገልግሎት/ኢ.ኤም.ኤስ/ በቁጥር eg156846735et ብንልክም የቱም የመስተዳድሩ አካል ደብዳቤውን ለመቀበል ፈቃደኛ ያለመሆኑ በ16/03/07 ከፖስታ አገልግሎቱ ተገልጾልናል፡፡ ይህ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 12 የተቀመጠውን ‹‹የመንግስት አሠራር ተጠያቂነት›› የጨፈለቀ ድርጊት በተገለጸልን ተመሳሳይ ጊዜ ደብዳቤውን የጻፈው የመላው ኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ/መኢዴፓ/ ሊቀመንበርና የትብብሩ ፋይናንስ ኃላፊ (ደብዳቤውን ሲያቀርቡ አንቀበልም የተባሉት) አቶ ኑሪ ሙዴሲር ‹‹ በመኪና ተገጭተው መደባደብ በሚችሉ ጀግና›› እና ግብረ-አበሮቻቸው ተደብድበው በአካላቸው ሦስት ቦታዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ይህ ትናንት በአቡበከር ላይ የተሞከረውን ተመሳሳይ የፈጠራ ውንጀላና ክስ የሚያስታውሰን ሲሆን ክሱ የማያዋጣ መሆኑ ሲታወቅ ‹‹ ተገጭቶ የሚደበድብ›› ወሮበላ ወደማሰማራት መሸጋገሩን ያረጋግጣል፡፡ እነዚህ ድርጊቶች በገዢው ፓርቲ/መንግስት የሚፈጸሙ ከተለመዱ የፈጠራ ውንጀላ፣እሥራት፣ድብደባ … የፍርኃቱ እርከን ወደከፋ ደረጃ መሸጋገሩን ከማረጋገጣቸው በተጨማሪ ቀጣይ ትግላችን የሚጠይቀውን ከፍተኛ መስዋዕትነት ያመለክታሉ እንጂ የህዝቡን የለውጥ ፍላጎትና ለዚያ የሚደረገውን ትግል አፍነው አያቆሙም ፣ለውጡን አያስቀሩትም፡፡ ትብብሩን ከትግሉ እንዲያፈገፍግ አያደርጉም፡፡

Tuesday, November 25, 2014

እስክንደር ነጋ አሸባሪ ከተባለ ጆን ኬሪና አል ባራዴየም አሸባሪዎች ናቸው ማለት ነው!

 በግርማ ካሳ

በየትም የሰለጠነው አለም እንደሚደረገው፣ በአገርና በሕዝብ ላይ ችግር የሚፈጥር ወንጀለኛ መያዝና መቀጣት አለበት። ሕግ መከበር አለበት። ይሄ ብዙ አያከራክረንም። ነገር ግን «ሕግ፣ ሕግ» እየተባለ፣ ፍጹም ሕገ ወጥ የሆኑ ተግባራት፣ ሕግ አስከባሪ ነን በሚሉ የሕወሃት/ኢሕአዴግ ገዢዎች እየተፈጸመ መሆኑን ነዉ አጥበቀን የምንቃወመዉና የምናወግዘው። የምንታገለውም። ሕግ ሁላችንንም በእኩልነት የሚዳኝ መሆኑ ቀርቶ፣ ጥቂቶች እንደፈለጉ የሚገለባብጡት፣ የመጨቆኛ መሳሪያ በትር መሆኑ ነዉ እያሳሰብን ያለው።

በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በተደረገ ስብሰባ ላይ «እንችላለን! በሌሎች የአፍሪካ ሃገሮች እንደሚቻል አይተናል። ኢትዮጵያ ከእነሱ ቢያንስ ቢያንስ አታንስም። ታሪክ እንስራ!» ሲል እስክንደር ነጋ ተናግሮ ነበር። በተለያዩ ድህረ ገጾች ላይ ይሄንን አቋሙን ሳይፈራ በግልጽ አስፍሯል። እንግዲህ በግብጽ የታየውን እንቅስቃሴ መደገፉ ነው ሽብርትኛ አስብሎ ወደ ወህኒ ያስወሰደው።
«እስክንደር፣ በግብጽ የተከሰተዉ በኢትዮጵያ እንዲከሰት መፈለጉና በዚያ ዙሪያ መንቀሳቀሱ በምን መስፈርትና ሚዛን ነዉ ሽብርተኘንት ተደርጎ ሊወሰድ የሚችለው ? » በሚለው ላይ አንስተን ትንሽ እንበል።

በግብጽ የነበረው እንቅስቃሴ ፍጹም ሰላማዊ የነበረ እንቅስቃሴ ነዉ። ከዚህ እንቅስቃሴ መሪዎች መካከል የነበሩ አንዱ ዶክተር ሞሃመድ አል ባራዴ ይባላሉ። በተባበሩት መንግስታት የአለም አቀፍ ኑክሊያር ኤጀንሲ ሰብሳቢ ሆነው ለበርካታ አመት ያገለገሉ የተከበሩ ሰው ናቸው። እንደ ሳዳም ሁሴን የመሳሰሉ ሽብርተኛ መንግስታት ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች በማከማቸት ለአለም ስጋት እንዳይፈጥሩ የታገሉ፣ የሰላም ሰዉ ናቸው። እኝህ ሰውና የሚመሩት ድርጅታቸው እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር በ2005 የሰላም ኖቤል ተሸላሚ ሆነዋል። ታዲያ ሰላማዊ በሆነ መልኩ፣ አምባገነኑ የሙባረክ መንግስት ለሕዝብ ፍቃድ ተጠያቂ እንዲሆን፣ የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ፣ መታገላቸው እኝህ የሰላም የኖቤል ተሸላሚን ሽብርተኛ ያደርጋቸዋልን ?

በአዲስ አበባ ጆን ኬሪ፣ ሃርድ ቶክ ቢቢሲ ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተማሪዎች ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሰጥተው ነበር። የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ቴዎድሮስ አዳኖም በዚያ ነበሩ። ጆን ኬሪ ንግግራቸውን ሲጀመሩ የተናገሩትን ማንሳት እፈልጋለሁ። በግብጽ ስለነበረው ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሽብርተኘንት ብሎ ስለሚጠራዉ፣ እንቅስቃሴ ሲናገሩ የሚከተለዉን ነበር ያሉት፡

«…the greatest concern has to be the lack of the fulfillment by governments in many countries, of the aspirations of people. Particularly the creation of jobs, and tሀ educational opportunities that are needed, for this modern world….In Egypt, that was not a revolution that was moved by Islamism, or any ideology ….It was young people.. ..it was you ..people who came to the square , and twitted each other , texted each other , e-mail each other and brought people»

Monday, November 24, 2014

30 ደቂቃዎችን በዝዋይ እስር ቤት (ግዞት)

‹‹በብርቱ ታምሜያለሁ›› አበበ ቀስቶ

በላይ ማናዬ

ዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በቦታው ተገኝቼ ለመጠየቅ እቅድ ከያዝኩ ረዘም ያሉ ቀናት አልፈዋል፡፡ እንዲያውም ጉዞው ከወዳጆቼ ጋር ሰብሰብ ብለን ቢሆን እንደሚመረጥ ተነጋግረንበት ነበር፡፡ ሆኖም ግን የዕለት ከዕለት ሩጫችን አላወላዳ ብሎን ባቀድነው ጊዜ ወደ ዝዋይ መጓዝ ሳንችል ቆይተናል፡፡ አርብ ህዳር 12/2007 ዓ.ም ግን እንዳሰብነው ሰብሰብ ብለንም ባይሆን በመጨረሻ አብሮኝ ከተጓዘው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ባልደረባ ወጣት ፍቅረማርያም አስማማው ጋር ከአዲስ አበባ በጠዋት ተነስተን ወደ ዝዋይ አምርተን ለ30 ደቂቃዎች ያህል የናፈቅናቸውንና የናፈቁንን እስረኞች ልንጎበኝ በቅተናል፡፡

ዝዋይ ለመድረስ ከ2 ሰዓት በላይ ጉዞ ማድረግ ነበረብን፤ በጠዋት ቃሊቲ መነሐሪያ በመገኘት የዝዋይን ትራንስፖርት ለመያዝ ስንገኝ መልካም አጋጣሚ ተከሰተ፡፡ አጋጣሚው እኛ ወደምንሄድበት ዝዋይ እስር ቤት ሊሄዱ የተሰናዱትን የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም እና ሌላ የስራ ባልደረባውን ያገናኘ ነበር፡፡ ቁጥራችን መጨመሩ ለእኛም ለምንጠይቃቸው እስረኞችም መልካም ነበር፡፡

ከተማዋ እንደደረስን ወደ አንድ አብረውኝ የተጓዙት ወዳጆቼ የሚያውቁት ቤት አመራን፤ ቡና በፔርሙስ ለመያዝ፡፡ ‹‹ተመስገን ደሳለኝ በእጅጉ ቡና ይወዳል አለኝ›› ታናሽ ወንድሙ፡፡ ቡናውን አስቀድተን ከከተማዋ ትንሽ ወጣ ብሎ ወደሚገኘው እስር ቤት አመራን፡፡ ጉዞው ደግሞ በጋሪ ነበር፡፡ ወደእስር ቤት የሚወስደው መንገድ እጅግ አቧራማ በመሆኑ ተጓዦች አቧራውን መልበሳቸው እሙን ነው፡፡ በእግር ለመጓዝ የፈቀደ ካለ ድልህ ቲባን በጫማዎቹ ልክ ይዋኝበታል፡፡ የእኛ ጉዞ በጋሪ ቢሆንም ከአቧራው ማምለጥ ግን አይቻልም፡፡

እስር ቤቱ በር ደርሰን ከጋሪ እንደወረድን ወደጥበቃዎቹ ቀርበን የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስም ሰጥተን የእኛን ሙሉ አድራሻ አስመዘገብን፡፡ የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስናስመዘግብ ‹‹ምኑ ነህ?›› የሚለው ጥያቄ ይነሳል፡፡ ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…እያልን አስሞላን፡፡ መዝጋቢ ፖሊሶቹ ቀና እያሉ በጥያቄ ያዩናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ወገኖች ‹ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…› ተብለው እንጂ ሌላ በምን ይገለጻሉ ታዲያ! በዚህ መሰረት የአራት እስረኞችን ስም አስመዘገብን፤ እነሱም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ናቸው፡፡ ጥብቅ ፍተሻውን አልፈን ልናያቸው የጓጓንላቸውን እስረኞች ወደምንገናኝበት ቦታ አመራን፡፡

ታሪክን ማደብዝዝም ማጥፋትም አይቻልም!

በአለማችን በተለይ አፍሪካ ዉስጥ የአገርን ብሄራዊ ኃብት የሚዘርፉ፤የህዝብን መብት የሚረግጡና አገርን እነሱ ባሰኛቸዉ አቅጣጫ ብቻ ይዘዉ የሚነጉዱ አያሌ ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት አሉ። እነዚህ ህዝብን የሚበድሉ መንግስታት ሁሉም በጥቅሉ አምባገነን ይባሉ እንጂ በመካከላቸዉ ጎላ ብሎ የሚታይ ትልቅ ልዩነት አለ። ሀኖም የቱንም ያክል ልዩነት ቢኖርም እንደ ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች እንመራዋለን የሚሉትን ህዝብ የሚንቁና የኛ ነዉ የሚሉትን አገር የሚጠሉ አምባገነን መንግስታት የሉም፤ በታሪክም ኖረዉ አያዉቁም። አምባገነን መንግስታት የስልጣን ዘመናቸዉን ለማራዘምና ከስልጣን ጋር ተያይዞ የሚመጣዉን ክብር፤ ዝናና ጥቅማ ጥቅም እንዳይቋረጥ ሲሉ የሚቃወማቸዉንና ለስልጣን ዘመናቸዉ አደጋ ነዉ የሚሉትን ሁሉ ያስራሉ፤ ይደበድባሉ ወይም ይገድላሉ። እነዚህን ነገሮች የወያኔ መሪዎችም ያደርጋሉ፤ ነገር ግን በወያኔና በሌሎቹ አምባገነን አገዛዞች መካክል እጅግ በጣም ትልቅ ልዩነት አለ። ለምሳሌ ወያኔዎች ዘረኛ አምባገነኖች ናቸዉ፤ የወያኔ መሪዎች ኢትዮጵያን እንደ ጥገት ላም አንጂ እንደ አገራቸዉ አይመለከቱም። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያን፤ ህዝቧንና ታሪኳን ይንቃሉ፤ ያንኳስሳሉ።

ባለፉት አምስትና ስድስት አመታት በግልጽ እንደተመለከትነዉ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ገበሬ ከመሬቱ አፋናቅለዉ ለምለም መሬቱን ለባዕዳንና ለህወሓት የጦር መኮንኖች ሰጥተዋል። መሬቴንና ቤቴን አልለቅም ብሎ የተቀናቀናቸዉን ደግሞ በጅምላ ገድለዋል። በከተሞች ዉስጥም ከተሜዉን ምንም ካሳ ሳይከፍሉት ዕድሜ ልኩን ከኖረበት ቤቱ እያፈናቀሉ ከነቤተሰቡ ሜዳ ላይ ጥለዉት መሬቱን ባለኃብት ለሚሏቸዉ የወያኔ ባለሟሎች ሰጥተዋል። በአጠቃላይ የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ አንድነት፤ በታሪኳና በህዝቧ ላይ እንዲህ ነዉ ተብሎ ለመናገር የሚዳግት ትልቅ በደል ፈጽመዋል። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በእናት አገራችን ላይ ያደረሱት በደል ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለምና ዛሬ ወደዚያ ዝርዝር ዉስጥ አንገባም፤ ዛሬ ትኩረት የምንሰጠዉ ወያኔ ደግሞ ደጋግሞ ከዘመተባቸዉና ሙሉ ኃይሉን ካሳረፈባቸዉ የአገራችን እሴቶች አንዱ ታሪካችን ነዉና የዛሬዉ ቆይታችን በዚሁ በታሪካችን አካባቢ ይሆናል።

ታሪክ በአንድ አገር ዉስጥ እያንዳንዱ ትዉልድ ከሱ የቀደመዉ ትዉልድ በግል፤ በቡድንና በማህበረሰብ ደረጃ የተጓዘበትን መንገድ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ካለፈዉ የምንማርበትና የወደፊቱን ጉዟችንን ለመጀመር በመረጃነት የሚያገለግለንን እዉቀት የምናገኝበት የጥበብ ድርሳን ነዉ። የማንም አገር ታሪክ ዉብ ሆኖ የሚያምርና የማያምር ሁለት ገጽታዎች አሉት፤ የማያምረንን የታሪክ ጠባሳ ወደ ኋላ ሄደን ማከም በፍጹም እንደማንችል ሁሉ የወደፊቱን ታሪካችንንም የብዙ ማህበረሰባዊ መስተጋብሮች ዉጤት ነዉና ያሰኘንን ቅርጽና ይዘት ልንሰጠዉ አንችልም። የታሪክ ዋናዉና ትልቁ ቁም ነገር የታሪኩ ባለቤት የሆነዉ ማህብረሰብ እራሱን ወደ ኋላም ወደ ፊትም የሚመለትበት መስኮት መሆኑ ነዉ። ምንም አይነት ታሪክ የሌለዉ ህብረተሰብ የለም፤ ካለም ከየት አንደመጣና ወዴት አንደሚሄድም አያዉቅም።

አገራችን ኢትዮጵያ ረጂምና ጥንታዊ ታሪክ ካላቸዉ ጥቂት አገሮች ዉስጥ አንዷ ናት። ይህ ረጂም ታሪካችን ደግሞ አንገት ቀና የሚያስደርግ የድልና የገድል ታሪክ አንደሆነ ሁሉ አንገት የሚያስደፋ የግፍና የበደል ታሪክም አለበት። የዛሬዉ ትዉልድ ኢትዮጵያዊ ካለፈዉ ታሪኩ ከበደሉም ከገድሉም ተምሮ የወደፊት አካሄዱን ከሞላጎደል መቆጣጠር የሚችል እድለኛ ትዉልድ ነዉና አባቶቹ ባቆዩለት ታሪክ ሊኮራ ይገባል። አንድ ህዝብ በታሪኩ እንዲኮራ ደግሞ ታሪኩ በተደጋጋሚ ሊነገረዉ ሊተረክለትና በጽሁም መልክትም በገፍ ሊቀርብለት ይገባል። የአገራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ለዚህ የታደለ አይደለም ፤ ምክንያቱም እንመራሀለን የሚሉት መሪዎቹ ታሪኩን የሚያንቋሽሹና የሚንቁ መሪዎች ናቸዉ።

Friday, November 21, 2014

መምጫውን የማያውቅ መድረሻውን ያጣል

ታሪክ ለሰው ልጅ ስሩና መሠረቱ ነው።ታሪኩንና መምጫውን የማያውቅ ህዝብ መድርሻውን የማያውቅና ራሱንም ለባርነት አሳልፎ የሰጠ ይሆናል፡፡ ለክብሩ ለእርሱነቱ ለህብረቱና ለነፃነቱ ፀንቶ መቆየት እና የጥንካሬውና ተሳስሮ የመዝለቂያው ሰንሰለት ታሪኩ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የአሜሪካ ባርያ ፈንጋዮች ትናንት በገፍ ከአፍሪካ በባርነት ያመጡዋቸው አፍሪካውያን አንድ ቀን በአንድ ቆመውና በህብረታቸው ጠንክረው ራሳቸውን ነፃ ለማውጣት እንዳይነሱ ሀ ብለው የነጠቋቸው ማንነታቸውን፤ ታሪካቸውንና መገኛቸውን ነበር፡፡ እንደ እቅዳቸውም እነሆ ዛሬ አብዛኛው ጥቁር አሜሪካዊ እኔ ማን ነኝ? መምጫዬስ ከወደየት ነው? በሚሉና በመሳሰሉ ጥያቄዎች ተተብትቦ ለምላሹ ሲውተረተር መገኘቱ፤ እንዲሁም ዛሬም ከተገዢነት መንፈስ ራሱን አላቆ በሁለት እግሩ ለመቆም ሲታትር ይገኛል፡፡

ሌላው የኢጣልያ ወራሪን ሀይል ቅስም የሰበረውና በአለም አቀፍ ደረጃ ቅሌት ያከናነበው የአድዋ ጦርነት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ቅሌት በደም አጥቦ ሀያልነቱን ለአለም ለማሳየት በሞከረበት ሁለተኛው ወረራ ወቅት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የአድዋ ጦርነት የመሩት የአፄ ሚንሊክ ሀውልትን ከጥልቅ ጉድጓድ መቅበር እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ባጠቃላይ አንድ ህዝብ እንደ ህዝብና ሀገር ጠንክሮና በነፃነት ኮርቶ ለመኖር ብሎም ከትውልድ ትውልድ መሸጋገር መቻል ከማረጋገጫው አንዱ የትናንት ማንነቱና የመገኛ ታሪኩ መሆኑን ከላይ በምሳሌነት ያነሳናቸው ነጥቦች ያረጋግጣሉ፡፡

ታሪክ ለአንድ ህዝብ የማንነቱ መገኛ፤ የመገኛው ምንጩና መምጫውን የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን የነገ መዳረሻውን የመመልከቻ መነፅርና ጠንክሮ የመንቀሳቀሻው ጉልበቱ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ መሳሪያ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ አንድ ህዝብ ታሪኩ ከጠፋ ሊገጥመው የሚችለው ችግርና ፈተና እንዲህ በቀላሉ የሚገመት ያለመሆኑንና እንደ ህዝብ እንደ ሀገር ቀጣይነቱን በቀላሉ መፍትሄ ከማይገኝለት ፈተና ውስጥ ይከተዋል ማለት ነው፡፡

ኢትዮጵያችን ዛሬ ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ ህልውናዋ አደጋ ላይ የወደቀበት መሆኑ ለማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ባለፉት 23 አመታት በዘረኞቹ የወያኔ ጉጅሌዎች እጅ ከወደቀችበት እለት ጀምሮ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆኑ የታሪካችንና የባህልችን ዋና ዋና እሴቶች ዋነኛ ኢላማ ሆነዋል፡፡ ይህንንም በተደጋጋሚና በግልፅ ከወያኔው መሪ እስከ ተራ ደጋፊው የሚወረወረው በትር ያረጋግጣል፡፡ ጉጅሌዎቹ የነፃነት ምልክት የሆነውንና በዕልፍ አዕላፋት ደም መሥዋዕትነት ፀንቶ የቆየውን ሰንደቅ ዓላማ በሶ መጠቅለያ ጨርቅ ከማድረግ ጀምረው ዛሬ በምሁራን ጥረትና በእያንዳንዱ ዜጋ ድጋፍ የተሰባሰቡት የታሪኮቻችን መዛግብት በጥንቃቄ ከተቀመጡበት (ቤተ-መዛግብት) እያወጡ ከማውደምና ለስኳር መጠቅለያነት እስከ መሸጥ ደርሰዋል፡፡

Thursday, November 20, 2014

ምርጫ ሲባል አማራጭ ሳያሳጡ መሆን ይኖርበታል!!!

                                  አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
              UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

                         ምርጫ ሲባል አማራጭ ሳያሳጡ መሆን ይኖርበታል!!!

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
...
በሀገራችን ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ጊዜ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚደረግ በመንግስት በኩል በከፍተኛ ደረጃ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት የተከናወኑት አራት ምርጫዎች ያየን እንደሆነ በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ወደፊት ሊወስዱ እንዳልቻሉ እሙን ነው፡፡ ይህም ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት በተለያየ መንገድ ሲገልፅ ቆይቷል፡፡ በተቃራኒው መንግስትና ገዢው ፓርቲ በፍፁም መለየት በሚያስቸግር ሁኔታ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ሆነው ተቀናጅተው ለአንድ ለአውራ ፓርቲ ግንባታ እየሰሩ እንደሆነ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህ የመንግሥትና የገዢው ፓርቲ ተግባር ምርጫን ያለ አማራጭ እንዲሆነ እያደረገው እንደሆነ ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡

በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ አባላት ላይ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ዘመቻ በሚባል ደረጃ እየተካሄደ ያለው አፈናና እስር፤ ከዚህም ባሻገር ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ ክልከላውና ወከባው ተጠናከሮ መቀጠሉ፤ ገዥው ቡድን የምር ተቃዋሚ ፓርቲ ናቸው ብሎ የሚያስባቸው ፓርቲዎች ለማዳከምና ከምርጫው ውድድር ውጪ ለማድረግ ያለው ቁርጥ አቋም የሚያሳይ ነው። ይህ የገዢው ቡድን አካሄድ በሀገራችን ዴሞክራሲያዊ የሆነ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት እንዲመሰረት ፍላጎት እንደሌለው በደንብ የሚያረጋግጥ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃና ፍትሐዊ በሆነ ምርጫ የሚፈልገውን ፓርቲ እንዲመርጥ እድል ሊጠሰው ሲገባ በሥርዓቱ በእኩል ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳያካሄድ የተለያዩ ጫናዎች እየተደረጉበት የሚካሄዱት ምርጫዎች ሁሉ ትርጉም አልባ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡ ይህ የገዢው ቡድን ሀላፊነት የጎደለው እንቅስቃሴ በተግባር የሚደግፈው ከሠላማዊ ትግል ይልቅ የኃይልና የአመፅ መንገድ እንደሚሆን የተረዳ አይመስልም፤ ይልቁንም በሠላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉትን ፓርቲዎች ወደ አላስፈላጊ መስመር በመግፋት ሀገራችን ወደ ብጥብጥና ወደ እርስ በእርስ ጦርነት እንድትገባ የሚያደርግ ሁኔታ እየተከተለ ነው የሚገኘው። በሥልጣን ላይ ያሉት ወገኖች ይህ አሳሳቢ ሁኔታ በትክክል እንዳያዩ ጭፍን የሥልጣን ጥም ጋርዷቸዋል፡፡

Tuesday, November 18, 2014

ታሪካችን የደብተራ ነው አላችሁኝ?

ከዋልን ካደርን ገና ብዙ ጉድ እንሰማለን። የኢትዮጵያን ታሪክ ማጠልሸት ሰሞኑን እንደ ወረርሽኝ ሆኗል። የኢትጵያን ታሪክ የደብተራ ተረት ነው ብሎ ማጣጣል፣ ደብተራን ከአማራ ጋር ብቻ ማያያዝ ያለማወቅ በሽታ ካልሆነ ምን ይባላል? አለማወቅን ማወቅ ጤና፣ አለማወቅን አለማወቅ ደግሞ በሽታ ነው።

ደብተራ ያየውን የሰማውን በከተበ ለምን ይንቋሸሻል? የደብተራ ጥፋቱ አስቀድሞ መሰለጠኑ ነው፤ ፊደል የስልጣኔ በር ነው፤ ደብተራ ደግሞ ፊደል የቆጠረ የመጀመሪያ ሰው ነው፤ የኢትዮጵያ ደብተሮች በጊዜያቸው ከነበሩት ሰዎች አስቀድመው የሰለጠኑ ናቸው፤ ስልጣኔውን ያገኙትም በፊደል በኩል ነው። አስቀድመው በመሰልጠናቸውም፣ ለሁላችንም የሚሆን ነገር ጽፈው አለፉ። ባይሰለጥኑ ኖሮ ታሪክን ለመጪው ትውልድ ስለማስተላለፍ አይጨነቁም ነበር። ከደብተራ ውጭ ታሪክን ለመጪው ትውልድ ጽፎ ስለማስቀረት ያሰበ ማን ነው? ተራው ገበሬ ዝናብ መጣ ሄደ፣ ተራው ነጋዴ አሞሌ ተወደደ ረከሰ፣ ተራው ወታደር ድንበር ሰፋ ጠበበ፣ ንጉስ ግብር ጨመረ ቀነሰ ከማለት ውጭ ታሪክ ጽፎ ስለማስተላለፍ ተጨንቆ ያውቃል? ስለጥበብ ስለውበት ተጨንቆ የጻፈውም ደብተራው ነው።

ደብተራ ባየው በሰማው፣ የጆግራፊ እውቀቱ፣ የእግሩ ጥንካሬ፣ የቀለም አቀባበሉና እድሜው በፈቀደለት መጠን ጻፈ። ሲጽፍ ይጨምራል፣ ይቀንሳል። የጨመረውን የቀነሰውን ማስተካከል ከደብተራ የተሻለ እውቀት ያገኘው የሁዋለኛው ትውልድ ሃላፊነት ነው። ታዲያ እንዲህ ሲባል ደብተራን በማድነቅ እንጅ በማንቋሸሽ አይጀመርም። ኒውተን ጋሊሊዮን አንቋሾ ጥናት አልጀመረም፣ አንስታይን ኒውተንን አንቋሾ አልተነሳም። የኛ ዘመንኛ ጻፊዎች ደግሞ የሁዋላውን አንቋሾ መጀመር እውቀት ይመስላቸዋል። ጽሁፋቸውም በውሃ ላይ እንደበቀለ ተክል የሚሆነው ለዚህ ነው፣ ስር አልባ ነው፤ እፍ ቢሉት እንደ ላባ በኖ ይጠፋል።
አሁን ደብተራ ባይጽፍ ኖሮ ታሪካችን የሰሃራ በታች ካሉት አገራት ይለይ ነበር?። ከሰራሃ በታች ካሉ አገራት በራሱ ቋንቋ ታሪኩን ጽፎ ያስቀረ ከእኛዋ ኢትዮጵያ ውጭ ሌላ አለ? አብዛኛው የጥቁሩ የአፍሪካ ታሪክ የተጻፈው በቅኝ ግዛት ጊዜ አይደለምን? ፈረንጆቹ ለእነሱ በሚጥማቸው መንገድ አይደለም የከተቡት? ምንጫቸውስ ምንድነው? ህንጻዎች እና ቁሳቁሶች አይደሉም? ታዲያ ደብተራ ታሪክ ጽፎ ባስቀረ፣ ድንጋይና ቁሳቁስ ከመፈለግ ባዳነ ለምን ይሰደብ?

Sunday, November 16, 2014

የሰንደቅ አላማችን ጠላት ወያኔና ወያኔ ብቻ ነዉ!

ሰንደቅ አላማ ለአንድ አገር ህዝብ የኩራት፤ የአልበገር ባይነት፤ የአንድነትና የታሪክ ተከታታይነት ምልክት ነዉ። ሰንደቅ አላማ በአንድ በኩል የወደፊቱን ብሩህ ተስፋ ክወዲሁ እያሳየን እየዟችሁ የሚለን፤ በሌላ በኩል ደግሞ በምናብ ወደኋላ እየወሰደን የድልና የመስዋዕትነት ታሪላችንን የሚያስታዉሰን የነጻነት፤ የሠላምና የብሩህ ተስፋ ማህደር ነዉ። የአገራቸን የኢትዮጵያ አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ሰንደቅ አላማ ትናንትናና ከትናንት ወዲያ በተስፋፊዎች አለመደፈራችንን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ዘረኞች የጫኑብንን የመከራ ቀንበር በቆራጥነት ሰብረን ነገና ከነገ ወዲያ የነፃነት አየር እንድንተነፍስ አስረግጦ የሚነግረን የአንድነታችን፤ የተገጋድሏችንና የድላችን ልዩ ምልክት ነዉ። አንድን ኢትዮጵያዊ ሰንደቅ አላማ ላንተ ምንህ ነዉ ብለን ብንጠይቀዉ ጥያቄዉን ዕድሜህ ስንት ነዉ ተብሎ እንደሚጠየቅ አንድና ሁለት ቃል ብቻ ተናግሮ አይመልስም። ሰንደቅ አላማም በአንድና በሁለት ቃላት ምንነቱ የሚገለጽ ተራ ቃል አይደለም። ኢትዮጵያዉያን ተማሩ አልተማሩ፤ ደሃ ሆኑ ኃብታም ፤ወንጀለኛ ሆኑ ወይም ሠላማዊ ለአገራቸዉ ሰንደቅ አላማ የተለየ ቦታ አላቸዉ። ሰዎች የአገራቸዉን ሰንደቅ አላማ የሚወዱትና ለሰንደቅ አላማዉ በክብር መዉለብለብ የህይወት መስዋዕትነት የሚከፍሉት ስለታዘዙ ወይም ስለ ሰንደቅ አላማዉ ተነግሯቸዉ አይደለም። በእርግጥም የሰንደቅ አላማ ክብርና የአገር ፍቅር ለሰዎች ሰንደቅ አላማዉን አክብሩ፤ አገራችሁን አፍቅሩ እየተባለ የሚነገር ነገር አይደለም። አገርንና ወገንን ማክበርና መዉደድ ሰንደቅ አላማን ከማክበርና ከማፍቀር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነዉ።የሰንደቅ አላማ ልዪ ክብርና የአገር ፍቅር ሰዎች ተወልደዉ ከሚያድጉበት ማህበረሰብ፤ ከቤተሰብ፤ ከጎረቤትና ከጓደኛ እንደ ምግብና እንደ ዉኃ እየበሉና እየጠጡ የሚያገኙት የሰዉነትና የዜግነት መገለጫ ታላቅ እሴት ነዉ።

ለዚህም ነዉ የማንም አገር ዜጋ አገሩ ዉስጥ ቢኖር ወይም ካገሩ ዉጭ፤ ቢታሰር ባይታሰር፤ ሀብታም ቢሆን ወይም ደሃ፤ የኔ ነዉ የሚለዉን የእናት አገሩን ሰንደቅ አላማ በፍጹም የማይረሳዉ። ከአገራቸዉ ዉጭ የሚኖሩ ሰዎች ደግሞ በተለይም ኢትዮጵያዉያን በተለያዩ ምክንያቶች የሚኖሩባቸዉን አገር ዜግነት ቢወስዱ እንኳን ሰንደቅ አላማቸዉን ባዩና ባስታወሱ ቁጥር የሚሰማቸዉ አገራዊ ስሜት እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ – እንዲያዉም ከአገራቸዉ ተሰድደዉም ሆነ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከአገራቸዉ ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ሰንደቅ አላማቸዉን ባዩ ቁጥር የአገራቸዉ፤ የወንዛቸዉ ፤ ተወልደዉ ያደጉበት መንደርና የልጅነት ትዝታቸዉ ባአይናቸዉ ላይ እየመጣ ዕንባ በዕንባ ይተናነቃሉ። ሰንደቅ አላማ ለአንድ አገር ህዝብ አንድ ነገር ነዉ፤ ብዙ ነገር ነዉ፤ ሁሉም ነገር ነዉ። ሰንደቅ አላማ ህዝብን ያስተባብራል፤ ያከባብራል፤ ያዋድዳል፤ መስዋዕትነትን፤ ፍቅርንና ብልፅግናን ያመለክታል።

Wednesday, November 12, 2014

ጊዜው የሕዝባዊ እምቢተኝነት ነው!!!

በአሁኑ ወቅት በአገራችን በከተሞችና በገጠሮች እየታዩ ያሉ ምልክቶችን በጥንቃቄ የመረመረ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መታዘቡ አይቀርም።

በአንድ በኩል፣ ወያኔ የተወገደባት፣ ፍትህ የሰፈነባትና የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ሆና የማየት ተስፋችን እየለመለመ ነው። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጂም ዓመታት በሕዝብ ላይ ሰፍኖ የነበረው የፍርሀት ደመና እየገለጠ በመሆኑ ተዘግተው የቆዩ አንደበቶች መናገርና “ይኸ ሁሉ ግፍ ለምን?” ብለው መጠየቅ ጀምረዋል። ይህንን መነቃቃት በአስተሳሰብም፣ በተግባርም፣ በኪነጥበብም እያየነው ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች ለውጥ በአገራችን ሊመጣ እንደሚችል ከማመን አልፎ ራሳቸውን በለውጥ አምጭ ኃይልነት መመልከት ጀምረዋል። በርካታ ወጣቶች ወያኔን በትጥቅ ለመገዳደር የወሰኑ ወገኖቻችንን እየተቀላቀሉ በዚህም ምክንያት ጉልበታቸውን እያፈረጠሙ ነው። የለውጡ እርሾ ከሲቪሉ አልፎ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በኢሕአዴግ ድርጅቶች ውስጥም እየተብሰለሰለ ነው። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት፣ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚጠቀምበት ኃይል መሆኑ እያበቃ በአንፃሩ የትግሉ አጋር የሚሆንባቸው ሁኔታዎች እየታዩ ነው። በሁሉም የሠራዊቱ ክፍሎች ጉምጉምታው ወደ ጩኸት እየተቀየረ በመሆኑ ሠራዊቱ በአለቆቹ ላይ የሚነሳበት ጊዜ እሩቅ አይደለም። በተለያዩ ምክንያቶች ህወሓትን ወይም ህወሓት የፈጠራቸውን ድርጅቶች የተጠጉ በአጠቃላይ ኢሕአዴግ በሚባለው ስብስብ ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችንም “ለመሆኑ ማንን ነው እያገለገልን ያለነው?” ብለው በመጠየቅ ላይ ናቸው። በዚህም ምክንያት ወያኔ ውስጡ እየተረበሸ ነው። ከኢትዮጵያም ውጭ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ ዘንድ ያለው ቁጣና ዝግጁነት ከወትሮው እጅግ የላቀ ነው። በአጭሩ፣ በሁሉም አቅጣጫ፣ ደረጃ በደረጃ የሕዝባዊ እምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል።

በአንፃሩ ደግሞ፣ የጨለማ ንጉሥ የሆነው ወያኔ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብን ወደ ፍርሀት ቆፈን ለመመለስ እስሩን ከመቸውም በላይ ያጧጧፈበት ጊዜ ነው። በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በአፋር በሶማሊ ... በመላው ኢትዮጵያ ብሩህ ራዕይ የሰነቁ ወጣቶችና አዛውንት ታድነው እየታሰሩ ናቸው። የወያኔ እስር ቤቶች በአርቆ አስተዋይ ዜጎቻችን ተሞልተዋል። ወትሮም ከፍተኛ የነበረው ስደት ብሶበታል፤ ለእውነት በጽናት የቆሙ ጋዜጠኞች ወይ ታስረው፣ አልያም ተሰደው አልቀዋል። የወያኔ የግዴታ ስልጠና አገሩን እያመሰው ነው። የኢትዮጵያዊያን ኑሮ በእጦቶች የታጀበ ሆኗል። የነፃነት እጦት፣ የፍትህ እጦት፣ የመብራት እጦት፣ የስኳር እጦት፣ የዘይት እጦት፣ የታክሲ እጦት፣ የመኖሪያ ቤት እጦት፣ እጦት፣ .... እጦት።

Monday, November 10, 2014

ግልጽ ደብዳቤ ”ለጠቅላይ ሚኒስትር” ኃይለማርያም ደሳለኝ

ከታሳሪ ዞን 9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስታችንን ያክብሩ!

ሠላም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር!? እንዴት ነዎት? ያስታውሱ ከሆነ የዛሬ ሁለት ዓመት አካባቢከፊሉ የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች ‘ግልፅ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ’

“ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እባክዎትን የተለያዩ የመንግስት አካላት የሕገ መንግስታችንን ድንጋጌዎች እየጣሱ ነውና እርስዎም በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 74/13/ መሠረት ሕገ መንስቱን የማስከበርና የማክበር ግዴታ ስላለብዎት ሕገ መንግስቱን ያክብሩ” በማለት አንዲት አጭር ደብዳቤ ፅፈንልዎት ነበር፡፡

ድንገት በተለያዩ ምክንያቶች የጻፍንልዎትን ደብዳቤ ካላነበቡት ወይም ማስታወስ ካልቻሉ ዛሬ ይሄን ማስታወሻ ስለምንፅፍልዎት ግለሰቦች አንድ ሌላ ማስታወሻ እንስጥዎ፡ ከ6ወራት በፊት /በሚያዚያ 2006 ዓ.ም/ ሶስት ጋዜጠኞችንና ስድስት ጦማሪያንን ‘ሕገ መንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ በመሞከር ወንጀል ጠርጥሬያችኋለሁ’ በማለት መንግስትዎ ልማታዊ ርምጃ (አብዮታዊ ርምጃ እንደሚባለው) ወስዶ ነበር፡፡

እኛም የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች የዚህ ‘ልማታዊ ርምጃ’ ሰለባ የሆንን ግለሰቦች ነን፡፡በርግጥ ከሁለት ዓመታት በፊት ‘ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስቱን’ ያስከብሩልን በማለት ጥያቄ ያቀረብንልዎት ግለሰቦች ‘ከ6 ወራትበፊት ሕገ መንግስቱን ለመናድ ሞክራችኋል’ በማለት መንግስትዎ ሲያስረን ሕገ መንግስቱ እንዲከበር ጠይቀን ሕገ መንግስቱን ለመናድ በመሞከር ወንጀል ተጠርጥረን ስንታሰር እስሩ በጣም ግራ አጋብቶን ነበር፡፡በዚህ ያልቆመው መንግስትዎ ክሱን ‘ሕብረተሰቡንና ሀገሪቱን ለማሸበር አቅዳችኋል ሞክራችኋል አሲራችኋል…’ በማለት ወደ ‘ሽብርተኝነት’ያሳደገው ሲሆን እርስዎም ከዚህ ጋር በተያያዘ ሃሳብዎትን ሲሰጡ ስለተመለከትንዎ ትንሽ ቅሬታ ይዘን መጣን፡፡

በቅድሚያ አሁን ያለንበትን ሁኔታ በትንሹ ብናስረዳዎት ቅሬታችንን ለመረዳት ያስችልዎታልና አንዳንድ ጉዳዮችን እንንገርዎት፡፡
ይሄን ማስታወሻ በምንፅፍልዎት ወቅት ከታሰርን ከ 200 ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን፣ነገር ግንጉዳያችን ገና በቅድመ ክስ (Pre Trial) የክርክር ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ ይሄ የሆነበት ዋነኛ ምክንያትም መንግስትዎ እንኳን ለእኛ ለተከሳሾች ለከሳሽ አካልም ግልፅ ያልሆነ ክስ በማቅረቡ ነው፡፡ ይሄንንም ስንል ልትፈፅሙት ነበር የተባለው ‘የሽብርተኝነት ድርጊት’ ሳይጠቀስ ‘በቃ የሽብርተኝነት ድርጊት ልትፈፅሙ ነበር’ በማለት በጨበጣ ስለመጣብን ነው፡፡

Ethiopia 2014: I Always Remember in November and in...

ALEMAYEHU G MARIAM 

Oh, Cruel November 2005! 

In 2005, Ethiopians faced unspeakable horrors. Following the parliamentary elections in May of that year, hundreds of Ethiopian citizens who protested the daylight theft of that election were massacred or seriously shot and wounded by police and security personnel under the exclusive command and control of the late regime leader Meles Zenawi. An official Inquiry Commission established by Zenawi documented that 193 unarmed men, women and children demonstrating in the streets and scores of other detainees held in a high security prison were intentionally shot and killed by police and security officials. An additional 763 were wounded**.

Every November since 2007, I have written consecratory (sanctifying) memorials in remembrance of the hundreds of innocent victims of the Meles Massacres. In my first memorial tribute in 2007,“Remember, the Ethiopian Martyrs of June and November, 2005 Forever!”, I reminded my readers that it was our moral duty “to bear witness for the dead and the living” in Ethiopia, to borrow a phrase from Elie Wiesel, the Holocaust survivor.
We must remember the victims of the Meles Massacres because, as Elie Wiesel said, we have “no right to deprive future generations of a past that belongs to our collective memory. To forget would be not only dangerous but offensive; to forget the dead would be akin to killing them a second time.”

I must confess that November is the cruelest month for me. If I could, I would skip straight from October to December. If I had the power, I would outlaw November. If there were no November, I would not have to remember. Mark Twain said, “If you tell the truth, you don't have to remember anything.” He was wrong. If you tell the truth you remember everything, especially the lies, the cries, the crimes and the massacres.

It is important for me to remember and to tell the truth about the crimes against humanity committed by the late Meles Zenawi and his criminal enterprise known as the Tigrean Peoples Liberation Front (TPLF). When Meles Zenawi ordered the massacre of hundreds of unarmed protesters in June and November 2005, he wanted to send a clear and unmistakable message to the Ethiopian people that he is so ruthless that he will kill, slash and burn on an industrial scale to keep himself and his TPLF in power forever. Meles Zenawi was an astute student of Reichsführer Heinrich Himmler: “The best political weapon is the weapon of terror. Cruelty commands respect. Men may hate us. But, we don't ask for their love; only for their fear.”