Thursday, December 10, 2015

Op-ed: The world must not forget the jailed journalists of Ethiopia

Today, on International Human Rights Day, the Ethiopian journalist Eskinder Nega, who was convicted on trumped up terrorism charges, will have spent more than four years in jail. Eskinder is just one of many Ethiopian journalists currently languishing behind bars, merely for doing their job. But unlike other journalists incarcerated on spurious terrorism charges such as the Al-Jazeera journalists freed from Egyptian prison earlier this year, the plight of jailed journalists in Ethiopia attracts little attention from the international community and the media.

Whilst the Aljazeera journalists, Peter Greste, Mohamed Fahmy and Baher Mohamed, became household names, few people outside of Ethiopia will have heard the names of Eskinder Nega, Temesghen Desalegn, Solomon Kebede, Yesuf Getachew, Woubshet Taye, Saleh Edris, and Tesfalidet Kidane. They have all fallen foul of Ethiopia’s 2009 Anti-Terrorism Proclamation, which criminalizes any reporting deemed to “encourage” or “provide moral support” to groups and causes which the government considers to be “terrorist”.

Tuesday, December 8, 2015

በገዛ አፈ-ሙዙ መቃብሩን የሚቆፍር የሽንፈትን ጽዋ ይጎነጫል!

ከሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ የአዲስ አበባ ከተማንና ዙሪያን ለማከለል ከወጣው የማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ፤ ገቢራዊነትና ሃሳቡን የተቃወሙ የኦሮሞ ተወላጆች እና የዕቅዱ ተቃዋሚዎች፣ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጆች እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እንዲሁም የየከተማዎቹ ነዋሪዎች ላይ የኃይል እርምጃ እየተወሰደ እንዳለ የአደባባይ ሀቅ ነው፡፡

ዜጎች እያሰሙት ያለውን ተቃውሞና የሃሳብ ልዩነት በኃይልና በጠብ-መንጃ ለመመለስ የተደረገውም አግባብነትና ኃላፊነት የጎደለው ጭፍን ተግባር እንደሆነ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት በጽኑ ያምናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ፣ መቶ-በመቶ ሁሉንም ተቋማትና መንግሥታዊ መዋቅሮች በጠቅላላ እንደልቡ የሚያዘውና ያሻውን የሚፈጽመው የኢህአዲግ መራሹ ኃይል፣ ልማትንና እድገትን በኃይልና በጉልበት እፈጽማለሁ እንዲሁም አስፈጽማለሁ ብሎ መነሳቱም መሠረታዊ የእብሪት ተግባር መሆኑም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አሳምሮ ያውቀዋል፡፡

በተለይም ደግሞ፣ ኢህአዲግ መራሹ መንግሥት በኢትዮጵያ ምድር ላይና በኢትዮጵያውያን ላይ የተከለው የጎሳ ፌዴራሊዝም ችግር ምን ያህል አስከፊ እንደሆነና ውጤቱም የዜጎችን ሞት፣ እስራት፣ ስደት፣ የንብረት ውድመትና የትምህርት መስተጓጎል ማስከተል እንደሆነ ታይቶበታል፡፡ በመሆኑም፣ የአዲስ አበባ ዙሪያ ነዋሪዎችም ሆኑ በሌሎች አካባቢዎች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉት ልማትም ሆነ እድገት በ“እኔ አውቅልሃለሁ” ባዩ የኢህአዲግ አንባገነናዊ ልማትና የጎሳ ፌዴራሊዝም ሳይሆን፣ በሕዝብ-ለሕዝብ-ከሕዝብ ፍላጎትና ስምምነት ላይ የተመሠረተን ልማትና እድገት ብቻ እንደሆነ መታወቅ አለበት፡፡

ከዚህ ዓላማና ግብ ውጪ የሚተገበር ማንኛውም የልማት ዕቅድና የከተማ ማካለልም ሁሉ የኢህአዲግ መራሹ መንግሥት አንባገነናዊ አስተዳደር ሁነኛ መገለጫ በመሆኑ አጥብቀን እንቃወመዋለን፡፡ በተከሰተው ብሔራዊ ቀውስና ችግር ዙሪያም በቀጥታ ለችግሩ ተጋላጭ ከሆኑት ዜጎች ጋር ሆነ ችግሩ በዋነኛነት ከሚያሳስባቸው የአዲስ አበባ ከተማና ዙሪያ ነዋሪዎች እንዲሁም ከተለያዩ ተቋማት ተማሪዎች ጋር ባስቸኳይ ውይይትና ንግግር እንዲደረግ እያሳሰብን፤ አንባገነኑ የኢህአዲግ መንግሥት እየተከተለው ያለውን የዜጎችን ጥያቄ በኃይልና በጉልበት ለማፈን ከሚያደርገው ፀረ-ዲሞክራሲያዊ ድርጊቱ እንዲቆጠብ እንጠይቃለን፡፡

በተመሳሳይ መልኩም፣ በጎንደር ከተማ በሚገኘው ማረሚያ ቤት ላይ ተከስቶ የነበረውን የእሳት ቃጠሎን ተከትሎ ኢህአዲግ መራሹ መንግሥት የተነሳውን የእሳት ቃጠሎ በማጥፋት፤ በሕግ ቁጥጥር ሥር የሚገኙትን ዜጎች ሕይወትና ደሕንነት ለመታደግ መሯሯጥ ሲገባው፣ ሕይወታቸውን ከቃጠሎው ለማዳንና ለሞከሩት ዜጎች የጥይት እሩምታ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ከዚህ መንግሥታዊ ተግባርና ቸልተኝነት ተነስተን እንደምንረዳው ከሆነ፣ አገዛዙ ለማንኛውም ዜጋና አገራዊ ጉዳይ የሚሰጠው ምላሽ ከጠብ-መንዣና ከጉልበት የማይዘል መሆኑን በግልጽ አስመስክሯል፡፡ ይህንንም መሰሉን ኢ-ሰብአዊና ኢ-መንግሥታዊ ተግባር የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት በቸልታ እንደማይመለከተው ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመግለጽ ይገደዳል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤትም መንግሥት የሚፈጽማቸውን ኃላፊነት የጎደላቸው ተገባራት እስኪያቆሙ ድረስ፣ አንባገነናዊው ሥርዓት የሚፈጸመው የሕገ-አራዊት ተግባራት እስካለቆሙ ድረስ፣ ሕጋዊና ሰላማዊ ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ – የዘመናችን ሙሴ!

ታዬ ብርሃኑ ከቨርጂንያ

በመጽሐፍ ቅዱስ ካሉ የቅዱሳን ታሪኮች ውስጥ የሙሴን ታሪክ አብዛኛው ኢትዮጲያዊ እንዳነበበው ስለማምን የሙሴን ታሪክ በዚህ ጽሁፍ ላይ መተረኩ አያስፈልገኝም። ሆኖም የዕብራውያን መልእክት ዕምነት ምን ማለት እንደሆነ የሚያስተምርበትን 11ኛው ምእራፍ ላይ ሌሎች ቅዱሳንን ጨምሮ የሙሴን ታላቅ እምነት ይጠቅሳል። ሙሴ በግብጽ ፈርዖን ቤተ መንግስት ውስጥ ጮማ እየቆረጠ፣ ጠጁን እየተጎነጨ፤ በወርቅና በገንዘብ ተከቦ መኖርን ትቶ በባርነት ከሚሰቃዩት ወገኖቹ ጋር መከራ መቀበልን እንደመረጠ ይተርካል። የንጉሱን ቁጣ ሳይፈራ በጊዜዋ ልዕለ ኃያል ሃገር የነበረችውን የግብፅን አገር ኑሮ ትቶ ከወገኖቹ ጋር የኤርትራን ባህር ተሻግሮ ወደ ተስፋይቱ ምድር ለመሄድ የወሰነው በእምነት ነበር። እምነት ማለት የማይታየውን እንደሚታይ አድርጎ በተስፋ መነጽር ማየት ነው።

ባለፉት አራት አስርት ዓመታት የሀገራቸን ኢትዮጵያ ጉዳይ በሁሉም ዘርፍ ከድጡ ወደ ማጡ እንደሆነ የዓይን ምስክር ነን። ሞት፣ ርሃብ፣ ስደት፣ ጎጠኝነትና የፍትህ እጦት የዘመናችን ታሪክ ነው። ወደድንም ጠላንም በየትኛውም ጎራ ብንቆምም፤ በፍትህ እጦት እየተገደሉ መንገድ ላይ ሬሳቸው ይጣል የነበሩት ወጣቶች፣ ተረሽነው በአንድ ጉድጓድ ውስጥ የተቀበሩት 60 ሚኔስትሮች፣ አገርን የባህር በር ማሳጣት፣ ድምጻቸው እንዲከበር ሊጠይቁ አደባባይ ሲወጡ በአጋዚ አልሞ ተኳሾች የተገደሉት የእነ ህጻን ነቢዩ ታሪክ የዚህ ትውልድ ታሪክ ነው። በአማራው፣ በኦጋዴንና በአኝዋኩ ላይ የተካሄደው የዘር ማጥፋት ዘመቻም የኛ ታሪክ ነው። ለአገር ለምድር እንደ ታቦት የሚከብዱና እድሜ ልካቸውን ቤተክርስቲያናቸውን እና አገራቸውን ያገለገሉት የኦርቶዶክስ ቤ/ክ አባቶች ስደትም የዚህ ትውልድ ታሪክ ነው።

ይሄ ትውልድ ይህንን ታሪክ ፈቅዶ አይደለም የሰራው። ጠብመንጃን መከታ ባረጉት በገዢው መንግስት ጫና ምክንያት ነው። ዝምም ብሎ አላየም። ይህንን ታሪክ ለመቀየር ከፕሮፌሰር አስራት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ሁሉም በሚችለው ሞክሯል። አብዛኛው የመታሰር፣ ሌላውም የስደትና የሞት ጽዋ ደርሶታል። እስከ አሁን ድረስ የተከፈለው መስዋዕትነት ዘረኛውን የወያኔ መንግስት ሊገረስሰው አልቻለም። ምናልባትም የትግሉ ስልት ሁሉን አቀፍ ወይም ሁሉንም የትግል ተልዕኮ ያላካተተ ስለ ነበር ይሆናል። አሁን ግን ከምስራቁ የአሜሪካ ክፍል የኢትዮጵያውያንን የትግል ተልእኮ በአንድ ላይ አካትቶ፣ የኤርትራን ባህር አሻግሮ፤ ወደ ተስፋይቱ ምድር በመውሰድ የዚህን ትውልድ ታሪክ የሚቀይር ልባምና አስተዋይ መሪ የዘመናችን ሙሴ አግኝተናል።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ በተመቻቸ ህይወት ይኖርባት ከነበረው ምድረ አሜሪካ፣ የደለበ ደሞዝ የሚያገኝበትን የፕሮፌሰርነትን ስራ ትቶ በወያኔ የአፓርታይድ መንግስት የሚሰቃዩት ወገኖቹ ነጻ ይወጡ ዘንድ መከራን መረጠ። ከሁሉም በላይ ሞትን ሳይፈራ እንደ ዓይን ብሌን የሚሳሳላቸው ቤተሰቦቹን ትቶ ምትክ የማይገኝለት ህይወቱን ለኢትዮጵያ ሀገሩ ሊሰዋ ወስኖ ወደ ትግል ሜዳ ሄደ። አስከፊ ታሪክ ያለው የዚህ ዘመን ትውልድ የሚያስደስትም ታሪክ አለው። የዘመናችን ሙሴ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የዚህ ትውልድ ታሪክ ነውና። ፕሮፌሰር ብርሃኑ እና የትግል አጋሮቹ ነጻነትን እምነት አርገው የድል ተስፋን ሰንቀው ዱር ቤቴ ብለዋል። እኛስ ምን እያደረግን ነው?

ይህችን አጭር ጽሁፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ ሰሞኑን የወያኔዎችን ደም ያንተከተከው የፕሮፌሰር ብርሃኑ ለአውሮፓ ፓርላማ የሰጠው የምስክርነት ቃል ነው። ሁላችን እንዳያነውና እንዳነበብነው በርቱዕ አንደበቱ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ኢትዮጵያው ውስጥ ያለውን ችግር ነቅሶ በማውጣት አቅርቦታል። በዚህ ትንታኔው ውስጥ የኔን ትኩረት የሳበውን ኃይለ ሃሳብ መጥቀስ እወዳለሁ። ፕሮፌስር ብርሃኑ ወያኔ በቤተ እምነት ውስጥ ጣልቃ እንደሚገባ አስረድቶ በኦርቶዶክስ ቤ/ክ አባቶች ላይ እስከ መሰደድ ያደረሰውን የወያኔ ጥፋት በአለም አደባባይ ይፋ አርጎታል። በተቃዋሚ የትግል ጎራ ያሉ መሪዎች ስለተሰደደችው ቤ/ክ እና አባቶች ከዚህ በፊት ሲያነሱት አለመስማቴ ሁሌም ያሳዝነኝ ነበር። የተሰደደችው ቤ/ክ ወይም ህጋዊ ሲኖዶስ ሰብዓዊ መብት፣ የህግ የበላይነት እና ፍትህ በምድረ ኢትዮጵያ እንዲከበር ከአውደ ምህረትም እሰክ ዓለም በአደባባይ ድምጻቸውን እያሰሙ የትግሉ አካል ተደርገው አለመወሰዳቸው ይገርመኝ ነበር። ሽማግሌ በሀገሪቷ ስለጠፋ እንጂ ከልጅነት እስከ ሽምግልና ቤተክርስቲያንን ያገለገሉ አባቶች በባእድ አገር ሲሰደዱ እንዴት ዝም ይባላል? ዳሩ ሽምግልና የእንጨት ሽበት የሆነበት ዘመን ላይ ደርሰናል። እነዚህ አባቶች ስደታቸውን ባርኮ በስደት ያለውን ህዝብ ቢሰበስቡም አያሌ አብያተ ክርስቲያናትን ቢመሰርቱም በየአውሮፕላን ጣቢያ በሽምግልና እድሜአቸው ሻንጣ እየተሸከሙ ህዝባቸውን ለማገልገል ቀና ደፋ ሲሉ ማየት ያቆስላል። የዮሴፍን ስደት የባረከ አምላክ የእነርሱንም ባርኳል። ፕሮፌስር ብርሃኑ ያገኘውን በረከት ቀድሞ የቅንጅት አሁን ደግሞ ህብረ ብሔር ፓርቲ የሆኑት አንድነትና ሰማያዊ ፓርቲ መሪዎች አላገኙትም። ወደፊት የወያኔ መንግስት በሌሎች ቤተ እምነቶች ላይ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት ሲያወግዙ ወያኔ በኦርቶዶክስ ቤ/ክ ላይ የፈጸመውን የቀኖና መደፍጠጥ፣ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የተሾመን መንበር ለስደት ማብቃቱን ማውገዝ ይገባቸዋል። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ለሌሎች ታጋዮች ተምሳሌት ሆኗል።

Saturday, November 28, 2015

ወያኔ ሰራሽ የርስበርስ ግጭት ደግሶችን እናምክን!!!

የወያኔ ስርዓት ኢትዮጵያ የተዋቀረችው በህዝብ ታሪካዊ አብሮነትና ተዛምዶ ላይ ሳይሆን የብሔር ብሔረሰብ ልዩነቶችን በማጥበቅና ልዩነትንም የርስበርስ ጥርጣሬና ግጭት ምንጭ እንዲሆን በማለም ነው። ልዩነት የግጭትና የጠብ ምንጭ እንዲሆን ተደርጎ ነው የተዋቀረውና ብፖለቲካ ደረጃ የተገፋው። አንዱ ብሔረሰብ ሌላው ብሔረሰብ ክልል ውስጥ ሲሆን ባዕድነት እንዲሰማውና እንዲሰጋ አንዱ አንዱን በጥርጣሬ እንዲመለከተው ተደርጎ ነው ሀያ አራት አመት ሙሉ የተገፋውና እየተገፋ ያለው።

ይህም ሆኖ በዘመነ ወያኔ በየቦታው የተከሰቱ የብሔር ሌብሔርሰብ ግጭቶች በሙሉ የተቀሰቀሱት በራሱ በመንግስት ባለስልጣኖች እንጂ መቼም ህዝብ ለሕዝብ ሆኖ አያውቅም። በተለያዩ የደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች አማሮችን ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ለማባረር የተወሰዱት ርምጃዎች ራሳቸው ሰለባዎቹ እንደሚናገሩት ለስቃይ የዳረጋቸው ነዋሪው ሕዝብ ሳይሆን ባለስልጣናቱ መሆናቸውን በግልጽ ሲናገሩ ሰምተናል።

በቤኒሻጉልና ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሰሞኑን ይፋ መሆኑ የተነገረው በአስቃቂ ሁኔታ ተገድለው ተቀብረው የተገኙ አማሮች አስከሬን መገኘቱ ታውቋል። ይህም ወያኔ ባስለጠናቸውና ባዘዛቸው ካድሬዎችና ባለስልጣኖች የተከወነ እንጂ በሕዝብ ተነሳሽነት የተፈጸመ አለመሆኑ የታወቀ ነው። ቀደም ሲል በመንግስት ደረጃ የተቀነባበረ አማሮችን የማፈናቀል ዘመቻ ተከታይ ስራ መሆኑን ለማወቅ ብዙ አዳጋች አይደለም። በወገኖቻችን ላይ በሚዘገንን መንገድ የተፈጸመው ግፍ ዘልቆ ይሰማናል:: ሊሰማንም የገባል። ቁጭታችንና ሀዘናችን ግን ወያኔ ወደሚፈልገው የሕዝብ ለሕዝብ ግጭት ምክንያት እንዳይሆን ከፍተኛ ትዕግስትና ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል።
ሰሞኑን በታሪክ ሊዘገብ ከሚችል ልዩነት ውጭ ባኗኗር በባህልና ቋንቋ የማይለያዩትን የሰሜን ኢትዮጵያ ህዝቦች ቅማንትና አማራ በሚል ለማጋጨት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ይህ ሰይጣናዊ አካሔድ በወያኔ የፖለቲካ ተንኮል እየተመራ እንዳለ የሚያሳዩ ብዙ መረጃዎች አሉ። የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ሁሉም ካላንዳች መድሎና ልዩነት ሀገሪቱ ላይ መብታቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ ሁሉም በየበኩላቸው የሚያደርጉትን ጥረትና ትግል እንደግፋለን። በህዝባችን መካከል ያሉት ግንኙነቶች ሊሆን የሚችለው እንዱ አንዱን የማገዝ እንጂ ርስበርስ የመጋጨትም ሆነ የመናቆር አይደለም።

ኢትዮጵያውያን ብሄርና ዘር ሳንለይ ይህንን የወያኔ ተንኮል ችግሩ ወደባሰ ደረጃ ሳይሄድ መቋቋምና ማክሸፍ ይጠበቅብናል። ይህ ታሪክነታችንና ታላቅ ሕዝብነታችንን የማይመጥን አሳፋሪ የወያኔ ፖለቲካ እንደሀገር እንዳያጠፋን ሁላችንም በንቃትና በቁርጠኝነት መቋቋም ይኖርብናል።

Wednesday, November 25, 2015

Famine in Ethiopia: Due to bad weather or policy Failure?

By: Asnake Demena

Twenty four years ago Meles Zenawi, the late Prime Minister of EPRDF was asked about his vision for Ethiopia and its people when he assumed power as head of the state after seventeen years of civil war. Meles declared that if his government remains in power, in ten years every Ethiopians will have at least three meals a day. He also anticipated that if his government remains in power from then onwards for twenty years, Ethiopians not only have three meals a day but also will have the luxury of choosing what to eat. More recently in 2011, the same Meles Zenawi said that “We have devised a plan which will enable us to produce surplus and be able to feed ourselves by 2015 without the need for food aid.”

A young boy waiting in front of his tukul for his mother as she arrives with a body of his 4-year old dead sister who died of malnutrition in Shashemene, Ethiopia: Source: NBC: & .Creeping famine-is-back-to-Ethiopia

Here we are now, after twenty four years of power monopoly by the EPRDF regime and five years later after the implementation of the so-called Growth and Transformation Plan, more than 11.3 million Ethiopians have nothing to eat let alone to choose what to eat. Arsi, Hararghe, Afar, Borena and Somali are the hardest hit areas of the latest famine in the country. Children are dying in the hands of their parents and suffering from famine related diseases. Nevertheless, the EPRDF regime has been blaming on bad weather particularly the El Niño for the recent brutal famine.

Even if the El Niño is partly attributed for drought in general, the famine we are witnessing toady, in Ethiopia is not the result of seasonal crop failure due to bad weather or natural calamity as the EPRDF regime would like us to believe. As a matter of fact, drought, climate variability and other natural calamities occur not only in Ethiopia, but also in any part of the world. However, drought does not necessarily result in famine. This implies that droughts are a normal component of Ethiopian life making famines inevitable unless the proper preventive measures are adopted. Hence, in examining the current famine in Ethiopia, I will stress the structural links between food shortage and the lack of good governance in general and the failure of policies and strategies in particular.

Fifty years ago, famine was simply understood as the result of food shortage due to seasonal crop failure or natural disasters. At that time, it was not difficult to understand the reasons for famine when poor technology and static economic systems hampered human beings from getting access to food, especially in the face of regional natural disasters. But today, natural forces and other climatic conditions cannot be responsible for famine causation as was the dominant mode of thinking five decades ago. So that it is logical to ask why famine is persist in Ethiopia in the ear of global surplus, high-technology early warning systems and “vibrant economic growth” in the country. Answering this question requires looking beyond technical factors, towards political explanations. This means that the real causes of famine in Ethiopia deeply rooted in the country’s history of civil war and repression. Therefore, analysis of the past and present famines in Ethiopia should focus on root causes of the problem, instead of seasonal symptoms.

“ረሃቡና ኢህአዴጋዊ እውነታዎች!” (ኤርሚያስ ለገሰ)

ህወሃት መራሹ መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ ረሃብ በተከሰተ ቁጥር የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ “የአየር ንብረት መዛባት” በሚል ውጫዊ ምክንያት ማላከኩ የተለመደ ሆኗል። ለአብነት ያህል የዛሬ ዘጠኝ አመት በኢትዮጵያ ረሃብ በተነሳ ወቅት “የሰሞኑ የረሃብ ፖለቲካ” በሚል ረዕስ የውስጥ ድርጀት ሰነድ ተዘጋጅቶ ነበር ደራሲው ጓድ መለስ ዜናዊ ነበሩ። በማስከተልም የፓርቲው ከፍተኛ ካድሬዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት ውይይት እንዲያደርጉበት ተደረገ። በዚህ ሰነድ ገፅ 6 ላይ የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ እንደሚከተለው ይገልጻል።

“ረሃቡ ከምን እንደሚመነጭ በትክክል ማስቀመጥ መፍትሄውን ለማስቀመጥ ወሳኝ ነው። የረሃቡ ቀጥተኛ ምንጭ ከአየር ንብረት መዛባት ጋር ተያይዞ የተከሰተው ድርቅ ነው። የአየር ንብረቱ መዛባትና ድርቁ እኛ ያልፈጠርነው ልናስተካክለው የማንችለው ነባራዊ ሃቅ ነው። በዚህ ነባራዊ ሁኔታ ማዕቀፍ ድርቁን ተቋቁመን ረሃቡን ለማስወገድ ያስቀመጥነው ስትራቴጂ ተዓምር ሰሪነቱ በንድፈ ሃሳብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በተግባር ተረጋግጧል። የረሃቡ ዋነና ምንጭም የአየር ንብረት መዛባትና ድርቅ ነባራዊ ሁኔታን መቋቋም ረሃብን ለማጥፋት የቀየስነው ስትራቴጂ በሚፈለገው ፍጥነት በሁሉም አካባቢዎችን ስላልተፈጸመ ነው” ይላል።

እስኪ ይታያችሁ! ከዛሬ ዘጠኝ አመት በፊት (በ 1999 ዓም) የድርቁ መንስዔ የአየር ንብረት መዛባት እንደሆነ ተነገረን። ከዚያ በፊትም ምንጩ ተመሳሳይ ነበር። አሁንማ ልማድ ሆኖብን በኢትዮጵያ ምድር በየሁለት አመቱ ረሃብ የሚከሰት ሲሆን ምንጩ የአየር ንብረት ለውጥ ሆኗል። በነገራችን ላይ በሃገራችን ላይ በተጠቀሰው አመት ድርቁ ወደረሃብ በመቀየሩ ምክንያት በርካታ ህጻናት እና እናቶች ሞተዋል። በአራቱም ማዕዘናት ዜጎች ቀዬአቸውን ለቀው ተሰደዋል። የተፈጠረው አስደንጋጭ ሁኔታ ከህሊና የሚጠፋ አልነበረም።

በዛን ወቅት “በምጥቁ መሪ!” አብዮታዊ አመራር ሰጪነት የተሰራው ወንጀል ዘመን ተሻጋሪና ነገ ከነገ ወዲያ ተጠያቂነትን የሚያመጣ ነው።

እንዲህ ነበር የሆነው፥

በኢትዮጵያ አዲስ ሚሊኒየም ዋዜማ የተከሰተው ድርቅ ወደረሃብ መሸገገሩን የሚያሳይ ረፖርቶች ከመላው ሃገሪቱ መሰማት ጀመሩ። የኢህአዴግ የፕሮፓጋንዳ ማሽን ከዛ አመት በፊት በነበሩት አራት አመታት ኢኮኖሚያችን በሁለት አህዝ አድጓል፥ ሚሊየነር አርሶ አደሮች መፍጠር ችለናል በሚል ቅኝት የሚመራ ስለነበረ ይህን መርዶ ለመቀበል አስቸጋሪ ሆነ። ረሃብን አስወግደናል ብለን ባወጅን ማግስት በረሃብ ተጠቅተን መገኘት በእርግጥም አሳፋሪ ነበር። የአመራርና የማስፈፀም አቅማችን፣ ምርጥ ልምዶች የማስፋት ስትራቴጂያችን ለአለም ተምሳሌት ሆኗል ባልን ጥቂት ቀናት ህዝቡ ረሃቡን መቋቋም አቅቶት እየተሰደደ መሆኑ መመልከት ፕሮፓጋንዳችን “ቢወቅጡት እምቦጭ” እንደሆነ የሚያመላክት ሆነ።

እንደ ተፈራው በዕልፍ አመቱ ዋዜማ የሰው ህይወት በየቦታው መውደቅ ጀመረ፥ ረሃቡን መቋቋም የማንችልበት ሁኔታ ግልፅ ሆኖ ወጣ። የመጀመሪያ ሰሞን እውነታውን አውገርግሮ ከማቅረብ ይልቅ ትክክለኛው መረጃ ተሰብስቦ ወደኢህእዴግ ቢሮ እንዲመጣ ልዩ ውሳኔ ተላለፈ። ለማመን በሚቸግር ሁኔታ የረሃቡ ዋነኛ ሰለባ ከሆኑት አካባቢዎች የሚመጣው መረጃ እጅግ አስፈሪና አስደንጋጭ ሆነ። ከሶማሊያ ጫፍ እስከ አብርሃ አጽብሃ የሚባል የትግራይ ቀበሌ ድረስ ህዝቡ የሚላስ የሚቀመስ ማጣቱ ታወቀ። የከፋ ረሃብ ያጋጠማቸው አካባቢዎች ልጆቻቸውን እየቀበሩ ቀዬአቸውን እየለቀቁ መሰደድ መጀመራቸው እሙን ሆነ።

በሚሊኒየሙ ዋዜማ የችጋሩ ዋነኛ ተጠቂ ከሆኑት አካባቢዎች የመጀመሪያው የሱማሌ ክልል ነበር። የሱማሌ ክልል ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ ጀምሮ ለስርዓቱ ተገዢ እንዳልሆነ በገሃድ የሚታወቅ እውነታ ነው። በዛ ላይ አካባቢው በጦርነት የሚታመስ መሆኑ የረሃብ አደጋው በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አደረገው። በወቅቱ የተፈጠረው ረሃብ በ10ሺዎች የሚጠጉ የቀንድ እና የጋማ ከብቶች መሞታቸው ታወቀ። ከ80 -100 የሚሆኑ ህጻናት በረሃቡ ምክንያት ህይወታቸው እንዳለፈ የሚያሳይ መረጃ የስም ዝርዝር ረፖርት ቀረበ።

ይህንን የሱማሊያ የረሃብ ሁኔታ የተቀበለው ጓድ በረከት ከ “ባለራዕዩ መሪ!” ጋር በመነጋገር አንድ ጠንካራ ትዕዛዝ ሰጠ። ጥብቁ ትዕዛዝ “ማንኛውም የሃገር ውስጥም ሆነ የውጭ ጋዜጠኛ፣ በመንግስት ክትትል የማይደረግበት በጎ አድርጎት ድርጀት (NGO) ወደሶማሊያ ዝር እንዳይል!” የሚል ነበር። እነሆ ላለፉት 10 አመታት የትኛውም የነጻ ፕሬስ ሆነ የውጭ ጋዜጠኛ ወደሶማሊያ ክልል ልሂድ ብሎ ጥያቄ ቢያቀርብ ኣይፈቀድለትም። ከጓድ በረከት ጋር የቅርብ ወዳጅነት የመሰረቱትም ቢሆን ፍቃድ አያገኙም። የተለያዩ ምክንያቶች እየተሰጣቸው ጥያቄዎች እንዲጥሉ ይደረጋል። በዚህ ምክንያት በሱማሊያ በረሃቡ የሞቱት ህጻናት ከሪፖርቱ ውጪ እንዲሆኑ ተደረገ። እስከ 100 የሚደርሱት ህውየታቸው ያለፉት ህጻናት ማህደር በኢህአዴግ ቢሮ ተቆለፈበት።

Sunday, November 22, 2015

CPJ Awards Zone9 Bloggers of Ethiopia: International Press Freedom Award

In April 2014, Ethiopian authorities arrested six bloggers affiliated with the Zone 9 collective. The bloggers–Abel Wabella, Atnaf Berhane, Mahlet Fantahun, Natnail Feleke, Zelalem Kibret, and Befekadu Hailu–were charged with terrorism.

The Zone 9 blogging collective was formed in May 2012 in response to the evisceration of the independent press and the narrowing of space for free expression. The name, “Zone 9,” is derived from the zones in Kality Prison, the main jail where Ethiopia’s political prisoners, including several journalists, are held. While Kality Prison is organized into eight different zones, the bloggers refer to the entire country as “Zone 9” because of Ethiopia’s lack of democratic freedoms, one of the bloggers told CPJ.

The collective is made up of nine bloggers–the six named above, and Soleyana S Gebremichael, Endalk Chala, and Jomanex Kasaye, all of whom are in exile. Soleyana has been charged in absentia.
In July 2015, weeks before U.S. President Barack Obama visited the country, Ethiopian authorities released Mahlet and Zelalem.

The Zone 9 bloggers were arrested along with three other journalists–editor Asmamaw Hailegeorgis and freelancers Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye, who were later released. The initial charges against the group included working with international human rights organizations and taking part in email encryption and digital security training. The group was subsequently charged with terrorism.
Since 2009, when Ethiopia’s anti-terror law was implemented, the government has used the sweeping legislation to imprison more than a dozen critical journalists, according to CPJ research. In 2012, blogger Eskinder Nega was sentenced to 18 years in prison and Woubshet Taye to 14 years, both on terrorism charges. CPJ’s 2014 prison census found that Ethiopia was the fourth worst jailer of journalists in the world, with at least 17 journalists behind bars. Ethiopia also ranked fourth on CPJ’s 2015 list of the 10 Most Censored Countries.