Friday, July 19, 2013

አሸባሪዉ ኢህአዴግና የፀረሽብር ህጉ መወገድ አለባቸዉ

ከተስፋዬ ተካልኝ

ኢትዮጵያንና ህዝቧን የአብሮነትን መሠረት ለመሸርሸርና ብሎም ለማጥፋት ሌተ ቀን የማይተኛዉ የህወሀት ኢህአዴግ አሸባሪ መራሹ መንግስት በህዝብ ጫንቃ ላይ ተቀምጦ ዜጎችን ማሰቃየት ከጀመረእነሆ ፪፪ አመት ተቆጥሮዋል።ነገር ግን የ፪፪ አመት ቆይታዉ ህዠብን ከማሸበር፣ ከመግደል፣ከማሰር ከማሰደድ፣ከመግረፍና ከማፈናቀል አልፎ በተመቸዉና የጥፋት ምርቃናዉ በመጣለት ቁጥር በዘረኞች መሪዎቹአማካይነት በፈለገዉ ሰዐት ከራሱ ህግና ስርአትዉጪ ከእንቅልፋ እንደሚነቃና የሚያደርገዉን እንደማያቅ ህፃን ልጅ የተለያዮ ህጎችን በማዉጣት ጭምር ህዝባችንን ከህዝባችን እንዲሁም ሀገሪቱዋን ባለቤትየሚያሳጣ አስነዋሪ ህጎች በማርቀቅና ድራማ በመስራት ማፍያ ስርአት መሆኑ ይታወቃል።

ከእነዚህ የህወሀት ኢህአዴግ አስነዋሪ ህጎች አንዱ እኤአ ፪፻፱ በሙዋቹ ቀንደኛ ማፍያ መሪያቸዉ መለስ ዜናዊ መሪነትና በሌሎች አጭበርባሪ ሆዳም የሀገር ፍቅር በሌላቸዉ ተከታዮች አማካይነት የፀረ ሽብርህግ አዉጥቶ ፭፬፩ እጅ በሚያነሱለት የፓርላማ አሻንጉሊቶቹ ድጋፍ ማፀደቁ የሚታወቅ ነዉ።

ይህ ህግ አሁንም በባለ ጥፋቱ መሪያቸዉ የሙት መንፈስ ራእይ ስምና በተተካዉ አሻንጉሊት መሪ ሀይለማርያም ደሳለኝ ህጉ እንደቀጠለ ሲሆን ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚያሸብረ ወያኔ ሆኖ ሳለ ነገር ግን በመሣርያየበላይነት በሀገሪቷ ዉስጥ ከወያኔ የተለየ ሀሳብ ያላቸዉ በህጉ የስቃይ ሰለባ እየሆኑ ነዉ ዛሬም።



ለዚህም ማስረጃ ሰሞኑን ወገናችን ተስፋዬ ተካልኝ በአንድነት ፓርቲ ጽህፈት ቤት ዉስጥ የሚሊዮኖች ድምፅ በሚል በሰጠዉ ቃለ ምልልስ ፪፫ ወራት፣ ለ፫ ወር ማዕከላዊ ለ፩፱ ወር ደግሞ በዝዋይ እስርቤት በወያኔ ኢሰብአዊና አረመኔያዊ የጭካኔ በደል ፍዳዉን አብልተዉ የቁም ሞት ገለዉ ከለቀቁት በዉኃላ በዚህ የፀረ ሽብር ህግ ምክንያት ህይወቱ ጉዳና ላይ ወድቋል ንፁሀን ዜጎች ከሱ ጭምር የህጉ ሠለባመሆናቸዉን ከአንደበቱ ሰምተናል።

ስለዚህ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ዛሬ ነገ ሳይል እንደ ተስፋዬ ተካልኝ እይነት ሚሊዮኖችን ከተለያዮ ግልፅና ስዉር የማሰቃያ ቦታዎች ሊታደጋቸዉ እንዲሁም አሸባሪዉ ህወሀት ኢህአዴግንና ፀረሽብር ህጉን ከኢትዮጵያ ማስወገድ አለበት።

እኔ ተስፋዬ ተካልኝ ነኝ እናንተስ?

በህወኃት ወያኔ ሞት!

የኢትዮጵያ ነፃነት!

ምንጭ፡ Millions of voices for freedom - UDJ

No comments:

Post a Comment