Tuesday, July 30, 2013

የኃይለማርያም ደሣለኝ አንድ ዓመት

የመለስ ዜናዊን ዕረፍት ተከትሎ ኃይለማርያም ደሣለኝ በቦታው ከተተኩ እነሆ አንድ ዓመት ሊደፍኑ ነው።

በቅርብ ጊዜያት የተቃውሞ ሰልፎች እንዲሁም የካቢኔ አባላት ብወዛ የተካሄደ ቢሆንም በምሥራቅ አፍሪካዊቱ ሀገር ብዙም የተለወጠ ነገር ያለ አይመስልም ብላለች የቪኦኤዋ ማርቴ ፋን ደር ቮልፍ ከአዲስ አበባ በላከችው ዘገባ።

ባለፈው ዓመት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን መታመም ተከትሎ ስለነበሩበት ሁኔታ ለሣምንታት በግምትና በጭምጭምታ ሲወራ ሰንብቶ ነኀሴ አሥራ አምስት ጠዋት የዕረፍታች መርዶ ተነገረ።
የኒህን የረጅም ጊዜ መሪ ዕረፍት ተከትሎ ነው ምክትላቸው የነበሩት ኃይለማርያም ደሣለኝ በህዝቧ ብዛት ከአፍሪካ ሁለተኛ የሆነቸውን ሀገር መሪነት ለመያዝ የተተኩት።

እርግጥ በቅርብ ወራት በሀገሪቱ ከዚህ ቀደም ያልተለመዱ በርካታ የመንግሥት ተቃዋሚ ሰልፎች ተካሂደዋል። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርም አብዛኞቹን የካቢኔ አባላት ቀይረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ እንደሚሉት ግን እነዚህ ክስተቶች በመንግሥቱ ውስጥ የአንዳችም መሠረታዊ ለውጥ አካል አይደሉም።

“ባሁኑ ወቅት ኃይለማርያም እያደረጉ ያሉት በገዥው ፓርቲ የፀደቁ ፖሊሲዎችን ተግባራዊ ማድረግ ነው። የአቅጣጫ እና የመሠረታዊ ፖሊሲ ለውጥ ይኖራል ብለው የሚጠብቁ ካሉ በርግጥ ያዝናሉ፡፡ ምክንያቱም እንዲህ ያለውን ለውጥ ለማካሄድ ፍላጎቱም፣ ዝንባሌውም የለም” ብለዋል አቶ ጌታቸው፡፡

Monday, July 29, 2013

‹ኦሮሞ ፈርስት› ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ህመም!

(በመልካምሰው  አባተ ተፃፈ)

ሰሞኑን አንድ ንፁህ ኦሮሞ ነኝ የሚል ወንድማችን ‹ኦሮሞ ፈርስት› የሚል ጣጣ አምጥቶ ጥቂቶቻችን አኩርቶ ብዙዎቻችን ጣጣ ውስጥ አስገብቶ ከፊሎቻችን አበሳጭቶ እሱ በህይወት አለ፡፡ ነገሩ ካበሳጫቸው ሰዎች መካከል እኔና ሃኪም ገዝሙ በዋናነት እንጠቀሳለን፡፡ ምክንያቱም እኔና ሃኪም ገዝሙ የብሄር ክልሶች ነን፡፡ የቀበሌ መታወቂያ የሌለን ለዚህ ነው፤ ብሔር ከሚለው ጎን የሚፃፍ ብሄር ጠፍቶ፡፡ ….ጋሽ ገዝሙስ የቀበሌ መታወቂያ ባይኖራቸው ክሊኒክ አላቸው፤ እኔ ነኝ እንጂ ክሊንክ የለኝ፤ መታወቂያ የለኝ፤ ብሔር የለኝ፤ ብሄረሰብ የለኝ፤ ለነገሩ እኔ ራሴ አለሁ እንዴ? ያያችሁኝ ካላችሁ ንገሩኝ እስቲ….

መቼም ዘረ - ንፁህ ነን የሚሉትስ ኦሮሞ ፈርስት፤ አማራ ፈርስት፤ ጉራጌ ፈርስት፤ ትግሬ ፈርስት…… ምናምን ፈርስት ብለው ጎረሩብን፤ ፎከሩብን፤ አቅራሩብን፤…..እኔና ሃኪም ገዝሙ ማን ፈርስት እንበል? በውነቱ ህገመንግስቱ ፈርስት የምንለው ነገር ይሰጠን ዘንድ በንዴት እንጠይቃለን፤ ህገ መንግስቱ ብዙ ፈርስቶች ስላሉት እኔና ጋሽ ገዝሙን ማስደሰት አያቅተውም መቼም፡፡ በዚህ አጋጣሚ የህገመንግስቱን ፈርስቶች ጠቀስ ጠቀስ ባደርጋቸው ደስ ይለኝ ነበር ደሞ፤ የምጠቅሳቸው በአይኔ ነው ታዲያ፤ ይሞታል እንዴ ታዲያ?!....

 ….የጋሽ ገዝሙ ክሊኒክ ሰሞኑን ስራ በዝቶበታል፤ ገበያው ደርቷል፤ ይሄን ጊዜ ነበር ጋሽ ገዝሙን ማዬት፤ የማይስቅ የአካል ክፍል የላቸውም፡፡ ገዳም ሰፈር በተባለው ምርጥ ሰፈር ከኔ ቪላ ቤት ጥቂት ወረድ ብሎ ይገኛል የሃኪም ገዝሙ ክሊኒክ፡፡ (መቼም ያገሬ ሰው ደግ ነው የኔ ቪላ ቤት ስል አምኖኝ ይሆናል፡፡ እንኳንም አመነኝ፡፡ ፅድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም፤ ካለማመን ማመን ሳይሻል አይቀርም፡፡…….)

የጋሽ ገዝሙ ክሊኒክ ሰሞኑን ለምን ገበያው ደራለት ብለው አንዳንድ ወገኖች ፌስቡክ አድርገውልኛል፡፡ እኔም የጥያቄውን ተገቢነት በመረዳት ጉዳዩን አጣርቻለሁ፡፡….ሃኪም ገዝሙ በገበያ ጥናታቸው በደረሱበት መሰረት እና ሾላ በድፍን በተባለው የንግግር ዘዴ እንደገለጹልኝ ከሆነ የክሊኒካቸው ገበያ የመድራቱ ምስጢር ‹ኦሮሞ ፈርስት› የተባለ እንደ ኤች አይቪ ቫይረስ መልኩን የሚለውጥ አዲስ ቫይረስ በመከሰቱ ነው፡፡…..ይህን ቫይረስ ከኤች. አይ. ቪ. ቫይረስ ጋር የሚያመሳስለው ሌላ ነገርም አለ፤ እሱም ምንድን ነው ቫይረሱ ከወደ አሜሪካ መምጣቱ ነው፤ እናት አገር ተማሩልኝ ተመራመሩልኝ ብላ የላከቻቸው የኛ ልጆች ናቸው አሉ ፖለቲካ ሳይንስ ላቦራቶሪ ውስጥ ሲመራመሩ ቫይረሱን ድንገት የፈጠሩት፡፡ ይህን ጉዳይ የሰሙ አንድ የአርሲ ክፍለሃገር ባላባት እንዲህ ብለው ፈጣሪን አመሰገኑ አሉ፤
እኔን ያንተ ምንዱባን
እንኳንም አረከኝ መሃን
ቆፍሬ ዘር የማልተክል
ትል ወልጄ ከእበት ጋር ከምተካከል!

የአማራ ብሔር ተወላጆች ዳግም ከጉራፈርዳ እየተፈናቀሉ ናቸው ተባለ


-    ሰማያዊ ፓርቲና መኢአድ ክስ እንመሠርታለን አሉ 


በደቡብ ክልል በቤንቺ ማጂ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ እየሩሳሌም ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ውስጥ ነዋሪ የሆኑ የአማራ ብሔር ተወላጆች፣ ዳግም እየተፈናቀሉ መሆኑን ሰማያዊ ፓርቲና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አስታወቁ፡፡

ሁለቱ ፓርቲዎች ሐምሌ 18 ቀን 2005 ዓ.ም. በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት መንግሥት ቀደም ብሎ በጉራፈርዳ ወረዳ፣ በሸፒ ቀበሌና በተለያዩ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ነዋሪ የነበሩት የአማራና የኦሮሞ ተወላጆች መፈናቀላቸውን ተከትሎ፣ መንግሥት በአፈናቃዮቹ ላይ ዕርምጃ እንደሚወስድ ቢያሳውቅም፣ ዜጐቹ ግን እስካሁን እየተፈናቀሉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ተወካይ አቶ ተስፋዬ ታሪኩ፣ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ቀርበው ለዓለም ሕዝብ ጭምር በሰጡት ማብራሪያ፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ እንዲፈናቀሉ የተደረጉ የአማራና የኦሮሞ (የዘር ማጥራት ወንጀል እንዳይመስል) ተወላጆችን ያፈናቀሉ ኪራይ ሰብሳቢዎች ላይ፣ መንግሥት ዕርምጃ እንደሚወስድና ተፈናቃዮችም ወደ ቀያቸው በአስቸኳይ እንደሚመለሱ የተናገሩ ቢሆንም ተግባራዊ አልሆነም፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡

ቀደም ብሎ ከ21 ሺሕ በላይ የአማራ ተወላጆች ከተፈናቀሉበት፣ ከቤንቺ ማጂ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ እየሩሳሌም ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ከሐምሌ 15 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ የአማራ ብሔር ተወላጆች እየተፈናቀሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌታሁን በበኩላቸው፣ ‹‹መንግሥት በአሁኑ ጊዜ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አጀንዳ ስላጡ ትኩረታቸውን ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ማድረጋቸውን ይናገራል፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ በድህነት በዓለም ካሉ አገሮች ከመጨረሻዎቹ ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃ ላይ በሆነችበት ሁኔታ በመንግሥት ላይ አጀንዳ ለማንሳትና ለመንቀፍ ከበቂ በላይ ምክንያት አለ፤›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡

‹‹መንግሥት በመገናኛ ብዙኀን ቀርቦ ለዓለም ጭምር ያሰማውን ዲስኩር ተግባራዊ ቢያደርገውና ተፈናቃይ ዜጐች ወደቤታቸው ቢመለሱ፣ መሬታቸው ቢመለስላቸው፣ ለጠፋባቸው ንብረት ካሳ ቢከፈላቸውና በድጋሚ ሌላ የማፈናቀል ወንጀል እንዳይደረስባቸው ጥበቃ ቢያደርግላቸው እኛ ሌላ ምን እንፈልጋለን?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ፓርቲዎቹ ክልሉ ድረስ በመጓዝና ተፈናቃዮቹን ቃለ መጠይቅ በማድረግ፣ በክልሉ ተወላጆቹ ከተፈናቀሉባቸው ቀበሌዎች፣ የአማራ ተወላጆች በሦስት ቀናት ለቀው እንዲወጡ የተለጠፈውን ስም ዝርዝራቸውን ጭምር በማስረጃነት በመሰብሰብ፣ ሙሉ ማስረጃው ተጨምሮ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሰኔ 5 ቀን 2005 ዓ.ም. ደብዳቤ መጻፉን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያዊው ዳያስፖራ

በታዬ ዘሐዋሳ

ከዞን ዘጠኝ ጦማር የተወሰደ

በሃገራችን በነበረው ፖለቲካዊ ቀውስ ወይም አመለካከት የተነሳበርካታ ኢትዮጵያውያን በስደት እንደሚኖሩ ይታወቃል:: የሚኖሩበትም ሃገር ብዛትና ስብጥር በራሱ ከሌሎች ሃገራት ዜጎች የተለየን ያደርገናል ብዬአስባለሁ:: እንደ ሃገራቱ ስብጥር እና ብዛት ሁሉ የሃበሻ አመለካከትም እጅግብዙ ነው:: ይህ ብዛት ያለው ስብጥር ደግሞ ወጥ የሆነ አመለካከት እንዳይኖረን አድርጓል::ክፍፍላችንም እንደዚያውብዙ ነው:: ፍረጃችንም ጭምር::የዛኑ ያክልም ኢትዮጵያዊ ዳያስፖራለመፈራረጅ ወይምለመሞጋገስ ከንፋስየፈጠነ ነው:: ፍረጃው ከተለያዩ አካላት ይጀመር እንጂ አብዛኛዎቹን ፍረጃዎች በማዳነቅና በማሟሟቅ ረገድ የሁሉም ድርሻ አለበት:: አንዲት የፌስቡክ ወዳጅ ስለፍረጃዎች ብዛትእና ጥልቀት ትዝብቷን አካፍላን ነበር:: ከነዚህ የርስ በርስ ፍረጃዎች ውስጥ የሚከተሉት በስፋትየምናስተውላቸው ናቸው:-

 .ኢቲቪ ወይም ኢሳት
 .ኢህአዴግ ወይም ተቃዋሚ
. አይጋፎረም ወይም ኢትዮጲያን ሪቪው
. አዲስዘመን ወይም ፍትህ
. ኢትዮጲያወይም ሞት ወይም ገንጣይ ተገንጣይ
. እምየሚኒሊክ ወይም አፄ ዮሃንስ
. ኢትዮጲያፈርስት ወይም ኦሮሞ ፈርስት
. ልማትወይም ሰብአዊ መብት
. ንኡስከበርቴ ወይም ደሃ
. ኪራይሰብሳቢ ወይም ልማታዊ
. ሰለፊስትወይም አህባሽ
. የውጪሲኖዶስ ወይም የሃገር ውስጥ ሲኖዶስ
. የምርጫትግል ወይም የትጥቅ ትግል
. ጠባብወይም አገር ወዳድ
. ባንዳወይም ጀግና
. የባንዳልጅ ወይም የጀግና ልጅ
. X ወይምY እያለ ይቀጥላል::

ይህን የፍረጃ ብዛት እና አይነት ለግዜው በዚህ እናብቃው:: የፅሁፌ መነሻ ርዕሥ በርካታ ሃሳቦችን ማስነሳት እንዲሁም ኢትዮጵያዊ ዳያስፖራንበተመለከተ የተለያዩሃሳቦችን ማንሳትና ማወያየት እንደሚችል ግልፅ ነው:: አነሰም በዛም እነዚህን ሃሳቦች እያነሱ መወያየትም ሆነ መተራረም ስለ ድክመታችን አውቀን የማስተካከያ እርምጃ እንድንወስድ ይረዳናል:: ድክመቱን በገደምዳሜ እያየንየምናልፈው ከሆነግን ለሃገራችንም ሆነ ለህዝባችን ፋይዳ አናመጣም:: መፅሃፉ እንዳለውም አስቀድሞ በአይናችን ያለውን ምሰሶ ማውጣት ስንችል ነው የጓደኛችንን ጉድፍ ማየት የምንችለው:: ነገርግን የኛ ዳያስፖራ እሱ ያለው እንጂ ሌላው የሚለው ትክክል አይደለም ብሎ የማሰብ አዝማሚያያሳያል::እናም ምናልባት የኔ ሃሳቦች ከተወደደው ዳያስፖራሃሳብ ጋር ካልተስማሙ የማይስማሙበትን ሁኔታ ለመስማት ዝግጁ መሆኔን አስቀድሜ ልግለፅ:: የባህርያችንን ጥልቀት ለማሳየትም ይመስላል "ኢትዮጵያየገባ አንድ ፀሃፊ በማግስቱ ስለ ኢትዮጵያውያን ከአንድ በላይ መፅሃፍ ሊፅፍ ይችላል:: በሁለተኛው ቀን ምናልባት ከተሳካለት ለጋዜጣየሚሆን መጣጥፍ ሊፅፍ ይችላል:: ሳምንት ሲቆይ ግን ያ ሰው ስለ ኢትዮጵያውያን አንድአረፍተ ነገር እንኳ መፃፍ አይችልም" አለየሚባለው:: ለማንኛውም ለዛሬ የሚከተሉትን "እዛም እዛም የረገጡ" ሃሳቦችንላንሳ:: ነገር ግን የማነሳቸው ሃሳቦች ከጥቂት ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራዎችጋር ግንኙነት የሌላቸው እና እንደማይመለከታቸውም ባውቅም ብዙሃኑን ይወክል ዘንድ እነዚያን ጥቂቶችም የፅሁፌ አካል አድርጌያቸዋለሁ:: ለዚህአስቀድሜ ይቅርታ እጠይቃለሁ::

1)  የእርስ በእርስ ፍረጃ መፍትሄ ይሆነናል?

ፍረጃ በማንኛውም ልኬትቢለካ ወደምንፈልገው የልማት ግብ ሊያደርሰን አይችልም::ክፍፍሎችንና ፍረጃዎችንእየተከተልን ስንጨቃጨቅእና ስንፈራረጅ ዓለም ጥሎን መሄዱ አይቀርም::  የፍረጃችንን ጥልቀትየሚያሳይ አንድ ትዝብት ላንሳ:: አንዱ የውጭ ሃገር ዜጋ ስለኛ ክፍፍል እና ፍረጃ ከሃበሻ ጋር ሲወያይ "እናንተኢትዮጵያውያን በእስካሁኑሂደት በብሄር፤ በጎሳ፤ በቋንቋ፤ በሀይማኖት እናበመሳሰሉት ተከፋፍላችኋል:: አሁን የቀራችሁ ነገር ቢኖር በስማችሁ ፊደል ቅደም ተከተል መከፋፈል ነው፡፡" አለየሚባል መራራ የቀልድ እውነታ አለ:: በብዛት እንደምንታዘበውም አብዛኛውስለወቅታዊው ፖለቲካየሚያወራልን ኢትዮጵያዊሁሉ አንድነትን ወይም ህብረትን የሚሰብክልን የራሱብሄር ከፍታ ቦታ ላይ ሊሆን እንደሚችል ካሰበ ብቻ ነው:: የርሱን ብሔር የተመለከተ ሌላ ታሪክ ወይም ድርጊት ከተነገረ ከርሱ በላይ የዘር ፖለቲካን አራማጅ የለም:: ፍረጃውም በአይነት በአይነት ተደርድሮ ይቀርባል:: ይህንን አይነት አካሄድን የሚያሳየን ደግሞ በተለያዩ ግዜያት ጣል በሚደረጉ አመለካከቶች ስር የሚሰጡ አስተያየቶችን መመልከትስንችል ነው:: እንደዚህ አይነት አመለካከትና አካሄድምናልባት የምንፈራውን ከማፋጠን ያለፈ ፋይዳ የለውም:: ስለ አንድነት ሲሰብክ የነበረ ኦሮሞ ስለ ኦሮሞ እርሱ የማያምንበት ተፅፎሲያነብ ለዛ ፅሁፍ መልስ ወይም ማስተካከያ እና መከራከሪያ ሃሳብ ከማቅረብ ይልቅ የፀሃፊውን ዘር እያነሱ ጥንብ እርኩሱን በማውጣት ፍረጃ የሚያወጣለት ከሆነምኑን ስለ አንድነት ሰበከው? ስለዘር ፓለቲካ ጎጂነት አሳምሮ አቀነባብሮ የሚሰብከንሰው ስለትግሬ መጥፎነት በማውራት እና በመፈረጅ ካጠናቀቀው የቱላይ ነው አንድነትን የሚያሳየው?አንድነት ሃይል ነው እያለ የሚያስተምር ሰውስለ አማራ ጨቋኝነት እያነሳ እና አማራውን እየፈረጀ ሌላው ብሄር አማራን እንዲጠላ ከሰበከ የቱ ላይ ነው አንድነቱ ያለው? አንድ ነን እያለ ትግሬን አትመኑ ካለን፣ አንድ ነን እያለ አማራ በድሎናል በማለት ያለፈ ታሪክ ካወራ፣ አንድ ነን እያለ ኦሮሞ የመጣው ከዚያ ነው ካለ የቱ ጋር አንድነቱ ያለው? የሚወራው አንድነትስ የማን ነው? አንድነቱ ከግለሰቦች ካልጀመረ እንዴትስ አንድነት ይሆናል? ይህን ትዝብት ለግዜው እዚህ ልግታዉና ወደ ቀጣይ ሃሳብ ላምራ::

የዘመኑ መንፈስ - በእውቀቱ ስዩም

ባገራችን ባሁኑ ጊዜ ብዙ ተከታይ ያለው ሃይማኖት ብሄርተኝነት ይባላል፡፡የብሄርተኝነት ምእመን ከሆንክ የነፍስ አባት ይኖርሀል፣ በጭፍን የምትቀበለው ቀኖና ይኖርሀል፣ ነገ የምትገባባት የተስፋ ምድር ይኖርሀል፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ ብርቱ ችግርህን የምትደፈድፍበት የመስዋእት በግ ይኖርሀል፡፡

ሃይማኖቶች ምእመናንን ብቻ ሳይሆን መናፍቃንንም ያፈራሉ፡፡ብሄርተኞች በስሜት የሚነድደውን ምእመን ብቻ ሳይሆን የኔ ቢጤውን መናፍቅም እንደሚያፈሩ አንርሳ፡፡ በነገራችን ላይ ሃይማኖትን መካድ ማለት ሃይማኖት የሚያነሳቸውን አብይ ጥያቄዎች መካድ ማለት አይደለም፡፡ እንዲሁም፣ ብሄርተኝነትን መካድ ማለት የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረሰቦች ህልውና መካድ ማለት አይደለም፡፡በዚህ ጉዳይ፣ መናፍቅ መሆን ማለት፣ የብሄርተኛ ነቢያት ስለ ጭቆና ስለ ነጻነት ብሎም ስለ ኢትዮጵያዊነት የሚያቀርቡትን አጉል እምነት መጠራጠር ማለት ነው፡፡

ከኢትዮጵያዊነት እንጀምር

ከዘመናችን የብሔርተኝነት ነቢያት አንዱ ጃዋር መሐመድ በቅርቡ ከእንቁ መጽሔት ጋር ባደረገው ቃለመጠይቅ ላይ ስለኢትዮጵያዊነት የሚከተለውን ይላል፡፡

‹‹…ኢትዮጵያን የመሠረታት የሶሰትዮሽ ጦርነት ግብግብ ነው፡፡በአማራው፣ በኦሮሞው፣ በትግሬው ግብግብ ውስጥ ወደ መጨረሻ ላይ በአመራር ስር የበላይነቱን የያዘው አማራው ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ አሁን የምናያት ኢትዮጵያ ማንነቷ በአማራ ባህላዊ ሥርጭት እና በአማራ ፖለቲካ የተገነባች ነች፡፡ …የኢትዮጵያ አገራዊ ማንነት የምንለው የአማራ ባህላዊ ማንነት ነው››
ጃዋር የኢትዮጵያን መሠረት የሦስት ብሄረሰቦች የስልጣን ግብግብ አድርጎ ወስኖታል፡፡ በመጀመርያ፣ ሌሎች ብሄረሰቦች በግብግቡ ተሳትፎ እንዳልነበራቸው አድርጎ ማቅረቡ አንድ ጉድለት ነው፡፡ ግን ዋናው ቁምነገር ይሄ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ የግጭት ውጤት ብቻ እንደሆነች አድርጎ ማቅረቡ ነው ትልቁ ስሕተት፡፡ ሲጀምር፣ የግብግብ ታሪክ መሠረት ይንዳል እንጂ መሠረት አይገነባም፡፡ እንደኔ ግምት፣ የኢትዮጵያ መሠረት የሆነው ብሄረሰቦች ለጋራ ሕልውና ሲሉ የሚያደርጉት የመደጋገፍ ታሪክ ነው፡፡

ዛሬ ዛሬ፣ ታሪክ ከላሾች፣ የብሄሮችን የ‹‹ግብግብ››ታሪክ ሞቅ አድርገው፣አኳሽተው ሲጽፉ፣የብሄሮች መደጋገፍ ታሪክን ግን ቸል ይሉታል፡፡ አለያም እጅግ በቀዘቀዘ ስሜት፣ በጥቂት መስመሮች ብቻ ጨረፍ አድርገው ያልፉታል፡፡ለነገሩ፣ከፋፋይነትን ብቸኛ ያስተዳደር ፈሊጥ አድርጎ የሚቆጥር ሰው በታሪክ ገጾች ውስጥ መመልከት የሚፈልገው ክፍፍልን ብቻ ነው፡፡ታሪክ ግን ብዙ በጎ የትብብር ገጠመኞችን መዝግቧል፡፡ለምሳሌ ጀግናው አጼ ዮሐንስ አራተኛ በበዛሬይቱ ኤርትራ የግብጽን ወራሪ ጦር ድል የነሡት የትግራይ ጀግኖችን ብቻ አሠልፈው አልነበረም፡፡ በዚህ ጦርነት ከግብጽ ጎን ሆኖ፣የተዋጋው አሜሪካዊው ጋዜጠኛ ዊልያም ዴይ እንደመሠከረው ወልቃይቶች፣ጥልጣል የተባሉ የአፋር ንኡስ ክፍሎች፣የወረኢሉ ኦሮሞዎች ለንጉሰነገስቱ ድጋፍ ለማድረግ ተሸቀዳድመዋል፡፡በራስ ወሌ የሚመሩ የአማራ ወታደሮች ተሳትፈዋል፡፡የጎንደር ቀሳውስት ለጦርነቱ ድጋፍ ለማድረግ አድዋ ገብተዋል፡፡ የጎጃሙ ራስ አዳል የደርሼልሀለሁ አለኝታቸውን አሳይተዋል፡፡ የሸዋው ንጉስ ምኒልክ ሳይቀር በመቶ የሚቆጠሩ በቅሎዎችንና ማበረታቻ ልከዋል፡፡ ዝርዝሩን ማንበብ ለሚፈልግ Muslim Egypt Christian Abyssinia የተባለውን የዚህ ደራሲ ማስታወሻ ገጽ 291-292 ያንብብ፡፡ መጽሐፉን በኢንተርኔት ቤተ-መጻህፍት ውስጥ በብላሽ ማግኘት ይቻላል፡፡

ከተለያየ መአዘን የመጡ እኒህ ኢትዮጵያውን ከዘመቻው የሚያገኙት ድልን ብቻ አልነበረም፡፡ በዘመቻ ወቅት ባህል ይዋዋሳሉ፣ቃላት ይወራረሳሉ፣ ስንቅ ያዋጣሉ፣ ልምድ ይለዋወጣሉ፡፡ በሂደት ተቃራኒ ከሚመስሉ ልማዶች የነጠረ ኢትዮጵያዊ ባህል እንደ አረቄ ይወጣል፡፡ ይህን በመዋጮ የተገኘ ባህል ‹‹የአማራ ባህል ››ብሎ ማጥበብ የጸና ድጋፍ ያለው አይመስለኝም፡፡
ጃዋር‹‹አሁን የምናያት ኢትዮጵያ ማንነቷ በአማራ ባህላዊ ሥርጭትና በአማራ ፖለቲካ የተገነባች ነች›› በማለት ሳይወሰን ‹‹የኢትዮጵያ አገራዊ መለያ ማንነት የምንለው አማራ ብሄራዊ ማንነት ነው›› ሲል ይጨምራል፡፡ ጎበዝ ኧረ በህግ አምላክ!!! የኢትዮጵያ ባህልኮ ካንድ አለት የተጠረበ ሕንጻ አይደለም፡፡ ከብዙ የመዋጮ ጡቦች የተገነባ ነው፡፡ ጃዋር እያንዳንዱን ጡብ ቀርቦ ቢመረምረው እዚህ የደረሰበት እርግጠኝነት ውስጥ የሚደርስ አይመስለኝም፡፡

Saturday, July 27, 2013

ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማሪያም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ግልፅ ደብዳቤ ላኩ! የቤኒሻንጉል ተፈናቃዮች አሁንም በችግር ላይ ናቸው” (መኢአድና ሠማያዊ ፓርቲ)


ከቤኒሻንጉል ክልል ተፈናቅለው ከነበሩት የአማራ ክልል ተወላጆች ጋር በተያያዘ የክልሉን የስራ ሃላፊዎችና መንግስትን ለመክሰስ፣ ሰማያዊ ፓርቲና መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ጥብቅና ያቆሟቸው አለም አቀፍ የህግ ባለሙያው ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማሪያም፤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ግልፅ ደብዳቤ መፃፋቸው ተገለፀ፡፡ ሁለቱ ፓርቲዎች ከትናንት በስቲያ ከሠዓት በኋላ በሠማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በጋራ በሠጡት መግለጫ፤ ተፈናቃዮቹ አሁንም ችግር ላይ መሆናቸውን፣ ልጆቻቸው ትምህርት ማቋረጣቸውን፤ በሚዲያ እንደሚነገረው ወደ ቀድሞ ኑሯቸው አለመመለሳቸውንና በአጠቃላይ ችግር ላይ መሆናቸውን በማስረጃ በማስደገፍ፣ የጉራፈርዳንና የቤኒሻንጉል ተፈናቃዮችን በማነጋገርና በበርካታ መረጃዎች የተደገፉ ዶክሜንቶችን በማያያዝ ዶ/ር ያዕቆብ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የላኩትን ደብዳቤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ፈርሞ መቀበሉንም ፓርቲዎቹ ገልፀዋል፡፡


የሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እንደተናገሩት፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ችግሩን በፓርላማ ቀርበው ማመናቸውን፣ ድርጊቱን ፈፅመዋል የተባሉት የክልልና የወረዳ ስራ አስፈፃሚዎች ከስራ መሰናበታቸውን፣ ተፈናቃዮቹ ወደነበሩበት ተመልሠው በሠላም እየኖሩ እንደሆነ የገለፁ ቢሆንም እውነታው ግን ከዚህ በተቃራኒው መሆኑን ዶ/ር ያዕቆብ ከተፈናቃዮች ጋር በመነጋገር ማረጋገጣቸውን ጠቁመው፣ ጉዳዩ ወደ ፍ/ቤት ከመሄዱ በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሠጡ ዶ/ር ያዕቆብ ለጠ/ሚኒስትሩ በላኩት ደብዳቤ አስታውቀዋል፡፡ ዶ/ር ያዕቆብ፤ አፋጣኝ ምላሽ ያሻቸዋል ያሏቸውን አራት ዋና ዋና ነጥቦች በደብዳቤያቸው ላይ ያሰፈሩ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ተፈናቃዮቹ ወደ ቀድሞ ቦታቸው በመንግስት ወጪ ተመልሠው መሬታቸው፣ የንግድ ተቋሞቻቸውና ቤት ንብረታቸው በአስቸኳይ እንዲመለስላቸው፣ ተፈናቃዮቹ ለደረሰባቸው ቁሳዊ ጉዳት፣ አካላዊና ሞራላዊ እንግልት መንግስት ተመጣጣኝ ካሳ እንዲከፍላቸው የሚመለከታቸውን አካላት እንዲያዝዙ፣ በቤኒሻንጉል የሚኖሩ የማንኛውም ብሄር ተወላጆች ተመሳሳይ ወንጀል እንዳይፈፀምባቸው ጥበቃ እንዲደረግላቸው እና ተዋዶና ተፋቅሮ የሚኖረውን ህዝብ በመከፋፈል የማፈናቀል ድርጊት የፈፀሙ የመንግስት ባለስልጣናት ህግ ፊት ቀርበው ቅጣት እንዲያገኙ ውሳኔ እንዲያሳልፉ የሚሉት ነጥቦች ተቀምጠዋል፡፡

ምርጫው ከጠረጴዛው ላይ ነው! (ከድምፃችን ይሰማ)

ትናንት በአለም አቀፍ ደረጃ የተካሄደው ልዩና አስደማሚ ተቃውሞ መቼም ቢሆን ከልባችን የሚጠፋ አይሆንም፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ከቤቱና አካባቢው ነቅሎ በመውጣት ፍትህን ሲጣራ የዋለበት የትላንቱ ጁምአ በእርግጥም ደማቅና ልዩ ነበር፡፡ ከተቃውሞው ድምቀት እና ማማር ጋር ሙስሊሙ ሀህብረተሰብ ማድረስ የሚፈልገውን መልእክት በሚገባና በተብራራ ሁኔታ አድርሷል፡፡ እውን ለዜጎች ፍላጎትና መሻት የሚጨነቅ አካል ካለ ምርጫው ከጠረጴዛው ላይ ነው፡፡ እውን ለሕገ የበላይነት መከበር፣ ለሕገ መንግስቱ መከበር፣ ለአገር እድገትና ልማት የሚገደው መንግስት ካለ ምርጫው ከጠረጴዛው ላይ ነው፡፡ ሕዝቡ በጁምአው ትዕይንት መልእክቱን ትናንትም አድርሷል፡፡


የህዝበ ሙስሊሙ ፍላጎት የሚንጸባረቀው በጁምአ ሰላት ተቃውሞዎች ብቻ አይደለም። በስራ እና በአቅም ማነስ፣ እንዲሁም በተለያዩ አለመመቻቸቶች ምክንያት ተቃውሞ በሚደረግባቸው መስጂዶች መስገድ ያልቻሉ በርካታ ሚሊዮኖች በየከተማው አሉ። የመንግስት ጭቆና ጫፍ በደረሰባቸው ከተሞች ደግሞ ተቃውሞ ማድረግ እየፈለጉ አጋርነታቸውን በዱአና ተሰብስቦ በአንድ መስጂድ በመስገድ ብቻ ለመወሰን የተገደዱ ከተሞች በርካታ ናቸው። እነዚህ ሁሉ ግን የህዝበ ሙስሊሙን ጥያቄ የሚጋሩና በመንግስት ጭቆናም እኩል የተማረሩ ናቸው። የመስጂድ ነጠቃውና መድረሳ እሸጋው በቀጥታ እየነካቸው ያሉ ናቸው። ልጆቻቸው በየሳምንቱ ለእስርና ድብደባ እየተጋለጡባቸው ያሉ ናቸው። 


መንግስት በበርካታ አጋጣሚዎች ተቃውሞው የህዝበ ሙስሊሙ በሙሉ እንጂ የጥቂቶች አለመሆኑን ማረጋገጥ ችሏል። አስቀድሞ በየወረዳና በየቀበሌው ባደረጋቸው ስብሰባዎች ሀዝቡ ተቃውሞውን እስከጥግ አሰምቷል፤ ችግሩን ተናግሯል። ካድሬዎችና የወጣት ሊግ አባሎችን ብቻ በጠራባቸው ስብሰባዎችም አባላት መንግስት እየተከተለ ባለው አቅጣጫ ደስተኛ አለመሆናቸውን በግልጽ አንጸባርቀዋል። በአንዳንድ ቦታዎች የኢህአዴግ አባልነት መታወቂያቸውን አውጥተው ‹‹እንኩ ተቀበሉን አንፈልግም!›› ያሉ አባላት ታይተዋል። ሁሉንም ግን ‹‹የራሳችሁ ጉዳይ›› የሚል አመለካከት የሚያራምድ የሚመስለው መንግስት በአስገራሚ ሁኔታ ችላ ብሏቸዋል።

ባለስልጣናቱ ከባለሀብት ጋር ያቋቋሙት የንግድ ድርጅት እየተመረመረ ነው

የስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የምርመራ ቡድን፤ በእነ ዳዊት ኢትዮጵያ መዝገብ ስር ተጠቃለው የሚገኙት ከፍተኛ ባለሀብቱ አቶ ማሞ ኪሮስ በሌላ መዝገብ ተጠርጥረው ከሚገኙ የጉምሩክና ገቢዎች ባለስልጣን ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ባቋቋሙት “ልማት ለእድገት” የተባለ ድርጅት ላይ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን ገለፀ፡፡ ድርጅቱን የሚገምት የባለሙያዎች ቡድንም ተቋቁሟል፡፡ አቶ ማሞ በስራ አስኪያጅነት ይመሩታል የተባለው ይህ ድርጅት በተለያየ ጊዜ ከህግ አግባብ ውጪ እቃዎችን ከውጭ ሀገር ያስገባ እንደነበር ለፍርድ ቤት ያስረዳው የምርመራ ቡድኑ፤ እስካሁን ይህን የሚያስረዱ ሰነዶች መሰባሰባቸውንና 4 ምስክሮች መቆጠራቸውን ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት አመልክቷል፡፡ በእኚሁ ባለሀብት በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ተደርገዋል የተባሉ 22 ኮንቴነር እቃዎች ሞጆ በሚገኘው ደረቅ ወደብ ተይዘው ምርመራ እየተከናወነ እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡

ከትላንት በስቲያ በዚሁ መዝገብ ስር የሚገኙትን የጉምሩክ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም ባለሀብቶችን ጉዳይ ችሎቱ የተመለከተ ሲሆን የምርመራ ቡድኑም ቀደም ሲል በተሰጠው የ10 ቀን የምርመራ ጊዜ ውስጥ ያከናወናቸውንና ይቀሩኛል ያላቸውን ስራዎች በዝርዝር በመግለጽ፣ ለ7ኛ ጊዜ የጠየቀው የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶለታል፡፡ በዚህ መዝገብ ከአቶ ማሞ ኪሮስ በተጨማሪ አቶ ዳዊት ኢትዮጵያ፣ አቶ ማሞ አብዱ፣ አቶ አሸብር ተሰማ፣ ፍፁም ገ/መድህን፣ እንዲሁም አቶ አበበለኝ ተስፋዬ የተካተቱ ሲሆን በተጠርጣሪዎቹ ላይ የምርመራ ቡድኑ በተሰጠው የ10 ቀን ጊዜ ውስጥ ከታክስና ቀረጥ ስወራ ጋር በተያያዘ በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ ሰነድ ተሰባስቧል፣ በ3 ኩባንያዎች ላይ የሚደረገው የኦዲት ስራም ተጠናቋል፡፡

በህገወጥ መንገድ የተገኘ ገንዘብን ህጋዊ አድርጐ መያዝ በሚለው በአቶ አሸብር ተሰማ ላይ የሰው ማስረጃ እየተሰባሰበና ክትትል እየተደረገ ነው፣ ምንጩ ያልታወቀ ሃብትን በተመለከተ በአቶ ዳዊት ኢትዮጵያ፣ በአቶ ማሞ አብዱ፣ በአቶ አሸብር ተሰማ እና በአቶ አበበልኝ ተስፋዬ ላይ ከክ/ከተሞች፣ ከባንክ፣ ከትራንስፖርት ቢሮዎች እንዲሁም ከክልሎች ማስረጃ ተሰባስቧል ብሏል፡፡ በሌላ በኩል የምርመራ ቡድኑ በዚህ መዝገብ ይቀሩኛል ብሎ የ14 ቀን ቀጠሮ የጠየቀባቸው ስራዎች፡- የቀሪ ሁለት ኩባንያዎችን ኦዲት ማጠናቀቅ፣ የታክስ ልዩነት በመፍጠር እቃዎችን አስገብተዋል በተባሉት ላይ የዘጠኝ ምስክሮችን ቃል መቀበል፣ በአቶ ማሞ ኪሮስ እና በባለስልጣናቱ ተቋቋመ ከተባለው ድርጅት ጋር በተያያዘ ተጨማሪ 5 ምስክሮችን ቃል መቀበልና ንብረቱን በባለሙያ አስገምቶ ሪፖርቱን መቀበል፣ የባለሙያ ምስክርነት ቃል መቀበል፣ በህገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ መያዝን በተመለከተ ከአዋሣና ጐንደር የንብረት ግምት ሪፖርትና የምስክር ቃል ተጠናቆ እንዲመጣ መከታተል የሚሉት ናቸው። በመርማሪ ቡድኑ ሪፖርት ላይም ተጠርጣሪዎችና ጠበቆቻቸው ከዚህ ቀደም በነበረው ችሎት ያቀረቡት መከራከሪያ እንዲመዘገብላቸው በመጠየቅና የየግል ምክንያታቸውን በማቅረብ፣ የዋስትና መብታችን ተከብሮ ጉዳያችንን በውጭ ሆነን እንድንከታተል ይፈቀድልን ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ የመርማሪ ቡድኑም በሰጠው ምላሽ፤ በሪፖርቱ እንደተገለፀው ቀሪ የምርመራ ስራዎች ስላሉ፣ ተጠርጣሪዎች በዋስ ቢወጡ ያላቸውን ስልጣንና ሃብት በመጠቀም ምስክሮችና ሊያባብሉ፣ ሰነዶችን ሊያሸሹ ይችላሉ በዚህም ፍትህ ሊጓደል ይችላል በሚል የዋስትና ጥያቄውን ተቃውሟል፡፡

Friday, July 26, 2013

በቅርቡ በኦሮሞ ወንድሞቻችን ላይ የተፈጸመዉ ሰቆቃ ሊቆጨን፤ ሊያንገበግበንና ሊያስተባብረን ይገባል

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አለምአቀፋዊ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ አንቀጽ ዘጠኝ፤ አንቀጽ አስርና አንቀጽ አስራ አንድ የማንኛዉም አገር ዜጋ ያለ አግባብ መታሰር እንደሌለበት፤ በወንጀል ተጠርጥሮ የሚታሰር የማንም አገር ዜጋ በአስቸኳይ ፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለበትና የፍርድ ቤቱ ሂደት አስከተፈጸመ ድርስ ደግሞ የተጠርጣሪዉ ዜጋ ንጽህና የተረጋገጠ መሆን እንዳለበት ይደነግጋል። በዚሁ የተመድ አለምአቀፋዊ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ድንጋጌ ሰነድ ላይ ተመስርቶ የተጻፈዉ የ1994ቱ የኢትዮጵያ ህገመንግሰት አንቀጽ 17 ንዑስ አንቀጽ ሁለት ደግሞ ማንም ዜጋ ያለ አግባብ መታሰር እንደሌለበት፤ ማንም ዜጋ ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ዉጭ መታሰር እንደሌለበትና በፍርድ ቤት ትዕዛዝ የታሰረ ዜጋም ቢሆን በአስቸኳይ ፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለበት በግልጽ ይደነግጋል። ኢትዮጵያ ደግሞ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ ያረቀቀችና ያጸደቀች አገር ብቻ ሳትሆን ከሃምሳ አንዱ የተመድ መስራች አገሮች ዉስጥ አንዷ ናት።

የ17 አመት የጫካ ዉስጥ ትግል ያካሄደዉና በ1983 ዓም አዲስ አበባ ገብቶ ላለፉት ሃያ ሁለት አመታት የኢትዮጵያን በትረ ስልጣን ጨብጦ የያዘዉ ህወሃት ኢትዮጵያ በፊርማዋ ያፀደቀችዉን የተመድን አለምአቀፋዊ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌም ሆነ እሱ እራሱ አርቅቆ የጻፈዉን የኢትዮጵያ ህገመንግስት ማክበር ቀርቶ የሰነዶቹ ምንነት በዉል የጋባዉ ድርጅት አይደለም። ህወሀት የተወለደዉና ጥርሱን ነቅሎ ያደገዉ ጫካ ዉስጥ ሲሆን ዛሬም ከ22 አመታት የከተማ ዉስጥ ቆይታዉ በኋላ ኢትዮጵያን ያክል ትልቅ አገር የሚያስተዳድረዉ በዚያዉ ተወልዶ ባደገበትና በተካነዉ የጫካ ዉስጥ ህግ ነዉ። ህወሀትን ይዞት ካደገዉ ባህሉና ከዋና መገለጫ በህሪይዉ ተላቀቅ ማለት ዉኃ መዉቀጥ ሊሆን ይችላል፤ ሆኖም የጥቁር ህዝብ የነጻነት ምልክት የሆነዉን የኢትዮጵያን ህዝብ በጫካ ዉስጥ ህግ መዳኘትና ማስተዳደር ግን የኢትዮጵያ ህዝብ በፍጹም ሊቀበለዉ፤ አለም አቀፉ ህብረተሰብ ደግሞ አፉን ዘግቶ ሊመለከተዉ የማይገባ በህዝብና በአገር ላይ የሚፈጸም ከባድ ወንጀል ነዉ።

Thursday, July 25, 2013

“በስመ ተቃዋሚ ተቃቅፎ መሳሳም” – ለትልቁ ዓላማ? (በሶሊያና ሽመልስ - Zone 9)


ከጥቂት ጊዜያት በፌት አንድ የመጽሐፍ ዳሰሳ ዝግጅት ላይ ተገኝቼ ነበር፡፡ መጽሐፉ “ፌኒክሷ ዛሬም፣ ሞታም ታንቀላፋለች” ሲሆን ጸሐፊዋ የቀድሞው የሕወሓት አባልና አመራር የአቶ ገብሩ አስራት ባለቤት ወ/ሮ ውብማር ናቸው፡፡ በዳሰሳው ወቅት በትግል ጊዜ ለምን መጽሐፉ ላይ የተጠቀሱትን ችግሮች እንዳልፈቱ ሲጠየቁ ወይዘሮዋ እንዲህ ብለው መልሰው ነበር፡፡

“ደርግን የሚያህል ጠላት ከፊት ለፊታችን እያለ እንዴት እርስ በርስ በመጣላት ጊዜ እናባክናለን? ነጻ ስንወጣ የሕወሓት ፖሊሲና ፕሮግራም ሁሉንም ነገር ይፈታዋል::” ብለን ተውነው ይላሉ፡፡

በኋላ ላይ ደግሞ ሕወሓትን ስለመለወጥ ሲጠየቁ ‹‹ሕወሓት ከዚህ በኋላ የሚለወጥ ድርጅት አይደለም አርጅቷል፡፡ 40 ዓመት በኋላ የድርጅት ባሕሪይ አይቀየርም›› ሲሉ ይከራከራሉ፡፡

የትኛው ጠላት? የትኛው ትልቁ ዓላማ?

አሁንም ሕወሓት ሥልጣን ከያዘ ከ20 ዓመት በኋላም ቢሆን የዋናው ጠላት ወይም “ትልቁ ዓላማ” ክርክር እንደ መተባበርያ  እና እነደመቻቻያ ሰበብ እንዲሁም እንደአለመተቺያ ምክንያት ይነሳል፡፡ ተቃዋሚዎች እንዲተባበሩ የሚጠየቁት “ዋናውን  ጠላት” ለማንበርከክ ነው፡፡ የትልቁ ጠላት መኖር አገራዊ የፖለቲካ ክርክራችንንም ሆነ የፓርቲ ፖለቲካችንን የሚበጠብጥ  ትልቅ ችግራችን እየመሰለኝ መጥቷል፡፡ መንግሥት/ገዥው ፓርቲ  የተሰኘውን ይህንን ጠላት ለማባረር በሚደረገው ጥረት ውስጥ ለትልቁ ዓላማ ተብሎ የምናጣቸውን ነገሮች ሳናስተውል የምናልፍበት ጊዜ ብዙ ነው፡፡ ምሳሌ እናንሳ ብንል ለትልቁ ዓላማ ሲባል የማይተች ጋዜጠኛ አለን፣ ለትልቁ ዓላማ ሲባል የተቃዋሚ ፓርቲ አይነካም፣ ለትልቁ ዓላማ ሲባል ውስጠ ፓርቲ ልዩነቶች ይታፈናሉ (ሲፈነዱ የሚያመጡት አደጋ መባሱ ላይቀር)፡፡ ለትልቁ ዓላማ ሲባል ሐሳብን በነጻነት መግለጽ መብትን የሚያፍኑ ሌሎች ትንንሽ ጨቋኞችን ማበረታታት የተለመደ ሆኗል፡፡ ለትልቁ ዓላማ ሰበብ ሲባል ጋዜጠኞች ላይ የጥላቻ ፓሮፖጋንዳ ይነዛል፡፡ ትልቁ ዓላማ ሁላችንም ስህተቶቻችንን የምንሸፍንበት አገራዊ የተቃውሞ ሰበብ ሆኖልናል፡፡

“ትልቁ ዓላማ”ና ትርጉሙ

አብዛኛው ተቃዋሚ ፓርቲዎች/ግለሰቦች  ዓላማቸው ቢጠየቁ  ሃገሪትዋ አሁን ካለችበት ሁኔታ በሁሉም መልኩ ተሻሽላ እንድትገኝ ማድረግ እንደሆነ ቢያንስ በግርድፉ ይናገራሉ ብዬ እገምታለሁ፡፡ አሁን ላለን የፖለቲካዊ ሁኔታ ትኩረት እንሰጣለን የምንል ቡድኖችም ሆነ ግለሰቦች በቋንቋ ብንለያይም፣ ብንጠየቅ የምንናገረው ሐሳብም ከዚህ የተለየ አይሆንም የሚል ግምት አለኝ፡፡ (የገዥው ፓርቲ ደጋፊዎች አሁን ባለችው ኢትዮጵያ እንደሚስማሙና እንደማይመለከታቸው ባስብም ኢሕአዴግም ራሱ በተቃዋሚዎች ቦታ ቢሆን የተሻለ አቅም እንደማይኖረው በመገመት  ይህንን ውይይት ወደራሳቸው ቢተረጉሙት አልጠላም፡፡) ነገር ግን አሁን ያለውን ነባራዊ የፓለቲካ ሁኔታ ከመቀየር ረገድ እየሠራን ነው የሚሉት አካላት ሁሉ የሚስማሙበት የሚመስለው ሌላው ነገር ሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት መቀየር የሚለውን አካሄድ ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ሠላማዊዎቹንም ነፍጥ ያነሱ ቡድኖችንም የሚያስማማ ሁለተኛው የጋራ ሐሳብ መሆኑ ነው፡፡ እንግዲህ ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች ላይ የሚስማሙት ተቃዋሚዎች በተመሳሳይ ሁኔታ መንግሥት ለመቀየር የሚያደርጉትን ጥረት ባለማስተባበር ሲታሙ ኖረዋል፡፡ “ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ” ተብለው ሲተቹ ከርመው ቢተባበሩም ደግሞው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከመሰባበር አላመለጡም፡፡

10 Poorest Countries in The World (All in Africa): Ethiopia placed in the 2 place

You probably heard that Ethiopia has been a fast growing economy in the content recording very high growth rate not just in Africa but the world as well. Yet the new measurement known as the Multidimensional Poverty Index, or MPI, that will replace the Human Poverty index in the United Nations’ annual Human Development Report says that Ethiopia has the second highest percentage of people who are MPI poor in the world, with only the west African nation of Niger fairing worse. This comes as more international analysts have also began to question the accuracy of the Meles government’s double digit economic growth claims and similar disputed government statistics referred by institutions like the IMF.

Niger
Ethiopia
Mali
Burkina Faso
Burundi
Somalia
Central African Republic
Liberia
Guinea
Sierra Leone

Eskinder Nega’s Letter on The New York Times

ADDIS ABABA, Ethiopia — I AM jailed, with around 200 other inmates, in a wide hall that looks like a warehouse. For all of us, there are only three toilets. Most of the inmates sleep on the floor, which has never been swept. About 1,000 prisoners share the small open space here at Kaliti Prison. One can guess our fate if a communicable disease breaks out.

I was arrested in September 2011 and detained for nine months before I was found guilty in June 2012 under Ethiopia’s overly broad Anti-Terrorism Proclamation, which ostensibly covers the “planning, preparation, conspiracy, incitement and attempt” of terrorist acts. In reality, the law has been used as a pretext to detain journalists who criticize the government. Last July, I was sentenced to 18 years in prison.

I’ve never conspired to overthrow the government; all I did was report on the Arab Spring and suggest that something similar might happen in Ethiopia if the authoritarian regime didn’t reform. The state’s main evidence against me was a YouTube video of me, saying this at a public meeting. I also dared to question the government’s ludicrous claim that jailed journalists were terrorists.

Under the previous regime of Prime Minister Meles Zenawi, I was detained. So was my wife, Serkalem Fasil. She gave birth to our son in prison in 2005. (She was released in 2007.) Our newspapers were shut down under laws that claim to fight terrorism but really just muzzle the press.

የመንግሥትን ስም ማጥፋት ማለት የክቡርነታቸውን …? (ፕ/ር መሰፍን ወልደማርያም )

ስም ምንድን ነው? መታወቂያ ነው፤ መጠሪያ ነው፤ ስም ማጥፋት ሲባል ስም አለ ማለት ነው፤ ከስምም አልፎ የገነነ ስም አለ ማለት ነው፤ ስለዚህም ሊጠፋ የሚችለው የገነነ ስም ሲኖር ብቻ ነው ማለት ነው፤ ደራርቱ ቱሉ፣ ፋጡማ ሮባ፣ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ የገነኑ ስሞች ናቸው፤ አንድ ሰው እነዚህን የገነኑ ስሞች አጠፋህ ቢባል ሊገባን ይችላል፤ ዘለቀ ወርዶፋ፣ አየለ ተከስተ ስማቸው ጠፋ ቢባል፣ መጀመሪያ የሚቀርበው ጥያቄ እነማን ናቸው? ዱሮስ የገነነ ስም ነበራቸው ወይ? የሚል ይሆናል፤ ስለዚህ መሰላሉን ያልወጣውን ሰው ውረድ ቢሉት ትርጉም የለውም።

ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ስም ነው፤ ዘርፈሽዋል ማናለብህ ስም ነው፤ ክቡር ፕ
ሬዚደንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ስም ነው፤ ታደሰ ክፍሎም ስም ነው፤ ደራርቱ ቱሉ ስም ነው፤ ውቢቱ ማስረሻ ስም ነው፤ አዜብ መስፍን ስም ነው፤ ቴዎድሮስ ካሣሁን ስም ነው፤ አበበ ቶላ ስም ነው፤ ሚካኤል በላይነህ ስም ነው፤ ሐጎስ በየነ ስም ነው፤ … እነዚህ ሁሉ ስሞች በመሆናቸው አንድ ቢሆኑም ከእያንዳንዳችን ጋር ባላቸው ግንኙነት ይለያያሉ፤ አንዳንዶቹን እናውቃቸዋለን፤ በተለያዩ መንገዶችም ቢሆን ከኑሮአችን ጋር የተያያዙ ስለሆኑ፣ ያስደስቱናል ወይም ያስከፉናል፤ ስለዚህም ሲያስደስቱን እናወድሳቸዋለን፤ ሲያስስከፉን እንወቅሳቸዋለን፤ ዋናው ጥያቄ የሚመጣው እዚህ ላይ ነው፤ ውቢቱ ማስረሻ፣ ዘርፈሽዋል ማናለብህ፣ ታደሰ ክፍሎም፣ አበበ ዋቅቶላ ማን እንደሆኑና ምን እንደሆኑ አላውቅም፤ ስለዚህ የነሱን ስም አንሥቼ የምደሰትበትም ሆነ የምከፋበት ምክንያት የለኝም፤ የኔ አይደሉም፤ የሚያስደስቱኝና የሚያስከፉኝ የኔ የምላቸው ናቸው፤ የኔ የምላቸው እነማን ናቸው? ወድጄም ሆነ ተገድጄ ጭንቅላቴ ላይ በእግራቸው የቆሙ ሰዎች አሉ፤ እኔ የኔ ባልላቸውም እነሱ የራሳቸው፣ ዕቃቸው አድርገውኛል፤ የምነቅፋቸውም ራሳቸውን የኔ ሳያደርጉ እኔን የነሱ ስላደረጉኝ ነው፤ ስለዚህም የኔ የሆኑት ሁሉ ሳወድሳቸው አይከፍሉኝም፤ ስወቅሳቸውም አይከሱኝም፤ ሳወድሳቸው ደስ የሚላቸውና የሚኩራሩት ስወቅሳቸው ለምን ይቆጣሉ? የማወድሳቸውም ሆነ የምወቅሳቸው የራሴን ጥቅም እያሰብሁ መሆኑን ሳይገነዘቡት ቀርተው ነው? ወደአራት ዓመት ግድም ሲሆነኝ ገና ጣልያን ሳይገባ አንዲት እግራቸው የማይንቀሳቀስላቸው አሮጊት ጎረቤት ነበሩ፤ ጠዋት ተሸክመው በር ላይ ያስቀምጧቸዋል፤ እንደልባቸው ሲለፈልፉ ይውሉ ነበር፤ በደንብ የማስታውሰው ‹‹ሠይፉ ዘለቀ … ተለቀለቀ! መስፍን ስለሺ ይበቃል ለሺ!›› እያሉ በየዕለቱ ይጮሁ ነበር፤ መስፍን ስለሺ የአራዳ ዘበኛ ሀነው በፈረስ ይታዩ ነበር፤ ሠይፉ ዘለቀ በድቅድቂት የሚሄዱ ነበሩ፤በኋላ አንደሰማሁትና ትንሽ ትንሽ እንደማስታውሰው ለጣልያን ገብረው ውርደት ደርሶባቸው ነበርና የአሮጊትዋ ትንቢት የያዘ ይመስላል፤ ለማናቸውም ሴትዮዋ ተከሰሱ ሲባል አልሰማሁም።

ከስድሳ ዓመታት ያህል በፊት በኒው ዮርክ አንድ ሰው በስም ማጥፋት ክስ መሠረተ፤ ፍርድ ቤቱ ከሱን ሲመረምር ከሳሽ ፖሊስ መሆኑን ተረዳ፤ ፖሊስ የሕዝብ አገልጋይ ነው፤ ስለሆነም በፖሊስ ላይ ከተገልጋዮቹ ሰዎች ትችት ቢቀርብበት የስም ማጥፋት አይሆንም፤ በተጨማሪም ዜጎች ሁሉ የማይገረሰስ ሀሳብን የመግለጽ መብት ስላላቸው፣ የሕዝብ አገልጋይ የሆነው ፖሊስ ስም እንዳይጠፋ ተብሎ ሕገ መንግሥታዊውን ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት መገደብ አይቻልም በማለት የኒው ዮርኩ ፍርድ ቤት በየነ፤ ፍርድ ቤቱ በብይኑ ላይ አንድ መሠረታዊ ሀሳብን አስገነዘበ፤ ስም ማጥፋት የሚባለው በተራ ሰው ላይ ወይስ በሕዝብ አገልጋይ ላይ የተፈጸመ መሆኑን መለየት እንደሚያስፈልግ አመለከተ፤ በአገራችንም አጼ ቴዎድሮስ ወንድምዋን የገደሉባት ሴት በሄዱበት ሁሉ እየተከተለች ንጉሠ ነገሥቱን ስትሰድብ፣ በሆነ ባልሆነው ሁሉ ገደል የሚጨምሩትና በእሳት የሚያቃጥሉት ንጉሠ ነገሥት ይቺን በንዴት የተቃጠለች ሴት ምንም አላደረጓትም! አጼ ምኒልክንም አሞካሽቶ ገጣጣ ያላቸው ምንም የደረሰበት አይመስለኝም፤–

ለመለስ ሙት አመት ማስታወሻ (ከፋሲል የኔአለም)


ከመለስ ሞት በሁዋላ ያለው የኢትዮጵያ ሁኔታ ከሌኒን ሞት በሁዋላ የነበረውን የሩስያ ሁኔታ ያስታውሰኛል። ሌኒን በቦልሼቪክ ፓርቲ ውስጥ የገዘፈ ስም ነበረው፣ በፓርቲው ውስጥ ያሰፈነው የዲሞክራሲያዊ ማእከላዊነት አሰራር የምእራቡን ዲሞክራሲን ለማይቀበለው የኮሚኒስት ታጋይ ሁሉ የሚመች ነበር ፤ በዲሞክራሲያዊ ማእከላዊነት መርህ መሰረት ማንም የድርጅቱ አባል የሆነ ሰው እንደልቡ መናገር ይፈቀድለታል፣ ውሳኔ ከተላለፈ በሁዋላ ግና ውሳኔውን ያለምንም ማቅማማት ይተገብራል። ሌኒን ሲሞት የሌኒንን ቦታ ለመያዝ ይቋምጥ የነበረው ስታሊን የመጀመሪያ እቅዱ ይህን የዲሞክራሲያዊ ማእከላዊነትን አሰራር ማፍረስ ነበር። ስታሊን ተናግሮ የማሳመን ወይም አዳዲስ ሃሳቦችን የማፍለቅ ስጦታ ወይም ችሎታ አልነበረውም። ትሮትስኪን የመሳሰሉ፣ ከስታሊን የተሻለ አስተሳሰብ እና ብቃት የነበራቸው፣ ሰዎች የዲሞክራሲያዊ ማእከላዊነትን አሰራር ተጠቅመው ወደ ስልጣን የሚመጡበት እድል ከፍተኛ ነበር፤ ስታሊን ይህንን አሰራር ካላስቆመው በስተቀር በክርክር የመሪነቱን ስልጣን ሊይዝ የሚችልበት እድል አልነበረውም፣ አፈረሰው።


ዲሞክራሲያዊ ማእከላዊነትን ማፍረስ ብቻውን ለስታሊን በስልጣን ላይ መቆየት ዋስታና የማይሰጥ በመሆኑ ስታሊን የፓርቲውን መስራችና የአብዮቱ መሪ የነበረውን የሟቹን የሌኒንን ስም ለመጠቀም ወሰነ። የመንግስት የመገናኛ ብዙሀን ሌኒን የተለየ ፍጥረት እንደነበር እንዲሰብኩ አዘዘ፣ ዜና መክፈቻና መዝጊያው ሁሉ “በሌኒን ራእይ” የታጀበ ሆነ። ጎዳናው ሌኒን፣ ካፌው ሌኒን.. ሆስፒታሉ ሌኒን፣ መጸዳጃው ሌኒን፣ ሌኒን.. ሌኒን… ሌኒን… እነትሮትስኪ በሌኒን ሙት መንፈስ መነገዱ እንዲበቃ ቢወተውቱም ለእነስታሊን የሚያሳምን አልሆነም፣ እንዲያውም ሌኒን ወደ “ሌኒኒዝምነት” ከፍ አለ…። ስታሊን የሌኒን የሙት መንፈስ ብቻውን ለረጅም ጊዜ በስልጣን ላይ እንደማያኖረው የተገለጠት ዘግይቶ ነበር፤ ይህ መገለጥ እንደታየው ወዲያውኑ ተቃዋሚዎችን አንድ በአንድ ጨረሳቸው።

Wednesday, July 24, 2013

የኃይሌ ወደ ፖለቲካው መድረክ መምጣት እያነጋገረ ነው

“ኃይሌ ወደ ፖለቲካ መግባቱ መብቱ ቢሆንም እንደስፖርቱ በፖለቲካውም የሚያንጸባርቅ አይመስለኝም” ዶ/ር መረራ

“በአገሪቱ የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል የለም። አገሪቱ የጡንቸኞች ሀገር ናት። … ገብቶ ይሞክረው” ፕሮፌሰር በየነ

“እኔ ኃይሌን ብሆን ኖሮ በግል ወደ ፖለቲካ ከምገባ ወደ ፓርቲ መግባቱን ነው የምመርጠው። ከፓርቲው ደግሞ የመጀመሪያ ምርጫዬ የሚሆነው አንድነት ፓርቲ ነው” ዶ/ር ነጋሶ

“ኃይሌ እስካሁኗ ደቂቃ ድረስ በግሉ ወይም በፓርቲ ወደ ምርጫ መግባቱን እንኳ ግልፅ አላደረገም … ፖለቲካ በግል ፍላጎት ብቻ የተወሰነ አይደለም። ፖለቲካ እራሱን የቻለ ፖሊሲ መቅረፅ ያስፈልጋል። … ፖሊሲ ማስፈፀም የሚቻለው በፓርላማው አብላጫ ወንበር ሲያዝ ነው፤ … አንድ ሰው ብቻ ከሆነ ግን “አጃቢ” የመሆን አደጋ አለው። አቶ ገብሩ

“አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ የተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በክብር እንግድነት እንዲገኝ ጥያቄዎችን ባለመቀበል በአንፃሩ የገዢው ፓርቲ ደጋፊ በሆኑ ማህበራት ላይ በክብር እንግድነትና በንግግር አድራጊነት መገኘቱ የሚያመለክተው የኃይሌ የፖለቲካ ተሳትፎ በገዢው ፓርቲ ይሁንታ ያገኘ መሆኑ ነው … ወደ ፓርላማ ለመግባት የወሰነውም የግሉን ክብርና ዝና መሻት እንጂ አዳዲስ የፖሊሲ ኀሳቦችን በመያዝ (አይደለም)…” አቶ ሀብታሙ
_______________________________________________________

ዝነኛው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ ከሁለት ዓመት በኋላ በሚካሄደው በ2007ቱ ጠቅላላ ምርጫ አዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ በመወዳደር ወደ ፓርላማ ለመግባት ማቀዱን ይፋ አድርጓል።

አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ በግል ወይም በፓርቲ ውስጥ ገብቶ ለመወዳደር ግልፅ ባያደርግም ከሁለት ዓመት በኋላ በምርጫው ተሳታፊ በመሆን የፖለቲካ ጅማሮውን እውን እንደሚያደርግ አስታውቋል። በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን የኢትዮጵያ “ፕሬዝዳንት ይሆናል” የሚለውን ዘገባ በማስተባበል ፕሬዝዳንት መሆን ግን እንደማይጠላ ተናግሯል።

ታዋቂው አትሌት ይሄንን አስተያየቱን በግልፅ ከሰጠ በኋላ በውጪና በሀገር ውስጥ ጉዳዩ አነጋጋሪ ሆኖ ቆይቷል። የኃይሌን የፖለቲካ ተሳትፎ ከሀገሪቱ የፖለቲካ ባህል አለመዳበርና አስቸጋሪነት አንጻር እያነሱ የአትሌቱን ተሳትፎ አምርረው የተቹ እንዳሉ ሁሉ መግባቱንም የሚያበረታቱ አልጠፉም።

በሀገሪቱ ያሉ የፓርቲ አመራሮችም የሻለቃ ኃይሌን የፖለቲካ ተሳትፎ የተደበላለቀ ስሜት እንደፈጠረባቸው ከሰጡት አስተያየት መረዳት ተችሏል።

ሰንደቅ ካነጋገራቸው የፓርቲ አመራሮች መካከል የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ኃይሌ ወደ ፖለቲካ መግባቱ መብቱ ቢሆንም እንደስፖርቱ በፖለቲካውም የሚያንጸባርቅ አይመስለኝም ሲሉ ባልተለመደ ሁኔታ ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በሲዳማ ምድር የሠላም አየር መተንፈስ ጀመረ!!

መላው የሲዳማ ህዝብ በዘመነ ሺፈራው ሽጉጤ ግፊኛና አሳር የበዛበት አገዛዝ ከባድና ዘግናኝ እንዲሁም ጭካኔ የተሞላበት በደል ሲደርስበት ከርሟል ፡፡

1. የ አቶ ሽፈራው ሽጉጤን ስም ሲታነሱ ተደርሶባችኋል ተብሎ ሰዎች ከሥራ ይባረራሉ፤ ይታሠራሉ፤ ከሚወዱአቸው ቤተሰባቸው ይለያሉ ወይም

2. የአቶ ሽፈራው ሽጉጤን ወንበር ተቀናቅናችኋል ተብሎ ሰዎች ከሥልጣን ይባረራሉ፤ ይታሠራሉ /ያውም እድሜ ልክ እስራት/፤ ቤተሰባቸው ይበተናሉ እንዲሁም ለጎዳና ተዳዳሪነት ይዳረጋሉ፤

3. በአቶ ሽፈራው ላይ የግድያ ሙከራ አድርጋችኋል እንዲሁም ይህን አመለካከት ተሸክማችኋል ተብሎ ሕዝብ በሙሉ አውጣጭኝ ይቀመጣል፤ ገበረው፤ ነጋደው፤ ተማሪ፤ የመንግስት ሠራተኛ፤ ባለሥልጠኑ ይሳቀቃል/ ይሸማቀቃል፤ ኑሮውን ከሚመራበት መደበኛ ሥራው ይስተጓጎላል፤ እራሱንና ቤተሰቡን ለችግር ይጋለጥበታል፡፡
ከአውጣጭኙ በኋላ ብዙዎቹ እድሜ ልክና በብዙ ዓመታት ተፈርዶባቸው ሥቃይ ይቀምሳሉ፤ ይጎሳቆላሉ፤ ቤተሰባቸው ይበተናሉ፤

4. የማስፈጸም አቅም አላቸው ተብሎ የሚገመቱና በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ግለሰቦችን፤ በተለይ ምሁራንና ቀደም ተብሎ ህዝብን በቅንነት በማገልገል ልማት ያስመዝገቡትን፤ በደኢህዴን/ ኢህአዴግ የሚጨፈለቁ ህገ-መንግስታዊ የህዝብ መብቶች ላይ እንደእርሱ በሁለቱ እጃቸውና በሁሉቱ እግሮቻቸው የማያጨበጭቡትንና እንዲሁም በህግ በላይነት የሚያምኑትን አንጡራ የህዝብ ልጆችን ባጠቃላይ የመንግስት ጠላት ናቸው ብሎ በመፈረጅና በጀሌዎቹ በማስፈረጅ እንዲሁም ከፍ ብሎ በአዲስ አበባ ለተሰየሙ ለሥርዓቱ መሥራቾች በማዋጋት ሠርተው እንዳይኖሩ በማድረግ፤ በማሳደድ፤ በማሳሰር ወ.ዘ.ተ የሲዳማ ህዝብ ወላጂ መካን እንዲሆን አድርጓል፡፡

5. የሲዳማ ህዝብን ልማት ጎድቷል ፤ መሬቶቹን ለድንበርተኛ ህዝብ አሳልፎ ሽጦአል፤ የህዝብ ደም እንዲፈስና ሠላም እንዲደፈርስ አድርጓል፤ የሲዳማን ህዝብ ወዳጂ ህዝቦች ጋር የማጋጨት ሥራ ሠርቷል፡፡

6. በአጠቃላይ በአቶ ሺፈራው ሽጉጤ ቅኝ አገዛዛዊ ዘመን ሲዳማ በታሪክ የማይረሳውና ማንኛውም መድሃኒት የማይሽረው ጠባሳ ተፈጥሮበታል፡፡

ህዝቡ ባደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል ይህንን የመከራና የሥቃይ ማለትም የግንጥ አለንጋ የሆነውን ግፈኛ፤ ሕሊውና የሌሽ፤ ሰው መሳይ አውሬ ከሲዳማ ምድር በማባረር ያገኘውንና መተንፈስ የጀመረውን የሠላም አየር እያጣጣመ ለቀጣዩና ለዋነኛው ህገ-መንግስታዊ ክልል የመሆን ትግሉን አጠናቅሮ እየቀጠለ ይገኛል፡፡

ይሁንና አንዳንድ አድር ባይ አመራር ተብዬዎችና ከእርሱ ጋር የጋራ የሚነግዱ ነጋደዎች በራሱ የዘረፈውን ገንዘቡ የሚጠቀምበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ሽፋን ለመስጠት በሽኝት ስም ገንዘብ እየሰበሰቡለት መሆኑን ስለተደረሰባቸው መንግስት ለኪራይ ሰብሳቢነት አመቻቺ ባለሥላጠናትንና ነጋዴዎችን ከእኩይ ድርጊታቸው በመግታት የጀመረውን የኪራይ ሰባሳቢነት ዘመቻውን እንዲያጠናክር ከወዲሁ እናሳስባለን፡፡

by፡ Sidaamaho Maganu No

ምንጭ፡ ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Human Rights Groups: Donor Countries Fuel Abuse in Ethiopia


Selah Hennessy, VOA news

Published on July 23,2013
LONDON — Two new reports published this month say sustainable development in Ethiopia is impossible without a specific focus on human rights. The reports say donor countries should bear responsibility for ensuring their aid money is not used to fuel abuse.

Ethiopia receives billions of dollars in international aid every year. It is money that is used to help improve basic services like access to health and education.

But human-rights campaigners say there also is widespread abuse that takes place in Africa’s second most populous country. And they say donors need to face up to what role their aid money might play in fueling that abuse.

Leslie Lefkow, the deputy director for Human Rights Watch’s Africa Division, said, “The Ethiopian government is resettling large numbers of pastoralists and semi-pastoralist communities in the name of better services. But often this resettlement process is accompanied by very serious abuses.”

የወያኔ የውስጥ ለውስጥ ሽኩቻ አሁንም አነጋጋሪ ነው::



  • የአውሮፓ ልኡክ ቡድን ቃሊቲን እንዳይጎበኝ ትእዛዝ ያወረደው ደብረጺሆን ነው::
  • በረከትን እና አዜብን ከነቡድናቸው በሙስና ለመጥለፍ ታቅዶ ነበር::


ወያኔ ለሁለት የተከፈለው ቡድን በአቶ ስብሃት በኩል ያለው በሃገር ቤት ያሉትን ወታደሩን እና ደህነንቱን በድጋፍ መልክ የያዘ ሲሆን የነበረከት ቡድን ደሞ አስተዳደራዊ ባለስልጣናትን እና የውጪ ሃይሎችን የሙጥኝ ብሏል:: በተለያየ ጊዜ የነበረከት ቡድን ቡድን ሃሳብ ለማስቀየር ሲሰራ የነበረው እና የሞከረው የሳሞራ የኑስ የስብሃት ደጋፊ መሆኑ ታውቋል::

የአቶ መለስ ዜናዊን ሞት ተከትሎ የበረከት እና የኣዜብ ቡድን የመንግስት ቁልፍ መዋቅሮችን ለመቆጣጠር እያደረገው መፍጨርጨር እና በአቶ ስብሃት ነጋ እና በአቶ አባይ ጸሃዬ ጥምር አመራር በሃገሪቱ ህግ እና ባለስልጣናት ላይ እያደረገ ያለው ጫና እና ተጽእኖ አነጋጋሪ እየሆነ መቷል::

የአቶ ስብሃት ቡድን የመረጃ ባለስልጣኑን ደብረጽዮን እና የስለላ መዋቅር አናት የሆነውን ጌታቸውን በመያዝ በሃገሪቱ አስተዳደራዊ ሂደቶች ላይ ከፍተኛውን ሚና እየተጫወቱ ሲገኙ በአሁኑ ወቅት ሃይለማርያም ምንም ምርጫ ስለሌለው በቅርብ እየተከታተለው የሚገኘውን የደብረጽዮንን ትእዛዝ እያስፈጸመ ሲሆን ይህ የሚያሳየውበሃገሪቱ ላይ እየተካሄደ ያለውን ቡድናዊ አምባገነነት ስብሃት እየመራው መሆኑን ይጠቁማል::

በወያኔ መዋቅር ውስጥ በከፍተኛ ፍርሃት ባለስልጣናት የሚመለከቷቸው እነ አቶ ስብሃት ነጋ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲ አማካሪ ሆኖ የተሾመውን በረከት ስምኦንን በፍርሃት ወጥመድ ውስጥ በመክተት ከጨዋታው ውጭ እያደረጉት ሲሆን የስብሃት ቡድን እየሰራ ያለውን ስራ ተከትሎ በሁለቱ ጎራዎች መካከል ከፍተኛ የሆነ የመዘላለፍ እና የመዛዛት ሁኔታዎች እስከመከሰት መድረሱ ታውቋል::

ዶ/ር ነጋሶ መድረክን በተመለከተ ከፓርቲያቸው የተለየ አቋም ይዘዋል

v  መድረክን ወደ ጥምረት /ቅንጅት ማውረድ አይጠቅምም
v  መድረክን ወደ ውህድ ፓርቲ መግፋቱ ጠቀሜታው አልታየኝም

በዘሪሁን ሙሉጌታ

የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በመድረክና አንድነት መካከል ስላለው ግንኙነት ለመጀመሪያ ጊዜ የግል አቋማቸውን ይፋ አደረጉ። ዶ/ር ነጋሶ በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ በላኩት ፅሁፍ መድረክን በተመለከተ የተለየ አቋም መያዛቸውን አረጋግጠዋል።

ዶ/ር ነጋሶ “የግንባርነት መስፈርትና መድረክ” በሚል ርዕስ ለሰንደቅ በላኩት ፅሑፍ መድረክን ወደ ጥምረት/ ቅንጅት ማውረድ እንደማይጠቅም እንዲሁም መድረክን ወደ ውህድ ፓርቲ መግፋቱ ጠቀሜታው አልታየኝም ሲሉ የግል አስተያየታቸውን ገልጸዋል።

የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት በቅርቡ “የአንድነት /መድረክ የፖለቲካ ግንኙነት እና የጋራ እንቅስቃሴ ከመቀናጀት እስከ ግንባር ያለው አጠቃላይ ሁኔታ ግምገማ” በሚል ባቀረበው የግምገማ ሰነድ ላይ መድረክ “ግንባር” የሆነበት አካሄድና ውሳኔ በአግባቡ ያልተመከረበት መሆኑን በመጥቀስ እንደገና ውይይት እንዲደረግ ከጠየቀባቸው ጉዳዮች አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
በግምገማ ሰነዱ ላይ መድረክ የአባል ፓርቲዎችን ፕሮግራም በማቀራረብ አንድ ወጥ የሆኑ ፓርቲ ሆነው የሚወጡበትን ዕድል መፍጠር ካልቻለ ትርጉም ያለው ስብስብ ይሆናል ተብሎ እንደማይጠበቅ መግለፁ አይዘነጋም።

ይሁን እንጂ ዶ/ር ነጋሶ መድረክ ሰፊ (Broad) ግንባር መሆኑን፣ በምርጫ ኢህአዴግ ቢሸነፍ እንኳ ኢህአዴግን ጨምሮ ከሌሎች ፓርላሜንታዊ ፓርቲዎች ጋር ብሔራዊ አንድነት መንግስት ለማቋቋም መወሰኑን ጠቅሰዋል።

በተያያዘ የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት ቀደም ሲል በቀረበው ሰነድ ላይ የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚ ከሶስት ወር በኋላ የደረሰበትን ሁኔታ እንዲያሳውቅ ባዘዘው መሠረት በቀጣይ ቀናት በጉዳዩ ላይ ውይይት እንደሚደረግ ለፓርቲው ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልፀዋል።

የአንድነት/መድረክ ግንኙነት በመስከረም ወር በሚካሄደው የአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በስፋት ከሚነሱ አጀንዳዎች ግንባር ቀደም ሊሆን እንደሚችልም ይጠበቃል።(ከዶ/ር ነጋሶ ጋር የተደረገው ቃለምልልስ እንደሚከተለው ቀርቧል)

የግንባርነት መስፈርትና መድረክ
በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ
የግል አስተያየት

በግንቦት ወር በአንድነትና በመድረክ መካከል ይፋዊ ውይይት ተከፍቷል፤ ቀጥለውበታልም። በዚህ ውይይት ውስጥ እስከ ዛሬ ድረስ አስተያየት አልሰጠሁም። በአንድነት ውስጥ ግን በግሌ ያለኝን አቋም፣ አመለካከትና አስተያየቶችን ማንፀባረቄ አልቀረም። በግሌ ሳንፀባርቃቸው የነበርኳቸውን አቋሞች፣ አመለካከቶችና አስተያየቶችን በጽሑፍም ለማስቀመጥ እሞክራለሁ።

የፓርላማው ውይይት መታፈኑን በይፋ ያጋለጠው ጋዜጠኛ ከስራ ተሰናበተ


የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት “የዴሞክራሲ ተቋማት ሚናና የአስፈፃሚ ተቋማት ኃላፊነት” በሚል ጥቅምት 23 ቀን 2005 ዓ.ም ያደረገውን ውይይት በኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በኩል ተቆራርጦና ተዛብቶ እንዲተላለፍ ተደርጓል በሚል አንድ ዜና መዘገቡ ይታወሳል።


ይህን ዜና በሰንደቅ ጋዜጣ የህዳር 5 ቀን 2005 ዓ.ም ዕትም “ኢቲቪ የከፍተኛ ባለሥልጣናትን ውይይት በማፈን ተወቀሰ” በሚል ርዕስ ከቀረበ በኋላ፤ በዚህ ዘገባ ላይ ተመድቦ የሠራው የቀድሞ የኢቲቪ ባልደረባ ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ ረቡዕ ህዳር 12 ቀን 2005 ዓ.ም በጉዳዩ ላይ ለዝግጅት ክፍላችን ምላሹን ሰጥቷል።

እነዚህ ዘገባዎች ከተስተናገዱ በኋላ፣ ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ ለሰንደቅ ጋዜጣ መረጃ እንደሰጠና ሚስጢር እንዳወጣ ተቆጥሮ የዲስፒሊን ክስ ቀርቦበታል። ኢ.ሬ.ቲ.ድ በዲስፒሊን ክሱ ላይ  አራት ከፍተኛ የሥራ አመራሮች በምስክርነት ዘርዝሮ አቅርቧል። የድርጅቱ የዲስፒሊን ኮሚቴ በከሳሽ በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እና በጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ መካከል የክስ ዝርዝር እና የመልስ መልስ ደብዳቤዎች ሲያዳምጥ ከሰነበተ በኋላ ግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም በቁጥር ቴ02.1/131-304/02/8/ በተፃፈ ደብዳቤ ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ  ከግንቦት 10 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ከሥራ የሚያሰናብተውን ቅጣት አሳልፏል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ባለቤትነት በጠ/ሚኒስትሩ ቢሮ ጥቅምት 23 ቀን 2005 ዓ.ም የተካሄደው ስብሰባ በመልካም አስተዳደር፣ በተጠያቂነት፣ በሙስና ችግሮችና በመሳሰሉት ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት የተካሄደ ሲሆን በዚህ ውይይት ላይ የኢፌዲሪ ምክትል ጠ/ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨምሮ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈጉባኤ አቶ አባዱላ ገመዳ፣ በሚኒስትር ማዕረግ የስኳር ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይ ፀሐዬ፣ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል፣ የእምባ ጠባቂ ተቋም ዋና እምባ ጠባቂ ወ/ሮ ፎዚያ አሚን፣ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን፣ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አበባው ስጦታው እና ሌሎችም የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር።

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የጠራውና የአስፈፃሚ አካላትና የዴሞክራሲ ተቋማት ሚናን በተመለከተ የተደረገው ውይይት፣ በዕለቱ በሥፍራው ባልነበረ ጋዜጠኛ ተገቢ ባልሆነ መልኩ ተቆራርጦና ተዛብቶ ለሕዝብ መቅረቡ ትክክል እንዳልነበረ በይፋ በመግለፁ ምክንያት ከሥራ የተሰናበተው የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ባልደረባ የነበረው ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻን ስለሁኔታው ፋኑኤል ክንፉ አነጋግሮታል።

ሰንደቅ፡- የዚህ ዜና መነሻ አንተን አድርገው ለመውሰድ ያስቻላቸው ምክንያቶች ምንድን ናቸው?

ጋዜጠኛ አዲሱ፡- ይህን ምላሽ መስጠት የሚችሉት እነሱ ናቸው። በሰጡኝ የክስ ዝርዝር ላይ ግን ሌላ ምክንያት ነው ያስቀመጡት። ወይም ደግሞ ላነሳኸው ጥያቄ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችለው የዚህ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ብቻ ነው።

ሰንደቅ፡- እንዴት?

ጋዜጠኛ አዲሱ፡- ምክንያቱም “ኢቲቪ የከፍተኛ ባለሥልጣናትን ውይይት በማፈን ተወቀሰ” ለሚለው ዜና መነሻ ለሰንደቅ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል በእኔ በኩል ያልኩትም አንዳች ነገር የለም። እንደማንም አንባቢ ይህ ዜና በሰንደቅ ጋዜጣ ከወጣ በኋላ ነው የተመለከትኩት። ስለዚህም መረጃ ከእኔ አግኝታችሁ ከሆነ አግኝተናል፤ ካላገኛችሁ አላገኘንም ለሚለው ምላሽ መስጠት የሰንደቅ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ይመስለኛል።

Tuesday, July 23, 2013

የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ETV ከዩቲዩብ (Youtube) ተባረረ




(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በዩቱዩብ የተለያየ ፕሮፓጋንዳዎቹን የሚያስተላልፍበት የዩቲብ ቻናል ተዘጋ። ዩቲዩብ ኢትዮጵያ ቴሌቭዥንን ማባረሩን የገለጸበት መልዕክት “YouTube account ethiopiantv has been terminated because we received multiple third-party notifications of copyright infringement from claimants including: David Tesema” ይላል።


ከዚህ ቀደም በቴሌቭዥን ጣቢያው የአፍሪካ ዋንጫን ሰርቆ በማስተላለፍ የሃገሪቱን ስም አንገት ያስደፋው የኢትዮጵያ ቲሌቭዥን አሁንም ከዩቲዩብ የተባረረው በተደጋጋሚ በኮፒ ራይት ሲመከርና ማስጠንቀቂያ ሲሰጠው አልሰማ በማለቱና ከድርጊቱም ባለመቆጠቡ እንደሆነ የዩቲብ አሰራር ያመለክታል።

ኢቲቪ ለዘፋኞች 5 ሳንቲም ክፍያ ሳይከፍል ሥራዎቻቸውን በሕብረትርዒት ላይ እንደሚያቀርብ፤ የውጭ ሃገር ፊልሞችንም ምንም ክፍያ ሳይፈጽም በታላቅ ፊልም ላይ እንደሚያሳይ የሚታወቅ ሲሆን ይህን ስርቆቱን በመቀጠል ዩቲዩብ ላይ ገንዘብ ለማካበትና ፕሮፓጋንዳውን ለማስተላለፍ መጠቀሙ እንዲባረር ምክንያት ሆኗል።

የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የዩቲዩብ ቻናል ከፕሮፓጋንዳዎች በተጨማሪ ለአርቲስቶች ክፍያ የማይፈጸምባቸው ድራማዎች፣ ዘፈኖች፣ አስገራሚ ታሪኮችና ሌሎችም ይቀርቡበት ነበር። ይህን የሰሙ አስተያየት ሰጪዎች”ሕዝብን መስረቅ የለመደ መንግስት በኢንተርኔት እሰርቃለሁ ሲል እጅ ከፍንጅ ተያዘ” ሲሉ ተሳልቀዋል።

ዘ-ሐበሻ በተደጋጋሚ ወደ ኢቲቪ የዩቲዩብ ቻናል በመሄድ እንዳረጋገጠቸው አካውንቱ ሲከፈት YouTube account ethiopiantv has been terminated because we received multiple third-party notifications of copyright infringement from claimants including: David Tesema” ይላል። ይህን ለማረጋገጥም፦

ZEHABESHA

የመንግስትን የሃይማኖት ጣልቃ ገብነት የሚያሳይ ተጨማሪ ሰነድ ተገኘ

የመንግስትን የሃይማኖት ጣልቃ ገብነት የሚገልጹ ተጨማሪ ሰነዶች በእጃችን ገቡ፡፡ ሰነዶቹ በ2004 መጀመሪያ አካባቢ ሲደረጉ የነበሩ የአሕባሽ ስልጠናዎች ዋነኛ አስተባባሪ እና አዘጋጅ መንግስት መሆኑን ያሳያሉ፡፡ በሰነዱ ላይ እንደተመለከተው በወቅቱ ይሰጥ ነበረው ስልጠና በመንግስት ሚዲያዎች እንደተገለጸው በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት አዘጋጅነት ብቻ ሳይሆን በመንግስትም ጭምር የተዘጋጀ እንደነበር ያሳያል፡፡ ‹‹የኢ/እ/ጉ/ጠ/ም/ቤት (መጅሊስ) ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የአህለሱናንና የሃይማኖት (የዲን) አስተምህሮት በተቀላጠፈ ሁኔታና ፍጥነት ለማካሄድ እንዲቻል የ200 አሰልጣኞች ስልጠና ለአንድ ወር (30) ለማካሄድ የሚያስፈልግ ዝርዝር የወጪ ግምት ለመጠቆም ተዘጋጅቶ የቀረበ ፕሮፖዛል›› በሚል ርእስ በቀረበው ይኽው ሰነድ ላይ፤ መንፈሳዊ የተባለው የአህለ ሱንና ስልጠና በመንግስት አዘጋጅነት የተካሄደ መሆኑን ያሳያል፡፡

መንግስት ከአሕባሽ ስልጠና ጋር በተያያዘ እጁ እንደሌለበትና የድርጊቱ ባለቤት መጅሊሱ እና ኡለማ ምክር ቤቱ መሆናቸውን ደጋግሞ ሲገልጽ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን ሟች ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህንኑ እውነታ ክደው በፓርላማ ንግግር ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡ ሆኖም በተለያዩ ጊዜያት ከመንግስት ባለስልጣናትና ከመጅሊሱ ቢሮዎች አፈትልከው የወጡ የሰነድ ማስረጃዎች መንግስት ነውጠኛውን የአሕባሽ አስተምህሮ በግድ በሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ ለመጫን ሐሳብ ከማመንጨትና ጥናት ከማድረግ አንስቶ እስከትግበራው ድረስ ዋነኛው ተዋናይ እንደሆነ አሳይተዋል፡፡ በቪዲዮ እና በድምጽ የተገኙ ማስረጃዎችም እውነታውን በዛ መልኩ ሲገልጡ ቆይተዋል፡፡

ይኸው አሁን የተገኘውም ሰነድ ከዚህ በፊት በስፋት ህብረተሰቡ የሚያውቀውን እውነት የሚያጠናክርና መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ መግባት የሚከለክለውን ሕገ መንግስት በመጣረስ በሃይማኖት ውስጥ መጤ አስትምህሮ እንዲነግስና ሙስሊም ዜጎችም በዚህ ምክንያት ለችግር እንዲዳረጉ ጥረት እያደረገ መቆየቱን አመላካች ነው፡፡ ለተባሉት ስልጠናዎች የፋይናንስ ወጪ የሚያደርገው መንግስት መሆኑንና ለመጅሊሱ ገቢ ተደርጎለትም በመጅሊሱ በኩል ወጪ እንደሚደረግ ከዚህ በፊት የወጡ ተመሳሳይ ሰነዶች ማመላከታቸው አይዘነጋም፡፡ በተጨማሪም ስልጠናው ለሚካሄድነትና የመንግስት ተቋም ለሆነው ኢትዮጵያ ፖሊስ ኢንስቲትዩት ለዝግጅቱ ማሳኪያ የሚረዳ ገንዘብ ለኢንስቲትዩቱ ገቢ እንዲሆን የተጠየቀበትና ገቢ የሆነባቸውም ሰነዶች በእጃችን ገብተዋል፡፡

Monday, July 22, 2013

ወያኔ የቀረበውን የሚያደማ እሾህ ነው! ሼህ ይማም ኑሩን ማን ገደላቸው?

በምርጫ 97 ማግሥት “ድምፃችን ይከበር” በማለታቸው ከሁለት መቶ በላይ ንፁሀን ዜጎች በግፍ መጨፍጨፋቸው በተነሳ ቁጥር የወያኔ ሹማምንት ከሰልፈኞቹ መሀል መሣሪያ የታጠቁ እንደነበሩና ሦስት ፓሊሶችም መገደላቸውን ይናገራሉ። የእነዚያ ፓሊሶች ሞት አሳዛኝ አውነት ሲሆን አሟሟታቸው ግን ጉዳዩን እንዲያጣራ ለተቋቋመው አጣሪ ኮሚሽን እንኳን ምስጢር ነው። ለጊዜው እውነት ተዳፍናለች፤ ፍትህ ተረግጣለች። ጊዜው ሲደርስ ግን የፓሊሶቹ አውነተኛ ገዳይ መውጣቱ አይቀርም። ይኽ ዛሬ ምስጢር የሚመስለን የሦስቱ ፓሊሶች አሟሟት “ንፁሀን ዜጎችን ለመፍጀት ሰበብ ለማግኘት ሲባል በሥራ ገበታቸው ላይ በነበሩ የፓሊስ አባላት የተፈፀመ አጅግ መሠሪና አስነዋሪ ወንጀል” ተብሎ የሚጠቀስበት ወቅት ይመጣል። ይህ የወያኔ ድርጊት ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርገው የአንድ ወቅት የተናጠል ክስተት አለመሆኑ ነው።

ከአሜሪካ ኤምባሲዎች ሾልከው የወጡ በርካታ ሰነዶች የተዘረገፉበት ዊኪሊክሰ በተሰኘው ድረገፅ የተገኙ መረጃዎች እንደሚያረጋግጡት ወያኔ ሰዎችን ገደሎ በተቃዋሚዎች እንደሚያላክክ አሜሪካ ታውቃለች። ከእነዚህ ሰነዶች አንዱ – ለምሳሌ – ወያኔዎች ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ ቦንብ አፈንድተው በተቃዋሚዎች ማሳበባቸው ተብራርቷል።

Press Release: USCIRF Calls on Ethiopia to Release Religious Freedom Advocates on Trial, July 22, 2013

FOR IMMEDIATE RELEASE

July 22, 2013 | by USCIRF

WASHINGTON D.C. -- On the one-year anniversary of the crackdown on Muslim protestors for peacefully advocating for their religious freedom rights, the U.S. Commission on International Religious Freedom (USCIRF) calls on the Ethiopian government to release 29 individuals who have been detained and put on trial.  

In July 2012, the government arrested hundreds of Muslims peacefully demanding that it cease interfering in their religious affairs and allow their community to vote freely for representatives on the Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council (EIASC).  While most were released, 29 were charged on October 29, 2012 under the government’s Anti-Terror Proclamation, accused of “intending to advance a political, religious or ideological cause” by force and the “planning, preparation, conspiracy, incitement and attempt of terrorist acts.”  It was the first time that Ethiopia’s terrorism law was used in connection with a religious freedom issue.

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት እና የአንድነት መሪዎች እንደ ጋንዲ!

ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)

ሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2005 ዓ.ም.

የሚሊዮኖች-ድምጽ-ለነጻነት የሚለው ስትራተጂካዊ ዘመቻ ግቡ ምን እንደሆነ እና እድሜው ሶስት ወሮች እንደሚሆን አንድነት ፓርቲ ግልጽ አድርጓል። ከመግለጫው እንደተረዳሁት አንድነት ፓርቲ ጊዜ ወስዶ ብዙ አውጥቶ እና አውርዶ ያሰላው ለነፃነት እና ለዴሞክራሲ የሚደረግ ዘመቻ ነው። አንድ ነገር ግልጽ መሆን የጀመረ ይመስለኛል። ከንዋዮች መንግስት ፍንቀላ ጀምሮ ኢትዮጵያችን ለ50 አመቶች ያህል ብዙ ህይወት እየከፈለች በፖለቲካ ስርዓት ለውጥ ትግል ጎዳና ስትወድቅ እና ስትነሳ ከርማ ዛሬ ትክክለኛውን ወደ ዴሞክራሲMillions of voices for freedom - UDJ የሚያደርሳትን ጎዳና ያገኘችው መሰለኝ። ወደፊትም መውደቅ መነሳት ሊኖር ይችላል። መንገዱም አልጋ ባልጋ አይሆንም። ይሁን እንጂ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ ኢትዮጵያ ትክክለኛውን ጎዳና ማግኘቷን አብስሯል። የዚህ ዘመቻ ስሌት የፖለቲካ ትግል ባህላችንን እድገት ያመለክታል። የስልጣኔም ምልክት ነው። የሚሊዮኖች-ድምጽ-ለነፃነት ዘመቻ በርቀት ብርሃን አሳይቷል። በዚህ ጉዳይ ላይ ሶስት ተከታታይ ክፍሎች ያሉት ጽሑፍ በማቅረብ የተሰማኝን ለአንባቢ አጋራለሁ። ክፍል ሁለት በሽብር ህግ እና በሽብርተኛነት በታሰሩት የሰላማዊ ትግል ሐዋርያት ዙሪያ ያተኩራል። ክፍል ሶስት ደግሞ ዛሬ በመካሄድ ላይ የሚገኘውን የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ እና ወደፊት የሚካሄዱ ተመሳሳይ ዘመቻዎችን ከብክለት እና ከውድቀት ለመጠበቅ ይረዳሉ የምላቸውን ምክሮች አንድ ሁለት እያልኩ ለአንባቢ አቀርባለሁ። ክፍል አንድ ግን የፖለቲካ ትግል ባህል ሽግግር በማድረግ ላይ መሆናችንን እንደሚከተለው ያቀርባል።

የትናንቱ እንደሚከተለው ነበር። የገደልን እኛ (The People)። የሞትን እኛ (The People)። የትግሉ እና የድሉ ባለቤት ግን እርስ በርስ ካጫራሱን ቡድኖች ውስጥ በጦርነቱ የቀናው ቡድን ሲሆን የመሰረተው መንግስት ደግሞ የጋራ አገራችንን የግል የጓሮ እርሻው ያደረገ እና ከቀድሞው የከፋ ሽብርተኛ አምባገነን ነው የሚል ነበር የትናንት የፖለቲካ ትግላችን ታሪክ። የትናንቱ የፖለቲካ ለውጥ ትግል ጎዳና በጦርነት የተሞላ ነበር። ብዙ ትምህርት ቤቶች ፈርሰዋል። መንገዶች ወድመዋል። የጦር ካምፖች እና የጦር መኪናዎች ጋይተዋል። ያ ሁሉ የኛ ንብረት ነበር። በህዝባችንም መካከል መቃቃር እና ክፍፍል እያደገ እንዲሄድ በማድረጉ የተወሰኑት ጥለውን እንዲሄዱ እና ከቀረነው ውስጥም ወደ ውጭ የሚመለከቱ እንዲፈጠሩ አድርጎ አንድነታችንን ክፉኛ አዳክሟል የትናንቱ የፖለቲካ መንገዳችን። አዲሱን አምባገነን መንግስት አብዣኛው የአገሪቱ ዜጎች ህጋዊ አድርገው ስለማይቆጥሩት እሱ ስልጣን የጨበጠበትን የመጨራረስ አዙሪት ጉዞ እንድንደግም የሚሰብኩን አዳዲስ ቡድኖች ተፈጥረዋል። የፖለቲካ ትግል ባህላችንም ቢሆን በመገዳደል ደም የተጨማለቀ በመሆኑ የመንግስት ስልጣን የጨበጡት ግለሰቦች ስብዕናቸው የተሟጠጠ ነው። ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ደግሞ በስልጣን ላይ የሚገኙት መሪዎች ፖለቲካ ባህል ከደም መጽዳት እና ስብዕናቸው የተሟላ መሆን ወሳኝ ነው። ባጭሩ ከሶስት ሺ አመቶች በላይ አብሮን የቆየው የፖለቲካ ትግል ባህላችን ከዴሞክራሲ ጋር ጸበኛ ነው።

‘የአረቡ ዓለም አብዮት ኢትዮጵያ ውስጥ ይመጣል ብለህ ታስባለህ ብለው ጠይቀውኛል” – ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

ዝግጅቱ የነበረው አሜሪካ ኤምባሲ ውስጥ ነው፡፡ ጥሪውም የደረሰን በአሜሪካ ኤምባሲ በኩል ነው፡፡ የተነገረኝም ቀደም ብሎ ነው፡፡ ከሦስት ሣምንት ወይም ከአንድ ወር ቀደም ብሎ ነው፡፡ ጊዜውን በትክክል ስለማላስታውሰው ነው፡፡ እኛ በዛ መሠረት ስብሰባውንም ይመሩ የነበሩት የአሜሪካ አምባሣደር ነበሩ፡፡ ስለዚህ እኔ የደረስኩት ግማሽ ላይ የእነሱ ስብሰባ እያደረጉ /አመታዊ ስብሰባ/ የለጋሽ ሀገሮች ስብሰባ፡፡ ስለዚህ ለኛ የተያዘው ፕሮግራም ከዘጠኝ ሰአት እስከ 10፡30 ነበር፡፡ እና የአሜሪካ አምባሣደር ንግግር እንዳደረጉ የእለቱ ልዩ እንግዳቸው እንደሆንኩ ካስተዋወቁ በኋለ ይዤ የቀረብኩትን ንግግር አቀረብኩ፡፡
ይዤ የቀረብኩት ፅሁፍ መጀመሪያም ስጋበዝ እንደተናገረኝ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ፖለቲካና ቀጠናው ላይ ነው፡፡ በተለይም ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ወደፊት ምን ሊያደርግ አስቧል እንደ አንድ አማራጭ የፖለቲካ ኃይል ሲመጣ ይዟቸው የተነሣቸው መሠረታዊ ሀሣቦች ዝርዝር የፖሊሲ አማራጮች ምንድን ነው የሚለውን አጠቃላይ የሆነውን የመጨረሻ እይታ ለማሣየት ነው የሞከርኩት፡፡ አቅጣጫውን የኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ አሠላለፍ ፣ የመንግስትን እርምጃዎችና ከ1997-2005 የሆኑትን ነገሮችን በእኛ እቅድ ላይ ያሉትን አጠቃላይ ሁኔታዎች ለማሣየት እንዲሁም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ ናት፡፡ የምስራቅ አፍሪካ ውስጥ ትልቅና የረጋ የብሔር ስብስብ ነው ያለው፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ሰላሙና ኃይሉ ለምስራቅ አፍሪካ ቅርብ ነው፡፡ ሜድትራኒያን አለ፣ ቀይ ባህር አለ፣ አባይ አለ፡፡ ሁለተኛ ነገር ይሄ ሽብርተኝነት የሚባለው ነገር አለ፡፡ ነዳጅ አለ እነዚህ ሁሉ ያሉበት ቀጠና ስለሆነ፣ እንደ አንድ የፖለቲካ አማራጭ ስንመጣ እንደዚህ ያሉት ችግሮች ሁሉ አጠቃላይ የሆነ እይታ ሊኖረን እንደሚችል ጠይቀውኛል፡፡ እኔም በፅሁፌ አብራርቻለሁ፡፡

ሀገራችን ኢህአዴግ አክራሪነትን እንደሚያሰሰጋት ተሰጋ!





ሀገራችን ኢህአዴግ አክራሪነትን እንደሚያሰሰጋት ተሰጋ!

ይቺ ጨዋታ ፍትህ ጋዜጣ አዲስ ታምስ መጽሄት ከዛም ልዕልና ጋዜጣ ባደረጉት መተካካት አሁን ተራውን ለተቀበለችው አዲሲቱ ፋክት መፅሄት የተላከ ነው፡፡ እስቲ የድረ ገፃችን አንባቢዎች ደግሞ ከተመቻቸው ያንበቧት ተብላ የተለጠፈች ናት!

ርዕሴ እንዳይረዝምብኝ ሰግቼ ነው እንጂ፤ “ሀገራችን ኢህአዴግ አክራሪነት እንደሚሰጋት  ተሰጋ (ድርብ ሰረዝ) ሁላችንም ይሄንን ጉዳይ እንዋጋ (አሁንም ድርብ ሰረዝ) ኋላ ይቆጨናል ሲያስከፍለን ዋጋ…(ቃል አጋኖ)  ብለው ደስ ይለኝ ነበር፡፡

እንግዲህ ጥናት አትኚዎች እና ምርምር አድራጊዎች ከፈለጉ ተመራምረው የምለውን “ፉርሽ” ያድርጉት እንጂ የእኔ አነስተኛ ጥናት ግን በአሁኑ ሰዓት ሀገሪቷን በጣም እያሰጋት ያለ አንድ አደገኛ ነገር እንዳለ አመላክቶኛል፡፡ እርሱም ኢህአዴግ አካራሪነት ነው፡፡

በተደጋጋሚ ኢህአዴግዬ እንደነገረችን ሀገራችን የኃይማኖት አክራሪነት ያሰጋታል ተብለናል፡፡ አረ ምን መባል ብቻ በዚህ የተነሳ የተለያዩ እርምጃዎች እና እርግጫዎች እየተወሰዱብን አይደል እንዴ…

Sunday, July 21, 2013

የእስክንድር ነጋ ደብዳቤ ከቃሊቲ እስር ቤት ለባራክ ኦባማ የተፃፈ


                     



                  ግልፅ ደብዳቤ ለኦባማ አስተዳደር!

                                 እስክንድር ነጋ
 
                             ከቃሊቲ እስር ቤት




 ሁላችንም እንደምናውቀው በሀያኛው ክፍለ ዘመን የመጨረሻ ዓስርታት በተለያዩ ክፍለ አህጉራት ውስጥ ባለ ታዲጊ ሀገር  ህዝቦች የተነሱ የፖለቲካ እና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች በቀዳሚነት በጠመንጃ ኃይሌ የተደገፉ ነበሩ፡፡ ኢትዮጵያም በተመሳሳይ  የታሪክ ክስተት ማለፏን የሚመሰክረው ዛሬም ወታደራዊ ስርዓቱን ብቻ ሳይሆን፣ ይህንን መንገዴ የመረጡትን ጥቂት  የተቃዋሚ ድርጅቶችንም በጦር ኃይል ድል አድርጎ ስልጣን ላይ ያለው ኢህአዴግ መሆኑ ነው፡፡ ይሁንና የቀዝቃዛው ዓለም  ጦርነት ማብቃትና የአሜሪካ ብቸኛ ሌዕለ ሀያል ሀገር ሆኖ መውጣት በኃይል የሚደረጉ ‹‹ፀረ-አምባገነን›› ንቅናቄዎች  ሰላማዊውን መንገዴ ብቻ እንዲከተሉ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡ የለውጡም ዋነኛ መፍትሄ አሜሪካ ለሰላማዊ ትግል  የምትሰጠው ከፍ ያለ ቦታ ብቻ ሳይሆን የምታደርገው እገዛም መሆኑ አከራካሪ አይደለም፡፡ በእርግጥ የአሜሪካ አስተዳደር  በሰላማዊ ትግል ላይ ያለው አቋምና ለትግሉ የሚያደርገው ቀጥተኛ አበረታችነት የሀገሪቱ መስራች አባቶች ካነፁት የሞራሌ እና  የፖለቲካ እሴት እንደሚነሳም አውቃለሁ፡፡  

 ሙሉውን ደብዳቤው ሊንኩን በመጠቀም ዳውን ሎድ በማድረግ ያንብቡት!

https://docs.google.com/file/d/0B6jhgT-afGuONWtmWlBWeXBqWGM/edit?pli=1

Girma Wolde-Giorgis Net Worth




Net Worth:  Stats $1.5 Million

Source of Wealth:Government and Politics

Girma Wolde-Giorgis Age:88years old

Girma Wolde-Giorgis Birth Place: Addis Ababa, Ethiopia

Girma Wolde-Giorgis Marital Status: Married






Girma Wolde-Giorgis net worth: Girma Wolde-Giorgis is the President of Ethiopia who has an estimated net worth of $1.5 million. Born on December 8, 1924 in Addis Ababa, Ethiopia, he attended an Ethiopian Orthodox Church school first then the Teferi Mekonnen School which was later renamed Scuola Principe di Piemonte or Prince of Piedmonte School. From 1942 to 1944, he received certificates in Management (in Holland), in Air Traffic Management (in Sweden), and Air Traffic Control (in Canada) under a training program sponsored by the International Civil Aviation Organization.

ብርቱ ሰው! (The Iron Man) – (ከተመስገን ደሳለኝ)

ሁላችንም እንደምናውቀው በሀያኛው ክፍለ ዘመን የመጨረሻ ዓስርታት በተለያዩ ክፍለ አህጉራት ውስጥ ባሉ ታዳጊ ሀገር ህዝቦች የተነሱ የፖለቲካ እና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች በቀዳሚነት በጠመንጃ ኃይል የተደገፉ ነበሩ፡፡ ኢትዮጵያም በተመሳሳይ የታሪክ ክስተት ማለፏን የሚመሰክረው ዛሬም ወታደራዊ ስርዓቱን ብቻ ሳይሆን፣ ይህንን መንገድ የመረጡትን ጥቂት የተቃዋሚ ድርጅቶችንም በጦር ኃይል ድል አድርጎ ስልጣን ላይ ያለው ኢህአዴግ መሆኑ ነው፡፡ ይሁንና የቀዝቃዛው ዓለም ጦርነት ማብቃትና የአሜሪካ ብቸኛ ልዕለ ሀያል ሀገር ሆኖ መውጣት በኃይል የሚደረጉ ‹‹ፀረ-አምባገነን›› ንቅናቄዎች ሰላማዊውን መንገድ ብቻ እንዲከተሉ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡



የለውጡም ዋነኛ መግፍኤ አሜሪካ ለሰላማዊ ትግል የምትሰጠው ከፍ ያለ ቦታ ብቻ ሳይሆን የምታደርገው እገዛም መሆኑ አከራካሪ አይደለም፡፡ በእርግጥ የአሜሪካ አስተዳደር በሰላማዊ ትግል ላይ ያለው አቋምና ለትግሉ የሚያደርገው ቀጥተኛ አበረታችነት የሀገሪቱ መስራች አባቶች ካነፁት የሞራል እና የፖለቲካ እሴት እንደሚነሳም አውቃለሁ፡፡

ዝርዝሩን ጽሁፍ ሊንኩን በመጫን ያንብቡ: http://www.ethiomedia.com/2013report/bertu_saw.pdf

የፀረ ሙስና ትግሉን ለመቀልበስ ያደፈጡ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መኖራቸው ሥጋት ፈጥሯል!!

መንግሥት ሙስናን እየተዋጋ የሚያስመስሉ ምልክቶች ቢስተዋሉም፣ የፀረ ሙስና ትግሉን ለመቀልበስ ያደፈጡ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መኖራቸው ሥጋት ፈጥሯል፡፡

የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሙሰኞችን በተመለከተ ሲናገሩ፣ ‹‹ወይ እነሱ ያሸንፋሉ ወይ እኛ እናሸንፋለን፤›› ብለው እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ነገር ግን መንግሥት ሙስናን ለመታገል ደፋ ቀና የሚለውን ያህል በመንግሥት ጉያ ሥር ተሸጉጠው የሙስና ትግሉን በመቀልበስና የሚገኘውን አይስክሬም ለመላስ የቆረጡ እንዳሉ እየታየ መሆኑን የሚገልጹ አሉ፡፡

በሁለቱ አካላት መካከል የሚደረገው ሽኩቻ ወይም ትግል በማን አሸናፊነት እንደሚቋጭ ባይታወቅም አሸናፊና ተሸናፊ የግድ እንደሚያስፈልግ ይታመናል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት እየጨሰ ከሚገኘው የፀረ ሙስና ትግል ባሻገር፣ በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ጉዳዮችን ጥቂት ዓመታት ወደኋላ መለስ ተብሎ ቢመረመርና አሁን ካለበት ደረጃ ጋር ቢመዘን የጉዳዩን አሳሳቢነት መረዳት ያስችላል በማለት የሚገልጹ አሉ፡፡

የቀድሞወ ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳ አስተዳደር ሥልጣኑን ከእሳት አጥፊው ባለአደራ አስተዳደር ሲረከቡ ወደ ከተማው ይዘው ከመጧቸው ቁም ነገሮች መካከል መልካም አስተዳደርን ማስፈን፣ ሙስናን መታገልና መሠረታዊ የሥራ ሒደት ለውጥ ተግባራዊ ማድረግ ይገኙበታል፡፡

በተለይ ከገቢ አሰባሰብና ከመሬት አስተዳደር ጋር ተያይዞ በርካታ የሙስና ተግባሮች እንደነበሩ በመታመኑ፣ በአሥሩም ክፍላተ ከተሞች ጠንከር ያለ ግምገማ መካሄዱ ይታወሳል፡፡ በእነዚህ ግምገማዎች በርካታ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች በሙስና መዘፈቃቸውና በርካታ ገንዘብ መመዝበሩ በተካሄደው ድርጅታዊና መንግሥታዊ ግምገማ ተረጋግጧል፡፡

የፓትርያርኩ ልዩ ጽሕፈት ቤት ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅን ዘጋ

-    ‹‹ኮሌጁን የመዝጋት መብት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ ነው››  የመንፈሳዊ ኮሌጁ ተማሪዎች

ከመጋቢት ወር 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ተማሪዎቹ በሚያነሷቸው የተለያዩ ጥያቄዎች፣ የመማር ማስተማር ሒደት ሲስተጓጎል በመቆየቱና ባለፈው ሳምንት ደግሞ የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት አጠቃላይ ፈተና እንዳይሰጥ ተስተጓጉሏል በሚል ምክንያት፣ የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት፣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የቀን ተማሪዎች ትምህርት ተቋርጦ እንዲዘጋ አደረገ፡፡

በመንበር ፓትርያርኩ ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ገሪማ ፊርማ የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ኮሌጁ ከሐምሌ 8 ቀን 2005 ዓ.ም. እስከ መስከረም አጋማሽ 2006 ዓ.ም. ድረስ ተዘግቷል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ሐምሌ 1 ቀን 2005 ዓ.ም. ሲሰጥ የነበረውን የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት አጠቃላይ ፈተና ተማሪዎቹ እንዳይሰጥ በማድረጋቸው ነው፡፡ ተማሪዎቹ ፈተናው ይሰጣል በተባለበት ዕለት የኮሌጁን ቢሮዎች በመዝጋትና ሊፈተኑ የመጡ መምህራንን በመከልከላቸው መሆኑን ደብዳቤው ያስረዳል፡፡ እንዲዘጋ በጽሕፈት ቤቱ ውሳኔ የተላለፈበት የቀኑ የትምህርት ክፍለ ጊዜ ሲሆን፣ ተማሪዎቹም ለሐምሌ 9 ቀን 2005 ዓ.ም. በሰላማዊ መንገድ የኮሌጁን ግቢ ለቀው እንዲወጡ በጥብቅ ያሳስባል፡፡  

አክሰስ ሪል ስቴት መንግሥት አቶ ኤርሚያስን በማግባባት ወይም በኢንተርፖል እንዲያስመጣለት ሊጠይቅ ነው

-    ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የተከፈላቸው ኮንትራክተሮች እየተከራከሩ ነው
-    የቤት ገዢዎች ዓብይ ኮሚቴና አዲስ የቦርድ አመራሮች ተመረጡ

በውጭና አገር ውስጥ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለመኖሪያ ቤት ግንባታ ከ1.4 ቢሊዮን ብር በላይ ከሰበሰቡ በኋላ፣ በኪሳራ ምክንያት ከአገር የወጡትን የአክሰስ ሪል ስቴት የቀድሞ ሥራ አስኪያጅና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ኤርሚያስ ጠቅል አመልጋን፣ መንግሥት በማግባባት ወይም በኢንተርፖል አማካይነት እንዲያስመጣለት ሰኔ 9 ቀን 2005 ዓ.ም. የተመረጠው አዲሱ የሪል ስቴቱ ቦርድና የቤት ገዢዎች በጋራ ሊጠይቁ ነው፡፡

ከ650 በላይ ባለአክሲዮኖች የሚገኙበት አክሰስ ሪል ስቴት አክሲዮን ማኅበር፣ ሰኔ 9 ቀን 2005 ዓ.ም. ባደረገው አጠቃላይ ስብሰባ፣ ቀደም ሲል በአቶ ኤርሚያስ ሰብሳቢነት ተሰይሞ የቆየውንና ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ሳያደርግ የቆየውን ቦርድ በመበተን አዲስ ቦርድ የሰየመ ሲሆን፣ ለሪል ስቴቱ ሙሉ፣ ግማሽና ሲሶ ክፍያ በመፈጸም መኖሪያ ቤት የገዙ 2,034 ግለሰቦች መካከል ከተመረጡ ዓብይ ኮሚቴ ጋር የሥራ ውል መፈራረማቸው ታውቋል፡፡  

በቀጣይ በጋራ ሊሠሩ ያሰቡት አክሰስ ሪል ስቴት በቀድሞው ሥራ አስኪያጅና ቦርድ ሰብሳቢ ተፈጽመዋል የተባሉትን ችግሮች ለመፍታት፣ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት ወሳኝ በመሆኑ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና ለሌሎች ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ደብዳቤ ማስገባታቸውን፣ የአዲሱ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ መኩሪያ ደጉ፣ የዓብይ ኮሚቴው ተጠሪ አቶ አክሎግ ሥዩምና የኮሚቴው አባል አቶ ደመክርስቶስ ዘመነ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡ 

Saturday, July 20, 2013

በመጪው ምርጫ ፓርላማ እገባለሁ፡፡ ግን ወዲያው ፕሬዚዳንት አልሆንም!

*ወደ ፖለቲካ የምገባው ህዝብ ማገልገል ስለምፈልግ ነው
*ኢትዮጵያን አርቀንና በረጅም ጊዜ የማናይ ከሆነ፣አባይን መገደብ አያስፈልገንም
*በውጭ ሆነው የሚቃወሙ አገራቸው ላይ መታገል አለባቸው ባይ ነኝ

ከጥቂት ዓመታት በፊት ጠ/ሚኒስትር የመሆን ፍላጐት እንዳለው ገልፆ የነበረው አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ፤ ሰሞኑን ከአሶሼትድ ፕሬስ ጋር ባደረገው ቃለምልለስ “የአገሪቱ ፕሬዚዳንት መሆን እፈልጋለሁ” በማለቱ የመነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ ሆኗል፡፡ በ2007 ዓ.ም በሚደረገው አገራዊ ምርጫ ተወዳድሮ ፓርላማ ለመግባት ያሰበው አትሌቱ፤ ከዚያም የአገሪቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ህዝብን ማገልገል እንደሚፈልግ ተናግሯል፡፡ 

አትሌት ኃይሌ፤ ከጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ፤ ለምን ወደ ፖለቲካ ሊገባ እንዳሰበ፣ ፕሬዚዳንት ሆኖ ቢመረጥ ለመስራት ስላቀዳቸው ተግባራትና ተያያዥ ጉዳዮች አውግቷል። 

እነሆ:- የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ፤ ከአትሌት ኃይሌ ጋር

ሰሞኑን “ፕሬዚዳንት መሆን እፈልጋለሁ”ማለትህን ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ከዘገቡ በኋላ ጉዳዩ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ እንዴት ነው ነገሩ?

እኔ የምልሽ ---- ፕሬዚዳንት እንድሆን ኖሚኔት (አጭታችሁኛል) አድርጋችሁኛል እንዴ? ፕሬዚዳንት የሚመረጠው በገዢው ፓርቲ ኖሚኔት ሲደረግ እና ሁለት ሶስተኛውን የፓርላማና የፌደሬሽን ም/ቤት ይሁንታ ሲያገኝ ነው፡፡ እና ይሄ ነገር ሲደጋገምብኝ ---- እንዴት ነው ተጠይቆልኝ ይሆን እንዴ እላለሁ፡፡ 

በዳያስፖራ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ግብረ ኃይል የተሰጠ መግለጫ

ሐምሌ 13 ቀን 2005 ዓ.ም

«ነጻነትን ማንም አይሰጥህም። እኩልነትና ፍትህንም ማንም አይሰጥምህ። ሰው ከሆንክ፣ አንተዉ እራስህ ተቀበለው» ነበር ያሉት፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ማልኮም ኤክስ። ነጻነትና ሰላም፣ ዴሞክራሲና ፍትህ፣ እኩልነትና መልካም አስተዳደር፣ ሌሎች የሚሰጡን ሳይሆን፣ ፈጣሪ በቸርነቱ የለገሰን፣ ደፍረንና ፈቅደን የምንቀበላቸው፣ የኛዉ የሆኑ በረከቶች ናቸው።

ነገር ግን ለአመታት መብታችንና ነጻነታችን፣ በጥቂቶች ተገፎ፣ ሁላችንም በየጓዳችን ስንናደድ፣ ስናማርር፣ ስናዝን፣ ስንራገም፣ ልባችን ሲደማ፣ «እንደዉ ምን ይሻላል? » እየተባባልን ስናወራ ቆይተናል። ለዜጎቿ ሁሉ እኩል የሆነች፣ ሕግ የበላይ የሆነባት፣ ፍትህ የሰፈነባት፣ ሕዝቡ ለመሪዎች ሳይሆን መሪዎች ለሕዝብ የሚንበረክኩባት፣ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለማየት ትልቅ ጉጉት አለን። 

ማልኮም ኤክስ እንዳሉት፣ ፍትህንና እኩልነትን እንዲያመጡልን፣ ሌሎችን መጠበቅ የለብንም። እያንዳንዳችን መንቀሳቀስ ይኖርብናል። በአገር ቤት፣ በጎንደርና በደሴ እንደታየው፣ ከፍተኛ፣ ሰላማዊ፣ የሰለጠነ የፍቅር ፖለቲካ ላይ ያተኮረ፣ እንቅስቅሴ እየተደረገ ነዉ። እንቅስቅሴዎቹ በባህር ዳር፣ በፍቼ፣ በጂንካ፣ በአርባ ምንጭ፣ በአዳማ፣ በመቀሌ፣ በወላይታ ሶዳ፣ በጋምቤላ በአሶሳ .. እያለ ይቀጥላል። በአገሪቷ ክልሎች ሁሉ ያለው ሕዝቡ መብቱንና ነጻነቱን እንዲያስከብር ቅስቀሳ ይደረጋል። ለምን ? የምንፈልጋት ኢትዮጵያ ልትመጣ የምትችለው እኛን ጨምሮ ሕዝቡ ቀን ሲል ብቻ በመሆኑ።

Friday, July 19, 2013

አሸባሪዉ ኢህአዴግና የፀረሽብር ህጉ መወገድ አለባቸዉ

ከተስፋዬ ተካልኝ

ኢትዮጵያንና ህዝቧን የአብሮነትን መሠረት ለመሸርሸርና ብሎም ለማጥፋት ሌተ ቀን የማይተኛዉ የህወሀት ኢህአዴግ አሸባሪ መራሹ መንግስት በህዝብ ጫንቃ ላይ ተቀምጦ ዜጎችን ማሰቃየት ከጀመረእነሆ ፪፪ አመት ተቆጥሮዋል።ነገር ግን የ፪፪ አመት ቆይታዉ ህዠብን ከማሸበር፣ ከመግደል፣ከማሰር ከማሰደድ፣ከመግረፍና ከማፈናቀል አልፎ በተመቸዉና የጥፋት ምርቃናዉ በመጣለት ቁጥር በዘረኞች መሪዎቹአማካይነት በፈለገዉ ሰዐት ከራሱ ህግና ስርአትዉጪ ከእንቅልፋ እንደሚነቃና የሚያደርገዉን እንደማያቅ ህፃን ልጅ የተለያዮ ህጎችን በማዉጣት ጭምር ህዝባችንን ከህዝባችን እንዲሁም ሀገሪቱዋን ባለቤትየሚያሳጣ አስነዋሪ ህጎች በማርቀቅና ድራማ በመስራት ማፍያ ስርአት መሆኑ ይታወቃል።

ከእነዚህ የህወሀት ኢህአዴግ አስነዋሪ ህጎች አንዱ እኤአ ፪፻፱ በሙዋቹ ቀንደኛ ማፍያ መሪያቸዉ መለስ ዜናዊ መሪነትና በሌሎች አጭበርባሪ ሆዳም የሀገር ፍቅር በሌላቸዉ ተከታዮች አማካይነት የፀረ ሽብርህግ አዉጥቶ ፭፬፩ እጅ በሚያነሱለት የፓርላማ አሻንጉሊቶቹ ድጋፍ ማፀደቁ የሚታወቅ ነዉ።

ይህ ህግ አሁንም በባለ ጥፋቱ መሪያቸዉ የሙት መንፈስ ራእይ ስምና በተተካዉ አሻንጉሊት መሪ ሀይለማርያም ደሳለኝ ህጉ እንደቀጠለ ሲሆን ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚያሸብረ ወያኔ ሆኖ ሳለ ነገር ግን በመሣርያየበላይነት በሀገሪቷ ዉስጥ ከወያኔ የተለየ ሀሳብ ያላቸዉ በህጉ የስቃይ ሰለባ እየሆኑ ነዉ ዛሬም።

Ethiopians in Norway demonstration against the dictatorship in Ethiopia

More than 15 Ethiopians living in Norway held a demonstration in Harstad , demanding the Ethiopian government to respect the rights of citizens.

“Free prisoners of consciousness”, “Respect the freedom of the press”, “Respect the freedom of thought and expression”, “The Norwagian Goverment should stop funding the regime”, “Stop corruption and racism” were among the slogans the protestors chanted.And also by the representative of the coordinator saied the following

Lack of freedom in Ethiopia:

Out of five countries in the world showing the greatest aggregate declines in freedom from 2007-2011, Ethiopia was fifth according to the previously mentioned 2012 study by Freedom House.

In the case of Ethiopia, it is well known within the country that the ethnic-based Tigrayan Peoples’ Liberation Front (TPLF) not only controls the ruling party, the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF), but it also controls every sector of society and every facet of life from the federal level to the kebele (neighborhood levels). This includes the parliament, civil service, the judiciary, the military, security forces, civic institutions, religious institutions, the economic system, the educational system and the administration of developmental aid; including the dispensation of food aid, fertilizers, seed and other developmental aid.

ከፍተኛ የሙስና ወንጀል ሲጋለጥ

ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በሶስት መርከብ ስሚንቶ አስጭነው አገር ውስጥ በማስገባት ከፍተኛ የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ። በተከለከለ ፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ አገር ቤት የገባው ስሚንቶ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አዜብና ግብረአበሮቻቸው እንደዛቁበት ያረጋገጡት ምንጮቹ፣ አያይዘውም ጉዳዩ በደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ እጅ እንደገባ አስታውቀዋል። በሕገወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ በመመደብና አስፈላጊውን ትእዛዝ በመስጠት እንዲሁም የጥቅም ተካፋይ በመሆን ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት አዜብ መስፍን ከዚህ ድርጊታቸው በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ ተመስርቶ የነበረውን ክስ እንዲቋረጥ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ይህና ሌሎች ተያያዥ የወንጀል ድርጊቶችን የሚያስረዱ ማስረጃዎች በአቶ ጌታቸው እጅ እንደገቡ አረጋግጠዋል። አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር በኮንትሮባንድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው ወደ አገር ውስጥ ያስገቧቸው የህክምና መሳሪያዎች ተይዘው ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ ክሱ እንዲቋረጥ ያደረጉት አዜብ መሆናቸውን የገለፁት ምንጮቹ፣ በተለያዩ ጊዜያት የገቡና የነጋ ገ/እግዚያብሄር ንብረት የሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ያለቀረጥ እንዲገቡ በማድረግ አዜብ መተባበራቸውን አያይዘው ገልፀዋል። ጉዳዩም «ክስ በማቋረጥ..» በሚል በሰነድ ተደግፎና ከሌሎች መሰል ድርጊቶች ጋር ተያይዞ በታሳሪዎች ላይ ክስ የቀረበ ቢሆንም፣ ዋናው ተዋናይ ግን አዜብ ሳይጠየቁ መቅረታቸው አነጋጋሪ መሆኑን ምንጮቹ አልሸሸጉም። ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ አስተያየት የጠየኳቸው ታዋቂ የሆኑ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ባለሙያ ፥ « መንግስት ስለ ፍራንኮ ቫሉታ ሕግ አውጥቷል፤ ይህን በመተላለፍ ሶስት መርከብ ስሚንቶን የሚያክል ነገር በታሳሪዎቹ ብቻ ሊፈፀም አይችልም፤ ከዚህ ሕገወጥ ድርጊት በስተጀርባ ትልቅና ቁልፍ ስልጣን ያለው ሰው እጁ እንዳለበት ግልፅ ነው።» ብለዋል።

መድረክ በመቀሌ በሚያደርገው ህዝባዊ ስብሰባ እንዳይቀሰቅስ ተከለከለ

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር(መድረክ) የፊታችን እሁድ ሐምሌ 14 ቀን 2005ዓ.ም. ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ በመቀሌ ከተማ ማጋጃ ቤት አዳራሽ ውስጥ ለሚያካሂደው ህዝባዊ ስብሰባ በመኪና ቅስቀሳ እንዳያደርግ መከልከሉን ከስፍራው የዓረና ትግራይ እና የአንድነት/መድረክ አመራሮች ገለፁ፡፡ መድረክ በሀገራዊ አንገብጋቢ ጉዳዮች ዙሪያ ከመቀሌና አካባቢዋ ነዋሪዎች ጋር ለመወያት ዝግጅቱን ያጠናቀቀ በመሆኑ ህዝቡ በነፃነት ይመክር ዘንድ በተዘጋጀው መድረክ ላይ እንዲገኝ በድምፅ ማጉያ እና በመኪና ቅስቀሳ ማድረግ እንደማይችሉና ለዚህም እውቅና እና ጥበቃ እንደማያደርጉ የከተማው ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ገ/ህይወት ካሳዬ መናገራቸውን የስብሰባው አስተባባሪ ከሞቴዎች ከመቀሌ በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡

“ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የምናደርገው ትግል በስም ማጥፋትና በፍረጃ አይገታም!” ሰማያዊ ፓርቲ

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

ሰማያዊ ፓርቲ በሃገራችን የሚፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰትና የአስተዳደር ብልሹነት እንዲስተካከል የመንግሥት አካላት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ በተደጋጋሚ ሲጠይቅ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ነገርግን እነዚህ ጥያቄዎቻችን በመንግሥት በኩል ምላሽ ስለተነፈጋቸው ጥያቄዎቹ ከፍ ባለደረጃ ትኩረት እንዲያገኙ ሆነው መቅረብ እንዳለባቸው ተገንዝበናል፡፡ በዚህም መሰረት ጥያቄዎቹን በሰላማዊ ሰልፍ መጠየቅ እንዳለበት ወስኖ ግንቦት 25 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም በአዲስ አበባ ባካሔደው ታላቅ ሠላማዊ ሠልፍ ጥያቄዎቹ እንዲመለሱ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ በተጨማሪም ጥያቄዎቻችን ከመንግሥት በኩል በሦስት ወር ጊዜ ምላሽ የማያገኙ ከሆነ ሌላ የተቃውሞ ሠልፍ ከፍ ባለ ደረጃ የሚጠራ ስለመሆኑ ፓርቲው አቋሙን በሰልፉ ዕለት አሳውቋል፡፡

ይሁን እንጂ ሰልፉ ከተጠናቀቀበት ዕለት ጀምሮ በገዥው ፓርቲና በመንግሥት ተወካዮች የተሠጡ መግለጫዎች ያስገነዘቡን መፍትሔ እንዲሠጣቸው ለቀረቡ ጥያቄዎች መንግስት ተገቢውን መልስ ለመስጠት ምንም ዓይነት ፍላጐት እንደሌለው ነው፡፡ ከዚህም አልፎ መንግስት ጥያቄዎቹ የቀረቡበትን መንፈስ እንኳ በቀናነት ለመቀበል ያልፈለገ መሆኑን ያሳያል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ፓርቲያችንን ለመጫንና ስሙን ለማጉደፍ በፕሮግራሙም ሆነ በሥራ እንቅስቃሴው የሌለበትን በአክራሪነትና በአሸባሪነት ለመወንጀል ተደጋጋሚ ጥረት እያደረገ መሆኑን ከሚሠጣቸው መግለጫዎች ተረድተናል፡፡

Thursday, July 18, 2013

የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ህዝባዊ ንቅናቄ ግብረ ኃይል ቀጣይ እቅዱን ይፋ አደረገ

የአንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ህዝባዊ ንቅናቄ ግብረ ኃይል ዛሬ ሐምሌ 11,2005 ዓ.ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ቀጣይ የህዝባው ንቅናቄ ዕቅዱን አፅድቋል፡፡

በዚሁም መሰረት በሚቀጥሉት የሀገራችን ከተሞች ህዝባዊ ስብሰባዎችንና ታላላቅ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፎችን ጠርቷል፡፡ በየክልሉ ያሉ የአንድነት ፓርቲ ድርጅታዊ መዋቅሮች ለፓርቲው ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት ግብረኃይሉ ያቀዳቸው ህዝባ
ዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎች ከአዲስ አበባ አስቀድሞ በክልል ከተሞች ለማድረግ የተወሰነ ሲሆን የህዝባዊ ንቅናቄው ማጠቃለያ የሚሆነው መስከረም አምስት ቀን 2006ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚደረገው ታላቅ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ይሆናል፡፡ ግብረ ኃይሉ መስከረም 5, 2006 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ያቀደው ሰላማዊ ታጋዮቹ አንዱአለም አራጌና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የታሰሩበትን ሁለተኛ አመት ለመዘከር እንደሆነ ታውቋል፡፡

ህዝባዊ ሰብሰባ የሚደረግባቸው ከተሞችና ቀኖቻቸው
====================================================

« ግድቡ እዚያ አይደርስም እንጂ ተሰርቶ ካለቀ የግድቡን ደህንነት የምትጠብቀው እራሷ ግብፅ ነው የምትሆነው» - ዶክተር መረራ ጉዲና ለአዲስ ዘመን


ከዶክተር መረራ ጉዲና ጋር በአባይ ወንዝ ዙሪያ በኢትዮጵያና በግብፅ መካከል በተነሳው አለመግባባት እንዲሁም ከተቃዋሚ ፓርቲዎች መንደር በተደመጠው ምላሽ ዙርያ እንደ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁርና እንደ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ያደረግነው ቃለ ምልልስ እነሆ።


አዲስ ዘመን፡- እንደ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲም ሊሆን ይችላል እንደ ተራ ኢትዮጵያዊ ወይንም ዜጋ ከግብጽ የምንማረው ነገር አለ፡፡ ግብጾች የቱንም ያህል መንግሥታቸውን አምርረው ቢጠሉ በሀገር ጉዳይ ግን ምንጊዜም አንድ ናቸው፡፡ በተለይ ደግሞ በዓባይ ላይ ያላቸው አቋም የተለየ ነው፡፡ ይሄንንም በቀጥታ ከተላለፈው የቴሌቪዥናቸው ስርጭት መረዳት እንችላለን፡፡ ወዲህ ወደ እኛ ሀገር ስንመለስ ግን በአባይ ላይ እንኳን አንድ መሆን አልቻልንም፡፡ በእዚህ ዙሪያ ምን አስተያየት አለዎት?

ዶክተር መረራ፡- እኔ ከምንም በላይ የምለው ኳሱ ያለው በኢህአዴግ ሜዳ ላይ ነው፡፡ በኢጣሊያ ዘመን ያየነው ነገር ነው፡፡ በእዚያ ዘመን የኢጣሊያን ባንዳ ሆነው ፔሮል ላይ ሳይቀር የሰፈሩና ያገለገሉ ኢትዮጵያውያን ነበሩ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ኃይለሥላሴ ሌላ ኢትዮጵያ ሌላ ብለው ከእሥር ቤት ወጥተው የተዋጉ እንደ ባልቻ አባነፍሶ ያሉ ኢትዮጵያውያን ነበሩ፡፡ ከእዚህ የምንማረው ምንድን ነው፣ መንግሥት ስትሆን ቀዳዳ እንዳይከፈት ማድረግ አለብህ፡፡ በሀገር ፖለቲካ ላይ ብሔራዊ መግባባት ካልፈጠርክ ግብጾች ነገም ሆነ ከነገ ወዲያ የውጭን ኃይል ሊጠቀሙ ይችላሉ፡፡

ኢህአዴግ በሩን እንዲከፍት የዓለም ባንክ አዘዘ! የማነቂያው ገመድ ከርሯል፤ “ትግሉ ይቀጥላል” ኦባንግ ሜቶ

ኢህአዴግ ለሚገዛት ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው ዕርዳታ የሚሠጠው የዓለም ባንክ፤ ለዕርዳታና ልማት የሚልከው ገንዘብ ኢህአዴግ የሕዝቡን ሰብዓዊ መብት ለመጣስ ተጠቅሞበታል በሚል ሙሉ ምርመራ እንዲካሄድ አዘዘ፡፡ የባንኩ ውሳኔ ኢህአዴግን የማነቂያው ገመድ እንደሚያከረው ተገለጸ፡፡ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ በተለይ ለጎልጉል በሰጡት መግለጫ “ይህ በጥናት ከምናካሂደው ትግል አንዱ ውጤት ነው፤ ገና ጅማሬ ነው፤ ጠንክረን እንሠራለን” አሉ፡፡

የዓለም ባንክ ለልማት ሥራዎች የሚሰጠው የእርዳታ ገንዘብ በኢትዮጵያ በተለይም በጋምቤላ ክልል የሚኖሩትን ዜጎች ሰብዓዊ መብት በመጣስ ላይ ውሏል በሚል ከዚህ በፊት ክስ ቀርቦበት እንደነበር ይታወሳል፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጉዳዩን ከ9 ወራት በፊት በዘገበበት ወቅት ተጠቂዎቹ ዜጎች ያቀረቡትን ማስረጃና የኢንስፔክተር ቡድኑ የሚያደርገውን ምርመራ በዝርዝር ሰፍሮ ነበር፡፡ በወቅቱ ምርመራውን ያደረገው የመርማሪ ቡድን (ኢንስፔክሽን ፓናል) በአካባቢው የሚገኙትን ተጠቂዎች ካነጋገረ በኋላ ለባንኩ የሥራ አመራር ቦርድ በሰጠው ሪፖርት በዕርግጥ የዕርዳታው ገንዘብ በሰብዓዊ መብት ረገጣ ላይ መዋሉን ይፋ አድርጓል፡፡

ይህ የኢንስፔክተር ቡድን ከፍተኛ ሥልጣን ያለው መ/ቤት ሲሆን የዓለም ባንክ ለአገራት የሚሰጠውን ገንዘብ በትክክለኛ ቦታ ላይ አለመዋሉን በመጥቀስ ክስ የሚያቀርቡ ወገኖችን ጉዳይ በመከታተልና ቦታው ድረስ የራሱን ምርመራ በማካሄድ ውጤቱ ተግባራዊ እንዲሆን የባንኩን እጅ የማስጠምዘዝ ዓቅም ያለው እንደሆነ ከዚህ በፊት ያካሄዳቸው የምርመራ ውጤቶች ይጠቁማሉ፡፡

አክራሪነት በኢትዮጵያ – ጥያቄዎች ለሃጂ ናጂብ

ከማከብራቸው የዲሞክራሲ አክቲቪስት መካከል አንዱ የሆኑት፣ አቶ ተድላ አስፋዉ፣ አቶ ጃዋር መሃመድ ለተናገራቸው አንዳንድ አባባሎች የሰጡትን ምላሽ አነበብኩ። አቶ ጃዋር የተወለደው በአርሲና በሃረርጌ ድንበር አካባቢ ነዉ። በዚያ አካባቢ ነዉ አርባ ጉጉ (ምእራብ አርሲ) እና በደኖ (ምስራቅ ሃረርጌ) የሚገኙት። ወያኔ/ኢሕአዴግና ኦነግ ስልጣን በጨበጡ ጊዜ፣ በአርባ ጉጉና በደኖ የተፈጸሙትን ሁላችንም የምናወቀዉ ነዉ። አካባቢዉን ከክርስቲያኖችና ከ«አማራዎች» ለማጽዳት ፣ ብዙዎች በቤታቸው ተቆልፎባቸው ተቃጥለዋል። ብዙዎች፣ ነፍሰ ጡር እህቶቻችን ሳይቀሩ፣ ጥልቅ በሆነ ጉድጓድ ዉስጥ፣ አይኖችቸው በጨርቅ ታስረዉ፣ በሕይወት ተወርውረዋል። አርባ ጉጉን ኦሕዴድ/ኢሕአዴግ ፣ በደኖን ደግሞ ኦነግ ነበር የሚያስተዳድሩት። በዚያን ወቅት ከፍተኛ ፀረ-አማራና ፀረ-ክርስቲያን የጥላቻ ዘመቻ ይደረግ ነበር። ብዙ ያልተማረው ሕዝብ፣ ተማሪዎች፣ ልጆች ፣ የዚህ ጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ሰላባዎች እንዲሆኑ፣ ይህን አይነት የጥላቻና የአክራሪነት አስተሳሰብ እንዲኖራቸው ተደርጓል።

አቶ ጃዋር መሃመድ የዚህ ዉጤት ናቸው። አሁን የሚያንጸባርቁት፣ ያኔ በልጅነታቸው ከኦሕዴድና ኦነግ አክራሪዎች የተማሩት ነዉ። ይህ አይነቱ የጥላቻና የአክራሪነት ፖለቲካ በኢትዮጵያ ዉስጥ ቦታ ሊኖረው የማይገባ፣ ለአገር ትልቅ ጠንቅ የሆነ ፖለቲካ ነዉ። አቶ ተድላም በዚህ ጉዳይ ላይ ጊዜያቸዉን ወስደው አክራሪነትን እና ጥላቻን ለማጋለጥ ላደረጉት አስተዋጾ ላመሰግናቸው እወዳለሁ።

ትንሽ ስለ ዓረና ትግራይ ፓርቲ

በአብርሃ ደስታ

ዓረና ትግራይ ፓርቲ ህዝባዊ ስብሰባ ጠራ

ፓርቲው ለእሁድ ሓምሌ 14, 2005 ዓም በመቐለ ማዘጋጃቤት አዳራሽ ህዝባዊ ስብሰባ መጥራቱ ተሰምቷል። ፓርቲው ‘አሉ’ በሚላቸው የህዝብ ችግሮች (ኑሮ ውድነት፣ የወጣቶች ስደት፣ የግብር አከፋፈል ችግሮችና የሙስና ሁኔታ፣ የመልካም አስተዳደር እጦትና የመሳሰሉት የህዝብ ችግሮችና በዓረና ትግራይ የሚቀርቡ አማራጭ መፍትሔ ሓሳቦች ከመቐለና አከባቢው ህዝብ ነዋሪዎች መወያየት እንደሚፈልግ አስታውቋል። ሁላችን ተጋብዘናል፤ እንሳተፋለን።

ስንሳተፍ ግን ምን እንጠብቃለን? ዓረናዎች የህዝብ ችግሮችና የመፍትሔ አማራጫቸውን ሲነግሩን የህወሓት ደጋፊዎች (መሳተፋቸው አይቀርም ከሚል ነው) ደግሞ ‘ እናንተ ዓረናዎች እኮ ያው ናችሁ። ህወሓት ነበራቹ። ያኔ ለውጥ አላመጣችሁም።’ የሚል የተለመደ የፕሮፓጋንዳ ስትራተጂ መጠቀማቸው አይቀርም።

እኔም እላቸዋለሁ፡ አዎ! አብዛኛው የትግራይ ህዝብ የህወሓት ታጋይ ነበር፤ የህወሓት ፓርቲ አመራር አባል ግን አልነበረም። እነኚህ የዓረና አባላትም የትግራይ ህዝብ አባላት እስከሆኑ ድረስ የህወሓት ታጋዮች ነበሩ። የህወሓት ታጋይ መሆን በራሱ ስሕተት አይደለም። ህወሓት እንደ ትግልና እንደ ገዢ መደብ የተለያዩ ናቸው። 

ግን ደግሞ የህወሓት ደጋፊዎች (አብዛኞቹ የህወሓት አባላት) ዓረናዎችና ህወሓቶች ‘ያው አንድ’ መሆናቸው የሚያምኑ ከሆነ ለህወሓት የሚሰጡትን ድጋፍ ለዓረናም መስጠት አለባቸው ማለት ነው፤ ምክንያቱም ‘ያው አንድ’ አይደሉም እንዴ? በአንድ በኩል ‘ዓረናና ህወሓት ያው ናቸው፤ አብረው ነበሩ። ስለዚህ ዓረና ፓርቲ ከህወሓት የተለየ ለውጥ ሊያመጣ አይችልም’ ብለው ይከራከራሉ። በሌላ በኩል ደግሞ ዓረና ትግራይ ፓርቲን በጠላትነት በመፈረጅ ህወሓትን የሚቃወም ሰው ፀረ የትግራይ ህዝብ ትግል አስመስለው ያቀርባሉ።

አዎ! እነኚህ ዓረናዎች የህወሓት ታጋዮች ነበሩ። የህወሓት የአመራር አባላት የነበሩ የዓረና ትግራይ አባላት ግን በቁጥር ሦስት ብቻ ናቸው። አንደኛ እነዚህ ሦስት ሰዎች ከህወሓት አመራርነት ወደ ዓረና አመራርነት ስለተቀየሩ ዓረናና ህወሓት ‘ያው አንድ’ ናቸው ሊያስብል አይችልም፤ ምክንያቱም የዓረና አባላት ሦስት ብቻ አይደሉም። 

ሁለተኛ እነኚህ ሦስት ሰዎች (ወይም ማንኛውም ሰው) ህወሓት ወይ ዓረና ወይ ሌላ የሚያደርጋቸው የፖለቲካ አስተሳሰባቸው (አመለካከታቸው) ነው። ሦስቱ የአመራር አባላት ከህወሓቶች ‘ያው አንድ’ ቢሆኑ ኑሮ ለምን ህወሓትን ለቀው ወጡ? ከፍተኛ ባለስልጣናት አልነበሩምን? ለምን ስልጣናቸውን ጠብቀው ‘ተከብረው’ አልኖሩም? ከህወሓቶች ያው ቢሆኑ ኑሮ ለምን በህወሓት መሪዎች ይሰደባሉ? ይዋረዳሉ? ይታሰራሉ?

በአንድ በኩል ‘ህወሓት የነበሩ ናቸው፣ በስልጣን በነበሩበት ግዜ ለውጥ አላመጡም’ ይባላል። በሌላ በኩል ደግሞ ‘ሰዎቹ ዓረና የሚል የተቃዋሚ ፓርቲ የመሰረቱት ስልጣን ፈልገው ነው’ የሚል የመከራከርያ ነጥብ አለ። ሁለቱም ነጥቦች እርስበርሳቸው ይጣረሳሉ። የህወሓት አመራር አባላት በነበሩበት ግዜ ከፍተኛ ባለስልጣናት ከነበሩ እንዴት ስልጣን ፈልገው ከህወሓት ወተው ሌላ ፓርቲ መሰረቱ ሊባል ይችላል? የስልጣን ጥማት ቢኖራቸው ኑሮ እንደ አንዳንዶቹ ‘ይቅርታ’ ጠይቀው ወደ ፓርቲው ተመልሰው ገብተው ስልጣን አይዙም ነበር?

‘ከህወሓት ጋር አብረው በሰሩበት ግዜ ለውጥ አላመጡም’ በሚል ሓሳብ ግን እስማማለሁ። አዎ! ተገቢውን ለውጥ አላመጡም። ነገር ግን በህወሓት የፖለቲካ ስትራተጂ መሰረት ለውጥ ወይ ውድቀት የሚያመጣው ግለሰብ ሳይሆን ድርጅቱ እንደስርዓት ነው። የህወሓት የፖለቲካ አሰራር ‘ዴሞክራቲክ ሴንትራሊዝም’ ነው። በ‘የተማእከለ ዴሞክራሲ’ (Democratic Centralism) እሳቤ መሰረት ማንኛውም የፓርቲው አባል (ወይ አባላት) ድርጅቱን የሚቃወም ሓሳብ ማራመድ አይችልም። የፓርቲው አሰራር መተቸት የሚቻለው በድርጅቱ ውስጣዊ ግምገማ ብቻ ነው። ተቃውሞውን ለህዝብ ይፋ ከሆነ የተቃወመውን ሰው ከድርጅቱ ይባረራል።

እነኚህ ከህወሓት የለቀቁ የአመራር አባላት ተቃውሟቸውን ሲገልፁ ቆይተዋል። ግን ለህዝብ ይፋ አልሆነም ነበር። በመጨረሻ ግን ከዓቅም በላይ ተወጥሮ ፈነዳ። መቃወማቸው ታወቀ። እንደዉጤቱም ፓርቲው ለቀው ወጡ። በዴሞክራቲክ ሴንትራሊዝም አመራር አባላት የማይደግፉትን አሰራር ጭምር እንዲተገብሩ ይገደዳሉ። የማያምኑበትን አሰራር ለመተግበር ሲገደዱ በስራቸው ዉጤታማ ላይሆኑ ይችላሉ። በህወሓት የፖለቲካ አሰራር መሰረት ለውጥ የሚያመጡ ወይ የማያመጡ ግለሰቦች ሳይሆኑ ድርጅታዊ ስርዓቱ ነው (የግለሰቦች ሚና የማይናቅ ቢሆንም)። እናም ህወሓትን የምንቃወመው ስርዓቱን እንጂ ግለሰቦችን አይደለም። 

ስለዚህ የዓረና አመራሮች በህወሓት እያሉ ተገቢውን ለውጥ ስላላመጡ አሁንም (በዓረና ፓርቲ) ለውጥ ሊያመጡ አይችሉም የሚል ድምዳሜ ትክክል አይመስለኝም። ምክንያቱም ሰዎቹ ‘ያው’ ቢሆኑ እንኳን የስርዓቱ አሰራር የተለያየ ነው (ወይም ተቀይሯል)። የህወሓትና የዓረና የፖለቲካ አሰራር የተለያየ ነው፣ በዓረና ፓርቲ ዴሞክራቲክ ሴንትራሊዝም አይሰራም። ዓረና ለውጥ ሊያመጣ ይችላል።

ህወሓት እየተከተለው ያለው የፖለቲካ ፍክክር ስትራተጂ ጤናማ አይደለም። የዓረና አመራሮች ያው ህወሓት የነበሩ ናቸው ካልን የህወሓት አባል የነበረ ሁሉ ከሌላ ፓርቲ ጋር መቀላቀል አይችልም ማለት ነው? (ይህን አቅጣጫ የራሳቸው የህወሓት አባላትን ፖለቲካ መብት የሚጋፋ ነው።) የህወሓት አባል የሆነ (ወይ የነበረ) ሰው የፈለገውን የፖለቲካ አመለካከት የመያዝ መብት የለውም ማለት ነው? የትግራይ ህዝብ ትግል ለነፃነት ካልሆነ ለሞት ነበር ማለት ነው? የህወሓት ታጋዮች የፈለጉትን ፓርቲ እንዲመሰርቱና እንዲደራጁ ካልተፈቀደላቸው የትግላቸው ውጤት ታድያ ምንድነው? ሌላ ዓፈና? በትግሉ የተሳተፉ ሰዎች እንዲህ መብታቸው ከተነፈጉ በትግሉ ያልተሳተፈ (በግዜ ምክንያት) አዲሱ ትውልድ የመደራጀት መብቱ እንደሚጠበቅለት በምን እርግጠኞች መሆን እንችላለን? ህወሓት ለነ ገብሩ አስራት ያልበጀች ለኔ ትጠቅማለች ብዬ እንዴት ልመን? 

የህወሓት መሪዎች ለህዝብ እንደሚሰሩ ይነግሩናል። በተግባር ግን ህዝብ አማራጭ የፖለቲካ ድርጅት እንዳይኖረው ይጥራሉ። በግብፅ የምናየው የፖለቲካ ቀውስ የሙባረክ መንግስት ያጠፋው ጥፋት ውጤት ነው። የሙባረክ መንግስት የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳይኖሩ ያደርግ ነበር። አሁን ችግሩን መፍታት የሚችል የተደራጀ ሃይል ጠፋ። ህዝቡ ቀውስ ውስጥ ገባ። ህወሓትም በተመሳሳይ መንገድ እየተራመደ ነው። ህዝብ አማራጭ ፓርቲ እንዳይኖረው የተለያዩ ተፅዕኖዎች እየፈጠረ ‘ከኔ በኋላ ሰርዶ አይብቀል’ እያለን ነው።

ህወሓት ለህዝብ ከቆመ ለምን ህዝቡ እንዲደራጅ አይፈቅድለትም? መደራጀትኮ ሓይል ይፈጥራል (‘ዉዳበ ሓይሊ እዩ!’ እንዶ ይብሉና አይነበሩን ግዲ!)። ህዝብ አማራጭ ፖለቲካዊ ድርጅት ሊኖረው ይገባል። 

ዓረና ፓርቲን ስንገመግም ‘አመራር አባላቱ እነማን ነበሩ?’ በሚል መሆን የለበትም። የትናንት አስተሳሰባቸው ስሕተት መሆኑ ተረድተው ሌላ የተሻለ ፖለቲካዊ አመለካከትና አሰራር ይዘው መጥተው ሊሆኑ ይችላሉ (ወይ ላይሆኑ ይችላሉ)። ‘ሌላ የተሻለ አሰራር አላቸው ወይስ የላቸውም ?’ የሚል ጥያቄ ለመመለስ የፖለቲካ ፕሮግራማቸውና ፖሊሲዎቻቸው መመርመር ያስፈልገናል። ለመመርመር ደግሞ ያቀረቡትን አማራጭ ማወቅ ያስፈልገናል። ለማወቅ ደግሞ የፓርቲው ሰዎች ከኛ (ከህዝብ) ጋር የሚገናኙበት መንገድ ሊመቻችላቸው ይገባል። ስለዚህ ህዝባዊ ስብሰባዎች መፈቀዳቸው ጥሩ ነው። አሁን የሚፈለገው የኛ ተሳትፎ ነው። በዚህ መንገድ ዓረና ፓርቲ ጥሩ አማራጭ መሆኑ ወይ አለመሆኑ ህዝቡ ይወስናል። 

እስቲ በአደራሹ ተገኝተን የዓረና ትግራይ ፓርቲ አማራጭ ሓሳቦች ምን እንደሆኑ ሰምተን እንገምግም። በዚህ ጉዳይ ከህዝባዊ ስብሰባው በኋላ አስተያየት እሰጥበታለሁ። 

የዓረና አማራጭ ሓሳብ ምንም (ጥሩ ወይ መጥፎ) ሊሆን ይችላል። ያም ሁኖ ግን ዓረና ፓርቲ አማራጭነቱ እንደተጠበቀ ነው። የአማራጭ መጥፎ ደግሞ የለም።

ለራሳቸው (ለህወሓቶች)ም ነፃ ልናወጣቸው ይገባል።

It is so!!!

Wednesday, July 17, 2013

EU urges Ethiopia to release journalists, revise terror law

By Aaron Maasho

ADDIS ABABA | Wed Jul 17, 2013 1:17pm EDT

(Reuters) - A European Union parliamentary delegation urged Ethiopia on Wednesday to release journalists and opposition politicians jailed under an anti-terror law, and revise the legislation that critics say is used to stifle dissent.

Ethiopian opposition parties routinely accuse the government of harassment and say their candidates are often intimidated in polls. All but two of the 547 seats in the legislature are held by the ruling party.

Critics point to a 2009 anti-terrorism law that makes anyone caught publishing information that could induce readers to commits acts of terrorism liable to jail terms of 10-to-20 years.

Last year, an Ethiopian court handed sentences of eight years to life to 20 journalists and opposition figures on charges of conspiring with rebels to topple the government.

"We note flaws in the impartiality of the judicial system," said Barbara Lochbihler, who led the delegation to the Horn of Africa country.

"Therefore we also call on the Ethiopian authorities to release all journalists, members of the opposition and others arbitrarily detained or imprisoned for exercising their legitimate right to freedom of expression, freedom of association, as well as freedom of religion and belief."

ጠንካራና የተደላደለ ስርአት መፍጠር የሚቻለው ነፃነትና ዴሞክራሲ በማስፈን መሆኑን የኢህአዴግ መሪዎች አልተገለፃላቸውም!!

አስራት አብርሃም (ቃለ መጠይቅ)

አቶ አስራት አብርሃም ይባላል፡፡ አቶ አስራት በወጣትነት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በስነ ፅሑፍ “ጎበዝ ተማሪ የመሆን ምስጢር”፣ “ከሀገር በስተጀርባ”፣ “መለስና ግብፅ” በቅርቡ ደግሞ “ፍኖተ ቃኤል” የሚሉ ስራዎችን ለንባብ አብቅቷል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የዓረና ትግራይ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በመሆንና የመድረክ ስራ አስፈፃሚ በመሆን በተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ ተሳትፎ አድርጓል፡፡ በቅርቡ ከነበረበት ዓረና/መድረክ የፖለቲካ ድርጅት እራሱን ያገለለ ሲሆን በዚህና በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢቦኒ መጽሄት ጋር ያደረገውን አጭር ቆይታ እነሆ.

ኢቦኒ፡- ፖለቲካ ላንተ ምንድነው?

አቶ አስራት፡-ፖለቲካ ለእኔ አንድ ወጥ የሆነ ትርጉም የለውም። ለምሳሌ በፊት የነበረኝ ምልከታ እና አሁን ያለኝ፣ በተለይ የፍልስፍና ትምህርት መማር ከጀመርኩ በኋላ “ፖለቲካ ላንተ ምንድነው?” ለሚለው ጥያቄ የተወሳሰበ መልስ ነው ሊኖረኝ የሚችለው። ሳይንሱ እንደሚለው ከሆነ የስልጣን ሳይንስ ነው ፖለቲካ! ስልጣን የመያዝና የማስጠበቅ ነገር ነው። ከእኛ አገር ነባራዊ ሁኔታ ተነስቼ ፖለቲካን ሳየው አንዳንዴ ደስ ደስ የሚል ሌላ ጊዜ ደግሞ መጥፎ ነገር መስሎ የሚታየኝ ወቅት አለ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ትልቅ ነገር የማሰብ፣ ትልቅ የመሆን፣ አገርን ወይም ወገንን ወደ ተሻለ የአስተሳሰብና የአኗኗር ደረጃ ለማድረስ የሚደረግ ትግል ይመስለኛል። የሰው ለሰው ግንኙነት ቀላልና ምቹ የማድረግ ጥበብ መስሎ የሚታሰበኝ ቀንም አለ።

ኢቦኒ፡- እንዴት?

አቶ አስራት፡- ፖለቲካው በደንብ ከገባህ በሁሉም ቦታ ላይ ነው የምታገኘው። ቤትህ ውስጥ ራሱ ልታገኘው ትችላለህ። ከባለቤትህ ጋርና ከልጆችህ ጋር የሚኖርህ ግንኙነትን ሁሉ ሊያጠቃልል ይችላል። ለምሳሌ በወሳኔ አስጣጥህ ይሳተፋሉ ወይ? በእነርሱና በአጠቃላይ የቤተሰብ የጋራ ውሳኔ ላይ ሃሳብ ይሰጣሉ ወይ? አንተስ እንደፊውዳል ጌታ ነው? እንደ ባርያ አሳዳሪ ነው? እንዴት ነው ራስህን የምታንፀባርቀው? ዴሞክራት ነህ? ሌበራል ነህ? እዚህ ላይ ሴት ልጅህ የወንድ ጓደኛዋን ወደ ቤትህ አምጥታ ብታስተዋውቅህ የሚኖርህ ምላሽ እንዴት ያለነው? ያንተ የብቻህ የሆነ ነገርስ ምንድነው? ትዳርህ ምን ሲሆን ነው ግድ የሚሰጥህ? ይህ ትዳር ቢፈርስ ግድ የለኝም የምትልበትስ ጊዜ የሚመጣው ምን ሲሆን ነው? በማንኛውንም ግንኙነት ውስጥ ቀይ መስመሮች አሉ፡፡ ጓደኝነት ምን ዓይነት ሲሆን ነው ቢቀጥል ጠቃሚ የሚሆነው? ቢፈርስ ግድ የማይኖርህስ መቼ ነው? በፍልስፍና መነፅር ስታየው ይህ ሁሉ ፖለቲካ ነው የሚሆነው።