
የሃገራቱን ደረጃ ስፔን በ1532 ነጥብ ስትመራ ፥ ጀርመን በ1273 ነጥብ ሁለተኛ እንዲሁም የላቲኗ ተወካይ ኮሎምቢያ 4 ደረጃዎችን በማሻሻል በ1206 ነጥቦች ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ቡታን ፣ ሳን ማሪኖ እና የተርክስ እና ሳይኮስ ደሴቶች ደግሞ ያለምንም ነጥብ የደረጃውን ግርጌ ይዘው ይገኛሉ።
በዚህ ወር ይፋ በሆነው የሃገራት ደረጃ ፥ ቀጣዩን የአለም ዋንጫ የምታስተናግደው ብራዚል 13 ደረጃ አሻሽላ 9ኛ ደረጃን ስትይዝ ፤ ጣሊያን 2 ደረጃ አሻሽላ 6ኛ በአንጻሩ እንግሊዝ 6 ደረጃዎችን ወደታች ወርዳለች።
በወርሃዊው ደረጃ መሰረት ሴኔጋል ፣ ስኮትላንድ እና ጊኒ ደረጃቸው በከፍተኛ ሁኔታ ሲያሻሽሉ ፥ የዋልያዎቹ የጳጉሜ 3 ተፋላሚ መካከለኛው አፍሪካ ፣ ጃማይካ እና ታይላንድ እስከ 30 ደረጃዎችን ወደ ታች በመውረድ አስከፊ የደረጃ ሽግሽግ አድርገዋል።
ምንጭ፡ የፊፋ ድረ ገጽ
No comments:
Post a Comment