Saturday, January 31, 2015

ሬድዋን ሁሴንና የወደቀው ክሱ !

በኢትዮጵያችን ህግ ትርጉሟን አጥታ፤ፍትህም ተዋርዳ ከተጣለች የህወሃትን እድሜ ብታስቆጥርም እነርሱ ግን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ስለ ህግ የበላይነት ማውራታቸውን አላቆሙም። እነዚህ ቡድኖች የህግ የበላይነት ሲሉ እነርሱ ከፍ ብለው ከህግ በላይ፤ ከእነርሱ መንደር ያለሆነው ደግሞ ዝቅ ብሎ ከሥር ከጫማቸው ሥር ሁኖ እነርሱን ተሸክሞ የሚኖርበትን ሥርዓት ማስጠበቅ የሚችለውን ህግ ነው። እናንተን መሸከም ከበደኝ፤ ቀንበራችሁ ሰበረኝ የሚል ሰው ከተገኘ የሚጠብቀው ፍርድ “አሸባሪነት” ነው። ይህ የክፉዎችና የልበ ደንዳኖች ፍርድ ፍትህ ተብሎ በህወህቶች መንደር ይወደሳል። መፅሃፍ እንዲህ ይላል “ክፍዎች ሰዎች ፍርድን አያስተውሉም”። ህወሃቶች ባወጧቸው ህጎች የስንት ንፁሃን ዜጎች ቤት እንደፈረሰ፤ ስንት ህፃናት አሳዳጊ አልባ እንደሆኑ፤ ስንቶች አገራችውን ትተው ተሰደው እንደጠፉ ቆጥረን አንዘልቀውም። በህወሃት መንደር ህግ ዜጎችን ማጥቂያ እና ማስጨነቂያ መሣሪያ እንጂ የፍትህ ማስከበሪያ መሳሪያ አይደለም። በህወሃት ህግ ብዙ ዜጎች ጠፍተዋል፤ ብዙዎች ደግሞ በብዙ ጭንቀት እና መከራ ውስጥ ይገኛሉ።

በህወሃት መንደር የተሰባሰቡ ግለሰቦች እንደምን ያለ ብርቱ ጭለማ እና ድንቁርና ውስጥ እንደሚገኙ በርካታ ምሳሌዎችን ማንሳት እንችላለን። ለአሁን ግን ማሰብ ካቆሙ ቅጥረኞች መካከል ሬድዋን ሁሴን የተባለው ግለሰብ የሆነውን እንመልከት። ሬድዋን ሁሴን፤ ጌቶቹ እና ሌሎች መሰሎቹ ያሉበትን ዘመን ረስተው ወይም መረዳት ተስኗቸው፤ ከስልጣኔ መንገድም ወጥተው እንዲሁ በጭለማ ዓለም እየተደናበሩ ይገኛሉ። ሬድዋን ሁሴን ያለበትን ዘመንና የያዘው የህዝብ ስልጣን የሚያስከትልበትን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ውጤት መገንዘብ ስለተሳነው ቀና ብሎ ተናገረኝ ባላው ወጣት ላይ በአሜሪካን አገር ክስ መመሥረቱን ስንሰማ በብርቱ ተደንቀናል። አገራችንም በእንደነዚህ ዓይነት ማስተዋል በጎደላቸው ግለሰቦች የምትመራ መሆኑም በእጅጉ ያሳዝነናል።

ሬድዋን ሁሴንን በቨርጂኒያ አገረ ግዛት ያገኘው ወጣት ህወሃቶች በወገኖቹ ላይ የጫኑባቸው ሸክም ያሳመመው፤ በዚህም ህመም የተቆጣ ቁጣውንም በሰላም የመግለፅ መብቱ ያለ ገደብ የተከበረባት አገር ውስጥ ኗሪ ነው። ሬዲዋን ሁሴንን የመሰለ ራሱን ለምናምንቴ ነገር አሳልፎ የሸጠ ትንሽ ግለሰብ ይቅርና የሃያሏ አገር አሜሪካን ፕሬዝዳንትም ብዙ ወቀሳና ስድብ ይደርስበታል።ፕሬዝዳንቱም የህዝብ ተቀጣሪ መሆኑን ስለሚያውቅ ተወቀስኩ ወይም አንድ ዜጋ ተናገረኝ ብሎ የበቀል ሰይፉን አይመዝም። ፕሬዝዳንቱ ተሰደብኩ ብሎ ክፉ ቢናገር የሚከተለው መዘዝ ከስድቡ የበለጠ ጉዳት ስለሚያደርስበት ስድቡን መቻል እና መሸከም የሥራው አንዱ አካል ይሆናል።ህግ ባለበት አገር የአገሩ መሪ ህዝቡን ፈርቶ ይኖራል እንጂ፤ ህዝብ መሪውን ፈርቶ አይኖርም። ሬዲዋንና መሰሎቹ ግን እንዲህ አይደሉም። ህዝብን ረግጠውና አስፈራርተው መኖር የጎበዝ ተግባር ነው ብለው አምነው ተቀብለዋል።

ህወሃት ትንሹንም ትልቁንም ፈርቶ፤ ፍርሃቱ በወለደው ጭካኔ ዜጎችን ሁሉ አስሮ መኖር ልማዱ ሁኗል። በኢትዮጵያ ዜጎች ህወሃቶችን ፈርተው፤ ህወሃቶችም ዜጎችን አስፈራርተው የሚኖሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ይሄ ሁኔታ ለማንም ወይም ለምንም እንደማይበጅ ለህወሃቶች ብንነግራቸውም ልቦናቸው በትዕቢት ታውሯልና አይሰሙንም። ሬድዋን ሁሴንም የዚህ መራራ ትዕቢት ትሩፋት ነው። እንደምን ሁኖ ቀና ብለው ያዩኛል፤ እንደምንስ ሁኖ ይናገሩኛል፤ እንደምንስ ሁኖ ስሜ በገበያ መሃል ይነሳል የሚል ትዕቢት ስለተፀናወተው ክስ መሠረተ፤ ክሱ ግን በህግ ፊት ሚዛን የማይደፋ በመሆኑ በአቃቤ ህጉ ውድቅ ተደረገ። ሬዲዋንም የፍትህን መራራ ፅዋ ተጎንጭቶ ሊውጣት ግድ ሆነበት። የህወሃት ቅጥረኞችና ህወሃቶች ውድቅ ከሆነው ከሬድዋን ህሴን ክስ

Zone 9 Bloggers Move to Trial on Amended ATP Charges in Ethiopia

Press Statement
Jen Psaki
Department Spokesperson
Washington, DC
January 29, 2015
 
 
The United States is concerned by the Ethiopian Federal High Court’s January 28, 2015, decision to proceed with the trial of six bloggers and three independent journalists on charges under the Anti-Terrorism Proclamation. The decision undermines a free and open media environment—critical elements for credible and democratic elections, which Ethiopia will hold in May 2015.

We urge the Ethiopian government to ensure that the trial is fair, transparent, and in compliance with Ethiopia’s constitutional guarantees and international human rights obligations. We also urge the Ethiopian government to ensure that the trial is free of political influence and continues to be open to public observation.

The use of the Anti-Terrorism Proclamation in previous cases against journalists, activists, and opposition political figures raises serious questions about the implementation of the law and about the sanctity of Ethiopians’ constitutionally guaranteed rights to freedom of the press and freedom of expression.

Freedom of expression and freedom of the press are fundamental elements of a democratic society. We call on the government of Ethiopia to support freedom of expression and freedom of the press to demonstrate its commitment to democracy as it approaches its May 2015 national elections.

Friday, January 30, 2015

ለህዝባዊ አመፅ ታጥቀን እንነሳ!

በቅዱስ ዮሃንስ

የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነቱን በትግሉ እንዲቀዳጅ በህብረት ለመታገል በያለበት እንደራጅ፡፡ ይህንን ለማለት ያነሳሳኝ ዋናው ጉዳይ ዘራኛውና አፋኙ ህውሀት መራሹ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በርካታ ዘግናኝ ወንጀሎችን ፈፅሟል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ያለ አግባብ ከመሬተታቸውና ከቤት ንብረታቸው መፈናቀል የዘረኛውን ስርዓት የተቃወሙትን የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ ተኩስ በመክፈት በመቶ ሺህ በሚቆጠሩ ንፁሀን ላይ ግድያና የአካል ጉዳት ፈፅሟል፡፡ ብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለው የወደፊት ራዕያቸው ድቅድቅ ጨለማ ተላብሷል፡፡ የዞን 9 አባላት የመብትና ዲሞክራሲያዊ ጥያቄ በማቅረባቸው እስር ቤት ተወርውረው የስነ ልቦና ጥቃት እየተፈፀመባቸው በሰቃይና በመከራ ህይወታቸውን እየመሩ ይገኛሉ፡፡ በወለጋ ክ/ሀገር በሺህ የሚቆጠር የአማራ ተወላጆች ላይ በኢህዴድ ካድሬዎች ጥቃት ደርሶባቸው ቤት ንብረታቸውን አጥተው ትቢያ ላይ ወድቀው ይገኛሉ። የጋንቤላ ተወላጆች ሌሎችም የሀገራችን ልጆች ላይ የስርዓቱን አስከፊነት በመቃወም ከሀገር ወደ ጎረቤት ሀገር በስደት የሚገኙትን ዜጎቻችንን በአፋኝ የፀጥታ ሀይል ሰራተኞች ታፍነው ከፍተኛ ድብደባና እንግልት ሰቆቃ ከተፈፀመባቸው በሁዋላ በሽብር ወንጀል ተፈርጀው ወደ ዘብጥያ ተወርውረዋል፡፡ እናት ሀገር ኢትዮጵያ ፋሽስታዊና አምባገነናዊ ወንጀል ሳቢያ ክብሯን፣ ነፃነቷን፣ ሰብአዊ መብቷን አጥታ ሊጆቿም መብት፣ ክብር ነፃነት አልባ ሆነው በወያኔ ፍርፋሪ ሆዳቸው ያበጠ በሆድ አደር ካድሬዎች እየተረገጡና እየተገረፉ እየተረገጡና እየተገረፉ ሰቆቃ ህይወት በቃሊቲ እየመሩ ይገኛሉ፡፡ ባጭሩ ከላይ እንደዘረዘርኩት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገውን ግፍና በደል ሳያበቃ በቅርበዩ ለፍትህ፣ ለመብት፣ ለዲሞክራሲ እኩልነት ብሎ የሞቀ ቤቱን ጥሎ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚታገለው ሀቀኛ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ የግንቦት 7 ዋና ፀሀፊ በአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ላይ የፋሺስቱ ወያኔ መንግስት አፍኖና አግቶ ይገኛል፡፡

ስለዚህ ይኼንን ከፍተኛ ታጋይ ለማስፈታት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የፆታ የዘር የሃይማኖት ልዩነት ሳይኖረን በጋራ የተባበረ የጋራ ድምፃችንን ለዓለም አቀፍ ህብረተሰብ ማሳወቅ ግዴታን ሲሆን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ህውሀት ለመደምሰስ ቆርጠን ባንድ ላይ በተባበረ ክንድ የህወሃትት አፓርታይድ ስርአትን ለመደምሰስ እንደራጅ ጊዜው አሁን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነቱን በትግሉ እንዲቀዳጅ በጋራ ለመታገል በያለንበት እንደራጅ በጋራ እንነሳ! አገራችንን ከአውሬዎች ለማዳን ሁለገብ ትግል እናፋፍም የአንዳርጋቸው ፅጌን ራዕይ ለማሳካት ሁላችንም በቆራጥነት ለትግል እንነሳ፡፡

ድል የህዝብ ነው!

Thursday, January 29, 2015

Ethiopian Government Intensifies Crackdown on Dissent

Ethiopia Crackdown on Dissent Intensifies(Human Rights Watch, Nairobi) – The Ethiopian government during 2014 intensified its campaign of arrests, prosecutions, and unlawful force to silence criticism, Human Rights Watch said today in its World Report 2015. The government responded to peaceful protests with harassment, threats, and arbitrary detention, and used draconian laws to further repress journalists, opposition activists, and critics.
“The Ethiopian government fell back on tried and true measures to muzzle any perceived dissent in 2014,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “Journalists and dissenters suffered most, snuffing out any hope that the government would widen political space ahead of the May 2015 elections.”

In the 656-page world report, its 25th edition, Human Rights Watch reviews human rights practices in more than 90 countries. In his introductory essay, Executive Director Kenneth Roth urges governments to recognize that human rights offer an effective moral guide in turbulent times, and that violating rights can spark or aggravate serious security challenges. The short-term gains of undermining core values of freedom and non-discrimination are rarely worth the long-term price.

Ethiopia’s dismal rights record faced little criticism from donor countries in 2014. Throughout the year, state security forces harassed and detained leaders and supporters of Ethiopian opposition parties. Security personnel responded to protests in Oromia in April and May with excessive force, resulting in the deaths of at least several dozen people, and the arrests of hundreds more. The authorities regularly blocked the Semawayi (Blue) Party’s attempts to hold protests.

Wednesday, January 28, 2015

በውንብድና የሚቆም የነፃነት ትግል አይኖርም!


በነብዩ ኃይሉ

እጥፍ ወርቅ በልስቲ በአንድነት ፓርቲ ውስጥ በተለያዩ የአመራርነት ቦታዎች ላይ ተሳትፋለች፡፡ እጥፍ ወርቅ የሰባት ወር ነብሰጡር መሆንዋ ህወሓት/ኢህአዴግ እና ምርጫ ቦርድ ብዙ ዋጋ የከፈለችበት ፓርቲ ላይ የሚያደርሱትን የማፍረስ ሴራ ተቃውማ ሰልፍ ከመውጣት አላገዳትም፡፡ በሰልፉ ላይ የገዢው ቡድን ፖሊሶችና የደህንነቶች ሲያዩዋት ደሟን ሊያፈሱ ቋመጡ፤ በአንዲት እንደ ቤተክርስቲያን ተሳላሚ ተከናንባ ቀበና መድሃኔዓለም ቤተክርስቲያንን በተደገፈች ወኪላቸውም ጥቆማ ጐትተው መሬት ላይ ጣሏት፤ አንገቷ ላይ የነበረውንም የወርቅ ሀብል በጥሰው በእጃቸው አደረጉ፡፡ ‹‹ነብሰጡር ነኝ፣ ሀላፊነቱን ትወስዳላችሁ›› እያለች ብትሟገትም ሽንጧ ላይ በጫማቸው ከመርገጥና በዱላ ጉዳት ከማድረስ አልተቆጠቡም፡፡

ለዘመናት በአገዛዝ ስርዓት ውስጥ ለማቀቀች እንደ ኢትዮጵያ አይነቷ ሀገር መንግስታት በዜጐቻቸው ላይ የሚወስዱት የሀይል እርምጃ አዲስ ላይሆን ይችላል፡፡ የህወሓት/ኢህአዴግ ተግባር ግን “መንግስት” ተብሎ እንዲጠራ የሚያደርገው አይደለም፡፡ ሽፍታ ለማለትም አይመጥንም፤ ሽፍታዎች ቢያንስ ለህፃናት፣ ለሴቶች እና ለአረጋውያን የርህራሄ ስሜት ያሳያሉ፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ ጋር ይህ አይታሰብም፤ ገዢው ቡድን ደም ማፍሰሱ የሚያረካው፣ የሚያስፎክረው፣ በማን አህሎኝነት የተወጠረ የወንበዴ ስብስብ ነው፡፡ ገዢውን ቡድን ከመንግስትነት ያስቆጠረው፣ በጭካኔ ተግባሩ ያስቀጠለው ግፍ መቀበልን የለመደው ድርቡ ቆዳችን ነው፡፡

በኢትዮጵያችን “ፖሊስ የህዝብ ነው” የሚለው አባባል ፌዝ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ፖሊሶች ህዝባዊነታቸውን ትተውና ረስተው
ለስርአቱ አድረዋል፡፡ ከህግ ይልቅ ደም ለጠማቸው አዛዦቻቸው ቅድሚያ በመስጠት ደም ለማፍሰስ ሲተጉ ይታያሉ፡፡ ወንጀል ተከላክለው ሳይሆን የንፁሀንን ደም አፍስሰው የሚሰጣቸው ሹመትና ሽልማት ከፍ ያለ ነው፡፡ የገዢው ፓርቲ ፖሊሶች ባለፈው ዕሁድ ጥር 17 ከአንድነት ጽ/ቤት የወጣውን ሰልፈኛ ደም ለማፍሰስ የተጠቀሙት ህወሓት በረሃ እያለ የሚጠቀምበትን የቆረጣ ስልት ነው፡፡ ያህንን ስልት ባለፈው አመት ሰማያዊ ፓርቲ ሳውዲ ኤምባሲ አቅራቢያ ባደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ላይም ተጠቅመውበታል፡፡ ፖሊሶቹ ሰልፈኛውን ለመበተን በአንድ አቅጣጫ ብቻ መንገድ መዝጋት በቂያቸው ነበር፤ ሆኖም የደም ግብር ያለባቸውን የገዢውን ቡድን ባለስልጠናት ለማስደሰት ሲሉ ሰልፈኛውን በሁሉም አቅጣጫ ከበው የግፍ በትራቸውን አሳረፉ፤የሻቸውንም ዘረፉ፡፡

ባሳለፍነው እሁድ የአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ላይ የተወሰደው ፍጹም ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት፤ ገዢው ቡድን ደም በማፍሰስ የሚረካ የወንበዴ ስብስብ እንደሆነ የሚያረጋግጥ ነው፡፡ የገዢው ቡድን ፖሊሶችና ደህንነቶች፣ አንድነት የጠራውን ሰልፍ ለማጨናገፍ ያለሙ ብቻ ሳይሆኑ የሰዎችን ደም ማፍሰስንም ግባቸው ያደረጉ ነበሩ፡፡ ለዚህም ነው የሰባት ወር እርጉዝ መሬት ላይ ጥለው በጭካኔ የረገጡት፣ ለዚህ ነው የአምልኮ ስፍራን በደም በተጨማለቀ ርካሽ ማንነታቸው አርክሰው በፀሎት ላይ የነበሩ የ70 አመት አሮጊት በጭካኔ የደበደቡት፣ ለዚህ ነው እጁ ተሰብሮ የወደቀን ጋዜጠኛ ከበው እንደ እባብ የቀጠቀጡት! ለዚህ ነው በድብደባው ባለመርካት ሴት ልጅ የያዘችውን ቦርሳ ወርቅና ሞባይል ቀምተው መሬት ላይ በመጣል ልብሷን የሚቀዳድዱት፡፡ ለዚህ ነው ከሰውነት አስተሳሰብ ወርደው የአውሬን ጭካኔ የተላበሱ ኃይሎች የነፃነት ታጋዮች ላይ በጠራራ ፀሐይ ውንብድና በመፈፀም የነፃነት ትግልን ለማስቆም የሚውተረተሩት፡፡

ገዢው ቡድን፣ ባሰለፈው ሰራዊትና በመሣሪያው ብዛት ተማምኖ የሚፈፅመው የአውሬ ተግባር በየትኛውም መለኪያ የነፃነት ትግሉን እንደማይገታው የሚያረጋግጠው እንደ ህወሓት/ኢህአዴግ በአውሬነት የብዙ ንፁሃንን ደም በጠራራ ፀሐይ ያፈሰሰው የግራዚያኒ ተግባር ነው፡፡ ግራዚያኒ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ደም ቢያፈስም የነፃነት ትግሉ ግን አልቆመም፡፡ የግራዚያኒ የግፍ ተጋሪ የህወሓት/ኢህአዴግ ተግባርም ትግሉን ከማፋፋም ባለፈ እንደማያኮስሰው መሰል አምባገነኖች ታሪክ ምስክር ነው፡፡

Tuesday, January 27, 2015

የሰላም በሮች ሲዘጉ የሁለገብ ትግል ስልት በሮች ይከፈታሉ!!!

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ አማካይነት እየደረሰበት ያለውን በደል ለሕዝብ ለማሰማት ጥር 17 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ጂንካና ሸዋ ሮቢት የተቃውሞ ሰልፎችን ጠርቶ ነበር። በተለይ በአዲስ አበባው ሰልፍ ላይ የተገኙ ወገኖቻችን ለህወሓት ፍጹም ታማኝ በሆነው የፓሊስ ክፍል ያለርህራሄ መደብደባቸው እና የተቃውሞ ሰልፉም በጉልበት መበተኑ ነፃነትና ፍትህ ናፋቂውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያሳዘነ ብቻ ሳይሆነ ያስቆጨ ጉዳይ ነው። በመላው ዓለም በሚደረጉ የተቃውሞ ሰልፎች ላይ የተለመደውን ድንጋይ ውርወራ እንኳን ሳይከጅሉ፤ የፓሊሶችን ሰብዓዊ ርህራሄ ለማግኘት “ፓሊስ የኛ ነው” እያሉ እየዘመሩ በፓሊስ ተደበደቡ። ሴቶችና አዛውንት ብቻ ሳይሆን ተላላፊ መንገደኞች እንኳን ከፓሊስ ዱላ አላመለጡም። ከሁሉም በላይ የሚዘገንነው ደግሞ የ 7 ወራት ነብሰ ጡር ሴትም በፓሊስ መመታትዋና ሆዷ መረገጡ ነው። ይህ እኩይ ተግባር የሚፈጥረው ቁጭት በህወሓት ላይ ብቻ አያበቃም። ትዝብቱ ለፓሊስም ተርፏል። ይህ የጭካኔ ተግባር ለፍትህና ለነፃነት በሚደረገው ትግል የሕዝብ አጋር ይሆናል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የፓሊስ ሠራዊትን የሚያዋርድ ነው። ደካማ እናቶችን፣ አረጋዊያንን፣ ባዶ እጃቸውን ተቃውሞ እያሰሙ ያሉትን ወጣቶችንና ነፍሰጡሮችን በጭካኔ መደብደብ ለራሱና ለሥራው ክብር ለሚሰማው ፓሊስ ውርደት ነው፤ የሞት ሞት ነው። የኢትዮጵያ የፓሊስ ሠራዊት አባላት ተግባራቸው ያሳፍራቸዋል፣ ይቆጫቸዋል፤ ቁጭታቸውንም ይህን ትዕዛዝ በሰጡ አለቆቻቸው ላይ በግልም ሆነ በተደራጀ መንገድ በሚወስዱት እርምጃ እናያለን ብሎ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ ያደርጋል።

የጥር 17 ቀን 2007ቱ ሽብር በአንድ ወቅት የተፈጠረ፤ በአንድነት ፓርቲ ላይ ብቻ ያነጣጠረ፣ የተናጠል ክስተት ሳይሆን ህወሓት ደግሞ ደጋግሞ ሲፈጽመው የነበረ ነው። ከዚህ በፊት በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ ፈጽሞታል። የአዲስ አበባ ከተማ ማስተር ፕላንን በተቃወሙ የተለያዩ ዩንቨርስቲዎች ተማሪዎች በተለይም በአምቦ ላይ የብዙዎችን ሕይወት የቀጠፈ ሽብር ነዝቷል። በቅርቡ ደግሞ በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ተመሳሳይ አረመናዊ ድርጊት ፈጽሟል።

አርበኞች ግንቦት 7: ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የህወሓት ታጣቂዎች በወገኖቻችን ላይ ያደረሱትን ድብደባ፣ ህገወጥ እስር፣ እና የተቃውሞ ሰልፍ ክልከላን አጥብቆ ይቃወማል። አርበኞች ግንቦት 7፣ በወገኖቻችን ላይ የደረሰው ህመም ህመሙ፣ ቁስላቸው ቁስሉ ነው።

ባለፉት ሃያ ሶስት ተከታታይ ዓመታት፣ በአምቦ፣ በጅማና በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞችና ገጠሮች፣ በባህዳር፣በጎንደርና በበርካታ የአማራ ከተሞችና ገጠሮች፣ በጋምቤላ፣ በሶማሊ፣ በአፋር፤ በአጠቃላይ በመላው ኢትዮጵያ በየአስፋልቱ፣ በየሜዳውና በየጥሻው በህወሓትና ተላላኪዎቻቸው የፈሰሰው የኢትዮጵያውያን ደም በከንቱ ፈሶ መቅረት የለበትም ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። አርበኞች ግንቦት 7 ከሌሎች መሰል ድርጅቶች ጋር በመተባበር የህወሓትን እድሜ በማሳጠር የእናቶቻችን እምባ ሊያብስ ዝግጁ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ኢትዮጵዊያን እንደከብት እየተደበደቡ ወደ ማጎሪያ የሚያጋዙበት እና በጠገቡ ሰላዮችና ፓሊሶች እየታነቁ የሚታረዱበት ጊዜ ማብቃት አለበት ይላል።

የቱን ያህል ቢለመንም ሆነ ቢወገዝ ህወሓት ለነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒን ምርጫ ዝግጁ ሊሆን ቀርቶ በምርጫ የሚወዳደሩት ፓርቲዎች እነማን እንደሆኑና እነማን በእጩ ተወዳደሪነት መቅረብ እንዳለባቸው ሳይቀር የሚወስን ዓይን አውጣ አጭበርባሪ ድርጅት ነው። ይህንን ከዚህ በፊት አይተነዋል፤ አሁንም በአንድነትና በመኢአድ ላይ እየተደገመ ነው። ህወሓት፣ በየአምስቱ ዓመታቱ በሚያደርጋቸው የሴራ ምርጫዎች በሚቀጥሉት አርባና ከዚያም በላይ ለሆኑ ዓመታት በሥልጣን ላይ የሚቆይበትን ስልት ቀይሶ የሚንቀሳቀስ፤ ኢትዮጵያን ለብዙ ዓመታት ለመግዛት ማድረግ የሚችለውን ክፋት ሁሉ ከማድረግ የማይመለስ አገር በቀል ቅኝ ገዥ ነው። ህወሓት የዘረጋው ሥርዓት ህገ-አልባነት፣ ፀረ-ሕዝብነት እና አምባገንነት ለማጋለጥ በሚል ርህራሄን በማያውቁ የሥርዓቱ አገልጋዮች ፊት ባዶ እጅ መጋፈጥ የሚፈጥረው የሞራል የበላይነትና የመንፈስ ጀግንነት ባያጠራጥርም የሚያስከፍለው ዋጋ ከሚገኘው ውጤት ጋር ማመዛዘን ግን እጅግ ተገቢ የሆነ የማይታለፍ ሥራ ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል።

Sunday, January 25, 2015

United Nations Review Should Condemn Crackdown – Human Rights Watch

Activists, Journalists Persecuted Under Draconian Laws

(Geneva) – United Nations member countries should call on Ethiopia to stop targeting activists and the media under draconian laws. The UN Human Rights Council will review Ethiopia’s human rights record under the Universal Periodic Review (UPR) procedure on May 6, 2014.

A Human Rights Watch submission to the UN on Ethiopia highlights its ongoing suppression of the media and nongovernmental organizations, and the lack of accountability for torture and other serious abuses by its security forces. The arbitrary arrest of nine bloggers and journalists on April 25 and 26, just 10 days before the review, reflects Ethiopia’s blatant disregard for fundamental rights and should be strongly condemned by UN members.

“The UN review is taking place just as Ethiopia is renewing its crackdown on free speech,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “To make this review meaningful, UN member countries should forcefully tell Ethiopia that its attacks on the media and activist groups are a blight on its human rights record.”
Since Ethiopia’s first UPR review in 2009, the human rights situation has deteriorated substantially. The authorities have shown harsh intolerance of any criticism of government actions and have sharply restricted the rights to free expression and association.

Despite Ethiopia’s commitment during the 2009 review to take “measures to provide for free and independent media,” Ethiopia now has one of the most repressive media environments in the world. Numerous journalists languish in prison, independent media outlets have been closed down, and many journalists have fled the country.

Critics of government policy – including journalists, rights activists, and opposition party supporters – risk harassment, arbitrary detention, and politically motivated prosecutions. Many prosecutions are carried out under repressive laws that have dramatically curtailed the ability of independent Ethiopian and international organizations to investigate and report on human rights violations and other concerns.

UK diplomats clash over Briton on death row in Ethiopia: Officials' fury after Foreign Secretary claims he couldn't 'find time' to help father-of-three facing execution


  • Andargachew Tsege was snatched by officials at Yemen airport last June
  • The 59-year-old was transferred to Ethiopia where he is thought to remain
  • Father-of-three moved to London in 1979 from native African country
  • He was dubbed 'Ethiopian Mandela' after exposing government corruption
  • Leaked emails revealed British officials' frustration at political inaction
  • Philip Hammond said he could not 'find time' for phone call on issue 


An explosive row has erupted between diplomats and Ministers over their reluctance to help a British man on death row in Ethiopia.

A series of extraordinary emails, obtained by The Mail on Sunday, reveal officials’ increasing frustration at political inaction over Andargachew Tsege.

Tsege, 59, a father-of-three from London, was snatched at an airport in Yemen last June and illegally rendered to Ethiopia. There are concerns he may have been tortured.

Yet Foreign Secretary Philip Hammond said he could not ‘find time’ for a phone call to raise the issue and did not want to send a ‘negative’ letter.

In one email, an exasperated official asks: ‘Don’t we need to do more than give them a stern talking to?’

Tsege, who has lived in the UK since 1979, has been called Ethiopia’s Nelson Mandela. Tsege fell out with his university friend ex-Prime Minister Meles Zenawi, after he exposed government corruption and helped establish a pro-democracy party.

In 2009, he was sentenced to death in his absence for allegedly plotting a coup and planning to kill Ethiopian officials – claims he denies.

He was abducted on June 23 while en route to Eritrea, emerging two weeks later in Ethiopia, where he has since been paraded on TV. It is not known where he is being held.

Saturday, January 24, 2015

እንኳን ደህና መጡ ወደ ወያኔ 2007 የምርጫ ጨዋታ!

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ እኔ ዳኛ ነኝ እያለ ቢለፍፍም አብዛኛው ኢትዮጵያዊ የምርጫ ቦርድ የወያኔ/ኢህአዴግ የመሃል ተጫዋች እንደሆነ ይገነዘባል። ይህ የዳኝነት ካባ ለብሶ የወያኔን የአጥቂ መስመር የሚመራ አካል በአሁኑ ሰዓት ዋነኛው ስራው የዳኝነት ካባውን ተጠቅሞ ጨዋታው ሲጀመር ለቡድኑ ወያኔ የሚያሰጉትን ጠንካራ ተቃዋሚዎች እና ፖለቲከኞች ሰበብ አስባብ እየፈለገ (Disqualify) እያለ ምርጫው ውስጥ እንዳይገቡ መከላከል ነው። በመኢሕአድ እና አንድነት ፓርቲ ላይ እያደረገ ያለውን ልብ ይበሉ።

የወያኔው ቋሚ ተሰላፊ ምርጫ ቦርድ ተቃዋሚዎቹን ሁሉ ምርጫ ውስጥ እንዳይገቡ ቢከለክል ምርጫ ተብዬው ጨዋታ ሊኖር አይችልም፣ ስለዚህ ወያኔን በምርጫው ወቅት የሚያጫውቱት ቡድኖች ስለሚያስፈልጉ አንዳንዶችን ያሳትፋል።

የምርጫው ቦርድ ጨዋታው በሚካሄድበት ወቅት ቡድኑ ወያኔ ሲጠቃ የዳኝነት ካባውን ደርቦ ከች ይልና ባሰማራቸው የምርጫ ድምጽ ቆጣሪዎች እና ታዛቢዎች (ሁሉም የወያኔ ካድሬዎች ናቸው) አማካኝነት ኮሮጆ ዘቅዝቆና ቀመሩን አስተካክሎ ቡድኑ ወያኔ 99.6% ድምጽ በማግኘት እንዳሸነፈ ያውጃል።

እንኳን ደህና መጡ ወደ ወያኔ 2007 የምርጫ ጨዋታ!

አንድነት ፓርቲ የምርጫ ቦርድ የሸረበበትን ሴራ ለመቃወም እሁድ ጥር 17 – 2007 ዓ.ም አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች ህዝባዊ ሰልፎችን ጠርቷል። ለዚህም አባላቱ የሰልፉን ጥሪ ለህዝብ ለማድረስ ከወያኔ ደህንነቶች ጋር እየተናነቁ ቅስቀሳውን ተያይዘውታል። መንግስት ተብዬው የወሮ በላ ቡድን አንድነት ፓርቲ በድንገት የጠራውን ሰልፍ እንዲተው ወይንም ቀኑን እንዲቀይረው ማስፈራራትንና መለማመጥን እያቀያየረ ለማግባባት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል።

እስርና ወከባም ተጧጡፏል!

ነብዩ ሃይሉ እስርን በተመለከተ እንዲህ ብሏል

“ቀደም ሲል በደህንነት ሃይሎች በቅስቀሳ ላይ ሳሉ በቁጥጥር ስር የዋሉትን የአንድነት ፓርቲ የብሄራዊ ምክር ቤት አባላት አቶ ያሬድ አለማሁ እና አቶ ሲሳይ ጌትነት ለመጠየቅ ባልደራስ አካባቢ ወደሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ያመሩት የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ለገሰ ተፋረደኝ ለእስረኞቹ እራት ለመግዛት በእቅራቢያው ወደሚገኝ ምግብ ቤት በማምራት ላይ ሳሉ ሲቢል በለበሱ ደህንነቶች አማካይነት ከዛንቺስ አካባቢ ወደሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ መወሰዳቸው ታውቋል፡፡”

እሁድ ጥር 17 – 2007 ዓ.ም የተጠራው ህዝባዊ ተቃውሞ አይታጠፍም! (አንድነት ፓርቲ)

ያለ ነጻ ሚዲያ – ምርጫ ወይስ ቁማር?

የሰብዓዊ መብት ድርጅት ሰሞኑን ሥጋቱን ይፋ ሊያደርግ ነው!

* ኢህአዴግ አሸነፈ፤ ፋና መሰከረ!

ምርጫ ያለ ነጻ ሚዲያ ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችል ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ተመልካች (Human Rights Watch) በያዝነው ሳምንት ማገባደጃ አካባቢ በኢትዮጵያ የሚዲያ ነጻነትን አስመልክቶ አጠቃላይ ዘገባ እንደሚያወጣ ተሰማ፡፡

ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ መረጃውን ያቀረቡና ከዘገባው ጋር ተዛማጅነት ክፍሎች እንደተናገሩት የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ይህንን ዘገባ ያጠናቀረው በተጨባጭ ከሚዲያ ጋር በተያያዘ ሰለባ የሆኑትን በሚዲያው መስክ የተሰማሩትን በማነጋገርና የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ በመሰብሰብ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ዘገባው ከዚህ በፊት ከወጡት ዘገባዎች ለየት ባለ መልኩ በፕሬስ ሚዲያው ላይ የተሰማሩትን ክፍሎች በስፋት የዳሰሰ ነው፡፡ በተለምዶው በጋዜጠኞች ላይ የሚደረገው አፈና በብዙ መልኩ የሚነገር ሲሆን በዚህ ዘገባ ግን ኢህአዴግ በአሳታሚነት፣ በአከፋፋይነት፣ በአታሚነት፣ በሻጭነት (አዟሪነት)፣ ወዘተ የተሰማሩትን እንዴት ስልታዊ በሆነ መልኩ እንደሚያዳክም፣ እንደሚያፍን፣ እንደሚያሰቃይና ባጠቃላይ ከሜዳው እንደሚያስወግድ የሚያስረዳ እንደሚሆን ጎልጉል ካገኘው መረጃ ለመገመት ተችሏል፡፡

በመጪው ግንቦት ከሚካሄደው ምርጫ ጋር በማያያዝ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ዘገባ በተለይ የኢህአዴግን ቋት የሚሞሉ ለጋሽ አገራት፣ ዓለምአቀፍ የፍትሕ አካላት፣ የሲቪክ ማኅበረሰቦች፣ ወዘተ ከወዲሁ ግንዛቤ ይዘው ኢህአዴግ አደርገዋለሁ ለሚለው “ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ” ምርጫ ያለ ነጻ ሚዲያ ተሳትፎ እንዴት ውጤት አልባ እንደሆነ የሚያስረዳና ጠለቅ ያለ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

በዘንድሮው ምርጫ ባልተጠበቀና ለመቀበል በሚያስቸግር መልኩ የአውሮጳ ኅብረት “በጀት የለም” በሚል ምርጫውን አልታዘብምም ብሏል፡፡ በይፋ የተሰጠው ምክንያት ይህ ቢሆንም ጉዳዩ የበጀት ሳይሆን “ኢህአዴግ ከኢህአዴግ ጋር የሚያደርገውን የ99.6 በመቶ የምርጫ ውጤት መታዘብ በራሱ ያስታዝባል” በሚል ነው ኅብረቱ ምርጫ መታዘቡን በቅድሚያ ትዝብት የተወው በማለት የተሳለቁ መኖራቸው ተሰምቷል፡፡ ሆኖም ግን ኢህአዴግ በበኩሉ “ባትታዘቡ ምን ገደደኝ” በማለት ኅብረቱ ምርጫውን ለመታዘብ አለመፈለጉን በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ትዝብት አልፎታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በዚህ ስለ ሚዲያ ነጻነት በሚያትተው አዲስ ዘገባና በኅብረቱ ውሳኔ ዙሪያ ኢህአዴግ “ዓለምአቀፋዊ ሽልማት ባገኙ የዘርፉ ባለሙያዎቹ” ተጠቅሞ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዴት ባለ “ነጻነት” የሚዲያ ሥራ እንደሚሠሩ በነዚሁ “ሚዲያዎች” ምላሽ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡

Thursday, January 22, 2015

ኢትዮጵያ የማን ነች?

“ኢትዮጵያ የማን አገር ነች” የሚል ጥያቄ ከዚህም ከዚያም እየተሰማ ነው። ህወሃቶች ከፈጠሯቸው ቀውሶች መካከል አንዱ ይሄው ነው። ዜጎች የአገር አልባነት ስሜት ውስጥ ገብተው የገዛ አገራቸውን “የማን ነች” ብለው እንዲጠይቁ መገደዳቸው።

ለኢትዮጵያዊያኑ ኢትዮጵያ አገራቸው እየሆነችላቸው አይደለም። ኢትዮጵያዊ መሆን ወንጀል እስኪመስል ድረስ በዜጎች ላይ ግፍ እየተፈፀመ ነው። የሚፈፀመው የግፍ ዓይነት ወሰን የለውም። ግማሹ በጠራራ ፀሃይ ደሙ እንዲፈስ ይደረጋል። ሌላው ለቁም ስቃይ ወደ ወይኒ ይጋዛል። ቀሪውም እትብቱ የተቀበረበትን አገር ትቶ ለመሰደድ ይገደዳል። በአገሪቷ ውስጥ የሚፈፀመውን ወሰን አልባ በደል የተመለከቱ ኢትዮጵያን ከውዳቂ መንግስታት ተራ መድበዋታል። በኢትዮጵያችን የዜጎችን መብት አስከብሮ ለመምራት ብቃት ያለው መንግስት ባለመኖሩ እጣ ፈንታችን እንዲህ ከውዳቂ አገራት ተርታ መግባት ሁኗል።

ኢትዮጵያን ለመምራት ብቃት ያለው መንግስት ቢኖር ኑሮ ለረዥም ዘመን በሰላም ተጎራብተው ይኖሩ በነበሩ ህዝቦች መካከል ግጭት ተፈጠረ መባልን ባልሰማን ነበር።ህወሃት አገሪቷን ከተቆጣጠረ ዘመን ጀምሮ ሆን ተብሎ በሚፈጠር ግጭት ብዙ ደም ፈሷል። አማራው ከኦሮሞው፤ ትግሬው ከአማራው እና ከአፋሩ፤ ሶማሌው ከኦሮሞ፤ኦሮሞው ከጉጂው፤ ኑዌር ከአኙዋክ፤ ዲዚ ከሱርማ፤ ሌሎችም ብዙ ግጭቶች በየቀየው ተፈጥረው አይተናል። የብዙ ዜጎችም ህይወት ተቀጥፏል። ይሄ ሁሉ ደም መፋሰስ የሚከሰተው ህወሃት ከህዝብ ፈቃድ ያልሆነ እና ከህዝቡ የተለየ በመሆኑ ነው።

ህወሃቶች ከህዝብ የተለዩ ብቻ ሳይሆኑ የህዝብ ጠላት መሆንን የመረጡ ብድኖች ስለመሆናቸው ብዙ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። ህወሃቶች “አማራና ተፈጥሮ” የትግራይ ህዝብ ጠላቶች ናቸው ብለው መፃፋቸው እና ማስተማራቸው የህዝብ ጠላት መሆንን ስለመምረጣቸው ቋሚ ምስክር ነው። ህወሃቶች በስልጣን የሚያቆየን በህዝቦች መካከል የሚፈጠረው አለመተማመንና የጠላትነት ስሜት ብቻ ነው ብለው ከልባቸው ያምናሉ። በህዝቦች መካከል የሚፈጠረው አብሮነት፤ አብሮነቱን ለማዘመን የሚረዳ መተማመን፤ ይሄም የሚወልደው አንድነትና ህብረት በህወሃት ዘንድ የሚወደድ ነገር አይደለም። በህወሃት ዘንድ የሚወደደው በህዝብ መካከል የሚፈጠረው የአለመተማመን ስሜት ይህም አለመተማመን የሚወልደው ግጭት ነው። ግጭት ተፈጥሮ የንፁህ ደም ሲፈስ በህወሃቶች መንደር ደስታ ይሆናል።በዜጎቹ ግጭት እና ደም መፋሰስ ተደስቶ የሚኖር ቡድን እንደ ህወሃት ዓይነት በየትም አገር ታይቶ አይታወቅም።

ከሰሞኑ በአማራ ክልል ነዋሪዎችና በትግራይ ክልል ነዋሪዎች መካከል ግጭት ተከሰተ መባልን ሰምተናል። ይሄ በጣም አሳፋሪና አሳዛኝ ነገር ነው። ህወሃት ከመፈጠሩ በፊት በሠላም ተጎራብቶ የሚኖር ህዝብ ዛሬ ደም መፋሰስ ደረጃ ወደ ሚያደርሰው ግጭት ተሻግሮ መስማታችን አሳፋሪ ነው። ህወሃቶች ከመቸውም ግዜ በላይ የኢትዮጵያ አንድነት ተጠናክሯል እያሉ ሳይታክቱ በሚያወሩበት በዚህ ግዜ አብሮ ለብዙ ዘመን የኖር ህዝብ ወደ ግጭት የመግባቱ ነገር የህወሃቶች ትሩፋት ሁኖ እናገኘዋለን። ህወሃቶች በዘመናቸው ካተረፉልን ቀውሶች መካከል ሳይጠቀስ የማይታለፈው በህዝቦች መካከል የሚፈጥሩት ግጭት ነው። በህዝቦች መካከል በሚፈጠረው ግጭት ብቻ እድሜያችን ይረዝማል ብለው ማመናቸው ህወሃቶች የገበቡት የክፋት አዘቀት ምን ያክል ጥልቅ እንደሆነ ያሰየናል።

ጥላቻ ለህወሃቶች የመኖሪያቸው ድንኳን ሁኖ አቆይቷቸዋል። ከእነርሱ ያልሆኑት በሙሉ ከጠላትነት በታች ስፍራ የላቸውም። ሁሉንም ጠላት አድርጎ ማየት ደግሞ ከፍርሃት እና በራስ ላይ ዕምነት ከማጣት የሚመነጭ መሆኑ ይታወቃል። አሁን አሁን እነዚህ ቡድኖች ፍራቻቸው ፈሩን ለቆ የራሳቸውን ጥላ የመፍራት ደረጃ ላይ ደርሰዋል። የራሱን ጥላ መፍራት የጀመረ ቡድን ራዕይ ኖሮት በሰከነ መንፈስ አገርን የመሰለ ትልቅ ነገር ለመምራት ብቃት አይኖረውም። ህወሃቶች አስቀድሞ በነበርው የአቅም ማነስ ተግዳሮታቸው ላይ ፍርሃት ታክሎበት አገሪቷን ወደ ከፋ ሁኔታ ሊወስዷት እየሞከሩ ነው።

Ethiopia: Media Being Decimated (Human Rights Watch)

(Nairobi) – The Ethiopian government’s systematic repression of independent media has created a bleak landscape for free expression ahead of the May 2015 general elections, Human Rights Watch said in a report released today. In the past year, six privately owned publications closed after government harassment; at least 22 journalists, bloggers, and publishers were criminally charged, and more than 30 journalists fled the country in fear of being arrested under repressive laws.

The 76-page report, “‘Journalism is Not a Crime’: Violations of Media Freedom in Ethiopia,” details how the Ethiopian government has curtailed independent reporting since 2010. Human Rights Watch interviewed more than 70 current and exiled journalists between May 2013 and December 2014, and found patterns of government abuses against journalists that resulted in 19 being imprisoned for exercising their right to free expression, and that have forced at least 60 others into exile since 2010.

“Ethiopia’s government has systematically assaulted the country’s independent voices, treating the media as a threat rather than a valued source of information and analysis,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “Ethiopia’s media should be playing a crucial role in the May elections, but instead many journalists fear that their next article could get them thrown in jail.”

Most of Ethiopia’s print, television, and radio outlets are state-controlled, and the few private print media often self-censor their coverage of politically sensitive issues for fear of being shut down.

The six independent print publications that closed in 2014 did so after a lengthy campaign of intimidation that included documentaries on state-run television that alleged the publications were linked to terrorist groups. The intimidation also included harassment and threats against staff, pressure on printers and distributors, regulatory delays, and eventually criminal charges against the editors. Dozens of staff members went into exile. Three of the owners were convicted under the criminal code and sentenced in absentia to more than three years in prison. The evidence the prosecution presented against them consisted of articles that criticized government policies.

While the plight of a few high-profile Ethiopian journalists has become widely known, dozens more in Addis Ababa and in rural regions have suffered systematic abuses at the hands of security officials.

Wednesday, January 21, 2015

ርዕዮት አለሙ (ከቃሊቲ እስርቤት)


ጥር 13/2007ዓ.ም

በቅድሚያ የልደት በዓሌን ለማክበር እዚህ የተሰባሰባችሁትንና እዚህ ባትገኙም አላማዬን በመደገፍ ፍቅርና ከብር የተሰጣችሁኝን ወገኖች ሁሉ ላመሰግን እወዳለሁ፡፡

በመቀጠል እኛም ራሳችን ሆንን ሌሎች ኢትዮጵያዉያን እንደሰዉ መኖር የሚችሉባትን ሀገር ለመፍጠር በየሙያ ዘርፎቻችሁ፣ በፓርቲ ተደራጅታችሁም ሆነ በሌላ በማንኛዉም መንገድ እየታገላችሁ ላላችሁ በሀገር ዉስጥና በዉጭ የምትኖሩ የማከብራችሁ ወገኖች በሙሉ ሶስት ዋና ነጥቦችን የያዘ አጭር መልዕክት ላስተላልፍላችሁ ፈልጋለሁ፡፡

ጊዜዉ የምንታገለው ስርአት ከመቼዉም በበለጠ ሁኔታ አምባገነንነቱ የበረታበት ወቅት እንደመሆኑ ከባድ የስራና የመስዕዋትነት ዘመን ከፊታችን እንደሚጠብቀን ግልፅ ነው፡፡ ተግባራዊነቱ ላይ ድክመት ቢኖርብንም ስራችንን ለማቅለልም ሆነ መስዕዋትነቱን ቀንሶ ባልረዘመ ጊዜ ዉስጥ ለድል ለመብቃት አንድነት ቁልፍ መሆኑን እኔን እናንተም አናጣዉም፡፡ የአንድነትን ተገቢነትና ጠቃሚነት እስካመንበት ጊዜ ድረስ ቆም ብለን ድክመቶቻችንን በመገምገም እና በተቻለ መጠን አላስፈላጊ ልዩነቶችን በማጥበብ ትግሉ የሚጠይቀውን ማንኛዉንም አይነት ህብረት ልንፈጥር ይገባል እስኪ አስቡበት፡፡

በተለያዩ እስር ቤቶች ዉስጥ የሚገኙ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና አባላት፣ የሃይማኖታቸዉን ነፃነት ለማስከበር የቆረጡ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችና ተከታዮች፣ የሀገርና የወገን ጉዳይ ያገባናል ያሉ በተለያዩ የትምህርትና የስራ መስኮች ላይ ተሰማርተዉ የነበሩ ግለሰቦች፣ እነዚህና የመሳሰሉትን እስረኞች ስታስቡ ምን ይሰማችኋል? ሁሉም በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ለሀገራችን ብሩህ ቀን ለማምጣት ወይም እንደሰዉ መብታቸው ተከብሮ ለመኖር ሲ,ታትሩ የነበሩ ግን በተለያየ ስም ተጠርተው ወደ እስር ቤት የተወረወሩ የኢትዮጵያችን ምርጥ ልጆች መሆናቸዉ እነደሚሰማችሁ አልጠራጠርም፡፡ እኔም የሚሰማኝ እንዲሁ ነው፡፡ ታዲያ እንዲህ በተሰማኝ ቁጥር እቆጫለሁ፡፡ የሁላችንም አላማ ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ቢሆንም ተነሳሽነቱን ወስደን ወደ አንድነት ለመምጣት ባለመሞከራችን ወይም በሙከራችን ባለመግፋታችን ምክንያት መከራችንንም ሆነ የድሉን ቀን እንዳራዘምን መረዳቴ የቁጭቴ ምክንያት ነው፡፡ በመሆኑም እድሉ በእጃችሁ ያለ እናንተ ከእንዲህ አይነቱ ቁጭት ትድኑ ዘንድ ይህን አምባገነን ስርዐት ከልባቸዉ የሚቃወሙትን ሁሉ በሆነ መንገድ ወደ አንድነት ለማምጣት የሚቻላችሁን ሁሉ እንድታደርጉ አበረታታችኋለሁ፡፡ ይህ ሳይሆን ቢቀር እንኳን ቢያንስ ቢያንስ አንዳችሁ ስለሌላችሁ አሉታዊ አስተያየት ከመስጠት መቆጠብ ግን ይኖርባችኋል፡፡

ስለ አንድነት ይህችን ያህል ካልኩ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ተገቢ የሆነ የትግል ስልትና አይነት ስለመጠቀም ጥቂት ለመተንፈስ ወደድኩ፡፡ ኔልሰን ማንዴላ Long walk to freedom በተሰኘ ግለ ታሪካቸዉ ላይ እንዳሰፈሩት የትግሉን ስልት የሚወስነዉ ጨቋኙ ነው፡፡ እኔም በዚህ አምናለሁ፡፡ አንድ ሰዉ ለሰደበዉ ሰውና ለተኮሰበት አንድ አይነት የአፀፋ ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ ጤነኛነቱ ያጠራጥራል፡፡ አንድ ጤነኛ ሰዉ ለሁለቱም የሚሰጠው የአፀፋ ምላሽ የተለያየና ለድርጊታቸዉ የሚመጥን እንደሚሆን ይገመታል፡፡ በሌላ አነጋገር የተበዳዩን ሰዉዬ ምላሽ የወሰነው በዳዩ ነው ማለት ነው፡፡ እኛስ ምን እያደርግን ነው ያለው? መረጥነው የትግል ስልት የምንታገለውን አካል ለማሸነፍ የሚያዋጣ ነዉን? የሚያዋጣ ከሆነስ በሚገባ ተጠቅመንበታል? እነዚህንና የመሳሰሉት ጥያቄዎች መጠያየቅና በቂ ምላሽ ማዘጋጀት ይኖርብናል፡፡ አሁን እየተሸከረከርንበት ካለሁ ክብም መዉጣት አለብን "የቱ ክብ?" ካላችሁኝ መልሴ እነሆ!

Tuesday, January 20, 2015

የአምባገነኖች ፀሐይ ጠልቃለች! (አናንያ ሶሪ)

በእኛ በኢትዮጵያ ህዝቦች ዘንድ ለ23 ዓመታት ተመዝኖ ቀሎብናል – ይህ የጥቂት ሽፍታዎች ቡድን! የመንግስትነት ስም ሊመጥነው የማይችል የውንብድናና የማፍያ ተግባር በ’መንግስትነት’ ሽፋን ሲራመድም ቆይቷል – ላለፉት ሁለት አስርታት፡፡ ዛሬ፡- ይህን በገሃድ የሚታይ ጥሬ-ሀቅ ያልተገነዘበ አንድም ኢትዮጵያዊ አይገኝ፡፡

ይህንን የጥቂቶች “የምዝበራ ፖለቲካል-ኢኮኖሚ” ለመሸፈን እና የተለየ ልባስ/ጭንብል ለማልበስ፤ እነዚህ መዝባሪዎች አያሌ ፎቆቻቸውን ከህዝብ በመዘበሩት የህዝብ አንጡራ-ሃብት አማካይነት ህዝብን ባፈናቀሉበትና ከቀዬው-በነቀሉበት በዚያው ስፍራ ላይ ለማቆም ችለዋል፡፡ ፎቆቻቸውን ያነፁት የእነርሱ-ዝርፊያ የሃገር-‘ልማት’ እንዲባልና በዚህም ሰፊው-ህዝብ ተደናግሮ ይህንን በአገር ላይ የሚሠራ “ጥፋት” በበጐ ጐኑ እንዲመለከተው ለማድረግ ነው፡፡

‘ልማት’ እና የዘር-ልዩነት ላይ ያተኰረ “የአፓርታይድ-ፌደራሊዝም” ም በግራና በቀኝ እግር ወደተለያየ አቅጣጫ ለመጓዝ የሚደረግ ዓይነት ከንቱ-መውተርተር መሆኑን በተግባር አይተናል፡፡ “አንቀጽ-39″ም በእኩልነት ላይ ወደተመሠረተ “አንድነት” ሳይሆን፤ በ”አድሎ”ና በተዛባ-መስፈሪያ ከተቃኘው የአሁኑ የብሔሮች-መበላለጥ አስከፊ ሁኔታ መውጫ/መለያያ በር ሆኗል፡፡ የመገንጠል – አሰፍሳፊነትም ከቀድሞው ጊዜ ይልቅ ዛሬ ላይ በርትቷል፡፡ ማንም በማንም መረገጫ – ስር መረገጥ አይፈልግምና!
ይህ “መዝባሪ-ቡድን” በነጋ በጠባ የሚምል የሚገዘትባቸው “ብሔር-ብሔረሰቦች” እኩል የሚሆኑት ህዳር-29 ብቻ ነው፡፡ ከህዳር 29 በስተቀር በቀሩት 364 (1/4ኛ) ቀናት እነዚህ ብሔሮች ወደዘመናዊው – እስር ቤታቸው ይገባሉና! የእስራት ሠንሰለታቸውም ‘አብዮታዊ-ዴሞክራሲ’ የሚባል ስውር የዕዝ-መዋቅር ነው፡፡ ከየብሔሮቹ የተውጣጡ ቱባ የጭቃ-ሹሞች ከሰሜን ጫፍ ወደደቡብ የሚንቆረቆረውን ቀጭን-ትዕዛዝ ተከትለው እንደ እንዝርት ይሾራሉ፡፡ ለቋንቋ ችሎታቸው ብቻ የተመለመሉት እኒህ ተላላኪና ጉዳይ-አስፈፃሚ የየክልል ጭቃ-ሹሞች በምንም ዓይነት መለኪያ የህዝባቸውን-ጥቅም እና ልዕልና ለማስከበር የሚችሉ አለመሆናቸውን ራሱ ህዝቡ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ማወቅ ብቻም አይደል ንቋቸዋል፡፡ በህዝባቸው ዓይን ውስጥም ሚዛን የማይደፉ ቀሊል ሆነው ተገኝተዋል፡፡

ይህን፡- በመሠረቱ የምዝበራ-ጥማት እና “የቁሳቁስ-ሰቀቀን” ያደረበት ገዢ-ቡድን ቅቡልነት /ተቀባይነት ለማላበስ፤ ላለፉት 23 ዓመታት ያልተፈነቀለ ድንጋይ አልነበረም፡፡ “ደርግንና ጭቆናን ገረሰስኩ!” በሚለው ዲስኩር የትግራይን-ህዝብ ከጐኑ ለማሠለፍ በአፍላ-የሥልጣን ዘመኑ ብዙ ደክሟል፡፡ ቆየት አለና ደግሞ፡- ‘የሃይማኖቶች እኩልነትን አረጋገጥኩ!’ ሲል ሙስሊም የህብረተሰብ ክፍሎችን የመደላደያ መሠረት ለማድረግ ረጅም ርቀት ተጓዘ፡፡ ከ1997ቱ ክፉኛ አወዳደቅ በኋላ ደግሞ፡- ‘በቃ እኔ የልማት-መንግስት ነኝ፤ ስለ ዴሞክራሲ አትጠይቁኝ’ አለና የልማት-ዝማሬውን ቀጠለ፡፡ በዴሞክራሲ-መድረክ ላይ፡- በብሔሮች እኩልነት፣ በሃይማኖት ነፃነት፣ በአገር ሉዓላዊነት በዜግነት መብት ወሳኝ-ነጥቦች ላይ ተፈትኖ የወደቀው ይህ “መዝባሪ-ቡድን”፤ በልማት መድረክም ላይ በማህበራዊ-ፍትህ፣ በገቢ ክፍፍል፣ በኢኮኖሚ-ብልጽግና፣ በመሠረታዊ-አቅርቦቶች ስርጭት፣ በመሬት ድልድል፣ በምርታማነትና በዜጐች ተጠቃሚነት ዙሪያ ዳግም ታላቅ-አወዳደቅ ወደቀ፡፡

ኢትዮጵያና የካቲት 11 ቀን 1967 ዓ. ም.


ገብረመድህን አርአያ (አውስትራሊያ)

ኢትዮጵያና የካቲት 11 ቀን 1967 በሚል ርእስ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ማቅረብ ተገቢ ነው ብዬ ተነሳሁ። የማቀርበውም ባጭሩ የሚከተሉትን በተመለከተ ይሆናል፤ የየካቲት 11 ቀን 1967 ዓላማ፤ ፖሊሲው፣ ለማን እና ለምን እንደተፈጠረ።

ቅድመ የካቲት 1967 ዋናው አስኳሉ የተፈጠረው፣ ማሕበር ገስገስቲ ብሄረ ትግራይ (ማገብት) በ1965 አካባቢ በቀ. ኃ. ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ነው። በትምህርት ላይ የነበሩ የትግራይና የኤርትራ ተማሪዎች ተሰብስበው ያቋቋሙት ማህበር ነው። ይህ ማህበር እንደተፈጠረ የወሰድው አቋምና የሚከተለው ፖሊሲ፣ በረቀቀ መንገና ጥናት ጸረ ኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነት፣ የኢትዮጵያን ህዝብ አንድነት፣ ፍቅርና ስላም ለማፍረስ የወጠነ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ኹከትና ብጥበጥ እንዲፈጠር የወሰነ በባእዳን የተፈጠረ ማህበር ነው። ማገብት ገና በረሃ ሳይወጣ ያዘጋጀው ፖሊሲው፣ ኤርትራና ትግራይ ነፃ የነበሩ ሃገራት ሲሆኑ በአማራው መንግሥት ቅኝ አገዛዝ ስር የወደቁ ናቸው የሚል ነው። አማራው የትግራይ ህዝብ ድመኛ ጠላት ስለሆነ ከሚኖርበት መሬት ዘሩን ማጥፋትና፣ በማንኛውም ጊዜ ህብረተሰብአዊ እረፍት እንዳያገኝ እናደርገዋልንም የሚል ፖሊሲ ነው። በተጨማሪም፣ ማገብት ተስፋፊነቱን በመቀጠል ታላቋ የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ሪፓብሊክ መንግሥት ለማቋቋም በማለም፣ ከሰሜን ጎንደር ወልቃይት፣ ፀገዴ፣ ፀለምት፣ ሁመራ፤ ከደቡብ ወሎ ደግሞ አሸንጌን ጨምሮ ወልዲያ፣ ራያና ቆቦን፣ አላማጣ፣ አፍላ ደራን ወዘተ ለም መሬቶችን በሙሉ ወደ ትግራይ ለማጠቃለል ያለመ ፖሊሲ ነው።

ሻእቢያ ማገብትን ለማጠናከር ብዙ ገንዘብ በማፍሰስና የተማሩ ኤርትራውያንን የሃሳብ ድጋፍ በማግኘታቸው ማህበሩም መሪዎቹም ተጠናክረው ወጡ። በቡድን የተሰባሰቡት የማገብት መሪዎች፣ አረጋዊ በርሄ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው። ዋናው መሪ ደግሞ አረጋዊ በርሄ ነበር። አባላቱ ደግሞ መለስ ዜናዊ፤ ስብሃት ነጋ፣ የማነ ኪዳነ፣ ቴዎድሮስ ሃጎስ፣ አስፍሃ ሃጎስ ወዘተ ሲሆኑ ዋናዎቹ አባላት ኤርትራውያን ነበሩ።

የማገብት መሪዎች ወደ ኤርትራ ጉዞ

የማገብት መሪዎች አዲስ አበባ ሆነው የሚፈልጉትን የፕሮግራም ዝግጅት ካጠናቀቁ በኋላ በጥር ወር 1967 አረጋዊ በርሄ የሚመራው ቡድን ሳህል በርሃ በመሄድ የአንድ ወር ወታደራዊ ትምህርትና ሥልጠና ከወሰደ በኋላ ወደ ደደቢት በረሃ አቀኑ። ቀደም በማለት ደደቢት በረሃ ይጠባበቁ የነበሩትም ተቀላቀሉ። የካቲት 11 ቀን 1967 የትጥቅ ትግሉ መጀመሩን በዋናው መሪ አረጋዊ በርሄ ታወጀ። የድርጅቱ ስምም፤ የዛሬው ህወሓት፣ ተጋድሎ ሓርነት ህዝባዊ ትግራይ (ተሓህት) ተብሎ ተሰየመ።

የፕሮግራሙ ዝግጅት

ቀደም ብሎ በረቂቅ የተዘጋጀው የፕሮግራም ፖሊሲ፣ ደደቢት በረሃ እንደገቡ በመጽሐፍ መልክ ሆኖ በእጅ ጽሑፍ እንዲዘጋጅ ተወሰነ። ለዚህ ሥራ አረጋዊ በርሄ፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን፣ ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊ፣ ስየ አብርሃና አውአሎም ወልዱ በመተባበር እንዲያዘጋጁት ተወሰነ። በትብብር ካዘጋጁት በኋላ፣ ስዩም መስፍን ሱዳን ደረስ በመሄድ በመጽሐፍ መልክ ተዘጋጅቶና ተባዝቶ እንዲያመጣ ተላከ፣ አዘጋጅቶም ደደቢት በረሃ ተመለሰ። በጊዜው የተሓህት የድርጅቱ ሊቀመንበር አረጋዊ በርሄ ሲሆን፣ የአመራር ቡድኑ ደግሞ ግደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀሃየ፣ ሥዩም መስፍን፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ገሰሰ አየለ፣ ሃይሉ መንገሻ (ነጠበ)፣ አስፍሃ ሃጎስ ነበሩ።

የዲማ ኮንፈረንስ

ዲማ በአጋሜ አውራጃ የሚገኝ የቦታ ስም ነው። የዲማ ኮንፈረንስ የተጠራበት ህወሓት ምክንያት የሚከተሉትን አንኳር አጀንዳ በመያዝ ነበር፣

1. የካቲት 11፣ 1967 የተሓህት አንደኛ ዓመት ስለነበር ለማክበር፣
2. የተሓህት/ህወሓትን ፕሮግራም ፖሊሲ/ማኒፌስቶን ለማጽደቅ፣
3. የተሓህት/ህወሓትን የድርጅት ውስጠ ደንብ (ሕግና ስነስርዓት) ለማጽደቅና፣
4. አመራር ለመምረጥ ነበር።

በዚህ መሰረት በአሉ ተከበረ። ተሓህት በዚህ ጊዜ የነበረው የሰው ሃይል አነስተኛ ነበር። ቢሆንም ግን ሁሉም የተማሩ ታጋዮች ነበሩ። ፕሮግራሙን ለማጽደቅ ውይይት ሲጀመር፣ በአብዛኛው ታጋይ ከባድ ውዝግብና ጭቅጭቅ ተነሳ። ፕሮግራሙ ሆን ተብሎ ፀረ-የኢትዮጵያ ሉአላዊነት፣ ጸረ ሕዝብ፣ በታኝና ጎጠኛ ነው ብሎ በማስቀመጥ አንቀበለውም አለ። የድርጅቱ ሊቀመንበር አረጋዊ በርሄና ጥቂት ደጋፊዎቹ ብዙሃኑን ትጋዮች በምስፈራራትና ከባድ ተጽእኖ በማሳረፍ ኮንፈረንሱ ፕሮግራሙን ተቀብሎ አሳልፎታል በማልት በተግባር ላይ እንዲውል አስደረገ። አብዛኛው ታጋይ የተቃወመውን ሕግና ስነስርዓት ሊቀመንበሩ ተቀብለነዋል ብሎ ደመደመ። አምባገነንነቱ የተጀመረው ብዚህ አይነት ሲሆ፣ ከጥቂት ወራት በኋላ ተሓህት ወደ ፋሽስትነት ተሸጋገረ።

ማ/ኮሚቴው ተመረጠ፣ ይሁን እና ለእነ አረጋዊ በርሄ ትልቅ የራስ ምታት የሆነባቸው መለስ ዜናዊ ሳይመረጥ መቅረቱ ነበር። በጊዜው የተመረጡት የማ/ኮሚቴ አባለት፣ አረጋዊ በርሄ የድርጅቱ ሊቀመንበር፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን፣ ስብሃት ነጋ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሴ ተክለ ናቸው። “ዘንበል አለ እንጂ አልፈሰሰም” እንደሚባለው፣ ከጥቂት ወራት በኋላ ሙሴ ተክሉና አግአዚ ገሰሰ በተንኮልና በተዘዋዋሪ መንገድ አመራሩ ካስገደላቸው በኋላ፣ ማሟያ በማለት መለስ ዜናዊ፣ ስየ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ፣ አጽብሃ ዳኘው ወደ ማ/ኮሚቴና ወደ አመራር ሃላፊነት ወጡ። አጽብሃ ዳኘው በነበረው ጸረ ተሓህት ፕሮግራም ምክንያት ሃለዋ ወያነ ገብቶ ተገደለ። በምትኩ ዶ/ር አታክልት ቀጸላ ተመረጠ። እርሱም እንድዚሁ በተሓህት ፕሮግራም ከፍተኛ ተቃውሞ ስለነበረው ገደሉት። ተሓህት ቀስ በቀስ ፍጹም ፋሽስት በመሆን ተቃዋሚ የሆኑትን ታጋዮችም ሆነ ሕዝቡን መፍጀት ጀመረ። አረጋዊ በርሄ፣ አባይ ፀሃየ፣ ስብሃት ነጋ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ስዩም መስፍን፣ መለስ ዜናዊ፣ ስየ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ በመተባባር ህዝብ የጨረሱ አረመኔ መሪዎች ናቸው። አሁን በሥልጣናቸው ስር ቢደበቁም ነገ ለፍርድ መቅረባቸው አይቀሬ ነው።

Sunday, January 18, 2015

የኢ.ሕ.አ.ግ. ዓለም አቀፍ ኮሚቴ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት


ጥር:- 5 ቀን 2007 ዓ/ም

ለተከበራችሁ ለድርጅቱ ሥራ አመራር አባላትና በዱር በገድሉ ከጠላት ጋር ለምትዋደቁ ታጋይ ጓዶች በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ፤ በማለት የአክብሮት ሰላምታችን እያቀርብን፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና በግንቦት 7 ለፍትህ ዴሞክራሲና የነጻነት ንቅናቄ መሀል የተደረገውን ውህደት በታወጀ ጊዜ የተስማን ደስታ እጅግ የላቀ ነው::

ይህን የአንድነትና የወንድማማችነት ትስስር የኢትዮጵያ ህዝብ በጉጉት የሚጠብቀው በመሆኑ ይህ ውህደት ለህዝባችን ታላቅ የምስራች እንደሆነ እናምናልን::

ለዚህ ታላቅ ውህደት ለወድፊቱ ለምታደጉት የስራ እንቅስቃሴ ሁሉ ከጎናቸሁ የምንቆም መሆኑን እያረጋገጥን መጪው ጊዜ ይህ ሃገር ሻጭና ዜጋን ገዳይ የሆነ ዘረኛ የወያኔ ኢሃዴግ ጎጠኛ ድርጅት ተወግዶ ሰላምና ደስታ ህይወትና ብልጽግና የሰፈነባት ዜጎችዋ ሃገሪ ብለው የሚኖሩባት ኢትዮጵያን ለማየት እንድንበቃ ሁለንተናዊ አንድነት እና ኅብረት ለነጻነት በር ከፋች መሆኑን አምነን በጋራ ለመቆም ቃል እንገባለን !!

አንድነት ኃይል ነው!!
የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዓለም አቀፍ ኮሚቴ

Thursday, January 15, 2015

Andargachew Tsige and the struggle for freedom (By Yilma Bekele)

Andargachew Tsige was taken prisoner by the TPLF Woyane regime on June 24/’13 while on transit at Sana, Yemen International Airport. He was removed from the airplane and flown to
Ethiopia. What was done was against all international conventions and is considered illegal. Ever since then he has been held in secret locations being interrogated as stated by the Ethiopian regime.

The illegal act has been condemned by most Ethiopian Opposition groups, the British Government, EU Parliamentarian Ana Gomez, Human Rights Watch, Amnesty International and Ethiopians both at home and in the Diaspora. As usual the Ethiopian government choose to ignore the concerns of all that care about the rule of law.

We Ethiopians are not surprised by the actions of the regime. It is just another illegal act by the few in a long procession of criminal acts committed against the people of Ethiopia. As a matter of fact we have become numb to the atrocities by the minority ethnic group in power. As far as Ethiopians are concerned it is just another abuse. We have been programed to shrug it off.

Arresting or taking the opposition member and painting the individual as a criminal element is not an act invented by the Ethiopian regime. Capitalist, Communist, Socialist, Monarchist or Fascist as the case may be always find some sort of justification to abuse the power they have and use negative labels to neutralize their opponents.

The Ethiopian regime has raised this act to higher level. In fact in the aftermath of the general elections in 2005, the late dictator put the whole opposition in prison for two years and released
them by forcing them to sign a fake apology. Since the emergence of TPLF as the victorious group and assuming power there is not one Ethiopian opposition group that has not sacrificed a leader to the Woyane Party. There is no need to mention names because this was not done in secret or under the cover of darkness but in broad daylight for the people to see and learn.

Ato Andargachew is just one additional victim. Ato Andargachew is viewed by the TPLF regime as the ultimate prisoner because he emphatically stated that the TPLF regime can only be brought down using violence as a means. He was not shy about it nor did he go underground. He did not just talk about it but went one step further and organized a group to practice what he preached. That was what the regime feared most and that is why they spent millions to follow all his movements and commit the ultimate crime of kidnapping.

I, with clear conscience cannot fault them for that. He was doing what he has to do to bring freedom and justice to our country. They did what they have to do to protect the power they have amassed the last twenty years knowing full well any change that comes to Ethiopia would ultimately end with those that committed the many crimes have to answer to a real court of law. It is a life or death struggle to TPLF politburo members and their underlings. It is a life and death struggle to my friend Andargachew and his comrades.

Wednesday, January 14, 2015

አንዳርጋቸው ጸጌ በህወሀት የሸፍጥ የምርመራ ወጥመድ ውስጥ (ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

 ቮልቴር (ፍራንኮይስ ማሬ አሮት) እንዲህ በሚለው ምልከታቸው በስፋት ይታወቃሉ፣ “አንድ ሰው ከሚሰጣቸው ምላሾች ይልቅ በሚያቀርባቸው ጥያቄዎች ምንነቱ ይገመገማል፡፡“

ቮልቴር ብልህነትን በተላበሰ መልኩ እንዲህ የሚል ምልከታም በተጨማሪ አካሂደዋል፣ “ጥሩንባቸውን እየነፉ እጅግ ብዛት ያለውን ህዝብ ካስጨረሱ ገዳዮች በስተቀር ሁሉም ህይወትን ያጠፉ ነብሰ ገዳዮች ይቀጣሉ፡፡“ ይኸ ነገር እንዴት ያለ እውነታ ነው እባካችሁ! አሁን በህይወት የሌለው መለስ ዜናዊ እና እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው የወሮበላ ቡድን በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት ወገኖቻችንን በመግደል ከምዕራቡ ዓለም የሚደረግላቸውን እርዳታ በመቀበል ፌሽታ እና ደስታ በማድረግ ከህዝብ እልቂት ሰይጣናዊ ወንጀሎቻቸው ለማምለጥ ላይ ታች በማለት በመንፈራገጥ ላይ ይገኛሉ፡፡

ባለፈው ሳምንት በአንዳርጋቸው ጽጌ ተሰጠ የተባለ የ10 ደቂቃ ከ31 ሰከንዶች ቆይታ ያለውን ሁለተኛ ጊዜ የቀረበ የሙያ ሳይሆን የልምምድ ድራማቸውን በህዝብ ግብር በሚተዳደረው ቴሌቪዥን በማይታዩ ጥያቄ አቅራቢ መርማሪዎች እና ሰዎች የእራሳቸውን የህሊና ዳኝነት እንዲሰጡ በሚጋብዝ መልኩ የተቀነጫጨበ እና በውል ለመረዳት የማይቻለውን ምላሽ የተባለውን ቃለ ተውኔት እንደሰጡ አድርገው አቅርበው ነበር፡፡

በኢትዮጵያ ባለው አገዛዝ የተቃዋሚ ቡድን ከሆነው እራሱን የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ለፍትህ፣ ለነጻነት እና ለዴሞክራሲ እያለ የሚጠራውን ድርጅት ዋና ጸሀፊ የሆኑትን አንዳርጋቸው ጽጌን እ.ኤ.አ ጁላይ 2014 በየመን ካለው ገዥ አካል ጋር የሸፍጥ ዱለታ በማድረግ በተሳካ ሁኔታ ወደር የማይገኝለትን ጠለፋ አካሂደው ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በ2009 እና በ2012 አንዳርጋቸው በሌሉበት አሸባሪ በሚል የሸፍጥ ውንጀላ በህወሀት ክስ ተመስርቶባቸው በዝንጆሮው የይስሙላ ፍርድ ቤት የሞት ቅጣት ተበይኖባቸው ነበር፡፡

የአቶ አንዳርጋቸውን አሳፋሪ እና ህገወጥ ጠለፋ በማስመልከት “ኢትዮጵያ፡ ልዩ የሆነ የወንጀል ትወና“ በሚል ርዕስ እኩይ ድርጊት መሆኑን በሳምንታዊ ጦማሬ ላይ አውግዠ ነበር፡፡

አንዳርጋቸው የእንግሊዝ ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ በትውልዳቸው ኢትዮጵያዊ ናቸው፡፡ ሆኖም ግን በጣም የሚያሳፍረው ነገር የእንግሊዝ ዜግነታቸው ለስም ብቻ የመሆኑ ጉዳይ ነው፡፡ አንዳርጋቸው ከእስር ቤት እንዲፈቱ የእንግሊዝ መንግስት ምንም ያደረገው ነገር ወይም ደግሞ በአስከፊነቱ በዓለም ታዋቂ ከሆነው የመለስ ዜናዊ እስር ቤት የሰብአዊ መብት ረገጣ እና ስቃይ ነጻ እንዲሆኑ የሰራው ስራ የለም፡፡ የህወሀት ወንድሞች ከስድስት ወራት በላይ አንዳርጋቸው ጽጌን ለተደጋጋሚ ጊዜ የብዙሀን መገናኛ የመድረክ የቅጥፈት ተውኔት ማሳያ ሲያደርጓቸው የእንግሊዝ መንግስት አንድም ዓይነት የወሰደው እርምጃ የለም፡፡

እ.ኤ.አ በ1963 በጸደቀው የኮንሱላር ግንኙነት የቬና ስምምነት መሰረት የእንግሊዝ መንግስት ፍጹም በሆነ መልክ ግዴታውን መወጣት አልቻለም፡፡ የእንግሊዝ መንግስት በውጭ የሚኖሩ ዜጎቹን ደህንነት በመጠበቁ እና እገዛ በሚጠይቁ ዜጎቹ ጉዳይ ላይ በሁለት ቢላዋ ምላሱ በማውራት ላይ ይገኛል፡፡ የእንግሊዝ ባለስልጣኖች እንዲህ ይላሉ፣ “በኮንሱላር ባለስጣኖቻችን ወይንም ደግሞ የዲፕሎማሲ ባለስልጣኖቻችን አማካይነት በውጭ ሀገር በችግር ላይ ለሚገኙ ዜጎቻችን የምንሰጠው እገዛ የውጭ ፖሊሲያችን የመሰረት ድንጋይ ነው፡፡“ ከዚህም በተጨማሪ የኮንሱላር እገዛ የእንግሊዝ ዜጎች ማግኘት ያለባቸው የህግ መብት አይደለም በማለት እንዲህ ይላሉ፣ “የእንግሊዝ መንግስት ለዜጎቹ የኮንሱላር እገዛ ለመስጠት ወይም ደግሞ የዲፕሎማሲ ጥበቃ ለማድረግ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ህጎች ግዴታ የለበትም፡፡“ ከዚህም በላይ በውጭ የሚገኙ ዜጎቻቸው የማሰቃየት ድርጊት እንዳይፈጸምባቸው ወይም ሊፈጸምባቸው እንዳይችል ለማድረግ የዜጎቻቸውን ደህንነት ለመጠበቅ የእንግሊዝ መንግስት የጸረ ማሰቃየት ስትራቴጅ አንዱ እና ዋና ተግባሩ ነው፡፡ የእንግሊዝ ንጉሳዊ ቡድን ጸሀፊ፣ ገጣሚ እና ወታደር የነበሩት ጌታ ዋልተር ራለህ ተገቢ በሆነ መልኩ እንዲህ የሚል ጥቆማ አድርገው ነበር፣ “ኦ፣ የማታለል ተግባራትን ስንፈጽም በነበረበት ጊዜ ምን ዓይነት ድር ማድራት እንደጀመርን!“

የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ቢሮ አንዳርጋቸው ጽጌ በወያኔ የዝንጀሮው የይስሙላ ፍርድ ቤት ሁለት ጊዜ የሞት ፍርድ የተበየነባቸው መሆኑን እና ከፍተኛ የሆነ ማሰቃየት እንደተፈጸመባቸው ከምንም ጥርጣሬ በላይ አሳምሮ ያውቃል፡፡ እስከ አሁን ድረስ በእንግሊዝ መንግስት የተደረገው ጸጸትን መግለጽ እና ከየመን ባለስልጣኖች ዘንድ ተደጋጋሚ የሆኑ መረጃዎችን መጠየቅ፣ ስለአንዳርጋቸው የእስር ሁኔታ ከቬና ስምምነት በተጻረረ መልኩ መረጃ ማግኘት ያለመቻል ችግር እንዲሁም አንዳርጋቸው ጽጌ በኢትዮጵያ የሞት ብይን ፍርድ እንዳይሰጥባቸው ለማድረግ ግልጽነት የጎዳላቸው አራምባ እና ቆቦ የሆኑ የማስመሰያ መግለጫዎችን ማውጣት እና ጉዳዩ አሳስቦናል የማለት የይስሙላ ጥረት ነበር፡፡ እንደ አንድ ዘገባ ከሆነ ሚስተር ሲሞንድስ የተባሉ አፍሪካዊ ሚኒስትር የኢትዮጵያ ባለስልጣኖች የኮንሱላር ተደራሽነትን የማይገልጹ በመሆናቸው ሚኒስትሩ የተሰማቸውን ጥልቅ ስሜት ገልጸው ነበር፡፡

Tuesday, January 13, 2015

በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ፣ ዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ መሀል የተደረገውን ውህደት በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፣



በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ፣ ዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ መሀል የተደረገውን ውህደት በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፣

በዛሬው ዕለት፣ ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ ለዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ፣ ድርጅቶች፣ ተዋህደን “አርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ”፣ በሚባል ሥም መጠራት መጀመራችንን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ስናበስር፣ እጅግ ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ባለፉት በርካታ አስርተ አመታት፣ለፍትህ፣ ለእኩልነት፣ ለነጻነት፣ መብትና አንድነት፣ ከፍተኛ ትግል ሲያካሂድ ቆይቷል። በአደረገውም ትግል እጅግ ከፍተኛ መስዕዋትነት ከፍሏል። ለከፈለው ከፍተኛ ዋጋ የሚመጥን ግን ምንም ዓይነት ውጤት አላገኘም። እንዲያውም ከጊዜ ወደ ጊዜ የመብት ረገጣው፣ አድሎው፣ ማስፈራራቱና ማዋከቡ ተጠናክረው መቀጠል ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ልትቀጥል የማያስችል ከፍተኛ የመበታተን አደጋ አንጃቦባት ትገኛለች ።

በሀገራችን ላይ ላንጃበበው ከፍተኛ የመበታተን አደጋ ምክንያት የሆነው በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ የአምባገነን ቡድን ነው። ይህ ዘረኛ አምባገነን ቡድን በሀገራችን ታሪክ በሥልጣን ላይ ከመጡ የገዥ ሃይሎች ጋር ሲወዳደር ሀገርን ለከፍተኛ አደጋ በማጋለጥ፣ ሕዝቧን በማወረድ፣ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ዕኩይ ሃይል መሆኑን በበርካታ ተግባራቶቹ ያለ ምንም ጥርጣሬ አረጋግጧል።

በሌላ በኩል ለቀድሞቹም ሆነ ለዛሬው ዘረኛው የወያኔ አምባገነን ገዥ በሕዝብና በሀገር ላይ በደል እየፈጸመ በሥልጣን መቆየት የቻለበት ምክንያት፣ በተቃዋሚነት የሕዝቡን ትግል ለመምራት የተንቀሳቀስን ድርጅቶች፣ የተቋቋምንበት ዓላማ መለያዬት ብቻ ሳይሆን፣ አንድ ዓይነት ዓላማ ያለንም ብንሆን፣ ከድርጅቶቻችን ጠባብ ፍላጎቶችና ስሜቶች ባለፈ፣ የሀገርና የሕዝብን ጉዳይ በማስቀደም በጋራ መሰባሰብና መታገል ስላቃተን ነው። በዚህም ድርጊታችን የራሳችንን ብቻ ሳይሆን የወገናችንንም የመከራ ዘመን እያራዘምን እንገኛለን ።

ይህ ሁኔታ በተለያዩ ተቃዋሚ ድርጅቶች መሀል ከፍተኛ ጥርጣሬና ፍርሀት ከመፍጠሩ የተነሳ በምንም ዓይነት ሁኔታ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶች በጋራ በሀገርና በሕዝብ ደረጃ ትርጉም ያለው ስራ መስራት አይችሉም፣ የሚለው አመለካከት የበላይነት እንዲያገኝ አድርጎታል።

በዛሬው ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ወደ ውህደት የመጣነው፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ፣፡ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ መዋሃድ መወሰናችንን ፣ ስንገልጽ በተናጠል ከሚደረጉ በጋራ የሚደረጉ የትግል ጥረቶች ውጤታማ ይሆናሉ በሚል ብቻ ሳይሆን፣ የተቃዋሚ ድርጅቶች፣ በምንም ዓይነት ሁኔታ በሀገርና በሕዝብ ደረጃ ትርጉም ያለው ሥራ በጋራ መስራት አይቻሉም የሚለውን፣ አስከፊ ተመክሮና አመለካካት ለመስበርም ነው።

በእኛ እምነት ከትናናሽ ድርጅቶች ዙሪያ ከሚሽከረከሩ ሀሳቦችና ስሜቶች ለመውጣትና ሀገራዊና ሕዝባዊ የሆነው ጉዳይ ለማስቀደም የወሰነ ማንኛውም ድርጅት፣ አርበኞችና ግንቦት7፣ የደረሱበት የውህደት ውሳኔ ወይም በሌሎች በጋራ ሊያሰሩ በሚችሉ ስምምነቶች አብሮ ለመስራት መወሰን የማይችልበት ምንም ምክንያት አይታየንም። በወያኔ አድሎ ስርዓት የተንገፈገፈና ትግሉን ለመቀላቀል የቆረጠ ማንኛውም ዜጋ፣ የተገኘውን አጋጣሚ በመጠቀም ትግሉን መቀላቀል ይችላል፣ የኢትዮያ ሕዝብ በአንድነት የተነሳ ቀን ደግሞ፣ የወያኔ ግብዓተ መሬት ይፈጸማል፣ ብለን ከልብ እናምናለን።

ታሪካዊው የጣይቱ ሆቴል በእሳት መጋየት በኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀሰቀሰ


በቅዱስ ዮሃንስ 

ባሳልፍነው እሁድ ጥር 3-2007 ማለዳ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ዘመናዊ ሆቴል የሆነው ታሪካዊው ጣይቱ ሆቴል ሙሉ በሙሉ በእሳት የወደመ ሲሆን ድርጊቱ ሆን ተብሎ የታሪክ ጸር በሆነው የወያኔ አገዛዝ ሴራ የተፈጸመ ነው ሲሉ ኢትዮጵያውያን በአገዛዙ ላይ ቁጣቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።  የእሳት አደጋ ብርጌድ መስሪያ ቤት በሆቴሉ አቅራቢያ ሆኖ ሳለ እሳቱ ከተነሳ በትንሹ ለአንድ ሰአት ተኩል ያህል አንድም የእሳት አደጋ መኪና አለመታዬቱና ብሆቴሉ አለመድረሱ በርካቶችን ከማስቆጣቱም ባሻገር በአገዛዙ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ሴራ ለመሆኑ እንደ አንድ አብይ ማስረጃ በስፋት እየተጠቀሰ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ታሪካዊውን የጣይቱ ሆቴል መውደም ተከትሎ  ቁጣቸውን በማህበራዊ ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት አንድ ግለሰብ እንዳሉት በቅርቡ ለዘመናት በወመዘክር ይገኙ የነበሩ በተለያዩ የአለም ቋንቋዎች የተፃፉ የኢትዮዽያን ታሪክ የያዙ መዛግብትና ጽሁፎችን በወያኔ ትዕዛዝ ለስኳር መጠቅለያነት በሚል እንዲሸጡና የቀሩት እንዲቃጠል አደረጉ። ዛሬ ደግሞ በኢትዮዽያ ታሪክ የመጀመሪያዉ ሆቴል የሆነዉንና ታሪካዊ ቅርሳችንን የእቴጌ ጣይቱ ሆቴል በተቀነባበረ ሴራ እንዲቃጠል አደረጉ። እነዚህ የባንዳ ዉላጆች በተመሳሳይ የጥፋት ድርጊታቸው በልማት ተብየ ስም የአቡነ ዼጥሮስን ሀዉልት እንዲነሳ አድገዋል፤ ጥንታዊ ገዳማትና አድባራትን አፈራርሰዋል። የቅርስ ምዝገባ በሚል ሰበብ የተለያዩ የቤተ ክርስቲያን ንዋዬ ቅድሳትና ጽላትን ሳይቀር ለምዕራቡ አለም መቸብቸባቸዉ የአደባባይ ሚስጢር ከሆነ ሰነባብቷል በማለት ይህ የወያኔ ቅርስን የማውደም ሴራ የአገዛዙን ሞት ያፋጥናል ሲሉ ቁጭታቸውን አስፍረዋል።

ሌላኛው ኢትዮጵያዊ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ በማንነትህ፣ በታሪክህ፣ በቅርሥህ ላይ እያላገጡ ያሉት የባንዳ ልጆች እምቢተኝነትህ በዝምታህም፤ በጩኸትም ገብቷቸዋል፣ ከቁጥጥራቸው በላይ ሆኖባቸዋል። የሕዝብ ምሬት ሊገነፍል ጫፍ ላይ መድረሱ ታይቷቸዋል፣ ጨንቋቸዋል፣ ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ተንቀጥቅጠዋል፣ ፈርተዋል፣ አሁን ላይ በደመነፍስ ነው እየገዙን ያሉት። ዛሬም እንደትናንቱ የአጥፍቶ አጥፊነት ባህሪያቸውን ነው እየደገሙት ያሉት። የጣይቱ ሆቴል መቃጠል የታሪካዊ ቅርስ ጥላቻቸው ጫፍ መድረስ መገለጫ ነው። አጥፊነታቸው ምን ደረጃ ድረስ እንደሆን ነው የሚያሳየው፣ የአውዳሚነት ባህሪያቸው ለታሪካችንና ለቅርሶቻችን ያላቸውን ጥላቻ ያሳያል። ዛሬ የታሪክ ቅርሥ የሆነው ጣይቱ ሆቴል ወደመ ነገሥ ባለተራው ማን ይሆን ? ሲሉ ቁጭታቸውን በጥያቄ ደምድመዋል።

የፋሽስቱ ወያኔን ከዚህ በላይ የምንታገስ ከሆነ ነገ ምንም ዓይነት የታሪክ አሻራ አናገኝም በማለት ቁጭታቸውን ያሰፈሩት ሌላኛው በድርጊቱ የተቆጬ ግለሰብ በበኩላቸው አምባገነኑ ወያኔ ታሪክን በጠራራ ፀሐይ ማቃጠሉን አሁንም ቀጥሎበታል። በዛሬው እለት በኢትዮጵያ የሆቴሎች ታሪክ የመጀመሪያውን የታሪክ ቤተ መዘክር የሆነውን የጣይቱ ሆቴልን እሳት ለኩሰው አጋይተውታል። እነዚህ የአገር ነቀርሳዎች እሳቱን ለኩሰው ሰዎች ገብተው እንዳያጠፉ ፖሊስ በቆመጥ እየጎመደ አባረረ፤ ዐይናችን እያየ ታሪካችን ሲቃጥል ተመለከትን። የእሳት አደጋ መከላከያ በሁለት መቶ ሜትር ርቀት ላይ እያለ በአራቱም አቅጣጫ እሳቱን ለማጥፋት አመቺ ቦታ ላይ ተቀምጦ ሆቴሉ ሙሉ በሙሉ እስኪወድም ድረስ የውሸት ቋት በሆነው ቴሌቪዢናቸው ገና እሳቱን አልተቆጣጠርነውም እያለ በህዝብ ሲሳለቅብ ተመለከትን። ያሳዝናል። በነገራችን ላይ ባለፈው ጊዜ ይህ ሆቴል በመልሶ ማልማት ስም እንዲፈርስ ወያኔ ወስኖ ነበር፤ ሕዝቡ ቁጣውን ሲያሰማ ግን ጊዜ ጠብቆ አቃጥለውታል ። ከዚህ በላይ ወያኔን መታገስ አገራችንና እና ታሪኳን ከፋሽስቶች ጋር አብሮ እንደማጥፋት ነው የማየው። ከዚህ በላይ የሃገራችንን ጥፋት ለማየት መፍቀድ ከባንዳነትም በላይ ባንዳነት ነው ሲሉ ግለሰቡ በጋራ የታሪክና የቅርስ ጸር የሆነውን የወያኔ አገዛዝ ለማስወገድ እንነሳ በማለት ወገናዊ ጥሪያቸውን በማቅረብ መልዕክታቸውን አስተላልፍዋል።

ጥንቅር በአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ዙሪያ


በቅዱስ ዮሃንስ

በግንቦት 7 የፍትህ፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እና በኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር የተደረገው ውህደት የትጥቅ ትግሉን ከዳር ሊያደርስ የሚችል ሐይል ይፈጥራል ሲሉ ኢትዮጵያውያን እምነታቸንና ድጋፋቸውን ገለጹ

ዘረኛውንና ከፋፋዩን የወያኔ አገዛዝን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ለማስወገድ በተለያዩ መንገዶች ሲታገሉ የቆዩት ሁለቱ ድርጅቶች ግንቦት 7 እና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር በጥር 2 ቀን 2007 አ.ም በኤርትራ በተካሄደው ስምምነት ውህደቱ በደማቅ ስነስርአት መፈጸሙን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በኤርትራ ከተካሄደው ጉባየ ቀደም ብሎ የግንቦት 7 ንቅናቄ በሁሉም የአለም አህጉራት ማለትም አፍሪካን ጨምሮ በአውሮፓ፤ ኤስያና ሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ አባላቶቹ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ስፊ ምክክር ማድረጉ የተመለከተ ሲሆን ውህደቱ በሁሉም አባላት ዘንድ በሙሉ ድምጽ ይሁንታን አግኝቶ ውሳኔ መተላለፉን የደረሰን መረጃ ያሳያል። በኤርትራ በተካሄደው በዚህ ታርካዊ ስምምነት ከመላው አለም የተሰባሰቡ በርካታ የድርጅቶቹን አመራሮች ጨምሮ የሌሎች ድርጅት ተወካዮች በክብር እንግድነት የተገኙ ሲሆን በመስራች ጉባየ አባላት ይሁንታን አግኝቶ የተመሰረተው አዲሱ ድርጅት አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ (አግኤደን) የሚል መጠሪያ እንደተሰጠው ለማወቅ ተችሏል።

በኢትዮጵያ የነፃነት ትግል መድረክ ተጨባጭ ለውጥ እንደሚያመጣ የተነገረለት ይህ ውህደት ከፋሺስታዊው አጋዘዝ ጋር በመሬት ላይ ለሚደረገው የትጥቅ ትግል ማርሽ ቀያሪ መሆኑ ተነግሯል። በጉባየው የተገኙት የአርበኞች ግንባር ሊቀመንበር አርበኛው መኣዛ ጌጡ የውህዱን እውን መሆንና አገራዊ ጠቀሜታውን ያጎላ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በተናጥል እየተደረገ ያለው ትግል ስንዝር ወደ ፊድ ማራመድ እንደማያስችል በመረዳት  ውህደቱ መፈጸሙን ታሪካዊና ለኢትዮጵያም ህዝብ አንድ የድል ምዕራፍ ያለው ክስተት ነው ሲሉ ገልጸውታል። የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ በበኩላቸው እንኳን ደስ ያላችሁ፤ በጉባያችሁ ላይ መገኘት ባልችልም ከዚህ በኋላ በየትኛውም እንቅስቃሴ ከጎናችሁ ታገኙኛላችሁ ሲሉ ቃል የገቡ ሲሆን ይህ ውህደቱ በስልጣን ላይ ያለውን ዘረኛውን የህወሃት አገዛዝ ማስወገድ ብቻ ሳይሆን ቀጣይ ለሚመሰረተው ዲሞክራሲያዊ ስርአት መሰረት የሚጥልም መሆን አለበት ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በጉባየው አንድነት ሃይል ነው በውህደቱ የተጀመረው ታሪካዊ ጉዞ ተጠናክሮ ይቀጥላል፤ ውህደቱ የአገራችን የትንሳኤ ምልክት ነው፤  ኢትዮጵያንና ህዝባችንን ከውርደት እንታደጋለን፤ ሞት ለፋሽስቱ ወያኔ፤ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ጋር በመሆን የዲሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ትግላችን በደማችን ይረጋገጣል የሚሉና ሌሎች በርካታ መፈክሮች በአዳራሹ ተስተጋብተዋል። ከእንግዲህ መለያየት የለም አንድ ሆነን ኢትዮጵያን ነፃ እናወጣለን ያለው አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ (አግኤደን) ለሌሎች በትጥቅ ትግል የተሰማሩ ድርጅቶችም እንዲቀላቀሉ ጥሪ ማቅረቡን ለማወቅ ችለናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በትጥቅ ትግል የፋሽስቱ ወያኔ አገዛዝን በማስወገድ የኢትዮጵያን የመከራና የጨለማ ዘመን ለማክሰም የሚንቀሳቀሱት የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር እና የግንቦት 7 ንቅናቄ አንድ የመሆናቸው የብስራት ዜና ይፋ መደረጉን ተከትሎ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሰፊ መነጋገሪያ ሆኖ ከመቀጠሉም በላይ በሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ከፍተኛ ድጋፍ እየተቸረው ሲሆን በተቃራኒው ውህደቱ በፋሺስቱ ወያኔ መንደር ከፍተኛ መደናገጥ መፍጠሩን የውስጥ ምንጮቻችን አመልክተዋል። የሁለቱን ድርጅቶች መዋሃድ ተከትሎ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ የማህበራዊና የመወያያ መድረኮች ላይ በመገኘት ድጋፍና አጋርነታቸውን

Sunday, January 11, 2015

ትናንት ከዉጭ ወራሪዎች የታደገን መከላከያ ሠራዊታችን ዛሬም ከአገር ዉስጥ ወራሪዎች ይታደገናል

አስተዋዩ የኢትዮጵያ ህዝብ እድገቱን ለሚመኙ አስተዋይ መሪዎች እለታደለምና ደሃ ነዉ፤ ረሀብተኛ ነዉ አልተማረም ወይም ኋላ ቀር ህዝብ ነዉ ማለት ይቻል ይሆናል፤ ሆኖም የኢትዮጵያ ህዝብ ያሰኘዉን ያክል ቢደኸይ ወይም ኋላ ቀር ቢሆን ለነፃነቱ፤ ለአንድነቱና ለግዛት አንድነቱ መከበር ያለስስት ደሙን የሚያፈስ ጀግና ህዝብ ነዉ። ይህ ጀግንነት ደግሞ አንደተረት በአፍ ተነግሮ የሚያበቃ ሳይሆን በመተማ፤ በአድዋ፤ በማይጮዉ፤ በወልወል፤ በፊልቱና በጎዴ የጦር ሜዳዎች ሊወጉትና ሊወሩት የመጡ ጠላቶቹ ጭምር የመሰክሩለት የታሪክ ሐቅ ነዉ።

የኢትዮጵያ ህዝብ ከጀግንነቱ ጋር አርቆ አስተዋይና ታጋሽ ህዝብ ነዉ፤ ሆኖም ይህንን ህዝብ የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ በተከታታይ የገዙት የገዢ መደቦች ጀግንነቱን ለራሳቸዉ ክብርና ዝና ታጋሽነቱን ደግሞ ለስልጣን ዘመናቸዉ ማራዘሚያ አድርገዉ የመከራ ዘመን እያስቆጠሩ ኖረዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ታጋሽ ህዝብ ቢሆንም እርግጫዉና ጭቆናዉ በበዛበት ቁጥር አምርሮ የሚነሳ ለገዢ መደቦች የማይመች ቁጡና እልህኸኛ ህዝብ መሆኑንም በተከታታይ አሳይቷል። ይህንን ደግሞ በ1966 ዓም ከዳር ዳር ባቀጣጠለዉ ህዝባዊ አብዮት በ1983 ዓም ደግሞ በአራቱም ማዕዘናት ባካሄደዉ ህዝባዊ አመጽ አሳይቷል። ሆኖም አብዮቱንና ህዝባዊ አመጹን ከትግል ሜዳ እስከ ፖለቲካ ስልጣን አደባባዮች ድረስ አቀነባብሮ የሚመራ የተደራጀ ህዝባዊ ኃይል ባለመኖሩ የኢትዮጵያ ህዝብ የታገለላቸዉ የትግል ዉጤቶች ሁሉ የአምባገነኖች መጠቀሚያ ሆነዉ ቀርተዋል።

የኢትዮጵያ ህዝብ ጀግና ነዉ፤ ተጋሽ ነዉ፤ ወይም አርቆ አስተዋይ ነዉ ሲባል እንዚህ እሴቶች ወንዱን፤ ሴቱን፤ ምሁሩን፤ ገበሬዉን፤ ሰራተኛዉንና መለዮ ለባሹን ሁሉ የሚያጠቃልሉ ህዝባዊ እሴቶች ናቸዉ እንጂ የአንድ ህብረተሰብ ክፍል ልዩ ንብረቶች አይደሉም። በእርግጥም አብዛኛዉ የታሪካችን ክፍል በአገር አንድነት ግንባታና ይህንኑ አንድነት ከዉጭ ወራሪዎች በመከላከል ጦርነት ላይ ያተኮረ በመሆኑ ጀግንነትን በቀጥታ የምናያይዘዉ ከዚሁ አገርንና የአገር አንድነትን ከማስከበር ስራ ጋር ነዉ። በእርግጥ አገርን ከጠላት መከላከል ጀግንነት ነዉ፤ ሆኖም መሳሪያ ተሸክሞ አገሩን ከጠላት የሚከላከል ሠራዊት ምን እለብሳለሁ፤ ምን እበላለሁ፤ በምንስ እዋጋለሁ ከሚለዉ ስጋት ተላቅቆ በሙሉ ኃይሉና አዕምሮዉ መዋጋት የሚችለዉ እንደነሱ ጀግና የሆነና በደጀንነት የተሰለፈ ህዝብ ሲኖር ብቻ ነዉ።

እስከ አድዋ ጦርነት ድረስ አገራችን ኢትዮጵያ የመሪዉን የክተት አዋጅ ጥሪ እየሰማ የሚዘምት ህዝብ እንጂ ቋሚ የመከላከያ ሠራዊት አልነበራትም። ባለፉት 60 አመታት ግን ኢትዮጵያ የምድር ጦር፤ አየር ኃይል፤ ብሔራዊ ጦርና እስከ ቅርብ ግዜ ድረስ ደግሞ የባሕር ኃይልን ጭምር ያካተተ ዘመናዊ የመከላከያ ሠራዊት ነበራት። ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ የአገራችንን በትረ ስልጣን እስከጨበጠበት እስከ 1983 ዓም ድረስ የነበረዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከሞላ ጎደል በመስኩ ልምድ፤ ችሎታና እዉቀት ባካበቱ ባለሙያዎች የተሞላና የአገረን ዳር ድንበር ከመጠበቅ ባሻገር ለወገናቸዉ ማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ ደህንነት ቀና አመለካከት ባላቸዉ አገር ወዳዶች የተገነባ ሠራዊት ነበር። ወያኔ በ1983 ዓም አዲስ አበባን ሲቆጣጠር ይህንን አገር ወዳድ የሆነ ፕሮፌሺናል ሠራዊት በትኖ ነዉ ለአንድ ድርጅት ጥቅምና ዝና በቆሙ፤ ፊደል ባልቆጠሩና ሙያዊ ብቃት በሌላቸዉ መሀይሞች የተሞላ መከላከያ ሠራዊት የተካዉ። እንደዚህ ስንል ግን ወያኔ በገነባዉ የአገር መከላከያ ሠራዊት ዉስጥ አገራቸዉ ኢትዮጵያን ከራሳቸዉ በላይ የሚወዱና ለአገራቸዉና ለወገናቸዉ ክብርና ጥቅም መስዋዕት ለመሆን የቆረጡ ሰዎች የሉም ማለት አይደለም፤ እንዲያዉም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሚመራዉና የግዳጅ ትዕዛዝ የሚወስደዉ አገራቸዉን በሚጠሉ ዘረኞች መሆኑ ነዉ እንጂ ዛሬም ቢሆን አብዛኛዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባል የእናት አገሩ ዳር ድንበር መደፈርና የወገኖቹ መረገጥ የሚያንገበግበዉ አገር ወዳድ ሠራዊት ነዉ።

Thursday, January 8, 2015

የወያኔ ከንቱ ፈሊጥ! “ጅብን ሲወጉ በአሕያ ተጠግቶ ነው”

በሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ጅብ እንደሆነ አድርጎ ያስባል፡፡ ይታያቹህ! ከየትኛውም ሀገር ሕዝብ በተለየ መልኩ ታጋሹን፣ ቅኑን፣ ቅዱሱን፣ ስስት ስግብግብነት የሌለበትን፣ አስተዋዩን፣ እሱ እየተቸገረ እየተራበ እነሱን ያጠገበውን ያደለበውን ቸር ምስኪን ሕዝብ ጅብ ነው ብሎ ማሰቡ አይደንቃቹህም? ምን ይደረግ ድንቁርና ተጭኗቸው ይሄን አስከፊ ድንቁርናቸውን ገንዘባችን ብለው አጥብቀው ይዘውት በየት በኩል አስተውለው ይሄንን ማንነቱን ይረዱለት? እናም ጅብ ነው ብለው በማሰባቸው አሕያ እየፈለጉ እሱን በመጠጋት በእሱ በመከለል ሲዎጉት ቆይተዋ ሰሞኑንም በሰፊው ይሄንን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

ወያኔ በዚህ በያዝነው በታሕሳስ ወር 2007ዓ.ም. ከታዋቂ ሰዎችና “ከከያኔያን (Artists)” ለ ሕዝብ ለሕዝብ አቅንኦተ ግንኙነት (Public diplomacy) እና ሕዝብን ለመደለል ተልእኮ በቻለው መጠን እሽ ያሉትን ከያሉበት ሰብስቦ ሁለት ቡድን አዋቅሮ አንዱን ወደ ግብጽ አንዱን ደግሞ የሕወሀት መሪዎች ለትግል አነሣስቶ ወኔ ከሰነቀላቸው ከኢሐፓ እየተነጠሉ ወጥተው ሕወሀትን የመሠረቱበትን 40ኛ ዓመት የምሥረታ በዓላቸውን ምክንያት በማድረግ “የትግራይ ሕዝብ ትግል” ሲሉ በሐሰት የሚጠሩትን ትግል ለመዘከር ወደ ደደቢት በረሀ ልኮ ወይም ሰዶ ነበር፡፡

በእርግጥ ግን ይሄ የሕወሀት ስኬት የትግራይ ሕዝብ አስተዋጽኦ ብቻ ነው? ወያኔዎች እየዋሹና የማይፈጽሙትን ወይም ያልፈጸሙትን ቃል እየገቡ የአማራ ገበሬዎችን አታለው ስንቅ ከመስፈር መረጃ እስከማቀበል፣ ፊት ለፊት እንዲጋፈጡ ተደርገው የመጀመሪያውን ጥይት ቀማሽ እንዲሆኑ ፈንጅ ማምከኛ እንዲሆኑ የተደረጉ ልጆቹን አብረው እንዲታገሉ ከመስጠት እስከ በጉልበቱ በገንዘቡ መደገፍ ከዚያም አልፎ በደርግ ሠራዊት ላይ ፊቱን በማዞርና በመውጋት ሁለንተናዊ ድጋፍ ከአማራ ገበሬ ባያገኙና የአማራ ገበሬ እንደ ጠላት ቢያያቸው ባያቀርባቸው ባያምናቸው ባይደግፋቸው ኖሮ ተከዜን አይሻገሩ እንደነበር ጠንቅቀው እያወቁ እዚህ ለመድረሳቸው ተመስጋኙ ተወዳሹ የትግራይን ሕዝብ ብቻ ሲያደርጉ እንደሰው ውለታ ይዟቸው ትንሽ እንኳን ስቅጥጥ አይላቸውም፡፡

በተደጋጋሚ በቴሌቪዥን (በምርአየ ኩነት) እየቀረበ እንዳያቹህት የወያኔ ባለሥልጣናት ከአማራ ገበሬዎች ጋር ምን ያህል በቅርበት በአካል ገጽ ለገጽ እንደሚተዋወቁ፣ በትግል ወቅት ያደረጉላቸውን ውለታ እንዳይረሱና የገቡትንም ቃል እንዲፈጽሙ ሲጠይቁ ሲያሳስቡ በተገጋጋሚ ተመልክታቹሀል፡፡ እንግዲህ ትውውቃቸውና ቅርርባቸው የዚህን ያህል ነበር፡፡ እንዴት አድርገው አታለው ያንን ሁሉ ድጋፍ ያገኙ እንደነበር ይሄ በቂ መረጃ ይመስለኛል፡፡ እነሱ ግን ቃላቸውን ጠብቀው እናደርግልሀለን ይሉት የነበረውን ሊያደርጉለት ይቅርና ውለታውን ከመርሳትምና ከመካድም አልፈው ጭራሽም ሊያጠፉት በሰይጣናዊ ሸር ሌት ተቀን ያሴሩበታል ይዶልቱበታል በተግባርም ይፈጽሙበታል፡፡ እንዴ! ደግፈን ተዋግተን ለዚህ ያበቃነው ጭራሽ ሊያጠፋን ተነሣብን? ብሎ ተነሥቶ እንዳይቀብራቸውም ሀገሪቱን ከተቆጣጠሩ ማግስት ጀምሮ “እንግዲህ ሀገር ሰላም ሆኗል ለትንንሹ ነገርም እኔ አለሁ እኔ እጠብቃቹሀለሁ” እያለ በየጊዜው በዘመቻ መሣሪያውን አስፈትተው ወስደውበታል፡፡ 

እኔም ህልም አለኝ ለኢትዮጵያ በ2015 እና ባሻገር!!!

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም 
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

“ልጆቻችሁ ወደፊት ምን ሊሆን እንደሚችል ይተነብያሉ…እናም ርዕይን  ይሰንቃሉ፣ የእናንተታላላቆች ደግሞ ህልምን ያልማሉ…”   

በመላው ዓለም ለምትገኙ ሁሉም አንባቢዎቼ እንኳን ለአውሮፓውያን አዲስ ዓመት በሰላምአደረሳችሁ!!!

በየዓመቱ ሁለት የአዲስ ዓመት በዓላትን አከብራለሁ፡፡ የመጀመሪያው እ.ኤ.አ ሴፕቴምበር 1 ቀን የሚውለውን የኢትዮጵያን አዲስ የዓመት በዓል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ እ.ኤ.አ ጃኗሪ 1 ቀን የሚውለውን የፈረንጆችን አዲስ የዓመት በዓል ነው፡፡ እንደዚሁም ሁሉ የሁለት አዲስ ዓመቶች በዓላማ ጽናት ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን ለመተግበር ቃልኪዳን እገባለሁ፡፡

“ለ2007 የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ውሳኔዎች” በሚል ርዕስ ባለፈው መስከረም ወር ባቀረብኩት ትችት በርካታ ድፍረትን የተላበሱ ውሳኔዎችን አስተላልፌ ነበር፡፡ ጥቂቶቹ ውሳኔዎች ለጥቂት ሰዎች በምንም መንገድ ሊተገበሩ የማይችሉ ተምኔታዊ መስለው ሊታይያቸው ይችል ነበር፡፡ የኢትዮጵያን ወጣቶች ሀሳቦች ለማቀጣጠል ብዕሬን (የኮምፒውተር መክፈቻ ቁልፌን) በመጠቀም በጽናት በመቆም እየዳኸ የሚሄደውን አስመሳይነት እንዲዋጉ፣ ጎጂ እንደምታ ያለውን ተስፋቢስነት እና የህዝቡን የተስፋቢስነት ሽባነትን በመዋጋት እንዲያዳክሙ ኃይሉን እንዲያዳክሙ እና የሰብአዊ መብትን በአዲስ መልክ እና በአዲስ አስተሳሰብ በማስተማር እና በመስበክ የህብረተሰቡን የጥላቻ ፖለቲካ በማስወገድ በሀገሪቱ ላይ በፍቅር እና በመተሳሰብ ላይ የተመሰረተ የሰለጠነ የፖለቲካ አካሄድ ስሩን እንዲሰድ ለማስቻል መጣር አለብን የሚል የግል ዉሳኔየን አስተላልፌ ነበር ላዲሱ ዓመት፡፡

ሁሉም ወጣቶች በጠንካራ ተስፋ የተሞሉ ሀሳባውያን ለመሆናቸው ጥርጥር የለኝም፡፡ የአዲስ ዓመት ውሳኔዎች በተፈጥሯቸው ስሜታዊነት የተንጸባረቀባቸው፣ ሀሳባዊነት የሞላባቸው እና እንዲያውም በእውነታ ላይ ያተመሰረቱ እና ተግባራዊ ሊደረጉ የማይችሉ መሆን አለባቸው ብዬ አምናለሁ ፡፡

አንድ ሰው የሰብአዊ መብትን ለማስከበር ቃል ኪዳን ሲገባ እና በጽናት ለመተግበር ውሳኔ ሲያሳልፍ ምክንያታዊ የሆኑ ሀሳቦችን በማቅረብ ሊደገፍ ይገባል ምክንያቱም በአምባገነኖች እና በሰብአዊ መብት ተሟጋቾች መካከል የሚደረገው ጠንካራ የሞት ሽረት ትግል በእራሱ በበጎ ነገር እና በጭራቃዊነት ዕኩይ ምግባራት መካከል የሚደረግ ትግል ነው፡፡ ሆኖም ግን መልካም ነገርም ሆነ ጭራቃዊነት ምግባሮች ዘላለማዊ አይደሉም፣ ሚጉኤል ሰርቫንተስ እንዲህ በማለት ጽፈው ነበር፣ “የጭራቃዊ ምግባር እድሜው በረዘመ ቁጥር መልካም ነገር እየቀረበ መምጣት አለበት”፡፡ በኢትዮጵያ ከምንጊዜውም በላይ ጭራቃዊነት ድርጊት ተንሰራፍቶ ባለበት ሁኔታ እ.ኤ.አ በ2015 በጎ ነገር በየማዕዘኑ ማንዣበብ አለበት! ስለሆነም እ.ኤ.አ በ2015 እና በቀጣይ ዓመታት ግዙፍ እና እጅግ በጣም ግዙፍ የሆኑ በጽናት ላይ የተሞሉ ውሳኔዎች በስራ ላይ መዋል አለባቸው፡፡ በኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በጽናት እንዲተገበሩ ከተያዙት ከእነዚህ ግዙፍ እና እጅግ በጣም ግዙፍ ከሆኑ ውሳኔዎቼ መካከል አንደኛው እንዲህ የሚል ነበር፣ “ስለኢትዮጵያ ህልም የእራሴን ርዕይ ሳይሆን አመለካከቴን ዘርዝሬ ማቅረብ እና ሌሎች ደግሞ በተመሳሳይ መልኩ የእራሳቸውን እንዲያቀርቡ ማድረግ አለብኝ ፡፡“ ሆኖም ግን በመጀመሪያ ደረጃ ህልሞች ምንድን ናቸው? ማለም ማለት ምን ማለት ነው? በህልም እና በሌሊት ቅዥቶች መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው?

ህልሞች ለህልም አላሚው ብቻ የተተው ልዩ የሆኑ ነገሮች ናቸው፡፡ ህልም አላሚው/አላሚዋ የእራሱን/ሷን ህልም በማለም ለእዚያ ህልም የእየራሳቸውን ትርጉም ይሰጡ እና ወደ ተግባር ይለውጡታል፡፡ ህልሞች ለግለሰቦች ብቻ አይደለም ጠቃሚነታቸው ሆኖም ግን ለህዝቦችም ጭምር ነው፡፡ ህልሞች የግለሰቡን/ቧን የማድረግ ዝንባሌ በእጅጉ ይገፋፉታል፡፡ የአፕል ኩባንያ ባለቤት ስቴቭ ጆብስ “ኮምፒውተርን በእያንዳንዱ ሰው እጅ ማስገባት“ የሚል ህልም ነበራቸው፡፡ በዚህም መሰረት በዓለም ታላቅ  ተፈላጊነት ያላቸው የኤሌክትሮኒክስ መሳሪዎችን  መፍጠር ችለዋል።  ጆብስ እንዲህ በማለት ተናግረው ነበር፣ “በመቃብር ቦታ ላይ ታላቁ ሀብታም መባል ለእኔ ትርጉም አይሰጠኝም…ዛሬ ጥሩ የሆነ አስደናቂ ነገርን ሰርተናል በማለት ወደ አልጋዬ ስሄድ ያ ለእኔ ልዩ የሆነ ትርጉምን ይሰጠኛል፡፡“

ህልሞች ለሀገሮች እና ለህዝቦች በጣም ጠቃሚ ነገሮች ናቸው፡፡ የአሜሪካ ህገመንግስት አርቃቂዎች ህልም ለማለም እራሳቸውን ከማዘጋጀታቸው በፊት ሊተገበር ቀርቶ ሊታሰብ የማይችልን ህልም አልመው ነበር፡፡ ህዝብ እራሱን በእራሱ በመረጠው መንገድ ማስተዳደር የሚችልበትን “እንከን የለሽ ስርዓት መገንባትን፣ ፍትህን እና ነጻነትን ለእነርሱ እና ለቀጣዩ ትውልድ ያረጋገጠ ማህበረሰብን አልመው እውን አድርገዋል፡፡”

መታረም የሚገባዉ ማነዉ? (ርዕዮት አለሙ ከቃሊቲ እስር ቤት)


በግል የህትመት ዉጤቶች አማካኝነት በሀገሬ ዉስጥ የምመለከታቸዉን ችግሮች ለህዝብ ማቅረብና እንደዜጋም መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስባቸዉን ሀሳቦች መጠቆም ከጀመርኩ አምስት አመታት አለፉ፡፡ የመጀመሪያ ፅሑፌን ያዘጋጀሁት " "ስህተቶችን" ለማረም የተፈፀሙ ስህተቶችና የስህተት ማረሚያ እርምጃዎች" በሚል ርዕስ እንደነበረ አስታዉሳለሁ፡፡ በዚህም ፅሑፍ የፕሬስ፣የፖለቲካፓርቲዎች ምዝገባና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የተመለከቱ አዋጆች የወጡበት ምክንያትና እንደሀገር የሚያሳድሩትን ተፅእኖ ለመዳሰስ ብሎም ኢህአዴግ ከስህተቶቹ እንዲታረም ለመምከር ሞክሬያለሁ፡፡

የኢህአዴግ ሰዎች በአንድ የገዢዉ ፓርቲ ልሳን በሆነ ድረገፅ አማካኝነት የማስጠንቀቂያ ይዘት ያለዉ ምላሽ መስጠት የጀመሩት ከላይ ከጠቀስኩት የመጀመሪያ ፅሁፌ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በአዲስፕሬስ ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ተቀጥሬ መስራት ስጀምር ግን ሁኔታዉ እየባሰ መጣ፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም አዳማ ላይ ከተለያዩ ሚዲያዎች ለተዉጣጣን ጋዜጠኞች የሰጠዉን ስልጠና ከተካፈልኩ በኋል ከስልጠናዉ ጋር በተያያዘ ለህትመት ያበቃሁት ፅሁፍ ኢህአዴጎችን በእጅጉ አስቆጣቸዉ፡፡ በመሆኑም ወደቢሮአችን ተደዉሎ ከኢህአዴግ ፅህፈት ቤት የተደወለ መሆኑ ከተገለፀ በኋላ ለጽሑፌ ምላሽ የላኩ በመሆኑ በፍጥነነት እንድናወጣዉ ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጠን፡፡ ምላሻቸዉን ለማዉጣት የእነሱ መደወልም ሆነ ትዕዛዝ አስፈላጊ አልነበረም፡፡ የዝግጅት ክፍላችን አንድ ጽሑፍ የቀረበበት አካል ምላሹን በዚያዉ በተፃፈበት የህትመት ዉጤት ላይ ማስነበብ እንደሚችል በህግ የተደነገገ መሆኑን ከማወቁም በላይ የትኛዉንም አይነት ሀሳብ ለማስተናገድ ክፍት ነበርና ምላሻቸዉን በጋዜጣችን ላይ ታተመ፡፡ በዚህ ብቻ ግን አልተገቱም፤ በወቅቱ የገዢዉ ፓርቲን ሀሳብ በማቀንቀን ይታወቁ የነበሩት እንደ ዳጉ ኢትዮጵያና ሰነድ ያሉ ጋዜጦች ሀሳቦቼን በሃሳብ መምታት ባለመቻላቸዉ ይሁን ባለመፈለጋቸዉ ተራ ዘለፋዎችን ያወርዱብኝ ጀመር፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የገዢዉ ፓርቲ ደህንነቶች ስልክ በመደወል፣ በዝግጅት ክፍላችን አድራሻ በስሜ ደብዳቤ በመላክና በአካልም በማግኘት ጭምር መንግስትን የሚተቹ ፅሑፎችን እንዳልፅፍ ሊያስፈራሩኝ ሞከሩ፡፡ "ማስፈራራት የሚቻለዉ የሚፈራ ሲኖር ነዉ" እንዲሉ ሙከራቸዉ ዋጋ አልነበረዉም፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪያ ፅሑፌን ለህትመት ከማብቃቴ በፊት ልከፍለዉ ስለምችለዉ መስዋዕትነት በሚገባ አስቤበታለሁ፡፡ የሀገሬን ጉዳይ በንቃት የምከታተል ዜጋ እንደመሆኔም ከገዢዉ ፓርቲ የተለየ ሀሳብ ያቀነቀኑ ሰዎች የደረሰባቸዉን በሚገባ አዉቃለሁ፡፡ በመሆኑም ከሁለት መጥፎ ምርጫዎች አንዱን ማለትም እነሱ የደረሰባቸዉን ግፍ እንዳይደርስብኝ የሀገሬን ጉዳይ በተመለከተ ፍዝ ተመልካች መሆንን ወይም በሙያዬ የምችለዉን አስተዋፅኦ አበርክቼ የሚመጣዉን መቀበል መምረጥ ነበረብኝ፡፡ ሁለተኛዉን የተሻለ መጥፎ ምርጫ ከመረጥኩ የሰነበትኩ በመሆኑም እየበረከቱ የመጡትን ማስፈራሪያዎች ከቁብ ሳልቆጥር የጋዜጠኝነት ስራዬን መቀጠል ቻልኩ፡፡ በዚሁ መሰረት ስራ ለመያዝ፣ የደረጃ እድገት ለማግኘትም ሆነ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከደህንነት ስጋት የፀዳ ኑሮ ለመኖር የኢህአዴግ አባል ካልሆነም ደጋፊ መሆን ከጊዜ ጊዜ ግድ እየሆነ መምጣቱን የሚያሳዩ፣ ገዢዉ ፓርቲ እንዳጎናፀፈን የሚገልፅልን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በተጨባጭ አለመኖሩን የሚሞግቱ፣ የኢህአዴግን እንደሀገር የማሰብ ችሎታ ወይም ፍቃደኝነት አናሳ መሆን የሚተቹና ሌሎችም መንግስት ቀናነት ቢኖረዉ ኖሮ ሊታረምበት የሚያስችሉትን በርካታ ፅሑፎች አቀረብኩ፡፡ አንድ ቀን ጧት ግን አምባገነኑ መንግስታችን ከጀመርኩት ጉዞ ገታኝ፡፡ ሰኔ10/2003 በወቅቱ እሰራባት በነበረችዉ ተወዳጇ ፍትህ ጋዜጣ ላይ የቀድሞዉን ጠቅላይ ሚኒስትር በተመለከተ ፅሑፍ ለህዝብ ማቅረቤን ተከትሎ ሰኔ14/2003 ዓ.ም ለእስር ተዳረግሁ፡፡

ማዕከላዊና ቃሊቲ ምንና ምን ናቸዉ?

ዉድ አንባብያን፤ ፊዘኛዉ መንግስታችን በሽብርተኝነት እንደሚጠረጥረኝ ገልፆ በእጆቼ ካቴና በማጥለቅ በቁጥጥር ስር አዋለኝ ካዋለኝ ከዚያ ቀን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለቁጥር የሚያታክቱ የመብት ጥሰቶችን እየፈፀመብኝ ይገኛል፡፡ ለአብነት ያህል እጅግ በጣም ጥቂቶቹን እነሆ!

Wednesday, January 7, 2015

Hailemariam’s fake “top 10 educated” list falls apart

By Abebe Gellaw

Haile mariamThe official website of India TV that had published a dubious online ranking two weeks ago that it claimed to be a list of the “top 10 most educated politicians in the world” has retracted the story.

Indiantvnews.com has now pulled back the “top 10” story and changed the title saying the random list was just intended to highlight the educational backgrounds of 10 leaders from around the world without any sort of ranking.

In response to an email inquiry challenging the authenticity of the original list that contradicts publicly available facts, Anushrav Gulati, an editor with the website, acknowledged mistakes in the confusing ranking. “The list was not intended to be any sort of ranking of politicians on the basis of their educational qualifications, but, on the other hand, is merely intended to highlight the educational backgrounds of ten persons,” the editor explained.

Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn was erroneously included in the list despite the fact that he and some of those ranked as being “most educated” turned out to be less educated than so many leaders who were not included in the list. Many leaders with PhD degrees and an impressive list of advanced academic credentials were not included while others with first degrees like Putin were listed among the “most educated politicians.”

Gulati blamed the mishap on the title which originally claimed to be a “top 10” ranking. “You are, perhaps, justified in pointing out that the title of the news item in question could be said to generate some amount of confusion.  We have modified the title to reflect the true intention behind the list as being one highlighting the educational backgrounds of 10 leaders from around the world.”

Hailemariam Desalegn was ranked as the 4th most educated politician in the world. However, it was highlighted to the website that he was not the most “educated politician in Ethiopia, let alone in the world.” In Ethiopia, a country whose literacy rate is one of the lowest in the world, there are several academics and scholars in politics who hold PhD degrees. It is, however, widely believed that educational qualification is less important in politics than other attributes such as humility, honesty, leadership, selflessness and the ability to inspire and empower others. TPLF’s puppet Hailemariam Desalegn is more known for his naked opportunism than his political acumen and leadership qualities.

ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌን እንሁን!!!

በህወሓት ሙሉ ቁጥጥር ስር የሚገኘው የፌደራል ፓሊስ በእሁድ ታህሣሥ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. የቴሌቪዥን ፕሮግራሙ በግፍ እስር ላይ የሚገኘውን የግንቦት 7 ዋና ፀሐፊን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አቅርቦት ነበር። ይህ የ10 ደቂቃዎች ምስል ለቁጥር በሚያታክት ብዛት ተቆራርጦ የተቀጣጠለ በመሆኑ አቶ አንዳርጋቸው ምን ተጠይቆ ምን እንደመለሰ ማወቅ አይቻልም። ስለሆነም በንግግሩ ይዘት ላይ አስተያየት መስጠት ይናገረው አይናገረው በአልታወቀ ጉዳይ ማብራሪያ መስጠት ይሆናል።  ስለዚህም፣ በንግግሩ ይዘት ላይ ጊዜ ከማጥፋት ህወሓት አንዳርጋቸው ጽጌን አሁን ማቅረብ ለምን እንደፈለገ መተንተን ይበልጥ ጠቀሜታ  አለው ብሎ ግንቦት 7 ያምናል።

አሁን ህወሓት በውስጥም በውጭም ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የገባበት ጊዜ ነው፤ በራሱ በድርጅቱ ውስጥም ሰላም የለም። ህወሓት የትግራይ ክልል ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሩ ስር እንደሆነ አድርጎ በመቁጠር መላዋን ኢትዮጵያን ለመዝረፍና ለማጥቃት እንደ መንደርደሪያ፤ በሌላኛው የኢትዮጵያ ክፍል ተቃውሞ ሲበዛበት ደግሞ እንደ መደበቂያ ዋሻ ሲጠቀምበት የነበረው ጊዜ አብቅቶ የትግራይ ሕዝብ በህወሓት ላይ ማመጹ በግልጽ በተግባር እየታየ ነው። በርካታ የትግራይ ልጆች በህወሓት ላይ ነፍጥ አንስተዋል፤ ከፊሎቹ ደግሞ በሰላማዊ ትግል ህወሓትን ማስወገድ ይቻላል ብለው በክልላቸውም ከክልላቸውም ውጭ ከህወሓት ጋር ፍልሚያ ገጥመዋል። ህወሓት መሠረቴ ነው ከሚለው የትግራይ ክልል ፈጽሞ ሊነቀል የሚችል መሆኑ ግልጽ ምልክቶች እየታዩ ነው። የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) ከትግራይና ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያገናኘው የአማርኛና የትግርኛ የቴሌቪዥን ፕሮግራም መጀመሩ የህወሓት ሹማምንትን ናላ ያዞረ እርምጃ ሆኗል።

የህወሓት ሌላው መተማመኛው የጦር ሠራዊቱ ነበር። ህወሓት፣ የኢትዮጵያን መከላከያ ጦር ሠራዊት ዘረኛ በሆነ መንገድ አደራጅቶ፤ ከፍተኛ አመራሩን በታማኝ አባላቱ ሞልቶ ተደላድሎ  የተቀመጠ መስሎ  ታይቶ ነበር። አሁን ግን ይህም ምስል አሳሳች እንደሆነ ግልጽ እየሆነ መጥቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት የኢትዮጵያ ጠላት የሆነውን ህወሓትን የማገልገል ፍላጎት የሌላቸው መሆኑን፤ እንዲያውም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን በመቆም የህወሓትን ውድቀት ለማፋጠን ያላቸውን ጉጉት በግልጽ እያሳዩ ነው። አየር ኃይል ውስጥ ያለው ተቃውሞ ገሀድ የወጣ  ዜና ሆኗል። እንደ አየር ኃይል ገሀድ የወጣ ዜና አይሁን እንጂ በሌሎችም የሠራዊቱ ክንፎች ያለው አመጽ ተመሳሳይ የጡዘት ደረጃ ላይ ደርሷል።

ብአዴን እና ኦህዴድ ውስጥ ለአገራቸው ለኢትዮጵያ፣ እንወክለዋለን ለሚሉት ሕዝብ እና ለራሳቸው ክብር ያላቸው አባላት ብቅ ብቅ እያሉ ነው። ብአዴንንና ኦህዴድ እንደ ድሮ ፍጽም ታማኝ አገልጋዮች የመሆናቸው ጊዜ እያበቃ ነው። ደኢህዴንም ቢሆን ሙሉ በሙሉ የሚታመን አይደለም። ጊዜው ለህወሓት እጅግ የመክፋቱ ምልክት ደግሞ እራሱ ህወሓት ውስጥም ስምምነት የሌለ መሆኑ ነው። ህወሓት ይይዘው ይጨብጠው ጠፍቶታል።

Saturday, January 3, 2015

“ለኢትዮጵያ አንድነት በጽናት እንቆማለን” - ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

የአፍሪካ አሜሪካዊ ደራሲ፣ ገጣሚ፣ የዳንስ ተወዛዋዥ፣ ተዋናይ እንዲሁም የሙዚቃ አቀንቃኝ የሆነችው ማያ አንጌሉ እንዲህ በማለት አውጃ ነበር፣ “የእኛን ጀግኖች እና ጀግኒቶች ማስታወስ እና መዘከር እንዴት ያለ ጠቃሚ ነገር ነው!“እኛም እነዚህንም የሀገር ጀግኖች እና ጀግኒቶች ተራ በተራ እያነሳን እናክብራቸው፣ እናወድሳቸው ምክንያቱም በአሁኑ ጊዜ ሀገሪቱ ከገባችበት ማጥ ውስጥ እንድትወጣ ለማድረግ እና ነጻነት እና ዴሞክራሲ በሀገራችን እንዲሰፍን እራሳቸውን ለመስዋዕትነት ያቀረቡ የሀገር ዕንቁዎች ናቸውና፡፡

1ኛ) እስክንድር ነጋ፡ የሀገሪቱ መናገሻ ከተማ ከሆነችው ከመሀል አዲስ አበባ በስተደቡብ በኩል ወጣ ብሎ በጥቂት ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ከሚገኘው በአስከፊናቱ ከሚታወቀው ከመለስ ዜናዊ የቃሊቲ የማጎሪያ እስር ቤት ታስሮ በመሰቃየት ላይ ከሚገኘው ከታዋቂው እና የኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት ቀንዲል ከሆነው ከእስክንድር ነጋ እጅ በድብቅ በወጣ ደብዳቤው “በጽናት እቆማለሁ” በማለት ጽፏል፡፡

እስክንድር “በጽናት እቆማለሁ!” ሲል ዝም ብሎ ስለእራሱ ለመጻፍ ፈልጎ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን በማጎሪያው እስር ቤት በመሰቃየት ላይ ስላሉት የስራ ባልደረባ ጋዜጠኛ ጓደኞቹ፣ ጦማሪያን፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና ስለሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ዓላማም ጭምር ነው፡፡ ከዚህም በላይ አንድ የህሊና እስረኛ ወይም ደግሞ አንድ የፖለቲካ እስረኛ ብቻውን በጽናት ሊቆም አይችልም፡፡ ብቻውንም በጽናት ቆሞ ብቻውን ውጤት ሊያመጣ እይችልም፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ኢትዮጵያ እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ ከሚጠራው የአምባገነን ወሮበላ ስብስብ መዳፍ ስር ወድቃ በመማቀቅ ላይ እያለች ለዚህ እኩይ ምግባር አራማጅ ዘረኛ ድርጅት የአደባባይ እስረኛ ምርኮኛ ሆኖ በጸጥታ ስለሚገኘው ከ90 ሚሊዮን በላይ ለሆነው ኢትዮጵያዊ/ያት ወገኑ ሁሉ መልዕክት ለማስተላለፍ አስቦ የጻፈው መሆኑን በድፍረት መናገር እችላለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ከወያኔ አምባገነን የወሮበላ ስብስብ ነጻ ለመውጣት እና እውነተኛ የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ ለመገንባት በጽናት ትቆማለች፣ እናም ታሸንፋለች!

እ.ኤ.አ በ2014 የተጠናቀቀውን አሮጌ ዓመት ምክንያት በማድረግ የእኔን ጀግና እስክንድር ነጋን እና የእኔን ጀግኒት ርዕዮት ዓለሙን እንደዚሁም በእነርሱም ስም ሁሉንም የፕሬስ ነጻነት የህሊና እስረኛ ጀግኖች እና ጀግኒቶች ኢትዮጵያውያን/ት የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች፣ ለምንም ለማንም ለድርድር ለማይቀርበው ነጻነት ምርኮኛ ለሆኑ ህዝቦች፣ ለነጻ እና ፍትሀዊ ምርጫ ለሚታገሉ፣ ለመልካም አስተዳደር እና ለሰብአዊ መብት መከበር ለሚታገሉ ወገኖች ሁሉ ደወል በመደወል ድምጼን ከፍ አድርጌ በመናገር አወድሳቸዋለሁ፡፡ እነርሱን በማወደስ በኩራት እንዲህ እላለሁ፣ “እንደ ፖለቲካ እስረኛነታችሁ በጽናት ቆማችኋል! እኛም በጽናት ቆመናል! ኢትዮጵያ በአምላክ ቸርነት እንደ አንድ ሀገር ብሄር በጽናት ቆማለች፡፡ የእኛን ነጻነት በመግፈፍ በባርነት እና በሁለተኛ ዜጋነት በማስቀመጥ ሲበዘብዙን እና ሲመዘብሩን ለመቆየት ዕቅድ አውጥተው የቆሙት ሆድ አምላኩ ፍጡሮች ጽናት እስከሚሟሽሽ እና ደብዛው እስከሚጠፋ ድረስ በጽናት እንቆማለን፡፡ ድል አድራጊነት ለእውነት በጽናት ለቆሙት ብቻ የተሰጠ ጸጋ ነው!“

ሸክስፒር እንዲህ በማለት ጽፈው ነበር፣ “ጥቂቶች ታላቅ ሆነው ተወልደዋል፣ ጥቂቶች ታላቅነትን በሂደት ይጎናጸፋሉ፣ ጥቂቶች ደግሞ ሁኔታዎችና ፈተና ታላቅነትን ያጎናፅፋቸዋል፡፡“ እንደዚሁም በተመሳሳይ መልኩ በእኛ ጀግኖች እና ጀግኒቶች ላይ እምነትን መጣል ይቻላል የሚል እምነት አለኝ፡፡ እንደ እስክንድር እና ርዕዮት ያሉ ዜጎች (ሁሉንም በኢትዮጵያ በማጎሪያው እስር ቤት በመማቀቅ ላይ የሚገኙትን ሌሎችን የህሊና እስረኞች ይወክላሉ) ጀግኖች እና ጀግኒቶች ናቸው ምክንያቱም በሀገሪቱ ላይ ፈታኝ የሆነ አደገኛ ሁኔታ በተፈጠረበት ጊዜ ጀግንነት በእነርሱ ላይ እምነቱን ጥሏልና፡፡ የእነርሱን የህይወት ዕጣ ፈንታ ፈልገው ባገኙበት ጊዜ እንደ አብዛኞቻችን ፊት ለፊት መጋፈጥን እርም ብለው አላስወገዱም ወይም ደግሞ እንደ ግመል ሽንት ወደኋላ አልተስፈነጠሩም፣ እንደዚሁም እንደ ተልባ ስፍር አልተንሸራተቱም፡፡ እነዚህ የጀግንነት ተምሳሌቶች የአሽከርነት ወይም የለማኝነት ባህሪን አልተላበሱም፡፡ እነዚህ የጀግንነት ቀንዲሎች ሌሎች ለከርስ ብቻ የቆሙት ሆዳሞች እንደሚያደርጉት ሁሉ ስብዕናቸውን በቤሳ ሳንቲም አልለወጡም፣ እንደሌሎች ቆርጦ ቀጥሎች አይደሉም፣ በጽናት ከቆሙለት ዓላማ አንዲት ጋት ወደኋላ አላፈገፈጉም፡፡ ላመኑበት ዓላማ በጽናት ቆመዋል፣ ይቆማሉም፡፡ በወሮበላ የጫካ አገዛዝ ነጻነት በሌለው አጥር የሌለው አስርቤት ውስጥ እየሰገዱ እና እየተንገዳወሉ ከመኖር ይልቅ ያመኑበትን ዓላማ በማራመድ ነጻነትን ይዞ በእስር ቤት መኖርን መርጠዋል፡፡

እስክንድር እና ርዕዮት በጉልበታቸው የሚንበረከኩ ቢሆን ኖሮ፣ ራሳቸውን ዝቅ አድርገው በማጎንበስ ቢለምኑ ኖሮ፣ ወንጀለኛ ተብለው የተፈበረኩባቸውን የሸፍጥ መሰሪ የውንጀላ ክሶች አምነው ይቅርታ ቢጠይቁ ኖሮ፣ የአሳሪዎቻቸውን እግር ቢልሱ እና ይቅርታ እንዲደረግላቸው ቢለምኑ ኖሮ ከማጎሪያው እስር ቤት ይወጡ ነበር፡፡ ከእነዚህ የዓላማ ጽናት ተምሳሌቶች ቀደም ብሎ አሁን በህይወት በሌሉት መለስ ዜናዊ እና ደቀመዝሙሮቻቸው አማካይነት ይቅርታ እየተደረገላቸው እንደወጡት በርካታ ወገኖች ሁሉ ያለምንም ችግር ከማጎሪያው እስር ቤት ይወጡ ነበር፡፡ በሸፍጥ የፍብረካ ወንጀል ክስ አሸባሪ በሚል የገዥው ወሮበላ ስብስብ የማደናገሪያ ታፔላ ተለጥፎባቸው በዝንጀሮው የይስሙላ ፍርድ ቤት 11 ዓመታት በእስራት እንዲቀጡ ተበይኖባቸው የነበሩት ጆሀን ፔርሰን እና ማርቲን ሽብዬ በተመሳሳይ መልኩ ይቅርታ ጠይቀው እንዲወጡ ነበር የተፈለገው፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል-አቀባይ ኢሳት ወይስ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት?


(ወሳኝ ሀገራዊ መረጃዎችን ከመንግሥት መጠበቅ የለብንም ይሆን?)

በኤልያስ ገብሩ
---------------------
በእያንዳንዱ ሀገር ያለ ገዥ መንግሥት የየራሱ መረጃ ለህዝቡና ለዓለም-ዓቀፍ ማኅበረሰብ የመስጠት ባህሪ፣ ልምድና ባህል አለው፡፡ ወሳኝ የሆኑ ሀገራዊ፣ መንግሥታዊና ኅብረተሰባዊ መረጃዎች በሚመለከታቸው የመንግሥታት የመረጃ ሰጪ አካላት በኩል መረጃው ለሚያስፈልገው ሁሉ መድረስ እንደሚያሻ እሙን ነው - በተለይ በዘመነ ግሎባላይዜሽን እና በ21ኛው ክ/ዘመን!
ኢትዮጵያን በተለያዩ ጊዜያት ያስተዳደሩ መንግሥታት ‹‹እየመራነው ነው፤ እያስተዳደርነው እንገኛለን›› ለሚሉት ሕዝብ መረጃን የሚሰጡበት የየራሳቸው አካሄድ ነበራቸው፡፡ በአሁን ወቅት ሀገራችንን እያስተዳደረ የሚገኘው ገዥ ፓርቲ ኢህአዴግ ነውና በእሱ ላይ ማተኮር ተገቢ ነው፡፡

ሕወሃት/ኢህአዴግ ከጫካ ጀምሮ ሀገሪቷን ተቆጣጥሮ ማስተዳደር እስከጀመረበትና አሁን እስካለበት ድረስ ‹‹አስተዳድረዋለሁ›› ለሚለው ሕዝብ መረጃን የሚያደርስበት የራሱ መንገድ እንዳለው ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ በሕዝብ ሀብት የሚንቀሳቀሱት የቴሌቭዥን እና የሬዲዮ ጣቢያዎቻችን ለሥርዓቱ በግልጽ ወግነው የሥርዓቱ የፕሮፖጋንዳ መሳሪያ ሆነው ለዓመታት ማገልገል መቀጠላቸው፤ የአደባባይ ሃቅ በመሆኑ ልለፈውና ወደዛሬ ጽሑፌ አንኳር ነጥብ ላምራ፡፡

ዛሬም በከተማ እየኖሩ በጫካ ባህል መታነቅ!

፩. የጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ህመም

በሽግግሩ መንግሥት ጊዜ ለአራት ዓመታት ፕሬዚዳንት በመሆን፣ ከዚያም በኋላ በጠ/ሚኒስትርነት ለ17 ዓመታት ኢትዮጵያን በበላይነት የመሯትን የሟቹ ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊን ማንሳት ዛሬ ግድ ነው፡፡ ጠ/ሚኒስትሩ በግንቦት ወር 2003 ዓ.ም ለዓለም ዓቀፍ ስብሰባ ሄደው ከተመለሱ በኋላ ጤንነታቸው ታውኮ እንደነበር ውስጥ ውስጡን ይወራ ነበር፡፡ በዚያው ሰሞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ አዘጋጅቶ መግለጫ ሰጥቶ ነበር፡፡ በአቶ መለስ ጤንነት ዙሪያ የሚናፈሱ ወሬዎችን ተከትሎ ከሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች ጥያቄ ቀረበ፡፡ የጽ/ቤቱ ሚኒስትር ደኤታ አቶ ሽመልስ ከማልም አቶ መለስ በመልካም ጤንነት ላይ መሆናቸውን ጠቁመው ‹‹ይኼ የኢሳትና የእሳት ወሬ ነው›› በማለት መልስ ሰጡ፡፡ በሂደት ይኼ ምላሻቸው እውነት አለመሆኑ ታየ፡፡ አቶ ሽመልስስ ቢሆኑ የተጠየቁትን እውነተኛ ጥያቄ ከመመለስ ባሻገር የኢሳትን ዘገባ ወደማጣጣል ለምን አተኮሩ?
የኢትዮጵያ መንግሥት የጠ/ሚ/ሩን መታመም አፍኖ ቢቆይም፣ በሰኔ ወር 2003 ዓ.ም በተካሄደው 19ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ስብሰባ ላይ ተካፋይ የነበሩት የሴኔጋሉ ፕሬዚዳንት ማኪይ ሳል አቶ መለስ መታመማቸውን ተናግረው ምሕረትን ተመኙላቸው፡፡ ስለመሪያቸው ጤንነት ማወቅ የፈለጉ ኢትዮጵያውያኖችና ትክክለኛውን እውነት አውቀን ለሕዝብ ተገቢውን መረጃ ማድረስ የፈለግን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች፤ በገዛ ሀገራችን ባይተዋር ሆነን ከሌላ ሀገር መሪ መስማታችን በወቅቱ አሳዛኝ ክስተት ነበር፡፡
ቀናቶች ካለፉ፣ በጉዳዩ ዙሪያ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ወሬዎች ከተናፈሱ በኋላ ‹‹አውቆ ከተኛበት›› በመነሳት መግለጫ መስጠት ግድ የነበረበት መንግሥት ሀሙስ ሐምሌ 15 2003 ዓ.ም ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ጋዜጠኞች መግለጫ መስጠት ግድ ሆነበት፡፡ እኔም በወቅቱ ‹‹ፍትህ›› ጋዜጣ ላይ ዘገባ ለመስራት ከቀኑ 9፡20 ሰዓት ገደማ በመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከታደሙ የሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች ጋር ተቀላቀልኩ፡፡ ከአፍታ ቆይታ በኋላ ሚኒስትር አቶ በረከት ስምኦን ገቡና ቦታቸውን ያዙ፡፡ አጠር ያለ ጋዜጣዊ መግለጫም ሰጡ፡፡ ከጎናቸው አቶ ሽመልስ ተቀምጠው ነበር፡፡

የአቶ መለስ መታመም የመግለጫው ዓላማ ዋናውና ቀዳሚው መሆኑን አቶ በረከት ጠቆሙና፤ ጉዳዩ በይፋ ያልተነገረበት እና ከአንድ ወር በፊት በጋዜጠኞች ቀርቦ የነበረው ጥያቄ የተስተባበለበትን ምክንያት አስረዱ፡፡ አያይዘውም ‹‹የገዥውን ባህል ማወቅ ጠቃሚ ይመስለኛል›› ገዥው ፓርቲ አብዛኛውን ጊዜ ዕድሜውን በበረሃ ያሳለፈ በመሆኑ በማንኛውም ሁኔታ መስዋዕትነት እየከፈለ ችግሮችን ተሸክሞ ማለፍ የሚችል ነው፡፡ በግለሰቦች ላይ የሚጋጥም ጉዳይ እንደ ትልቅ ነገር ተደርጎ የሚወሰድ አይደለም፡፡ ሕመምና የመሳሰሉት ችግሮች የአብዛኛው አመራር የሕይወት አካል ነው፡፡›› በማለት መልስ ሰጡ፡፡ በወቅቱ አቶ በረከት ‹‹የገዥውን ባህል ማወቅ ጠቃሚ ይመስለኛል›› የምትለዋ አገላለጽ ጥያቄ ፈጥራብኝ ነበር፡፡

Thursday, January 1, 2015

ቀኑ ሲቃረብ መውጫው ይጠባል!

ኢትዮጵያ ሀገራችን በታሪኳ ከአስከፊ የፈተና አረንቋ ውስጥ ተገፍታ የገባችበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ዜጎችዋ ከፋሽስት ኢጣልያ በከፋ ሁኔታ ይህ ቀረሽ የማይባል የመከራ መአት የወረደባቸውና እየወረ ደባ ቸው የሚገኝበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመን ወያኔ ብቻ ነው፡፡ እስር ቤቶች ሞልተው ተጨማሪ እስር ቤቶች መገ ንባት ከልማት ተቆጥሮ የሚፎከርበት ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የሀገሪቱ ብሄራዊ ባንክ ንብረት የሆ ነው ወርቅ በባሌስትራ ለውጦ እስከ መዝረፍ የደረሰ በጠራራ ፀሀይ የህ ዝብና የሀገር ሀብት ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ በጥቂቶች የሚዘረፍበት ዘመን ቢኖር የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የጅምላ እስር፤ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ ስደትና መፈናቀል፤ ይበልጡንም በታሪካችን ታይቶ በማያውቅ መልኩ ለሞት፤ ለእስር፤ ለመፈናቀልና ለስደ ት ምክንያቱ የተገኘንበት ዘውግ የሆነበት ዘረኛ ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡

ባጠቃላይ ላለፉት 23 አመታት ወያኔ ማድረግ የሚችለውን አስከፊ ነገር ሁሉ በሀገርና በህዝብ ላይ ሲፈፅም ቆይቷል፡፡ ዛሬ ከ23 አመ ታት በዃላ ሀገራችንና ህዝባችን ያልተዘፈቁበት የችግር ማጥ፤ ያልደረሰ የሀብትና የሰብአዊ ውድመት፤ ያልተፈፀመ የግፍና የሰቆቃ አይነት የለም፡፡ ወያኔ ይህን ሁሉ ሲፈፅም መሳሪያ አድርጎ ከተጠቀመባቸው ተቋማት ውስጥ ዋነኛዎቹ የመከላከያ፤ ፍርድ ቤትና የፖሊስና የደህንነት መሆናቸው ጥያቄ የለውም፡፡ የእነዚህ ተቋማት አባላት ከወያኔ ጥቃት ሰለባ ከመሆን ባይተርፉም የዚህን ወንጀለኛና ዘረኛ ቡድን እድሜ በአንድ ቀን በመጨመሩ ስራ ላይ ከፍተኛውን ድርሻ እንደያዙ ዛሬም መገኘታቸው አሌ የማይባል እውነት ነው፡፡ይህ ሲባል ግን በሀገርና በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ክህደት፤ ግፍና ሰቆቃ የሚያማቸው፤ መከራው መረራቸው፤ ብሶቱ ብሶታቸው የሆኑ አባላት የሉም ማለት እንዳልሆነ፤ ይልቁንም አብዛኛዎቹ የዚህ ስሌት ተካፋይ ስለመሆናቸው የሚጠራጠር የለም፡፡

ነገር ግን ከህዝብ አብራክ በወጡና ልጆቹን ሳይመግብ በከፈለው ታክስ በተደራጀ የመከላከያ፤ የፖሊስና የደህንነት ተቋማት ውስጥ የምትገኙ አብዛኛውና የግፉ ቀማሽ የሆናችሁ አባላት ዛሬ የምትገኙበት ሁኔታ እንደ አለፉት 23 አመታት በማወቅም ሆነ ባለማወቅ፤ ከዛሬ ነገ የተሻለን ነገር ተስፋ በማድረግ፤ በግርግሩ ፍርፋሪ ሊወድቅልኝ ይችላል ከሚል ራስ ወዳድነት…… ወዘተ በመሳሰሉ በርካታ ምክንያቶች ለፍትህ፤ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ብሎም ለኢትዮጵያችን ቀጣይ ህልውና በሚደረጉ ህዝባዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በመቆም ብሎም የጥቂት ዘረ ኛች ስልጣንና ምቾት እድሜ ለማራዘም የተጓዛችሁበት መንገድ ብዙም ማስኬድ ከማያስችልበት፤ ይልቁንም ዛሬ ከሁለት መንታ መንገድ የ ደረሳችሁበትና ቆም ብሎም ማየትና ማገናዘብን ከሚጠይቅ ወቅት ላይ ትገኛላችሁ፡፡ አንዱ በዘረኝነት በትር እየተወቀጡ የወያኔ ሎሌ ሆኖ መቀጠል፤ ሌላው ከህዝብ አብራክ የተገኛችሁ ናችሁና ከህዝብ ወገን ተቀላቅሎ ሀገርን፤ ወገንንና ራስን ነፃ ለማውጣት መነሳት..

ስንቴ፣ በስንቱ እንታለላለን?

በፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም

ከብዙ ዓመታት በፊት ሪፖርተር ጋዜጣ የኢሳይያስ አፈወርቂና የድርጅቱ አቀንቃኝ ነበረ፤ ዛሬ ከሌሎች ብዙዎች ጋር በመቃብር ውስጥ ያለው የመጀመሪያው የሪፖርተር መጽሔት በሙሉ ውዳሴ ኢሳይያስ አፈወርቂ ነበር፤ የሞተው መለስ ዜናዊ እያለ የሪፖርተር መጽሔት ኢሳይያስን በመጀመሪያ እትሙ ሲያወድስ ነበር፤ በቅርቡ ደግሞ ደፋሩ የወያኔ አባት ስብሐት ነጋ ለኤርትራ ያለውን ልዩ ፍቅር በሚያስገርም ሁኔታ ገልጾ ነበር፤ ለኤርትራ ቆመን እንዋጋለን አስከማለት ደርሶ ነበር፤ መለስ ዜናዊ በልዩ ጥበቡ መጀመሪያ ኤርትራን ባዕድ አደረገ፤ ቀጥሎም ጠላት አደረገ፤ ክፉ ጦርነት ተደረገ፤ በጦርነቱ ያሸነፈ የለም፤ በፍርድ ግን ኤርትራ አሸነፈች ተባለ፤ ፍርዱ ዋጋ-ቢስ ቦሆንም!

ዛሬ ደግሜ ሪፖርተር ሌላ ስብከት ይዞ መጥቶአል፤ በመጀመሪያ ሪፖርተር ጋዜጣ ለኢትዮጵያዊነት ያለውን ወይም የሌለውን ስሜት ከየት አመጣው? ብዬ እንድጠይቅ እገደዳለሁ፤ አንዱ የሪፖርተር ጋዜጠኛ ‹‹ኢትዮጵያዊ ዝብሀል መንነት የለን፤›› ብሎ በአጽንኦት ጽፎ ነበር፤ ዛሬ በሪፖርተር ርዕሰ አንቀጽ ላይ ያነበብሁት ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት እንዳለ ነው! ለመግቢያ ያህል ይበቃኛል፡፡
ሪፖርተር በታኅሣሥ 22/2007 ርእሰ አንቀጹ የሚከተሉትን ሀሳቦች ሊያስጨብጠን ሞክሮአል፤

1. ‹‹አንዱ የሌላውን ድክመትና ጉድለት ከራሱ ጥንካሬ ጋር እያወዳደረ ከማየት ይልቅ የአገርና የሕዝብ ጠላት አድርጎ መፈረጅ ይቀለዋለ፤›› ይህ የሚፈጸመው ‹‹በገዢው ፓርቲና ዋነኛ በሚባሉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ነው፤›› ማንም ኢትዮጵያዊ ይህንን ርእሰ አንቀጽ በትክክልና በጥሞና ሳይታለልና ሳይሞኝ ማንበብ አለበት፤ እዚህ ላይ ሪፖርተር በገዢው ፓርቲና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መሀከል ያለውን ግብግብ በሁለት እኩዮች መሀከል የሚደረግ አድርጎ ይዘግበዋል፤ ገዢው ፓርቲ የሚለው በደንብ የታጠቀ የፖሊስና የጦር ሠራዊት፣ በሎሌለንት የሠለጠኑ ዓቃቤ ሕጎችና ዳኞች፣ በመደብደብና በማሰቃየት የሠለጠኑ የጸጥታ ሰዎችና መርማሪዎች፣ በአይጥ፣ በቱሀንና በቁንጫ የተወረሩ እስር ቤቶች ያለውን ገዢ ፓርቲ ባዶአቸውን ከቆሙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ጎን ለጎን አቁሞ ይናገራል፤ እግዚአብሔር ያያል፤ ታሪክም አንድ ቀን ይዘግባል፡፡

2፣ ‹‹ቅራኔአቸውን አርግበው ለመራጩ ሕዝብ ውሳኔ ተገዢ እስካላደረጉ ድረስ ስለምርጫም ሆነ ስለዴሞክራሲ መናገር አስቸጋሪ ነው፤›› ይህ አሁንም ለሁለቱም በእኩልነት የተነገረ ይመስላል፤ እግዚአብሔር ያያል፤ ታሪክም አንድ ቀን ይዘግባል፡፡