Thursday, May 28, 2015

አምስተኛው ዙር የድምጽ ዘረፋ . . . (ክንፉ አሰፋ)

የ”ምርጫው” ድራማ እየተተወነ ሳለ፤ የቦርዱ ሊቀመንበር ዶ/ር መርጋ በቃና እና ምክትል ሊቀመንበሩ ዶ/ር አዲሱ ገብረእግዚአብሔር ለአቦይ ስብሃት ስልክ ደወሉ።

“ሃሎ?”
“ሃሎ፣ አቦይ ስብሃት ኖት?”
“ነኝ፣ ምን ፈለግክ?”
“ዶ/ር መርጋ በቃና እና ዶ/ር አዲሱ ገብረእግዚአብሔር ነን።”
“ችግር መስማት አልፈልግም። የታዘዛችሁትን አደረጋችሁ?”
“99.8% ህዝብ አልመረጠንም። ግን በታዘዝነው መሰረት ውጤቱን ገልብጠነዋል!”
“0.2% ብቻ ነው የመረጠን ማለት ነው?”
“አዎን ጌታዬ። ሌላ ምን እንታዘዝ?”
“99.8% ህዝብ የስም ዝርዝሩን አንብብልኝ።” አሉ አቦይ ስብሃት እየተባለ ይወራል።

አንድ ወዳጄ ስለ አቦይ ስብሃት የነገረኝ ታወሰኝ። ሰውዬው ከግመል እንኳን የማይሻል እንስሳ ብጤ ነው። ግመል ሳትጠጣ ለቀናት ትሰራለች አቦይ ስብሃት ደግሞ ሳይሰራ ቀኑን ሙሉ ይጠጣል። አብዛኞቹ የህወሃት አባላት እድሜያቸው እንደ አስተሳሰባቸው ስላረጀ ጨዋታቸው ከውሃ ጋር ነው። ከውድ ውሃ ጋር!  ድንጋይን ውሀ ያስጮኸዋል!

ሜዳው የኢህአዴግ፣ ዳኛው ኢህአዴግ፣ ታዛቢው ኢህአዴግ፣ ድምጽ ቆጣሪው ኢህአዴግ እንዲሆን ተደርጎ የተዘጋጀው “ምርጫ” እነሆ ተጠናቀቀ። በአፈና የታጀበው ምርጫ ጸጥ-እረጭ ባለ ድባብ ተጠናቅቋል። ልክ አስገድደው እንደሚደፍሩ ወሮበሎች፤ በሃይል ጠልፈው ያላቻ ትዳር እንደሚመሰርቱ ጉልበተኞች፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያለፍቃዱ እንደገና የአምስት አመት የትዳር ቁርኝት ውስጥ ገብቷል።  ሌላ አምስት አመት። ሌላ የህወሀት ዘመን። ሌላ የጥርነፋ ዘመን!  ሌላ የቁምራ ዘመን! ሌላ የመፈናቀል ዘመን! ሌላ የመሬት ነጠቃ ዘመን! ሌላ የስደት ዘመን!. . .

የህወሃት ሰዎች አሁን የጭንቀቱ ምእራፍ ሁለት ላይ ናቸው። በዛሬው እና በትላንቱ እለት የህወሃት ባለስልጣናት ተሰባስበው በፐርሰንቱ ምደባ ላይ ውይይት ይዘዋል። ዘረፋው ላይ ሁሉም በ 100% ይስማማሉ። ምደባው ላይ ግን ችግር አለ።  አንዳንዶቹ ይህ ጉዳይ ተአማኝነት እንዲኖረው ለተቃዋሚዎቹ ትንሽ መልቀቅ ይኖርብናል ሲሉ ለሎች ደግሞ ይህንን ሃሳብ ይቃወማሉ። ጥቂት ተቃዋሚዎችን ፓርላማ እንዲገቡ መፍቀድ አለብን የሚሉ ተከራካሪዎች “ሌባ ከሰረቀው ጥቂቱን ቢሰጥ” እንደማይጎዳው ይናገራሉ።  ይህንን የማይቀበሉት ግን የተቃዋሚዎች በፓርላማ መግባት ራስ ምታት እንደሚሆንባቸው በስፋት መክረዋል። 547 መቀመጫ የነበረው የቀድሞው ፓርላማ ውስጥ እውነትን የያዘ አንድ ተቃዋሚ ብቻ ጭንቅላታቸውን በጥብጦት እንደነበር ሁሉም አይዘነጉትም። ይህንን በድጋሚ መፍቀድ አልያም ውግዘቱን በመቀበል መሃል ባለ አጣብቂኝ ውስጥ ከርመዋል። ውጤቱን ከሰሞኑ ይፋ ያደርገዋል ዶ/ር መርጋ።

የዘንድሮው ዝርፍያ ጤናማ አይደለም።  ልክ እንደ ቦራት ዘ-ዲክታተር ፊልም ተወዳዳሪዎችን እግር እግራቸውን እየመቱ ለብቻ ሮጦ፤ በራስ ዳኛ የድል ዋንጫ መረከብ? ይህ በእውነት በዚህ በ21ኛው ዘመን እጅግ የሚያሳፍር ተግባር ነው። ተቃዋሚ ሃይሎች በምርጫው ክርክር እና በትውልድ ስፍራቸው ላይ የነበራቸው የሕዝብ ድጋፍ ምን ያህል እንደሆነ በግልጽ በታየበት ሁኔታ ህወሃቶች 100% አሸንፈናል ሲሉ ከሌብነታቸው ይልቅ ንቀታቸው ጥርስ የሚያስነክስ መሆኑን ለአፍታ እንኳ አላስተዋሉትም። እጅግ ትንሽ ጭል ብላ የነበረችውን ዲሞክራሲ በምድረ ኢትዮጵያ ገድለው፣ ከፍነው ቀበሩት። አዲዮስ ዲሞክራሲ . . .

ፈረንጆች የሚሉት አባባል አለ። “ለነብሰ-ገዳዮች ትክክለኛ ዲሞክራሲ ማለት ፍጹም አምባገነን መሆን ነው።”

Wednesday, May 27, 2015

Statement by the EU Spokesperson on elections in Ethiopia

"Ethiopia has peacefully concluded its pre-election process and voting and many parties and participants have actively engaged in the process. The National Electoral Board of Ethiopia has put hard work and organisational efforts into ensuring that as many of Ethiopia's 36.8 million registered voters as possible had the chance to exercise their vote.

The EU is encouraged that the process was largely peaceful and orderly. It takes note of the preliminary statement of the African Union Election Observation Mission, the only international mission present to observe the elections, including the areas for further improvement identified by the Mission.

The electoral process was discussed in the framework of the EU-Ethiopia political dialogue with the Government and with the main political actors involved. Among the issues discussed, emphasis was placed on an open political space, the freedoms of expression, association and assembly, and the neutrality of the electoral authorities, as vital to sustain the confidence of all voters and the accountability of those elected, as well as help combat extremism.  

Arrests of journalists and opposition politicians, closure of a number of media outlets and obstacles faced by the opposition in conducting its campaign have limited the space for open debate and had a negative impact on the overall electoral environment. All parties need to adhere to the provisions of the African Charter on Democracy, Elections and Governance.

Ethiopia's May 24 Parliamentary and Regional Elections

Press Statement
Marie Harf
Deputy Department Spokesperson, Office of the Spokesperson
Washington, DC

May 27, 2015

The United States commends the people of Ethiopia for their civic participation in generally peaceful parliamentary and regional elections on May 24. We acknowledge the National Electoral Board’s organizational efforts and the African Union’s role as the only international observer mission on the ground. We also note the importance of the nine televised party debates as progress in fostering open public discussion of the challenges facing the country. We encourage all candidates, political parties and their supporters to resolve any outstanding differences or concerns peacefully in accordance with Ethiopia’s constitution and laws.

The United States remains deeply concerned by continued restrictions on civil society, media, opposition parties, and independent voices and views. We regret that U.S. diplomats were denied accreditation as election observers and prohibited from formally observing Ethiopia’s electoral process. Apart from the election observation mission fielded by the African Union, there were no international observer missions on the ground in Ethiopia. We are also troubled that opposition party observers were reportedly prevented from observing the electoral process in some locations.

ፊታችንን ከምርጫ ፓለቲካ ወደ ሁለገብ ትግል እናዙር!- የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

ግንቦት 18 2007 ዓ.ም

ምርጫ 2007 ተጠናቆ ተወዳዳሪም አወዳዳሪም የሆነው ህወሓት ይፋ ውጤት እስኪገልጽ እየተጠበቀ ነው። ሁሉ በእጁ ነውና ባለሥልጣኖቹ ምን ዓይነት ውጤት እንደሚስማማቸው እስከሚነግሩን ጥቂት ቀናት ይወስዱ ይሆናል። ከፈለጉ ሁሉን የፓርላማ ወንበሮች ሊወስዷቸው ይችላሉ፤ ካሻቸው ደግሞ ጥቂቱን ለተቃዋሚዎች ሊሰጡ ይችላሉ። ወሳኞቹ እነሱ ናቸው። በዚህ የፓርላማ ወንበሮች እደላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጽ አንዳችንም ሚና የለውም።

ምርጫ የሕዝብ የሥልጣን ባላቤትነት ማረጋገጫ ከሆኑ አቢይ ዲሞክራሲያዊ ተቋማት አንዱ መሆኑ የታወቀ ነው። ሆኖም ግን ነፃ ተቋማት በሌሉበት፤ በአምባገነኖች አስፈፃሚነት የሚደረግ ምርጫ የመራጮች ነፃ ፍላጎት መግለጫ በመሆን ፋንታ የገዢዎች ሥልጣን ማረጋገጫ መሣሪያ ይሆናል፤ ከአገራችን እየሆነ ያለውም ይህ ነው።

የዘንድሮው ምርጫ 2007 ከዚህ በፊት ከነበሩ በባሰ ለአፈና የተጋለጠ የነበረ መሆኑ ከጅምሩ በግልጽ የታየ ጉዳይ ነበር። በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲዎች ላይ አገዛዙ የወሰደው የግፍ እርምጃ የዚሁ የምርጫ ዘረፋ ስትራቴጂ አካል ነበር። ከዚያ በተጨማሪም መራጮች እውነተኛ ፍላጎታቸውን በነፃነት መግለጽ እንይችሉ ዘርፈ ብዙ ጫናዎች ሲደረግባቸው ቆይቷል። የተወዳዳሪ ፓርቲዎች አባላት እንደተፎካካሪ ሳይሆን እንደጠላት ሲሳደዱ፣ ሲታሰሩ፣ ሲደበደቡና ሲገደሉ ሰንብቷል። በምርጫው ሰሞንና በዕለቱ በተለይ ከተሞች በባዕድ ጦር የተወረሩ መስለው ነበር። ይህ ሁሉ ስነልቦናዊና አካላዊ ተጽዕኖ ታልፎ የተሰጠው ድምጽ ቆጣሪው ራሱ “ተወዳዳሪ ነኝ” ባዩ ህወሓት ነው።

በእንዲህ ዓይነት ምርጫ መሳተፍ ትርፉ “በሕዝብ ድምጽ ተመረጥኩ የማለትን እድል ለአምባገኑ ህወሓት መስጠት ነው”፤ “ለዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብም የተምታታ መልዕክት ማስተላለፍ ነው”፤ ”ለህወሓት ተጨማሪ ገንዘብ ማግኛና የኢትዮጵያን ሕዝብ መከራ ማራዘሚያ ነው“ በሚል በዚህ ምርጫ ላይ ማዕቀብ እንዲደረግ አርበኞች ግንቦት 7 ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል። በርካታ ወገኖቻችን የምርጫ ካርድ ቢያወጡም የደረሰባቸውን ጫና ተቋቁመው በምርጫው ባለመሳተፍ ላሳዩት ጽናት አርበኞች ግንቦት 7 አድናቆቱን ይገልፃል።

ህወሓት በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ የምርጫ ጉዳይ እና የምርጫ ፓለቲካ ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓም የተጠናቀቀ ቢሆንም እንኳን ተጨማሪ ማስረጃ ለሚፈልጉ ግንቦት 16 ቀን 2007 መጥቶላቸዋል። አሁን ከፊታችን የተደቀነው ጥያቄ የሚከተለው ነው – አገራችን ከህወሓት አፈና ነፃ ለማውጣት ያለን አማራጭ መንገድ ምንድነው?

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ህወሓት ከኢትዮጵያዊያን ጫንቃ የሚወርደው ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አመጽን ባቀናጀ ሁሉገብ ትግል ነው ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ለሁለቱም የትግል ዘርፎች ተስማሚ የሆኑ አደረጃጀቶችን አዘጋጅቷል።

ሕዝባዊ እምቢተኝነት፣ ታጋዩ ከመኖርያ ወይም ከሥራ ቦታው ሳይለቅ በህቡዕ የሚከናወን ትግል ነው። ሕዝባዊ አመጽ ደግሞ ከመኖሪያና ሥራ ቦታ ለቆ መንቀሳቀስን ይጠይቃል። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች የህወሓትን ህጎች በመቃወም የሚደረጉ ናቸው። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች ድርጅት፣ ዲሲሊንና ጽናትን ይጠይቃሉ። ለድላችን ሁለቱም የትግል ዘርፎች እኩል ዋጋ አላቸው። እናም ከዛሬ ጀምሮ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንደዝንባለውና አቅሙ በሚመቸው የትግል ዘርፍ ይሳተፍ። ሕዝባዊ ኃይልን መቀላቀል የቻለ ይቀላቀል፤ ያልቻለው በያለበት ተደራጅቶ በሕዝባዊ እምቢተኝነት ይታገል።

በየመኖሪያ ሠፈሩና በሥራ ቦታዎች የሚቋቋሙ የአርበኞች ግንቦት 7 ማኅበራት በርካታ ሥራዎች አሏቸው። ከሁሉ አስቀድሞ ድርጅትን ማጠናከር የሁላችንም ድርሻ መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም፤ እናም ትኩረታችን እዚያ ላይ እናድርግ። እያንዳንዳችን ከሚመስሉንና ከምናምናቸው ጋር ተነጋግረን እንደራጅ፤ ወያኔ የሸረሸረብንን በራስ መተማመን እና የእርስ በርስ መተማመንን መልሰን እንገንባ። ውስጥ ውስጡን ጠንካራ አገራዊ ኅብረት እንፍጠር፤ የዕለት ተዕለት ተግባሮቻችን ደግሞ አካባቢያዊ ይሁኑ። ድርጅታችንን እያጠናከርን ወያኔን ከሁሉም አቅጣጫ እንሸርሽረው እንገዝግዘው። በዚህ መንገድ በሚደረግ ሕዝባዊ ትግል የሚገኝ ድል ፈጣን ከመሆኑን በላይ የድሉ ሕዝባዊነት ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ይሆናል።

Friday, May 22, 2015

ኢህአዴግ ሆይ ነቄ ነን ተቀየስ! (ርዕዮት አለሙ – ከቃልቲ እስርቤት)

ርዕዮት አለሙ – ከቃሊቲ እስርቤት

አራት ሆነን ወደምንኖርበት የአሁኑ የማግለያ ክፍል ከመግባቴ በፊት በርካታ እስረኞች በተለምዶ የአራድኛ ቃላት የሚባሉትን በመጠቀም ሲነጋገሩ የመስማት እድል ነበረኝ፡፡ ለርዕሴ የመረጥኳቸው ቃላትንም ያገኘሁት ከነሱው መሆኑን መግለፅ ይኖርብኛል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፤

አንዳንድ እስረኞች የሚፈልጉትን አንዳች ነገር ለማግኘት በጉልበታቸው ወይም ጤፍ በሚቆላ ምላሳቸው ይጠቀማሉ፡፡ ሀይልን በመጠቀም ያስገድዳሉ ወይም ያታልላሉ ማለት ነው፡፡ እንዲህ አይነቶቹ እስረኞች እንደለመዱት ለማድረግ ሲሞክሩ አንዳንዴ ደፋርና የማይታለሉ እስረኞች ላይ ይወድቃሉ፡፡ እናም ለማታለል ወይ ለማስገደድ የሞከረች ባለጌ የሚጠብቃት መልስ “ነቄ ነን እባክሽ! ተቀየሽ! ንኪው!”የሚል ይሆናል፡፡ እኛን ማታለልም ሆነ ማስፈራራት ስለማትችይ ይቅርብሽ፡፡ ዞርበይልን እንደማለት ነው፡፡

ኢህአዴግም እያደረጋቸው ያለው የማታለል ሙከራዎችና ተገቢ ያልሆኑ የሀይል እርምጃዎች ተመሳሳይ ምላሽ ሊያሰጡት እንደሚገባ አምናለሁ፡፡ የዘንድሮውን ምርጫ ለማለፍ ከወትሮው በከፋ ሁኔታ እየሄደባቸው ያሉት እነዚህ ሁለት ጠማማ መንገዶች መጨረሻቸው አውዳሚ ነው፡፡ በመሆኑም “ኢህአዴግ ሆይ ነቄ ነን ተቀየስ!” በማለት እኛና ሀገራችንን ይዞ ወደጥፋት እያደረገ ያለውን ግስጋሴ መግታት ይገባል፡፡

ጠማማ መንገድ አንድ

የፈሪ ዱላውን የመዘዘው ኢህአዴግ

ኢህአዴግ የተቃዉሞ ድምፆችን በሰማበት አቅጣጫ ሁሉ ዱላውን ይዞ የሚሮጥና ያለሀሳብ የፈሪ ምቱን የሚያሳርፍ ደንባራ መሆኑን በተደጋጋሚ በተግባር አይተናል፡፡ በሰሜን አፍሪካ አመፅ ተቀሰቀሰ ሲባል ለአመፅ ምክንያት የሚሆኑ ድክመቶቹንና ጥፋቶቹን ከማስወገድ ይልቅ ነቅተው ሊያነቁብኝ ይችላሉ ብሎ የጠረጠረንን ጋዜጠኞችንና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን ለእስር መዳረጉ ከቅርብ ጊዜ ተዝታዎቻችን ውስጥ ይጠቀሳል፡፡ የሩቁን ብንተወው እንኳ ማለት ነው፡፡

በሀይማኖት ተቋማት ውስጥ እንኳ ሳይቀር ገብቶ ያለአግባብ ያሰራቸው የሙስሊም ሀይማኖት መሪዎችና አማኞች የማደናበሩ ማሳያዎች ናቸው፡፡ ካለፈው አመት ጀምሮ የምርጫውን ዝግጅት ማድረግ የጀመረው እንደለመደው ከሱ የተለየ ሀሳብ የሚያንፀባርቁ ጋዜጦችንና መፅሔቶችን በመዝጋትና፣ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን በማሰርና በመደብደብ ነበር፡፡ በምሳሌነት የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና የሶስቱን ጋዜጠኞች ጉዳይ ማንሳት ይቻላል፡፡

ዘንድሮ ደግሞ ኢህአዴግን በድፍረት በመሄስ የሚታወቀውን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ ምርጫ ቦርድን በመጠቀም ያለአግባብ ከፓርቲያቸው እንዲገለሉ ያደረጋቸውን የአንድነት ፓርቲ አባላትን በግፍ ማሰሩን ተያይዞታል፡፡ በተመሰረቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለኢህአዴግ ፈተና የሆኑበት ደፋሮቹ የሰማያዊ ወጣቶችም የኢህአዴግ ሰለባ እየሆኑ ነው፡፡ የየትኛውም ፓርቲ አባላት ያልሆኑና ቅሬታቸውን በተለያዩ መድረኮች ያሰሙ በርካታ ግለሰቦችም ተመሳሳይ እጣ ገጥሟቸዋል፡፡

ኢህአዴግ ይሄን ሁሉ የፈሪ ዱላውን እያዘነበ የሚገኘው በሚወስዳቸው እርምጃዎች ከተቃዉሞ ድምፆችና እንቅስቃሴ የሚገላገል እየመሰለው ነው፡፡ እንደተሳሳተ ማን ቢነግረው ይሻል ይሆን? የራሱን ዜጎች ማክበር ስለማይሆንለት የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንድትነግርልን ብናደርግ ሳይሻል አይቀርም፡፡ ለማንኛውም የሚኒስትሯን ጉዳይ ለጊዜው እንተወውና በሀገራችን ዴሞክራሲ ሰፍኖ ለማየት የቆረጥን እኛ ግን ከትግላችን ለሰከንድም ቢሆን እንደማናፈገፍግና በዚህም ምክንያት የሚደርስብንን ሁሉ ለመቀበል ፍቃደኞች እንደሆንን ልንነግረው ያስፈልጋል፡፡ “ኢህአዴግ ሆይ እየበዛኸው ያለኸው ግፍና በደል ይበልጥ ጠንካሮች ያደርገናል እንጂ አንተ እንደፈለከው አያንበረክከንም ነቄ ነን ተቀየስ” ልንለውና ጥንካሬያችንንም በተግባር ልናሳየው ይገባል ፡፡

የወያኔን የይስሙላ ምርጫ አስመልክቶ ከዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተላለፈ ጥሪ!


የተከበራችሁ እናቶቼና አባቶቼ፤ እህቶቼና ወንድሞቼ እንዲሁም ልጆቼ የምትሆኑ ወጣቶች!! አገራችን የምትገኝበትን አስጨናቂ ሁኔታ ሁላችንም እንረዳለን። የህወሓት/ኢሕአዴግ ፋሽስቶች ቡድን እየገረፈ፣ እያሰረና እየገደለ በካርዳችሁ መርጣችሁ የምርጫ ድግሴን ካላሞቃችሁልኝ እያለ ነው። እንኳንስ ዛሬ ታዛቢ በሌለበት፤ ታዛቢ እያለም እንኳን ወያኔ የሕዝብን ድምጽ በትክክል ቆጥሮ አያውቅም። ወያኔ ለህዝብ ድምጽ ምንም ደንታ የሌለው የኋላቀር ወሮበሎች ቡድን ነው::

ለስንት አስርት ዓመታት ለወያኔ ባርነት እንገብራለን? ለሀያ አስምስት ዓመታት ተገዛን፣ ተገደልን፣ ተቀጠቀጥን፣ ታሰርን፣ ተሰቃየን፣ ልጆቻችን በአገራቸው ተስፋ ቆርጠው ሲሰደዱ በበረሀ ንዳድ አለቁ፤ በባህር ሰጥመው ቀሩ፤ በባዕዳን አረመኔዎች እንደከብት ታረዱ፤ ቤንዚን ተርከፍክፎባቸው ተቃጠሉ። ሀይማኖታችን ተዋረደ፤ ባህላችን ረከሰ፤ ታሪካችን ተናቀ። በልማት ስም ወልደን ከከበድንበት ተፈናቀልን፤ አገራችን አደገች እያለ ሕዝብ በኑሮ ውድነት ተሰቃየ። በልቶ ማደር ብርቅ ነው። እንደሙጫ የሚያጣብቀንን ማህበረሰባዊ ትስስር በስልጣን ለመቆየትና ህብረተሰቡን ለመዝረፍ ሲል ሆን ብሎ እያፈራረሰው ነው:: ይኽ ሁሉ አይበቃንምን? ይኸ ሁሉ አይመረንምን?

ወላጆቼ፣ እህት ወንድሞቼ!ውርደት ይብቃን። የተረገጥንና የተገደልን አንሶን ፍጹም ማንንም ሊያሞኝ በማይችል የለበጣ ምርጫ ወደን የተረገጥን፤ ፈልገን የተገዛን ለማስመሰል ወያኔ የሚያደርገውን ሩጫ እናክሽፈው:: ከፊታችን ያለውን ምርጫ ባለመሳተፍ ምሬታችንን እንግለጽ።

ዛሬ በግሌ እና በአርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ስም ጥሪዬን አቀርባለሁ። በዚህ ምርጫ አትሳተፉ። የምርጫ ካርዳችሁን ቀዳችሁ ጣሉት። እናምርር። ካላመረርን ለውጥ ሊመጣ አይችልም። ይልቅስ ለማይቀረው የመጨረሻው ትግል ራሳችንን እናዘጋጅ::

አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሞ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር ትብብር በመፍጠር የአገር አድን ኃይል በመገንባት ላይ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት አንከፋፈልም። ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ያካተተ ስብስብ ፈጥረን በኅብረት አገዛዙን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ ትግል ነው። የትግሉም ባለቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ ነው። ክርስቲያን ሙስሊም፤ ወንድ ሴት፤ ወጣት አረጋዊ ሳንል፤ በብሔርም ሆና በቋንቋ ሳንከፋፈል ሁላችንም ይህን አስከፊ ሥርዓት በቃህ እንበለው።

Thursday, May 21, 2015

የአሜሪካ እርዳታ አምባገነኖችን ማጠናከሩ ይቁም፣ ግልፅ ደብዳቤ ለአሜሪካ መንግሥት ሃላፊዎችና ለአሜሪካ ሕዝብ

ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር)

Click here for English version

የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግንኙነት ከመቶ ዓመታት በላይ ነው። ይኼ ግንኙነት በሁለቱ ሃገሮች መካከል ሊኖር የሚገባውን የእኩልነትና የጋራ ጥቅም መሰረት ያደረገ እንደ ነበረ ታሪክ ያስታውሳል። መንግሥታት ቢለዋወጡም በሁለቱ ሃገሮች መካከል የተመሰረተው የቆየ ግንኙነት አይፈርስም የሚል እምነት አለኝ። የኢትዮጵያ ስደተኞች አሜሪካን የመጀመሪያ መድረሻ አድርገን አሜሪካዊ የሆንንበትና ወደፊትም የምንሆንበት ዋና ምክንያት የአሜሪካ አስኳል እሴቶች–ነጻነት፤ የግለሰብ ክብር፤ ፍትህ-ርትእ፤ የሰብአዊ መብቶች መከበር፤ በሕግ ፊት ማንኛውም ግለሰብ እኩል መሆን፤ የሕግ የበላይነትና ዲሞክራሳዊ አገዛዝ ስለሳቡንና የመስራት እድል በጎሳ ሳይሆን በሞያ የሚወሰን መሆኑን ስላወቅን ነው። ዛሬ ብዙ መቶ ሽህ የኢትዮጵያ ትውልድ በአሜሪካ ይኖራል፤ ድምጽና መብት አለው። በኢትዮጵያ የማናገኘውን በተሰደድንበት አሜሪካ እናገኛለን። ይኼን እድል ተጠቅመን ለተወልድንባት ሃገር ጠበቃ እንሁን።

በሁለቱ ሃገሮች የተመሰረተው የቆየ ግንኙነት በወታደራዊው፤ ሶሻሊስት አምባገነን መንግሥት ዘመን ተለውጦ አሜሪካኖች አቋማቸውን ለውጠው ተተኪ መንግሥት ይጠባበቁ እንደ ነበር ብዙ ማስራጃዎች አሉ። ደርግን የተካው የጎሳ ልሂቃን ቅንጅት ህወሓት በበላይነት የሚያሽከረክረው የኢህአዴግ መንግሥት ከምእራብ ሃገሮች፤ በተለይ ከአሜሪካ ጋር ያለው የጥቅም ትሥስር እጅግ በጣም የጠነከረ ነው። የኢትዮጵያ እድገት ፈጣን የሆነው በውጭ እርዳታ፤ ስደተኛው በሚልከው ገንዘብ፤ በሃገር ውስጥ ብድርና በቅርቡ በውጭ ኢንቬስተሮች ድጋፍ ነው። ኢኮኖሚው በራሱ ለመንቀሳቀስ አልቻለም፤ ፍትኅ ከሌለ አይችልም። በአሜሪካኖች ስሌት፤ በፈራረሰው፤ እርጋታና ሰላም በሌለበት የአፍሪካ ቀንድና አካባቢ (በሰሜን ኤርትራ፤ በምስራቅ፤ ሶማሊያ፤ በምእራብ ደቡብና ሰሜን ሱዳን፤ በባህር ማዶ በየመን፤ በሶሪያ፤ በኢራክ፤ በሰሜን አፍሪካ በሊብያና በግብፅ) ያለውን የርስ በርስ ግጭት፤ የሃገሮች መፈራረስና የሃብት ውድመት ሲመለከቱ ኢትዮጵያ “የእርጋታና የልማት” ደሴት ናት ወይንም ትሆናለች ብለው ማመናቸው አያስገርምም። ግዙፉ እርዳታ ከዚህ ስሌት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው። ጸረ-ሽብርተኛነት ሰብሳቢ መርህ ሁኗል። አሜሪካኖች ያላስተዋሉት፤ ቢያስተውሉትም የሚመጣውን ችግር ከራሳቸው ጊዚያዊ ጥቅም ባሻገር ያልተገነዘቡት፤ አምባገነኖች ፀረ-ሽብርተኛነትን ምክንያት በማድረግ ራሳቸው ሽብር ፈጣሪዎችና ሽብርተኞች መሆናቸውን ነው። የሰብአዊ መብቶችና የነጻነት መገፈፍ ሁለተኛ ወይንም ሶስተኛ ደረጃ የያዘው ለዚህ ነው። የሕዝብ መብቶች በተከታታይ ሲጎዱ አፍራሽ ኃይሎች፤ ሽብርተኞችን ጨምሮ መግቢያ ቀዳዳ ያገኛሉ፤ ስደተኝነት እየከፋ ይሄዳል።

የአሜሪካ መንግሥት መሪ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ልክ የዛሬ ሁለት ዓመት በደቡብ አፍሪካ እንዲህ ብለው ነበር። “በአፍሪካ ሃገሮች በሙሉ የማንኛውም ግለሰብ ክብር ቢከበር አሜሪካኖችም ነጻ ይሆናሉ። እኔ የማምነው እያንዳንዳችን ነጻ ለመሆን ከተፈለገ የሁሉም ሰብአዊ ቤተሰቦችና ግለሰቦች ከድህነት ወይንም ከበሽታ ወይንም ከጭቆና ነጻ መሆን አለባቸው።” ይኼ እሴት የአሜሪካኖች እሴት ነው፤ የመላው በነጻነት ለመኖር የሚፈልግ ሕዝብ እሴትና ተስፋ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ለክብሩ፤ ለፍትህ፤ ለነጻነት፤ ለሕግ የበላይነትና ለዲሞክራሲ ሲታገል ከዓመሳ አመታት በላይ ሁኗል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት በአንድ አምባ ገነን ፓርቲ ስትገዛ ቆይታ አሁንም በአራት ቀናት በሚካሄድ “የይስሙላ ምርጫ” የተጠበቀ ውጤት ለሚከተሉት አምስት አመታት ትገዛለች። የኢትዮጵያ የመንግሥት ስርዓት ልክ የፈረሰውን የሶቬት ሕብረት አገዛዝ የሚመስል ጋርዲያን የተባለው ጋዜጣ “ኦርዌሊያን” የሚለው፤ ወይንም በእኔ አመለካከት ፍጹም የሆነ በስለላ መረብ የተቆራኘ፤ በአንድ አናሳ ብሄር የበላይነት የመከላከያ፤ የስለላና የኢኮኖሚ የበላይነት የሚተዳደር አገዛዝ ነው።

ይኼ አገዛዝ ያለ ዓለም ትሥስር የገንዘብ የስለላ፤ የመከላከያ፤ የዲፕሎማሲና ሌላ ድጋፍ ህይወት አይኖረውም። የማይካደው ገዢው ፓርቲ ባለፉት ሃያ አራት አመታት ለልማት ድጎማ ብቻ አርባ ቢሊየን ዶላር ተሰጥቷታል። ኢህአዴግ ከሙስናው፤ ከሃገር በገፍ እየተሰረቀ ከሚሸሽውና ከሌላው ውድመት የተረፈውን ተጠቅሞ መሰረተ ልማት አካሂዷል። ከእድገቱ ባሻገር መታየት ያለበት ሃቅ፤ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ የምግብ እርዳታ ጥገኛ ከሆነችው፤ ወጣቱ ትውልድ በገፍ ከሚሰደድባት ኢትዮጵያ ተሰርቆ የሸሸው ሃብት ግምት አስር ቢሊየን ዶላር ነው። ይኼ ስንት ፋብሪካ ይከፍት ነበር፤ ለስንት ወጣቶች የስራ እድል ያቀርብ ነበር? የተሰረቀው ተሰርቆና ከሃገር ሸሽቶ፤ የተረፈው መንገድ ስርቷል፤ ሃዲድና ግድቦች እየሰራ ነው። ይኼ ግዙፍ እርዳታና መንግሥት ከባንኮች ተበድሮ ሰማይ ጠቀስ ፎቆች፤ ቪላዎች፤ መንገድና ሌላ ቢሰራ ምኑ ያስደንቃል? የማይካደው ኢትዮጵያ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ደረጃ ጥገኛ መሆኗ ነው። ኢትዮጵያ ዛሬ በያመቱ የአራት ቢሊየን ዶላር እርዳታ ተቀባይ ሁናለች፤ ከአፍሪካ ከፍተኛው ከሆነ

ለውጤታማ ድል፤ ተግባራዊ ትብብር!

በመርህ ላይ በተመሠረተ ትብብር ወያኔን በጋራ ታግሎ ማሸነፍ እና በየደረጃው የሚገኝ የመንግሥት ስልጣን ነፃ፣ ፍትሀዊና ተዓማኒን በሆነ የሕዝብ ምርጫ ብቻ የሚያዝበት የፓለቲካ ሥርዓት መገንባት የአርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ተልዕኮ ነው። በዚህም መሠረት አርበኞች ግንቦት 7፣ በተግባራዊ እንቅስቃሴ ላይ ከሚገኙት ከትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ ከጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ፣ ከቤንሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ እና ከአማራ ዴሞክራሲ ኃይል ንቅናቄ ጋር በመርህ ላይ በተመሠረተ ትብብር በጋራ ለመታገል የሚያስችለውን ስምምነት ላይ እየደረሰ ነው።

ይህ የትብብር ጥረት ብዙ ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ የኢትዮጵያን ሕዝብ ጠንካራ ድጋፍ ይሻል።


  1. ህወሓትን ከስልጣን የማባረር ኃላፊነት የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ኃላፊነት ነው። ይህ ትልቅ ኃላፊነት በአንድ ወይም በጥቂት ድርጅቶች ላይ መጣል የለበትም። ይህ ትብብር ይህንን የጋራ ኃላፊነትን በጋራ ለመወጣት የተደረገ በዓይነቱ አዲስ የሆነ ተግባራዊ ትብብር ነው።
  2. ህወሓት በትግራይ ውስጥ መቶ በመቶ ተቀባይነት ያለው አስመስሎ ፕሮፖጋንዳ ሲነዛ ቆይቷል። ህወሓት፣ የትግራይና የአማራ ሕዝብ በጠላትነት እንዲተያዩ፤ የትግራይ ሕዝብ ራሱን ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነጥሎ እንዲያይ የረዥም ግዜ እቅድ አውጥቶ ተግባራዊ እያደረገ ነው። ይህን እኩይ ሴራ ማክሸፍ የምንችለው በፀረ-ወያኔ ተግባራዊ ትግል በጋራ ስንቆም ነው። ይህ ትብብር ለአገራችን አንድነትና ዘላቂ ሰላም ወሳኝ የሆነው በፀረ ህወሓት አቋሙ የጠነከረ የትግራይ ሕዝብ እንዲኖር ወሳኝ ሚና ይኖረናል ብለን እናምናለን።
  3. በአሁኑ ሰዓት የህወሓት አገዛዝ የቆመው ዘረኛ በሆነ መንገድ ባደራጀው ጦር፣ በስለላ ድርጅቱ እና ኃያላን መንግሥታት ለጥቅማቸው ሲሉ በሚያደርጉለት ሁለተናዊ ድጋፍ ነው። እነዚህ ህወሓትን ደግፈው የያዙ ኃይሎች ጠባቸው ከመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር መሆኑን በተግባር የምናሳያቸው ተግባርን መሠረት ያደረገ ጠንካራ ኅብረት ፈጥረን ስንገኝ ነው።
  4. ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ነባራዊ ማኅበራዊ ሀቅ ምክንያት ከፓለቲካ አመለካከት ይልቅ በወል ማንነት ላይ የተመሠረቱ ድርጅቶች የሚበዙበት ሆኗል። የኢትዮጵያን ችግር ለመፍታት ሁለቱን አመለካከቶች መሠረት አድርገው በተደራጁ ድርጅቶች መካከል ትብብር መፍጠር ወሳኝ ነው።

Monday, May 18, 2015

Washington Post: As Ethiopia votes, what’s ‘free and fair’ got to do with it?

Terrence Lyons writes: EPRDF dominates all major political, economic, and social institutions, has virtually eliminated independent political space, and opposition parties are fractured and harassed. Ethiopia has jailed more journalists than any other country in Africa.

Ethiopia, Washington’s security partner and Africa’s second most populous country, is scheduled to hold national elections on May 24. The ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) and its allied parties won 99.6 percent of the seats in the last round of elections in 2010. There is no doubt that the ruling party will win again.

The party has ruled since 1991 when it seized power following a prolonged civil war. It dominates all major political, economic, and social institutions, has virtually eliminated independent political space, and opposition parties are fractured and harassed. Ethiopia has jailed more journalists than any other country in Africa.

The EPRDF is an extremely strong and effective authoritarian party. Yet Wendy Sherman, the Under Secretary of Political Affairs in the Department of State, recently said, “Ethiopia is a democracy that is moving forward in an election that we expect to be free, fair and credible.” What roles do elections play in authoritarian states and what, if anything, do they have to do with “free, fair, and credible” standards?

Part of the answer is to recognize that elections and political parties in autocratic states play different roles than they do in democratic states. Electoral processes are used by authoritarian regimes to consolidate power and to demonstrate the ruling party’s dominance, as argued by scholars of comparative politics such as Schedler and Gandhi and Lust-Okar. Research by Geddes shows that single-party authoritarian regimes tend to be more stable and last longer than military or personalistic ones. Strong partiesmanage instability by encouraging intra-elite compromise, co-opting opposition, and institutionalizing incentives to reward loyalty. Elections and strong political parties thereby contribute to “authoritarian resilience,” as scholars note with reference to China, Iran and Syria, and Zimbabwe.

Non-competitive elections are common in authoritarian states and incumbents often win by incredible margins. In Sudan, President Omar al-Bashir won 94 percent of the vote in April 2015 elections, Uzbek President Islam Karimov over 90 percent in March 2015, and Kazak President Nursultan Nazarbayev 97 percent in April 2015. Rwandan President PaulKagame, when asked if his 93 percent landslide in 2010 represented the will of the people, reportedly answered: “So, 93 percent – I wonder why it wasn’t higher than that?” The EPRDF’s 99.6 percent victory in 2010 createdcredibility problems in North American and European capitals where diplomats often asked, “Couldn’t they have just won by 60 or 75 percent?” But the point of elections under authoritarian rule is not to obtain a working majority or to win international approval. The purpose is to dominate domestic politics completely and thereby deter any leader from thinking he or she could challenge ruling party successfully. The dramatic, overwhelming victories send an important domestic message of strength and power, even as they strain credibility abroad.

ኢትዮጵያና አሜሪካ

በፕሮፍ. መስፍን ወልደ ማርያም

ዱሮ ዱሮ ምዕራባውያን የሶቭየት ኅብረትን ኮሚዩኒዝም መስፋፋት ለመቋቋም ከእሥራኤል ሌላ አጋር ሊሆኑ የሚችሉ አገሮችን ሲያስሱ፣ ኢትዮጵያ፣ ቱርክና ፋርስ እየታጩ ነበር፤ አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር የተወዳጀበትና በአስመራ ቃኘው ጣቢያን የተከለበት አንዱ ምክንያት ይኸው ነው፤ የፋርስ ጉዳይ ከንጉሠ ነገሥቱ መፈንቅለ መንግሥትና ሞት ጋር አበቃ፤ ቱርክ እያንገራገረም ቢሆን የሰሜን አትላንቲክ አገሮች ማኅበር ውስጥ አለበት፤ እሥራኤል በአረቦች አካል ላይ እሾህ እንደሆነች ጥጋበኛ የአሜሪካ ቅምጥል ሆናለች።

የፋርሱ ጉዳይ ከፋርሱ ንጉሠ ነገሥት ጋር እንደተያያዘው ሁሉ የኢትዮጵያም ጉዳይ ከኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ጋር የተያያዘ ነበር፤ የእውቀት ጥበብ (ቴክኖሎጂ) እያደገ ሲሄድ የቃኘው ጣቢያ ለአሜሪካ አማራጭ የሌለው መሆኑ ቀረ፤ አሜሪካ ኮተቱን ይዞ ወደህንድ ውቅያኖስ ሲሄድ ኢትዮጵያን ችላ ማለት ተጀመረ፤ መቃቃሩ እየበረታ ሲሄድ የአሜሪካ እብሪትና የኢትዮጵያ ኩራት ተጋጩ፤ አጼ ኃይለ ሥላሴ የአሜሪካኑን አምባሳደር አስከማስወጣት ደረሱ፤ ጨዋታ ፈረሰ ዳቦ ተቆረሰ ያኔ ተጀመረ፤ የፋርሱ ንጉሠ ነገሥት ሲገለበጥ ቀጣዩ አገዛዝ ከአሜሪካ ጋር ጠላት እንደሆነው የአጼ ኃይለ ሥላሴም አገዛዝ ሲገለበጥ ቀጣዩ አገዛዝ ከአሜሪካ ጋር ጠላት ሆነ።

አሜሪካ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያውያን ጉዳይ ጣልቃ እየገባ የፈጸመውና እየፈጸመ ያለው ግፍ የጀመረው ከዚያ ወዲህ ነው፤ የደርግ አገዛዝ ኮሚዩኒስት መሆኑን አወጀ፤ የደርግ አገዛዝ ከሶቭየት ኅብረት ጋር ማኅበርተኛ መሆኑን አወጀ፤ የደርግ አገዛዝ የአሜሪካ መንግሥት ዓለም-አቀፍ ቄሣራዊነትን የሚያራምድ መሆኑን እየደሰኮረ የአሜሪካ ባላጋራ መሆኑን አስታወቀ፤ ይህ ሁሉ እውነት ነው፤ ነገር ግን አንዱም የኢትዮጵያን ሕዝብ ፈቃድ ያዘለ አይደለም፤ አንዱም ኢትዮጵያን እንደአገር የሚያስጠይቅ አይደለም። ከላይ ለተጠቀሱት የደርግ ‹አዋጆች› የአሜሪካ መንግሥት መልስ የሰጠው ለደርግ መንግሥት ሳይሆን ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ነበር፤ መልሱ ይህ ነበር፤ አንደኛ ኢትዮጵያን የወረረችውን ሶማልያን ረዳ፤ ሁለተኛ ሻቢያንና ወያኔን የሚረዳውን የኑሜሪን ሱዳንን ረዳ፤ ሦስተኛ ሻቢያንና ወያኔን ረዳ፤ አራተኛ የኤርትራን መገንጠል ደገፈ፤ አምስተኛ የወያነን አምባ-ገነን አገዛዝ በኢትዮጵያ ላይ ተክሎ አቅፎታል፤ እነዚህ የአሜሪካ መልሶች ደርግ ወንበሩን አስረክቦ ቃሊቲ ከገባ በኋለም መቀጠላቸው የአሜሪካ ጠብ ከደርግ ጋር ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያም ጋር የሆነ ያስመስላል።

በኢትዮጵያውያን ድካምና በአሜሪካ ጫና ኢትዮጵያ ዛሬ ሁለት ሆናለች፤ በአንዱ ክፍያ ላይ አሜሪካ እግሩን ዘርግቶ አድራጊ ፈጣሪ ቢሆንም በሌላው ክፍያ ላይ እግሩን ማስገቢያ አላገኘም፤ ብዙ ሰው ያልተረዳውና የሚያስደንቀው የአሜሪካ ዶላርና የአሜሪካ ጫና ኤርትራን ማንበርከክ አለመቻሉን ነው፤ ሎሌ ሆኖ ጌታ ከመምሰል ደሀ ሆኖ መከበር ይሻላል፤ ይህ የቀድሞው የኢትዮጵያዊነት አልበገርም-ባይነት፣ የክብርና የኩራት ምልክት ነው፤ አልጠፋም!

Sunday, May 17, 2015

ድምፅ አሰጣጣችን በምን ሰሌት ቢሆን ያዋጣል?

ዳዊት ዳባ

“የተራቡትን መርጠን ከምንቸገር ያው የጠገበው ይሻለናል” የሚል መልክት ያላት ማዘናጊያ ሀሳብ በየፌስ ቡክ ላይ ተበትናለች። ሲጀመር በልቶ ጠገብኩ የሚሉ መቼ ነገሱብንና። በዛ ላይ ያለአባከና በሰፊው የለመደ ሆድ ለሌላ አምስት አመት ከበሉን ለመረጃ እንኳ አጥንታችንም አይጋኝም አትቀልዱ። የሚኖር አይመስለኝም እንጂ በዚህና “ድምጽ መሰረቁ ላይቀር” አይነት አንድምታ ባላቸው ምክንያቶች ተንተርሶ ለወያኔ ድምፁን የሚሰጥ ካለ በቁሙ የሞተ ነው። ውጤቱ ምንም ሆነ ምንም እሱና አምላኩ ብቻ በሚያውቁት መደበቂያ ውስጥ ሆኖም እንኳ የማነበትን ማድረግ ካልቻለ “ሙትቻም” ያንሰዋል።

በተመሳሳይ ተቃዋሚሞዎች ሰርተውት፤ አድርገውትና፤ ሆነውት ቢሆን ስንል የምናነሳቸው ሀሳቦች በሙሉ እዚህ ጊዜ ላይ ሲደርስ ለጊዜው የግድ የሆነ ቦታ አስገብተን ልንቆልፍባቸው ግድ ይላል። በይበልጥም ካለንበት ተጨባጭ አገራዊ እውነታ አኳያ ድምጻችንን ለመስጠት መሰረት የምናደርገው ድርጅቶች የላቸው አገራዊ እቅድ፤ ጥቅላላ ጥንካሬያቸውና ያሳዩት ቁርጠኛነት እንዲሁም ፖለቲካዊ ፍላጎታችን ብቻ ከሆነ ብዙ ተቃዋሚ ለምርጫ በቀረቡበት ድምጻችንን ስለሚከፋፈል አሁነም ወያኔ ተጠቃሚ ሊሆንበት የሚችልበት ጎን አለው። እንደምንመርጥበት ክልል ፤ በምንመርጥበት ጣቢያ እንደቀረቡት ተቃዋሚ እጩዎች አይነትና ብዛት፤ ያእጩው ጥሩ ግለሰባዊ ስብእና ባጠቃላይ ለመመረጥ ያለ የተሻለ እድል፤ በምንመርጥበት አካባቢ ነዋሪ የሆነው የበዛው የማህበረሰባችን ክፍል ፖለቲካል ዝንባሌና ፍላጎት የመሳሰሉ ቁም ነገሮችን ግምት ውስጥ አስገብቶ ድምጻችንን መስጠቱ ላሁኑ አዋጭ ብልጠትም ያለበት ያደርገዋል።

ይህን የምለው ተቀናቋኝ ድርጅቶች በአንድ ሆነው ለምርጫው ባይቀርቡም ዜጎች ከውስጣቸው አንዳቸውን ብቻ ምርጫ አድርገው ሊያወጡ የሚችልበት ነባራዊ ሁኔታ ቢኖር ኖሮ እመክረው ነበር። ባስበው ባስበው ላሁኑ የሚቻል አይደለም ወይ ስላልታየኝ ነው። ወደ ሁለት ማጥበብ ግን ይቻላል። ያም ሆኖ በድርጅትም ሆነ በግለሰብ ደረጃ ከፍላጎት በዘለለ የሚቻልበት መሬት የረገጠ በቂ ነባራዊ ሁኔታ አለ የሚል ካለ ሀሳቡን ወደ ህዝብ ሊገፋው ጊዜው አሁን ነው።

በግልፅ ማስቀመጥ ያስፈልጋል። በአገራችን ጥርት ብሎ የወጣ በግልፅ ለማናችንም የሚታይ ሁለት አይነት ፖለቲካዊ ፍላጎቶች አሉ። እነዚህን ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ሙሉ በሙሉ አይወክሉም ሊሉ የሚችሉ ሊኖር ቢችሉም በበቂ የያዣቸውና ጎልተው የወጡ ሁለት ተቀናቃኝ ድርጅቶች አሉ። ሰማያዊ ፓርቲና መድረክ። ላማሸነፍና ለውጥ ላማምጣት ድምጻችንን የምንሰጥ ከሆነ በመጀመርያ ሌሎቹን በሙሉ ላሁኑ እንደሌሉ አድርገን እንነሳ። በሁለተኛ ደረጃ ሰማያዊና መድረክንም ምርጫዎቻችን ለማድረግ የምናፎካክር ከሆነም አሁንም ሂደቱ ወያኔን ይጠቅማልና ድምፅ ለመሰጠት የምንወስንበት ሌላ አይነት ስሌት ልንቀምር የግድ ይገባል።

አዲስ አበባ፤ አማራ ክልል፤ ማህበረሰባዊ ስብጥራቸው ከፍተኛ የሆነ ትላልቅ ከተሞች ላይ በሙሉ ለሰማያዊ ፓርቲ ያለ ድጋፍ በዝቶ እስከታየ የመድረከም ሆነ የሌሎች ፓርቲ ደጋፊዎች ድምጻችሁን ለሰማያዊ ፓርቲ ምንም ሳታንገራግሩ ስጡ። ብልጥ ለሆነና ጨዋታው ለገባው ሰማያዊ ፓርቲ የሚኒልክን ስርአት ሊመልስ ነው ተብሎ የተነገረውና ያመንንም ብንኖር። እንዲሁ የመድረክ ደጋፊዎች በብዛት ያሉበት አካባቢ ሆኖ የመድረክ እጩ ከሌለ ለሰማያዊ በመቀጠል ለሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች በደረጃ ባበረ መንገድ ድምጻችሁን ለመስጠት ዶልቱ።

ሌላህም ከአዲስ አበባ ውጪ የመድረክ እጩ ቀርቦ ሰማያዊ ፓርቲ እንደማያሸንፍ እያወክ ድምፅህን ለሰማያዊ ፓርቲ ብጭራሽ አትስጥ። ድምፅችንን በተባበረ ምንገድ ለመድረክ ለመስጠት እንዶልት። አሁን ያለውን ፌደራላዊ አከላል አምርረህ የምትቃወምም ቢሆን። በአማራ ክልልና በትላልቅ ከተሞች የሰማያዊ ፓርቲ እጩ እስካለ ሳታንገራጋር ለሰማያዊ ፓርቲ ድምጽህን ስጥ። የሰማያዊም የመድረክም እጩ ከሌለ ብቻ ለመኢአድ ከዛም ለሌሎች ተቀዋሚዎች በደረጃ ድምጽህን ስጥ።

ለቀድሞው የአንድነት አመራር “ እናርድሃለን፣…ራስህን በጥይት እንበትነዋለን….” የሚል ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው

የመንግሥት ደህንነቶች ለቀድሞው የአንድነት ፓርቲ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት ተክሌ በቀለ የመጨረሻያሉትን እናርድሃለን፣…ራስህን በጥይት እንበትነዋለን..የሚል ማሰጠንቀቂ መስጠታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ማስጠንቀቂያውና ማስፈራሪው በሌሎቹም የቀድሞው የፓርቲ አመራሮች ላይም የቀጠለ ሲሆን፣በዛው ዕለት የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አባልና የማኀበራዊ ጉዳይ ኃላፊ የነበረው አቶ አለነ ማፀንቱ መታሰሩ ታውቋል፡፡በተለይ የአቶ ተክሌ በቀለ ሁኔታን በተመለከተ ራሳቸው በአጭሩ እንደሚከተለው አስቀምጠውታል፡፡

ለሆነ ጎዳይ ከእንድ ጓደኛየ ጋር ዛሬ ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡30 ላይ ከቦሌ ተነስተን ኮተቤ(02) አካባቤ ሄድን፡፡ የቤት ታርጋ የለጠፈች ነጭ መኪና 4 ጎሮምሶችን ይዛ ትከተን ነበር፡፡ ቦታ ስተን ኑሮ የሆነ መታጠፊያ ላይ ወደ ኋላ ስንዞር ተገጣጠምን፡፡ ባንድ መስመር ስዞር ቦታ የዘጋሁባቸዉ መስሎኝ ይቅርታ ስጠይቃቸዉ የሚነዳው ወንድም መኪናዉን አቁሞ ሳይወርድ የስድብ መዓት አወረደብኝ፡፡ ያ ያገሬ ልጅ! ከዚያም ሄዱ፡፡እነማን እንደ ሆኑም ገባኝ፡፡ ጓደኛየ ወደ ቢሮዉ ገብቶ ጉዳዩን ጨርሶ እስኪወጣ ወርጄ ስጠብቀዉ በመኪኗ ተመልሰዉ መጡ፡፡ በማዶ ላይ የቀን ሰራተኞች ምሳ በልተዉ ሰዓቱ እስኪደርስ ጥላ ላይ ያረፉ ነበሩ፡፡ሁኔታዉን ይከታተሉ ኖሮ ትተዉኝ ሲሄዱ መጥተዉ ጠየቁኝ፡፡የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባል እንደነበርኩና አሁን እንደሌለሁበት፤የስርኣቱ ደህንነት ነን ባዮች ሲሆኑ እያስፈራሩኝ መሆኑንም ስነግራቸዉ በጣም ተናደዱ፡፡ለምን ግርግር አትፈጥርም ነበር አንለቃቸዉም ነበር…..ክብር ለዜጎች! ውድ ህይወት ተከፍሎበት በነበረ ስርዓት ውስጥ፤ህግ አክባሪና ሃይማኖተኛ በሆነ ማህበረሰብ ዉስጥ ተወልዶ ያደገ፤ከድሃ ግብር ደሞዝ የሚበላ የደህንነት ሰራተኛ ነኝ ባይ “እናርዳሃለን….መንግስት ነን፣ ራስህን በጥይት እንበትነዋለን…የምትሰራዉን ሁሉ እናዉቃለን…እድሉን ተጠቀምበት የመጨረሻህ ነዉ….” የሚሉ ቃላት እንዲናገሩ ሰልጥነዉ ሲላኩ በእዉነት ያሳፍራል፡፡ ዱላ ቀረሽ ስድብ አዝንበዉብኝ መኪናቸዉን አስነስተዉ እብስ አሉ፡፡ የመጀመሪያየ ባይሆንም የከዚህ ቀደሞቹ ግን ጨዋዎች ነበሩ! ግን፤ አርፈንም እንድናርፍ አይፈቀድልንም እንዴ? እኛ እንሰራው የነበረው ፖለቲካ ፍጽም ሰላማዊና ህገ መንግስታዊ ነበር፡፡ አሁንም መብታችን ነዉ፡፡ የነአሞራዉ ደም የፈሰሰዉ ለዚህም እንደነበር እንረዳለን፡፡ተሸብራችሁ ከሆነ በስራችሁ እንጂ በኛ አይደልም፡፡ እኛ ግን ለግዜው ከጨዋታው ውጪ ስላደረጋችሁን በጨዋታው ሜዳ የለንበትም፡፡ ለማስጠንቀቂያውም ለመረጃውም ስርዓት አለው፡፡ የመንግስት አካል የሆነ ተቋም በፈለገዉ መንገድ ህጋዊ ሆኖ ማናገር ይችላል፡፡ መንግስትነት ትልቅ ሃላፊነትና ተቋም መሆኑን ልንነግራችሁ አቅም የለንም፡፡ የተበተነን የቀድሞ የፓርቲ አመራር ማስፈራራትና ማሰር ተራ ብቀላ ይመስላል፡፡ ተራ ህይወት እየመራንም፤አርፈን ተቀምጠንም ልትተዉን ካልቻላችሁ በግፉ መንገድ ግፉበት፡፡ እኛ ከማን እንበልጣለንና ነው!!!

አገራችንና ሕዝባቸን ማዳን ግባችን አድርገን በአንድነት አንሰራለን። የጋራ መግለጫ

አገራችንና ሕዝባቸን ማዳን ግባችን አድርገን በአንድነት አንሰራለን።

የአንድነት፣ የመከባበር፣ የመቻቻል እና የነፃነት ምሳሌ የሆነችው አገራችን እኩይ አላማቸውን ለማሳካትና የስልጣን እድሜያቸውን ለማራዘም በሚንከላወሱት የወያኔ ቡደን አገራችንና ሕዝባችን ከምንግዜውም በከፋ ደረጃ ላይ አድርሰዋታል።

ወጣቱ በአገሩ ላይ ተምሮና ሰርቶ የመኖር እድሉ ለወያኔው አገዛዝ ማደር አልያም አገሩን ጥሎ መሰደደ በሆነበት ሁኔታ ውስጥ አገሩን ጥሎ የሚሰደደው ዜጋ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ለመሰደድ በሚያደርገው ጉዞ ምን ያህሉ በበርሃ እንደሚቀርና የአሳ እራት እንደሆነ የመገናኛ ብዙሃን በሰፊው ሲዘግቡት ቆይተዋል።

በተለያየ አገር በስደት ከሚፈልጉት አገር የደረሱትና የእለት ጉርሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ለማገዝ ደፋ ቀና በሚሉበት ሂደት ውስጥ በደቡብ አፍሪካ በቁማቸው በአሳት መቃጠል፣ በሊቢያ አይናቸው እያየ መታረድና በጥይት መደብደብ ሆኗል እጣ ፋንታቸው።

እናም አገርና ሕዝብ በእንደዚህ አይነት አስከፊ ሂደት መቀጠል የለበትም የወያኔም የግፍ አገዛዝ ሊበቀው ይገባል በሚል ቀደም ብለን ይህን በታኝ ስርዓት በትጥቅ ትግል እየተፋለምን ያለን ደርጅቶች እኛ አንድ ሆነን ሕዝቡን አንድ በማደረግ አገራቸንና ሕዝባችንን ነፃ ማውጣት የሚገባን ወቅት አሁን ነው በሚል ስርዓቱን ለማስወገድ በሚደረገው የትግል ሂደት በትብብር መስራት አለብን በሚል ውይይት ጀምረናል።

ወደፊት በሚኖረው የትግል ሂደት በትብብር፣ በጥምረት ብሎም በውህደት ለመስራት በውይይት ላይ የምንገኘው ድርጅቶች፡-

1. የትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ
2. የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ
3. የቤንሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ
4. የአማራ ዴሞክራሲ ሃይል ንቅናቄ
5. አረበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ

Wednesday, May 13, 2015

አይሲስን ስንቃወም ህወሓትን አለመርሳት!

በአይሲስ በግፍ በታረዱብን ወገኖቻችን የተሰማን ሀዘንና ቁጭት ከፍተኛ ቢሆንም እንኳን ከአዕምሮዓችን መውጣት የሌለበት ሀቅ አለ። ይህ ሀቅ “ያስጠቃን፣ ያሳረደን ወያኔ ነው” ከሚለውም ያለፈ ነው። መረሳት የሌለበት ሀቅ፣ ከአይሲስ የከፋ ጨካኝ በአገራችን የመንግሥት ሥልጣን የተቆጣጠረ መሆኑ ነው።

የህወሓት ፋሽስት ጦር በበደኖ፣ በአዋሳ፣ በሀረር፣ በጋምቤላ፣ በጎንደር፣ በኦጋዴን፣ በአዲስ አበባ፣ በሸካና መዠንገር፤ እንዲሁም በሚታወቁም በማይታወቁም የማሰቃያ እስር ቤቶች አይሲስ እየፈፀመ ካለው የባሱ ወንጀሎች በወገኖቻችን ላይ ፈጽሟል፤ አሁንም እየፈፀመ ነው። ባሳለፍነው ሣምንት እንኳን በሁመራ ወገኖቻችን የራሳቸውን መቀበሪያ ጉድጓድ ቆፍረው በጅምላ ተገድለዋል። በአይሲስና በህወሓት መካከል ያለው ልዩነት አይሲስ ነውረኛና አረመኔዓዊ ተግባሩን በቪዲዮ እየቀረፀ ለዓለም ሲበትን ህወሓት ግን እነዚሁኑ ነውረኛና አረመኔዓዊ ተግባሮችን እየፈፀመ መረጃዎች አፍኖ መያዙ ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ግን ህወሓት ሰዎችን ከነሕይወታቸው ጉድጓድ ውስጥ የቀበረ አረመኔ፣ እኩይ ድርጅት ነው።

ስለሆነም ለዓለም ሰላም ስጋት የሆነውን አይሲስን ስንቃወም የራሳችንን አይሲስ – ህወሓትን – አለመርሳት እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው።

በሌላ በኩል ደግሞ ህወሓት፣ የአይሲስን እኩይ ተግባራት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር እና ከዲሞክራሲያዊያዊ ፓለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ጋር ለማገናኘት እያደረገ ያለው ጥረት ምን ያህል አደገኛ ተግባር እንደሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲረዳው ያስፈልጋል። ዓይን አውጣ ሌባ ንፁሁን ሰው “ሌባ” እንደሚለው ሁሉ የኛው አይሲስ ራሱን ንፁህ አስመስሎ ሌሎችን “አይሲስ” ማለቱ ሊነቃበት ይገባል።

ሌላው ተያያዥ ጉዳይ ደግሞ ስለስደተኝነት የሚሰጠው ገለፃ ነው። ህወሓት ለስደተኝነት ምክንያቱ ደላሎች እንደሆኑ ይናገራል። ይህ የጉዳዩን ግንድ ትቶ ቅርንጫፎች ላይ ማትኮር ነው። ህገወጥ ደላሎች ራሳቸው ሊኖሩ የቻሉት ገንዘብ ከፍለውና የሕይወት ሪስክ ወስደው ለመሰደድ የሚፈልጉ ዜጎች በመኖራቸው ነው። ችግሩን በቅንነት ለመመርመር የሚፈልግ “ይህን ያህል ሰው የሕይወት ሪስክ እየወሰደ ከአገር ለመሰደድ ምን አነሳሳው?” ብሎ መጠየቅ እና ምላሽ ማግኘት ይኖርበታል። በሀገር ውስጥ በነፃነት ተረጋግቶ መኖር፣ ሠርቶ የማደግ ተስፋ ቢኖር ኖሮ ይኸን ያህል ሰው የአደጋውን ከፍተኛነት እያየ ለመሰደድ ይነሳሳ ነበርን? ኢትዮጵያዊው ከስደት ሊያገኝ የሚሻው ምንድነው? እንደ ወያኔ ካድሬዎች ገለፃ ከሆነ ከስደት ሊያገኝ የሚችለው አገሩ ውስጥ እያለለት ነው ኢትዮጵያዊ የሚሰደደው። ይህ ምን ዓይነት አመክኖ ነው? ከዚህ የባሰው ደግሞ ስደትንም የእድገት ውጤት አድርጎ የማቅረብ በሽታ ነው። ይህ እውነት ከሆነ፤ ህወሓት ለኢትዮጵያ አመጣሁላት የሚለው እድገት ውጤት ረሀብ፣ ስደት፣ መርዶ፣ እስር፣ ስቃይ፣ ሞት ከሆነ እንዴት “እድገት” ብለን እንጠራዋለን። ለስደተኝነት መብዛት ህገወጥ ደላሎችን ብቻ ተጠያቂ ማድረግ፤ “እኔ ከደሙ ንፁህ ነኝ” የማለት ያህል ነው። በህጋዊዎቹም በህገወጦቹም ደላሎች ውስጥ የወያኔ ሰዎች በቀጥታም በተዘዋዋሪም እንዳሉበት መረጃዎች ያመለክታሉ። ገንዘብ ባላበት ሁሉ የወያኔ እጅ መኖሩ ፀሐይ የሞቀው ሀቅ ነው። የሰዎች ዝውውር የህወሓት አንዱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ መሆኑ የማይታበል፤ በቀላሉ ማረጋገጥ የሚቻል ሀቅ ነው።

ደርግን ያስናፈቀ አገዛዝ!

እኔ ለደርግ ሥርዓት ጥሩ ስሜት የለኝም፡፡ በእርግጥ ደርግ ያደረገውን የቀይ ሽብር ፍጅት በወቅቱ ገና መወለዴ ስለነበር በዐይኔ ዐላየሁም፡፡ ይሁንና የሆነውን ሁሉ ግን አባቴም በኢሕአፓነቱ የደርግ ጥቃት ሰለባ ስለነበር እሱ ከነገረኝም ሆነ እኛ ዜጎች የደርግንም ሆነ የሌላውን ማንነት ከመረዳት አንጻር ከታሪክ ብዙ የምንረዳው ነገር አለና ለደርግ ጥሩ ስሜት የለኝም፡፡ ከፈጸማቸው የግድያ እርምጃዎች ጋር በተያያዘ አሁን ሀገራችን ላለችበት ዘንቀ ብዙ ችግሮች ተጠያቂ እንደሆነም አስባለሁ፡፡ በተለይም እነዚያ ብዙ የተማሩ ብዙ የሚያውቁ ብዙ የውጪ ግንኙነት ልምድ የነበራቸው የ62ቱ የቀዳማዊ ዐፄ ኃይሌ ሥላሴ መንግሥት ሚንስትሮችን ጉዳይ ሳስብ ዘወትር ይከነክነኛል፡፡ ኢትዮጵያ ከስር የተነቀለችው ዐይኖቿ የጠፋው ያኔ ነው፡፡ እነ ጠቅላይ ሚንስትር አክሊሉ ሀብተ ወልድን የሚያህል እጅግ አስተዋይ፣ አርቆ አሳቢ፣ ደከመኝ ሰለቸኝን የማያውቅ ትጉ፣ ተናግሮ ሊያሳምነው የማይችለው ሰው የሌለው ብልህ፤ በእነዚህ ብቃቱም በመንግሥታቱ ድርጅት ታሪክ ኮከብና አንጸባራቂ ዲፕሎማት (አቅናኤ ግንኙነት) የነበረን ታላቅ ሰው የመሳሰሉ ብርቅየ የሀገራችን ፖለቲካ (እምነተ አሥተዳደር) ቁልፍና መዝገቦች ያለ አግባብነት ያለው ፍርድ በግፍ መግደሉ ነው ሀገሪቱ መስመር ስታ ወዳልሆነ አቅጣጫ መንጎድ የጀመረችው፡፡

ሰሞኑን የፕሬስ (የጥፈት) ነጻነት ቀን ሚያዚያ 25 (May 3) በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ታስቦ ነበር:: ታዲያላቹህ በሀገራችንም ይሄንን የጥፈት ነጻነትን ቀን በዓል ለማክበር ለማሰብ እነማን ተሰባሰቡላቹህ መሰላቹህ? ጥፈትን (ፕሬስን) የገባችበት እየገቡ የሚያሳድዷት ጭፍሮች ተሰባስበው ታደሙና “ይሄው በዓልሽን እያከበርንልሽ ነው” ብለው ጥፈትን (ፕሬስን) ሲያፌዙባት ሲቀልዱባት ሲሳለቁባት ሲያበግኗት ዋሉ፡፡ ጥፈት (ፕሬስ) በጣም አሳዘነችኝ እንደምን ታር! እንዴት ትበግን! እንዴት ትደብን! ብየም አሰብኩላት፡፡ ጨጓራዋ ተልጦ ቆሽቷ ደብኖ እየጨሰች ታየችኝ፡፡ መድረኩ ላይ ተሠይመው እየተንጎባለሉ በመደስኮር ሲያቃጥሏት ከነበሩት የጥፈት ጠላት የወያኔ ጭፍሮች አንዱና በሀገሪቱ የጥፈት (የፕሬስ) ነጻነት እንዳለ ተደርጎ እንዲታሰብ ብቻ ተቋቁመው ከሚሠሩ የኅትመት የብዙኃን መገናኛዎች ባለቤቶች አንዱ የሆነው ሰው ምን አለ መሰላቹህ? እኔ ማንን ለማለት እንደፈለገ ቢገባኝም እንዴት ሆኖ እንደሆነ ግን ሊገባኝ አልቻለም፡፡ እንዲህ ነበር ያለው “አትመጣም ወይ መንጌ አትመጣም ወይ? እያለ የደርግን መልሶ መምጣት በመናፈቅ የሚጨፍር የፖለቲካ ፓርቲ ስለ ፕሬስ ነጻነት ተሟጋች እንዴት ሊሆን ይችላል?” ነበር ያለው፡፡ ሌላኛው ደግሞ አሁን በዚህ ወቅት “ነጻ ጥፈት (ፕሬስ) አለ በሚገባም እየሠራ ነው…..” በማለት ሌሎችን አለመኖሩን በማስረጃ አስደግፈው የሚሟገቱትን እንደ ሲ.ፒ.ጀ. ያሉ የዓለም አቀፍ ድርጅቶችን አቋምና ክስ ለማጣጣል ጥረት አደረገ፡፡ የሚገርማቹህ ይህ ሰው አንድ ወቅት ላይ የዚህ ዓለም አቀፍ ድርጅት ተሸላሚ የነበር ሰው ነው፡፡ እነዚህ ግለሰቦች ቀድሞውንም ቢሆን ሥውር ተልእኮ ስለነበራቸው በነጻው ጥፈት ተሰማሩ እንጅ አንጻራዊ በሆነ መልኩ ነጻው ጥፈት የተሻለ ይሠራ በነበረበት ወቅት አገዛዙ በነጻው ጥፈት (ፕሬስ) ላይ ያለውን አያያዝና አቋም ቀንደኛ ተችና ተቃዋሚ ሆነው ኖረው አሁን ላይ ጭራሽ አገዛዙ ነጻውን ጥፈት (ፕሬስ) ደብዛውን ባጠፋበትና የለየለት አንባገነን በሆነበት ወቅት ከወትሮው ይበልጥ መቃወምና መታገል ሲኖርባቸው ሲጠበቅባቸው እነኝህ የነጻው ጥፈት ውጤት ጋዜጣ ባለቤት ነኝ ባይና ነጻ ጋዜጠኛ ነኝ ባይ ግለሰቦች የአገዛዙ ደጋፊ ሆነው ከአገዛዙ ጋር ሊሠሩ ሊሰለፉ የሚችሉበት አንዳችም ምክንያት የለም፡፡ የስለላ ተልእኮ ነበራቸው ለመመሳሰል ተቃዋሚ ሆነው በሚገባ ተወኑ አንደኛው እንዲያውም እስከመሸለም ድረስ ደረሰ ወዲያው ግን ተነቃባቸው ስለተነቃባቸውና ስለተገለሉም “ከተነቃ አይገደድም” ብለው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡ ያለው ነገር ይሄ ነው ሌላ ምንም ምሥጢር የለውም፡፡

አገዛዙ የፈጸመውን ግፍና ወንጀል ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዐይን ለመሠወር ሲል የውጭ ዜጎች ድርሽ እንዳይሉ ወደ ተከለከሉበት አገዛዙ መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብት ረገጣና የዘር ማጥፋት ወንጀሎችን በፈጸመባቸው የሀገራችን አካባቢዎች የተፈጸሙትን ኢሰብአዊ ድርጊቶቹን ለማጣራትና መረጃ ለመሰብሰብ ባለመቻላቸው ምክንያት የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ሠራተኞች በተለያየ ዘዴና መንገድ መረጃ ለመሰብሰብ መሞከራቸውን ይሄ ጋዜጠኛ ነኝ ባዩ ወያኔ በዚህ በዓል ዝግጅት ላይ ሲናገር እንደሰማቹህት ነጻ ጋዜጠኛ መስሎ ይሰልል በነበረበት ወቅት ካየውና ካጋጠመው ተነሥቶ በመኮነንና እንደ ወንጀል በመቁጠር በወቅቱ ሲሠራው ከነበረው የስለላ ሥራው እየጠቀሰ ይናገር ነበር፡፡ ይሄ ሰው ከመሰሎቹ ጋር ሆኖ ባለፈው የሕወሀት 40ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በሚከበርበት ወቅት ወደ ስፍራው ተጉዘው ጉብኝት ካደረጉት ጋዜጠኞችና ከያኔያን ነን ባዮች ጋር በመሆን በጉብኝታቸው መጨረሻ ላይ ባለ 6 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት በማንኛውም እረገድ ከሕወሀት ጎን እንደሚሰለፉ ለሕዝብ በብዙኃን መገናኛ ካረጋገጡ ምንደኞች አድርባዮች ባንዶች አንዱ ሆኖ እያለ ነው እንግዲህ ዛሬም ሳያፍር አጻ ጋዜጠኛ ነኝ ሊለን የሚሞክረው፡፡

Monday, May 11, 2015

ፀረ ኢትዮጵያ የሆነውን የሕወሓት ቡድን ለማስወገድ ሁላችንም በህብረት እንነሳ!

በቅዱስ ዮሃንስ

ላለፉት 24 አመታት በሕወሓት አምባገነናዊ የጭቆና አገዛዝ ስር የወደቀችው አገራችን ኢትዮጵያ ስላለችበት ጭንቅ እና መከራ፤ ህዝባችን ስለሚኖርበት የምድር ሲኦል ብዙ ብዙ ተብሏል። የሕወሓት መሪዎችና የቡድኑ ፀረ-ኢትዮጵያዊነት አቋም፤ በአገር እና በወገን ላይ የፈፀሙትን በደልና ግፍ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ጠንቅቆ ያውቀዋል ብየ በፅኑ አምናለሁ። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚፈልገውንና የሚመኘው ነገር ቢኖር በአገራችን ላይ ሰላም ሰፍኖ፣ የህዝብ መብት ተጠብቆ፣ የዜጎች አንድነትና የአገር ህልውና ተከብሮ፣ በአለም እያዋረደን ካለው የድህነት ችግራችን ተገላግለን ማየት እንደሆነ እሙን ነው።

ይሁን እንጂ በዚህ አስከፊ ክፉ ዘመን፤ ከረሃቡም፣ ከችግሩም፣ ከግድያውና ከእስራቱ በላይ፣ የኢትዮጵያችን ህልውና፣ የአገዛዙን ስልጣን በያዙ ፀረ-ኢትዮጵያ ቡድኖች ምክንያት ከፍተኛ አደጋ ውስጥ ወድቋል፡፡ በተጨማሪም በሕወሃት መሪዎች እብሪትና ማናለብኝነት የጠፋው የህዝብ ህይወት፣ የተዘረፈው የአገር ሃብት፣ የባከነው እውቀት እና ጉልበት በቀላሉ የሚታይ እንዳልሆነ ይታወቃል።  

በነገራችን ላይ ባለፉት 24 የጨለማ አመታት በአገራችን ለደረሰው ውርደትና ጥፋት የሕወሓት ቡድን የአንበሳውን ድርሻ ይውሰድ እንጂ የተቃዋሚ የፖለቲካ ሰዎች ነን የምንል ሁሉ በቀጥታ ይሁን በተዘዋዋሪ ለተፈፀመው ጥፋት ተገቢ የሆነውን የየራሳችንን የጥፋት ድርሻ መቀበል ይኖርብናል፡፡ ህዝብም ቢሆን በተለይ አቅሙና ችሎታው የነበረው ሁሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን መረን በመልቀቅ እና መሪዎችን በማቅበጥ ለደረሰው ጥፋት እራሱ ሃላፉነት መቀበል የሚገባው መሆኑን ሳልጠቁም ማለፍ አልፈልግም። በስልጣን ላይ ያለው አስከፊው የሕወሓት አገዛዝ የሚያዋርደን እኛ እስከፈቀድንለት ድረስ እንደሆነ ሁሉ ፖለቲካ ድርጅቶች መሪዎችም በህዝብ ላይ መቀለድ የሚችሉት ህዝብ እስከፈቀደላቸው ድረስ መሆኑን ልናውቀው ይገባል። የፖለቲካ ድርጅቶች የህዝብን አደራ እንዳይበሉ፣ የህዝብ ቅስም እንዳይሰብሩ፤ በማን አለብኝነት ያሻቸውን እንዳይፈፅሙም ምን ያህሎቻችን ነን ከዳር ቆመን ከማውራት አልፈን በውስጣቸው ገብተን ልንቆጣጠራቸው፤ በህዝብ ስሜት መቀለድ አትችሉም ብለን የሞገትናቸው?
 
ስንቶቻችን ነን ሁሉንም የፖለቲካ ሰዎች በድፍን ከማማትና አይረቡም ከማት አልፈን ከግብዝነት እና ከአድር ባይነት በላይ ተሻግረን  አጥፊዎቹን ፊት ለፊት መናገር ድፍረቱን የተላበስን? ስንቶቻችን ነን ሊደገፉ የማይገባቸውን ድርጅቶችና የፖለቲካ መሪዎች አገራዊና ህዝባዊ ከሆነ ጉዳይ ምክንያት ውጭ በጭፍን በመደገፍ የጥፋት ስራ የሚሰሩበት እድሜያቸውን እየቀጠልንላቸው ያለነው? ለዚህ ደግሞ እያመንን ተከዳን ብቻ እያልን ማማረር ሳይሆን ሁሉም ይህንን የእምነት ክህደት አዙሪት ለመስበር ምን ሰርቻለሁ የሚል ጥያቄ ማንሳት ተገቢ ነው፡፡

ስለዚህ አሁን ሁላችንም የህወሃትን የጥላቻና ንቀት ፖለቲካ በመስበር፤ ለአገዛዙ የአንድ ቀን የስልጣን እድሜ መስጠት የኢትዮጵያውያን ውርደት ማስቀጠል መሆኑን በማወቅ ለራሱ ክብር የሚሰጥ እና በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራው ዜጋ ሁለ በያለበት ኢትዮጵያችንን ከጥፋት ቡድኖች ለመታደግ ሊንሳ ይገባል። ህወሃት የሃገራችንን ውበቷን፣ ክብሯን እና ግርማዋን ከማንም በላይ አዋርዷዋል፡፡ የዜጎቿም መታወቂያ እስር እና ስደት ሆኗል። ደምና አጥንት ቆጥሮ ተደራጅቶ ደምና አጥንት እየቆጠረ ዜጎችን የሚያዋርድ እና የሚያሰቃይ ዘረኛ ቡድን በኢትዮጵያችን ራስ ላይ ተቀምጦ እያየን እስከ መቼ ዝም ብለን በባርነት እንገዛለን። የስልጣን ህልውናውን ለማርዘም እንዲረዳው አስጠያፊ ዘረኝነትንና ጎሰኝነትን በኢትጵያ ላይ የዘረጋውን የህወሃት ዘረኛና ጠባብ ቡድን ከአገራችንና ከህዝባችን ጫንቃ ለማውረድ በያለንበት ተደራጅተን ልንፋለመውይገባል። ኢትዮጵያ የእኔም ሃገር ነች ማለት መጀመር አለብን፡፡ በዘረኝነት በሽታ የናወዙት የህወሃት ሹማምንት አገሪቷን እንደፈለጉ ሲያደርጓት ዕያዩ ዝም ማለት አገር እና ክብርን ከማሳጣት በተጨማሪ ለጥፋቱ ተባባሪ በመሆን ከመጠየቅ አያድንም።

ዛሬ ኢትዮጵያችን ከጥፋት የሚታደጓት ከደም እና ከአጥንት ልቆ ማሰብ የሚችሉ ዜጎቿን ከምንጊዜውም በላይ ትፈልጋለች። አሁንም አገራችን ለፍትህ፣ ለእኩልነት እና ነፃነት ዘብ መቆም የሚችሉ ዜጎቿን አድኑኝ ስትል ትጣራለች። ለሚመጣው ትውልድ ጥቂቶች ብዙሃኑን ተጭነው፤ ብዙሃንም ጥቂቶችን ተሸክመው መከራቸው በዝቶ የሚኖሩበት አገር ትተንላቸው እናልፍ ዘንድ ፈጽሞ አይገባም። በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የሆኑና የዘረኛው ቡድን ግፍና በደል ያንገፈገፋቸውና እያንገፈገፋቸው ያሉ የሰራዊቱ አባላት ከታሪክ ተወቃሽነት ለመዳንና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት መነሳትና አገር አድኑን የነፃነት ትግል መቀላቀል ያለባቸው ጊዜም ዛሬ ነው። በተጨማሪም ጥቂት ዘረኞችና ዘራፉዎች አገሪቷን እንደፈለጉ ሲቀራመቱ እያየን እኔ ምን አገባኝ የሚባልበት ጊዜ ላይ እንዳልሆንን ሁሉም ዜጋ ሊገነዘብ ይገባል።

ስለዚህም ከአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፤ ከእምነት ማካሄጃ ስፍራዎች እስከ የአገዛዙ መስሪያ ቤቶች፤ ከአርሶ አደሩ መንደር እስከ ምሁራኑ ሰፈር፤ ከአገር ቤት እስከ ውጭ ሃገረት ያለው ዜጋ ሁሉ የሕወሓት አገዛዝን በማስወገድ አገሩንና ህዝቡን ከጥፋት ለመታደግ በያለበት የነፃነት ትግሉን ልንቀላቀል ይገባል ስል ወገናዊ ጥሪየን አቀርባለሁ።

ድል የህዝብ ነው!



Friday, May 8, 2015

የተጨናገፈው፤ የዕልቂት ድግስ (ሚያዚያ 30ን ከስፍራው)

(በደረጀ ሀብተወልድ፤ኢሳት-በማእደ- ኢሳት የቀረበ)

በጎቹ ጨፌው ላይ - በፍቅር ያዜማሉ፣
ተኩሎች አድፍጠው - ይጠባበቃሉ፣
ጩኸት ሊበረክት-ሊፈስ ሲል ዕንባ፣
እረኛው በድንገት-መሀል ጣልቃ ገባ።
አገር በደም ባህር-ሊጠመቅ ተፈርዶ፣
ውሀ ጥምቀት ሆነ-ከላይ ዝናም ወርዶ።

ቅንጅት፤ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ የጠራውን የሚያዚያ 30/1997 ዓ.ም ሰልፍ ለመዘገብ ወደ መስቀል አደባባይ ያመራሁት እኩለ-ቀን ላይ ነው። ከረፋዱ 4 ፡00 ሰ ዐት ጀምሮ ታክሲዎች መደበኛ ሥራቸውን ትተው ሰዎችን በነፃ ወደ መስቀል አደባባይ ማመላለስ በመጀመራቸው፤ሰልፉ ምን መልክ ሊኖረው እንደሚችል መገመቱ ቀላል ነበር።ቀድሜ ወደ ሥፍራው የተንቀሳቀስኩትም፤ ማለፊያ መንገድ ሳይዘጋጋ ወደ አደባባዩ ለመቅረብ እንድችል ነው።እንደወትሮው ሁሉ ዛሬም መቅረፀ-ድምፄንና ካሜራዬን አንግቤያለሁ። የወቅቱ ሀዳር ቀጥሎም የአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ማኔጅንግ ኤዲተር የነበረው ዳዊት ከበደ፤ እንዲሁም የሀዳር ምክትል ዋና አዘጋጅ የነበረው ፈለቀ ጥበቡ አብረውኝ አሉ።

የሰው ጎርፍ ከየአቅጣጫው እየተግተለተለ ወደ አንድ ሥፍራ ተከማችቶ እንደ ረጋ ውቅያኖስ ሆነ።ዳርቻው የማይደረስበት ውቅያኖስ።
መለስ፤ ከአንድ ቀን በፊት ያዩትን የኢህአዴግ ሰልፍ በማድነቅ “ማዕበል” ብለው መጥራታቸውን ያስታወሰው ሪፖርተር ጋዜጣ ፤ከቅንጅት ሰልፍ በሁዋላ ባወጣው ርዕሰ-አንቀጽ ” ለማዕበልም፤ ማዕበል አለው” በማለት ነበር ለመለስ ንግግር ምላሽ የሰጣቸው።
የማዕበሎች ሁሉ ማዕበል።
ምኒልክ ጋዜጣ ደግሞ፦”ሱናሚ”ሲል ነው የጠራው።
የሚገርም ቀን።

ሚያዚያ 30/ 97፦ በኢትዮጵያ የሺህ ዓመታት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የታዬ ህልም ሚመስል ትዕይንት።ሚሊዮኖች ነፃነታቸውን በአደባባይ በማወጅ ዲሞክራሲን በጋራ የዘመሩበት ታሪካዊ ቀን።

ሆኖም፤የሰልፉ አስተባባሪዎች ለዕለቱ የተሰናዳውን ፕሮግራም ለማቅረብ ዝግጅታቸውን እንዳጠናቀቁ ፈፅሞ ያልተጠበቀ ነገር ሆነ-መብራት ጠፋ። በወቅቱ ተቀርፎ የነበረው የአዲስ አበባ የመብራት ችግር፤ ከረዥም ወራት በሁዋላ የቅንጅት ሰልፍ ፕሮግራም ሊጀመር ደቂቃዎች ሲቀሩት እንደ አዲስ ተቋረጠ።

እንደ ትናንት የኢህአዴግን ሰልፍ በተንቦገቦገ መብራት ያስተናገደው አደባባይ፤ዛሬ ሚሊዮኖች ለወጡበት ሰልፍ ብርሀኑን ነፈገ።
በተደጋጋሚ ወደ መብራት ሀይል ባለሥልጣን ስልክ በመደወል የተደረገው ጥረትም ሳይሳካ ቀረ።
ጥቂት ሰዎች- ዕልፎችን፦“የጀኔሬተሩ ቁልፍ በእኛ እጅ እሰከሆነ ድረስ ብርሀን እንድታዩ አንፈቅድላችሁም” አሏቸው።
በሆነው ነገር ህዝቡ ተቆጣ። ከዳር እስከ ዳር የተቃውሞ ጩኸት ማሰማት ጀመረ።

የህዝቡ ቁጣ ከቁጥጥር ውጪ እንዳይሆን የሰጉ የቅንጅት አመራሮችም ፤ የእጅ ማይክራፎን ይዘው በሰልፉ መሀል በመዟዟር ‘ከመብራት መቋረጥ ጀምሮ ሆነ ተብለው እየተፈፀሙ ያሉትን ማናቸውንም የሚያበሳጩ ድርጊቶች ህዝቡ በትዕግስት እንዲያልፋቸው’ በአደራ ጭምር ተማፀኑ።
“…እነሱ የፈለጉት በብስጭት ወደ ህገ-ወጥ ድርጊት እንድንገባ ነው።እያመቻቹን ያሉት የሀይል እርምጃ ለመውሰድ ነው።ንቁባቸው! እንኳን መብራት ማጥፋት ሌላም ነገር ቢፈጽሙ ከህጋዊና ሰላማዊ መስመራችን የማንነቃነቅ የዲሞክራሲ ሰልፈኞች መሆናችንን እንድናሳያቸው፤ ደግመን ደጋግመን አደራ እንላለን!!”
ህዝቡ የመሪዎቹን ጥሪ ተቀብሎ የሚሆነውን ነገር በትዕግስት መጠባበቅ ጀመረ።
በላዩ፤አናት የሚበሳው የፀሀይ ቃጠሎ አለ።

ህወሃቶች እንደ ዘኬዎስ!!

ሰዉዬው በሕዝቡ በጣም የተጠላ ነው። የገዢው ቡድን አካል ነው። በሕዝቡ ላይ ብዙ ግፍ ይፈጽማል። ሰዎች የዚህን ሰው ሞት እንጂ መልካም ነገር አይመኙም። ሁልጊዜ እንደተረገመ ነው። ዘራፊ ነው። በሙስና የተጨማለቀ። ለሰው ፣ ለድሃው ርህራሄ የሌለው። የሌላዉን ደም እየጠጣ የከበረ። በጣም የተጠላ ሰው።

አንድ ቀን በሚያስደንቅ ሁኔታ ከዚህ ሰው የማይጠበቅ ነገር ተሰማ ። ከዚህ በፊት የበደላቸውን እንደሚክስ፣ ከዚህ በፊት ያደርግ እንደነበረው ግፍን ከመፈጸም እንደሚቆጠብ ተናገረ። ምን ተፈጠረ ? ምን አዲስ ነገር ሆነ ? ተፈጥሯዊ የሆነ የተለወጠ ነገር የለም። ሌላ የመንግስት ስርዓትም አልተለወጠም። ይህ ሰው ከነበረው ስልጣን አልተነሳም። ምን የተለየ ነገር ተከሰተ ?
ይህ ሰው አንድ ቀን ከአንድ ታላቅ ሰው ጋር ተገናኝ። ይህ ሰው ዘኬዎስ ይባላል። የተገናኘውም ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ነበር።

ዘኬዎስ ለሮማዊያን (ያኔ እስራኤልን ይገዝዙ የነበሩ)ሚሰራ፣ ለነርሱ ግብር የሚቀበል ቀራጭ ነበር። የገዢው ቡድን ( የሮም) አገልጋይ ነበር። አሁን በአገራችን ያለዉን ምሳሌ ከተጠቀምን፣ ይህ ሰው "ወያኔ" ነበር እንደማለት ነው። ትላንት ሕዝብ ሲያስጨንቅ የነበረው "ወያኔው" ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ሲያገኝ ሕይወቱ ተቀየረ።

ስለ ጌታ አስቀድሞ ሰምቶ ሊያየው ይፈልግ ነበር። አጭር ስለነበረና በጣም ከመጠላቱ የተነሳ ከህዝቡ ጋር ቢቀላቀል ሊሰደብ ወይንም ሊደብደብ ስለሚችል፣ ሰው ሳያየው በሩቅ ጌታን ለማየት ፣ ጌታ በሚያልፍበት መንገድ ላይ ካለ ዛፍ ላይ ወጥቶ ጠበቀ። ሰዎች በዚያ ያልፋሉ፤ ግን አላዩትም። እዚያች ዛፍ ስር ሲደርስ፣ ጌታ ቆም አለ። ሰዎች ያላዩትን ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አየው። አዎን "ወያኔዉን"፣ በሕዝብ የተጠላዉን ጌታ አየው።

"ኢየሱስም ወደዚያ ስፍራ በደረሰ ጊዜ፥ አሻቅቦ አየና። ዘኬዎስ ሆይ፥ ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛልና ፈጥነህ ውረድ አለው። ፈጥኖም ወረደ። በደስታም ተቀበለው።" ይላል የሉቃስ ወንጌል ምእራፍ 19 ።ሌሎች ከዚህ በሕዝብ ከተጠላ ፣ ህዝብን ሲያሰጨነቅ፣ ከሚገባው በላይ ግብር እየተቀበለ ድሃን ሲዘርፍ ከነበረ ሰው ጋር መነጋገሩ አስገረማቸው። "ከኃጢአተኛ ሰው ጋር ሊውል ገባ ብለው አንጐራጐሩ" እንደሚል ቃሉ፣ በጌታ ሁኔታ አልተደሰቱም።

Wednesday, May 6, 2015

የተቀዳደደዉ የዜጐች ነጻነት በኢትዮዽያ

በመሃመድ አሊ

በግንቦት 1983 በኢትዮዽያ አቆአጣጠር ሕ.ወ.ሀ.ት መራሹ ጦር የመንግስት ወንበር ከተቆጣጠረ በኋላ ግዜዉ የሚያሥገድደዉንና በምዕራባያዉያንም ተፅእኖ ጭምር አዲሥ ሊባል የሚችል ሕገመንግስት ማርቀቁ ይታወሳል፡፡

በ1985 የፀደቀዉ የኢትዮዽያ ሕገመንግስት ቀድሞ ከነበሩት የደርግና የዘዉዳዊ መንግስት በብዙ መልኩ እንደሚሻል በሃገር ዉስጥም በዉጭ መንግስትም ችሮታ ተለግሶት ነበር፡፡ ሆኖም የበግ ለምድ የለበሰዉ ተኩላ ባሕሪዉ የመንግስት ስልጣንን ላለመልቀቅ ራሱ ያፀደቀዉን ሕገመንግስት በየግዜው እየሸረሸለዉ ይገናል፡፡ ከቶም እየናደዉ ካሉት ሕጎች መካከል የዜጐች የመናገር፣ የመፃፍና የመደራጀት መብት ዛሬ ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ተሸርሽፘል፡፡

በ1997 በዜጎች የመደራጅት መብት ተጠቅመዉ ሕብረብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ መብትን በተግባር ለማዋል ተቀናጀተዉ የነበሩ ፓርቲዎች በሐገሪቱ ሕዝብ ንቃተ ሕሊና ማዳበራቸዉ ስልጣን ላይ የተቀመጠዉን የወያኔ መንግስት አስደምብሮት አዉሬያዊ ባሐሪዉ እንዲገነፍል አድርጐታል፡፡በወቅቱ ተከስቶ የነበረዉ አዲስ የዴሞከራሲ ጅምር ሕብረተሰቡ መቅመሱ በሰዉ ልጅ ላይ ድርድር አለመኖሩን አሳይቶ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ነገሮች ሁሉ መገልበጣቸዉ በይፋ መታየት ጀመፘል፡፡

ዛሬ ኢትዮዽያዊ በሐገሩ የዜግነት መብት በነፃነት የመናገር ፣የመፃፍም ሆነ መደራጀቱ በጥርጣሬ እንዲታይና ወህኒ ማደርያዉ እንዲሆን እያስደረገዉ ይገኛል፡፡ ሐገራችን የዜጐች መብት የተጨፈለቀበት በመሆኑ ሰዉ እርስ በርሱ መተማመን እያቃተዉ በጥርጣሬና በመፈራራት እየኖረ ገዢዉ ፓርቲ አንባገነንነቱን ከመቼዉም ግዜ በላይ በማናር አንዱን ከሌላናዉ ጋር በማጋጨት ዜጐች ተግባብተዉ እንዳይኖሩ እያደረገ ይገኛል፡፡በኢትዮዽያ እስር ቤቶች ከጋዜጣና መፅሔት ስራ ጋር የተገናኙ አዘጋጆች፣ ሪፖርተሮች፣ የጋዜጣና መፅሔት ባለቤቶች ስለ ነፃነት በመፃፋቸዉ ብቻ የመከራ ግፋትን እንዲቀምሱ ተደርጋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ በ1997 በብዛት ይታዩ የነበሩ ጋዜጣና መፅሔቶች ዛሬ ለዐይን አይታዩም፡፡በከተማዋ በመንግስት የሚደጐሙ ጥቂት የፓርቲ ልሳን የሆኑ ነፃ መሰል ጋዜጦች እንጂ አንድም ነፃ ፕሬስ አይገኝም፡፡ እስከ ቅርብ አመት ስለ ነፃነትና ስለ ዜጐች መብት ሲዘምሩ የነበሩ ጋዜጦች ወይ ከሐገር ተሰደዋል አልያም እጅና እገሮቻቸዉ ተጠፍሮ ወህኒ ገብተዋል፡፡እስር ላይ ከሚገኙ ዜጎች መካከል 80 በመቶ የሚሆኑት የዜጐች መብት ላይ ጥያቄ የሚያቀርቡ የነቁና የተማሩ ኢትዮዽያዊያን ናቸዉ፡፡ በመንግሰት ወንበር ላይ ከተቀመጡት ባለሥልጣናት በላይ በኢትዮዽያ እስር ቤቶች ሐገሪታን መምራት የሚችሉ የነቁ ሙሑራን ወህኒ ታጉረዋል፡፡

በኢትዮዽያ በአሁኑ ግዜ በየትኛዉም የዜጎች መብት ላይ በነፃነት ሚናገሩ ዜጎችን ማግኘት አይቻልም፡፡ ከአምስት በላይ ሰዎች አንድ ቦታ ላይ ተሰብስበዉ መነጋገር ካለባቸዉ ለመንግስት ማሳወቅ እንዳለባቸዉ ይፋ ባልሆነ መንገድ እየተገለፀ ይገኛል፡፡ በቅርቡ አንድ ጋደኛዬ በትምህርት ጉዳዮች ላይ ባዘጋጅዉ አጫጭር ዉይይቶች በተደጋጋሚ ከደህንነቶች ማስፍራሪያና ዛቻ ገጥመዉታል፡፡

የቁልቁለቱን ጉዞ እናስቁም፤ ውርደት ይብቃን!!!

የህወሓት አገዛዝ ፋሽስታዊ ባህርያት እያደር መረን እያጣ፤ ነውረኛ እየሆነ መጥቷል። በአሳለፍነው ሣምንት ብቻ እንኳን አስነዋሪ ይዘት ያላቸው ሁለት ፋሽስታዊ ክስተቶችን አስተውለናል።

አንዱ በምርመራ ስም በታሳሪዎች ላይ የሚደረገው አሳፋሪ ሰቆቃ ነው። በገላቸው በሚያፌዙና በሚሳለቁ ተቃራኒ ፆታ መርማሪዎች ፊት ለሰዓታት ተመርማሪዎች ራቁታቸውን እንዲሆኑ የሚደረግበት እና እየተፌዘባቸው የሚደበደቡበት ሥርዓት መኖሩ የጉዳቱ ሰለባዎች ይፋ ሲያወጡ እፍረቱ ለመርማሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ይህንን ጉድ ተሸክመን ለኖርነው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ነው። በተለይም ደግሞ እንዲህ ዓይነት ክብረነክ ሰቆቃ በሴቶች ላይ እየተፈፀመ መሆኑን ስንሰማ አገራዊ ውርደቱ ያሸማቅቀናል። እንዲህ ዓይነቶችን በሰው ስቃይና እፍረት የሚዝናኑ ጉዶችን ተሸክመን የምኖር መሆናችን ሁላችንን ያዋርደናል። ይህንን አስነዋሪ “የምርመራ ዘዴ” ያጋለጡት የዞን 9 ብሎገሮች፣ ጋዜጠኞችና ፓለቲከኞች ክብርና ሞገስ የሚገባቸው ጀግኖች ሲሆኑ የተዋረዱት እነሱ ሳይሆኑ እኛ ኢትዮጵያዊያን መሆናችን ሊሰማንና “ውርደት በቃ” ልንል ይገባናል።

ሁለተኛው አሳፋሪ ድርጊት ደግሞ ወገኖቻችንን በግፍ ባረደው አይሲስ በተሰኘው አሸባሪ ድርጅት ላይ የህወሓት አገዛዝ የተለሳለሰ አቋም ወስዷል ብለው ራሱ ህወሓት በጠራው ሰልፍ ላይ ተቃውሞዓቸውን ባሰሙ ወጣቶች ላይ አገዛዙ የወሰደው የኃይል እርምጃና ከዚያም ወዲህ እየተደረገ ያለው ነገር ነው። አገዛዙ ለፕሮፖጋንዳው ይጠቅመኛል ብሎ በጠራው ሰልፍ ወጥተው ተቃውሞዓቸውን የገለፁ ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተደብድበዋል፤ በጅምላ ወደ እስር ቤቶች ተግዘዋል። የአገዛዙ ካድሬዎች ወገኖቻችንን የፈጀውን አይሲስን በመቃወም ፋንታ የራሱ የህወሓትን ውል አልባ ህግ አክብረው በመንቀሳቀስ ላይ ያሉትን ሰማያዊ ፓርቲ፣ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን እና አረና ፓርቲን እየወነጀሉ መሆኑ አጅግ አሳፋሪ ነገር ነው። የአይሲስን አረመኔአዊ ድርጊት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር ለማገናኘት በህወሓት የደህንነት ቢሮ አማካይነት እንቅስቃሴ መጀመሩ እየተሰማ ነው። ለወጣቱ በብዛት መሰደድ በምክንያትነት የሚያቀርቡት ደላሎችን መሆኑ አላዋቂነት ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ቅራኔው በኢትዮጵያዊያን መካከል እርስ በርስ እንዲሆን ያለመ መሠሪነት ነው። ከዚህም አልፎ የትግራይ ወጣቶችን ነጥሎ በመሰብሰብ “ትምክህተኞች ሊበሉህ ነውና ታጥቀህ ሳይቀድሙህ ቅደም” እያሉ መቀስቀስ በመንግሥት ደረጃ የእርስ በርስ እልቂትን ከማደራጀት ተለይቶ አይታይም። የሥርዓቱ ይሉኝታ ቢስነት የደረሰበት ዝቅጠት ገላጭ ከሆኑ ነገሮች አንዱ “እስከምርጫ መጨረሻ ድረስ ልጆቻችሁን አስረን እናቆይላችሁ” እያሉ ወላጆችን እስከመጠየቅ መድፈራቸው ነው።

ከላይ በአጭሩ የተዘረዘሩት ኩነቶች የሚያረጋግጡት ህወሓት የተማከለ አመራር አጥተው መንገድ የጠፋቸው፤ ሆኖም ግን እጃቸው ውስጥ የገባው ስልጣንና ሀብት ላለማጣት ምንም ነገር ከማድረግ የማይመለሱ አውሬዎች ስብስብ መሆኑ ነው። እንዲህ ዓይነቱን የአውሬዎች ስብስብ የሚገዛው የህግም ሆነ የሥነ-ምግባር ገደብ የለም። ህወሓት እስር በርሳችንን አባልቶ አገራችንንና ሕዝቧን ወደ ማንወጣው አዘቅት ከመክተቱ በፊት ራሱ ህወሓትን ማስወገድ እና በምትኩት ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን መገንባት የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ነው። ይህ ካላደረግን አሁን በወህኒ ቤቶች የሚደረገው ዜጎችን ልብስን አስወልቆ የማዋረድ አስነዋሪ ተግባር ነገ በአደባባዮች የማይደረግ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ የለንም። ይህ ትውልድ ኃላፊነቱ ካልተወጣ ህግን አክብረው ከአገዛዙ የተለየ ሀሳብ እናራምዳለን የሚሉ ወገኖቻችን በሙሉ አደጋ ውስጥ ናቸው። በህወሓት መሠሪ ተግባራት ሳቢያ በክርስትናና እስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን መካከል ያለው መግባባት እንዲሻክር እየተደረገ ነው። ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም። ይህንን ማስቆም ያለብን እኛ ሁላንችንም ነን። በአደባባይ መደራጀት ሲከለከል በምስጢር መደራጀትን መልመድ የኛ ኃላፊነት ነው። የኢትዮጵያ አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓልን ስናከብር ከቀደምቶቻችን ልንወርስ ከሚገቡን እሴቶች አንዱ ለክብራችን ዋጋ መክፈል ያለብን መሆኑን ጭምር ነው። የኢትዮጵያዊያን ክብር በወያኔ ሲዋረድ እያየን ዝምታን ከመረጥን ከዚህም የባሰ እንዲመጣ መፍቀዳችንን እንወቀው።

Monday, May 4, 2015

Journalists to Remember on World Press Freedom Day

May 4, 2015
Amnesty International

Eskinder Negaan Amnesty International Prisoner of Conscience, is a prominent Ethiopian journalist who was arrested and sentenced to 18 years imprisonment after making speeches and writing articles criticizing the government and calling for freedom of expression to be respected. In June 2012, he was found guilty of “preparation or incitement to terrorist acts, “participation in a terrorist organization,” and “high treason.” His wife, Serkalem, once a publisher and journalist in Ethiopia, was also arrested and held in captivity during the birth of their son until able to flee to the United States, where they await Eskinder’s return. Read more…