Monday, March 30, 2015

የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ 2007 ዓ.ም

የምርጫ ማኒፌስቶም ሀገራችን አሁን ካለችበት የኢህአዴግ አምባገነናዊ አገዛዝ ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በሚደረግ ሽግግር ወቅት በሀገራችን ሰማያዊ ፓርቲ በምርጫ ተወዳድሮ ማሸነፍ ቢችል የሚያከናውናቸውን ተግባራት በዝርዝር የሚተነትን ነው፡፡ ይህ የምርጫ ማኒፌስቶ በዋናነት በሦስት ምዕራፍ የተከፈለ ሲሆን የመጀመሪያው የፖለቲካ ሥርዓቱ አደረጃጀት ምን መምሰል እንዳለበት የሚገልፅ ክፍል ነው፡፡ በዚህ ምዕራፍ ሰማያዊ ፓርቲ ባለፉት 24 ዓመታት የህወሀት/ኢህአዴግ መራሹ ሥርዓት በሀገራችን ላይ የፈፀማቸውን የፖሊሲ ሰህተቶች በዝርዝር የሚያስቃኝ ሲሆን፤ በአንፃሩም ፓርቲው በሥልጣን ላይ ቢቀመጥ በዋነኛነት በቋንቋ ላይ የተመሰረተውን የፌደራል ሥርዓት በመቀየር መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥን፣ የሕዝብ አሰፋፈርን፣ ልማትና ሌሎች ማህበራዊ ትስስሮችን መሰረት ያደረገ ፌዴራላዊ የመንግስት አወቃቀር አማራጩን የሚያሳይበት ሲሆን፤ የመንግሥት አወቃቀሩ፣ የነፃ-ፕሬስ፣ መከላከያ ፖሊስና ደህንነት አደረጃጀቱ እንዲሁም የውጭ ግንኙነት አማራጭ ፓሊሲው በዝርዝር የሚዳሰሱበት ከፍል ነው፡፡

በሁለተኛዉ ምዕራፍ የማህበራዊ ሥርዓቱን በተመለከተ የተዘረዘሩ ነጥቦችን የያዘ ሲሆን ህወሃት /ኢህአዴግ የሀገራችን ሕዝብ ማህበራዊ ዕድገት ላይ ያስከተለውን ሁለንተናዊ ቀውሰ በማስቃኘት፤ በሰማያዊ ፓርቲ የማህበራዊ ጉዳይ መሰረታዊ ፍልስፍና መሰረት ጤነኛና በእውቀት ላይ የተመሠረተ በራሱ የሚተማመን ዜጋን ለመፍጠር ዋነኛ ምሰሶ ተደርጎ በሚቆጠረው ትምህርትና ጤና ላይ ያለውን ፖሊሲ በመዳሰስ፤ አረጋውያንና በተፈጥሮና በአደጋ የአካልና የአዕምሮ ጉዳት የደረሰባቸውን የኅብረተሰብ ክፍሎች በተመለከተ የፓርቲውን እይታ ይተነትናል፡፡ በተጨማሪም ሃይማኖት፣ ባህል፣ ኪነ-ጥበብ፣ ስፖርት እና ሌሎች ማኅበራዊ ጉዳዮችን የሚገነዘብበት ድርጅታዊ እይታዎች ያስቃኛል፡፡

በመጨረሻም በዚህ ማኒፌስቶ በጥልቀት የተገለፀው የፓርቲውን የኢኮኖሚ አማራጭ የሚያሣየው ምዕራፍ ነው፡፡ በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የህወሃት/ኢህአዴግ ሥርዓት እከተለዋለሁ የሚለውን ገጠርን ማዕከል ያደረገ ግብርና መር የኢንዱስትሪ ልማት የኢኮኖሚ ፖሊሲ ከዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ በማስቀደም ልማት የሀገሪቱ መሠረታዊ ጥያቄ ስለሆነ በሚል ለኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲ ቅንጦት እንደሆነ በመቁጠር ’’ሁሉ ነገራችንን ለልማት’’ በሚል ሰበብ በሀገራችን ኢኮኖሚ ለውጥና ዕድገት ላይ የፈጠረውን ደንቃራ በጥልቀት ይመረምራል፣ ትችቱንም ያቀርባል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ በሕዝብ ተመርጦ የመንግሥትነትን ሥልጣን ቢይዝ፤ በሀገሪቱ ውስጥ ሊያሰፍን የሚሻውን የኢኮኖሚ መርህም ያሳያል፡፡ በዚህም መሠረት ሰማያዊ በሀገራችን ተግባራዊ ለማድረግ ያቀዳቸዉን የኢኮኖሚ ፖሊሲ አማራጮች በዝርዝር ያስቀመጠ ሲሆን በዋነኝነትም የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ በተመለከተ አርሶ አደሩን የመሬቱ ባለቤት የሚሆንበትን መብት ማረጋገጥ፤ እንዲሁም ሁሉም የኢኮኖሚ ዘርፎች የትኩረት አቅጣጫ ገበያ መር ሆኖ ዜጎች በፈለጉት ሙያ እና የሥራ መስክ ተሰማርተው፣ ሀብት የማፍራት፣ በሕጋዊ መንገድ የንብረት ባለቤት የሚሆኑበት በተጨማሪም በሀገሪቱ በሁሉምአቅጣጫዎች ተሰማርተው የሚሠሩበትን መብት የሚያረጋግጥ እንዲሆን የሚረዳ የፖሊሲ አማራጩን አስቀምጧል፡፡

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Thursday, March 26, 2015

አርበኞች ግንቦት 7… እየመጡ ነው!


ሰሞኑን ወያኔ እየደለቀው የሚገኘው “የጦርነት ክተት አዋጅ” አታሞ ለጆሯችን አዲስ አይደለም፡፡ የተለመደ ከተራና ትርጉምየለሽ የፖለቲካዊና ወታደራዊ ፕሮፖጋንዳ ያላለፈ ፍርሃት ከወለደው ጭንቀት የመነጨ ቅዠት /Nightmare/ የእንቅልፍ ዓለም እንቅስቃሴ /Somnambulism/ ነው፡፡ ህ.ወ.ሓ.ት ጠብመንጃና ጥይት እንጂ የመዋጋት ስነ-ልቦና ፈፅሞ በውስጡ የሌለውን መከላከያ ሰራዊቱን ቢያንስ፣ ቢያንስ በየስድት ወሩ ወደ ኤርትራና ሱዳን ድንበሮች የስጠጋል፣ መልሶ ያሸሻል ያስጠጋል መልሶ ያሸሻል፡፡ በኦጋዴን በኩልም ከኦብነግና አልሸባብ ጋር በተያያዘ እንዲሁ ነው፡፡ አራቱን የሂሳብ ስሌቶች እንኳን ጠንቅቀው የማያውቁት የወታደራዊ ሳይንስ ሽፍታ “ጨዋ” የህ.ወ.ሓ.ት ጀነራሎች ተግባራቸው ሁሉ ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ ከሆነ ከራርሟል፡፡ ሟች በሌለበት ገዳይ መሆናቸው እና የሚገባላቸው አያገኙም እንጂ ወጣቶችን በሀገር መከላከያ ስም ለስልጣናቸው እድሜ ማራዘሚያ ለመመልመል ማስታወቂያ ማውጣታቸውም ቢሆን ከዚህ በፊት እየተደጋገመ ያሰለቸን ጉዳይ ነው፡፡

ወያኔዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ ዛሬም ወደፊትም አይዋጉም፡፡ በ1991 ዓ.ምና በ92 ዓ.ም የተዋጋው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው፡፡ በትንሹ ከ100 ሺህ በላይ የድሀ ልጆች በከንቱ ረግፈው ቀርተዋል፡፡ ድሉ ግን የወያኔዎች ብቻ ነበር፡፡ አሁንም ቢሆን የወያኔዎ ዕቅድና ፍላጎት ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ ሽማግሌው ስብሃት ነጋ ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ የትግርኛ ፕሮግራም “የኤርትራ ጉዳይ ያስተዳደር እንጂ የቅኝ ግዛት አይደልም…” በማለት ከ40 ዓመታት በኋላ ድርጅታቸው ህ.ወ.ሓ.ት አቋሙን መለወጡን ማስታወቃቸው፤ በተጨማሪም ወያኔ-ኢህአዴግ ለምርጫ ቅስቀሳ በየጊዜው የሚለቃቸው ዶክመንተሪዎች የአድዋን ድልና ሌሎችን የህዝቡን ስነ-ልቦና ማስተሳሰሪያ ጠንካራ የታሪክ ክሮች እየመዘዘ ማሳየቱ ከዛሬ 14 እና 15 ዓመታት በፊት እንደሆነው ህዝቡን ለጦርነት በማነሳሳት የድሃ ልጅ የሆኑ ወጣቶችን ደመራ በማድረግ ዳር ሆነው ለመሞቅ ነው፡፡ የሰሞኑ ፕሮፖጋንዳቸው ንፋስ ትክክለኛ አቅጣጫ ይሄ ነው፡፡ ነገር ግን በጠብመንጃ አስገድደው አፉን በማስከፈት የግፍ ገፈት እየጋቱት የሚገኘውን መከረኛ የኢትዮጵያ ህዝብ ልክ እንደበፊቱ ዛሬም በቀላሉ ማታለል እንደማይቻል ልቦናቸው ጠንቅቆ ያውቀዋል፡፡

ወያኔ ፈለገም አልፈለገም ጦርነቱ አይቀሬ ነው፡፡ ህዝቡ ራሱን መጠየቅና መልስ መስጠት ያለበት ቁምነገር ቢኖር ወያኔ ጦርነት የሚገጥመው ከነማን ጋር ነው? የሚለውን ነው፡፡ ወያኔ በጥሩንባ እንደሚያስለፍፈው ጦርነቱ የምር ከኤርትራ ጋር አይደለም፡፡ ኤርትራ ውስጥና በኤርትራ ዙሪያ በሚገኙ ጀምበር እቶን እሳቷን ከምታራግፍባቸው ነዲድ የሚተፉ በረሃዎች ውስጥ ከመሸጉ የነጻነት ፋኖዎች የምንጊዜም ጀግና የኢትዮጵያ ልጆች ጋር እንጂ፡፡ እነዚህ የነፃነት አርበኛ ውድ የኢትዮጵያ ወጣቶች ትምህርታቸውን፣ ስራቸውን፣ ስልጣናቸውን፣ ትዳራቸውን፣ አንዳንዶቹ ልጆቻቸውን… ባጠቃላይ የተደላደለ ኑሯቸውን ትተው ከአገርቤት፣ ከአውሮፓና ከአሜሪካ ወደ በረሃ የወረዱት ለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት ሲሉ ብቻ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት፣ ነፃነት፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ሲባል ክቡር ህይወታቸውን ዋጋ ለመክፈል ተዘጋጅተው በሃሩር እየነደዱ ቁራሽ ቂጣ አሸዋና ጭቃ በተቀላቀለበት ድፍርስ ውሃ አወራርደው ከዘንዶ፣ እባብና ጊንጥ ጋር እየታገሉ ውለው የሚያድሩ ናቸው፡፡ ዛሬ የዋጣቸውን ጥቅጥቅ ጨለማ ሳይሆን ከተራራው ወዲያ ከአድማስ ማዶ የምትታየውን፣ የነፃነት ጎህ የቀደደባትን፣ የነገዋን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ አሻግረው እዕምሯቸው ውስጥ በሚገኙ ትልልቅ ዓይኖቻቸው እየተመለከቱ መንፈሳቸው በፅናት የተሞላና ነብሳቸው በፍስሃ የተጥለቀለቀች ታሪክ ለመስራት የሚሻሙ ሀዋሪያዎች ናቸው፡፡ ከግማሽ ምዕተ ዓመታት በላይ ሲንከባለል የመጣ የህዝብ የነፃነት ጥያቄ ከትከሻቸው ላይ ያረፈ ለህዝብ ሲባል ልክ አንደ ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ሞትን ገጥመው ያሸነፉ የዚህ ትውልድ አካል ናቸው፡፡
ስልጣን ፈላጊነት፣ ማናቸውም ቁሳዊ ፍላጎቶችና ልክ እንደ ደደቢቱ ህ.ወ.ሓ.ት ከህዝብ የተደበቀ ስውር ዓላማ ፈፅሞ የሌላቸው አልፋና ኦሜጋ የሆነ ታሪክ በደማቸው ለመፃፍ ከሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ተፈጥረው በአንድ ዓላማ ዙሪያ በመሰባሰብ በአንድነት የቆሙ ንፁህና ጭቁን የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ ይሄንን እውነት የኤርትራ በረሃ ተራሮች፣ በአፅም ስብርባሪ የዳበረው አፈር፣ ሳር ቅጠሉ ጭምር አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ስልጣንና ቁሳዊ ፍላጎት ያለው ኢትዮጵያ ውስጥ እንጂ በኤርትራ በረሃዎች ውስጥ አይደለም፡፡ ስልጣንና ገንዘብ ለማግኘት የሚያስፈልገው ህሊናን ሸጦ ከወያኔ መጠጋት እንጂ በረሃ ወርዶ አፈር ላይ መተኛት አይደለም፡፡ ይህ ከበረዶ የነጣ ሀቅ ደግሞ ነገ በተግባር ይገለፃል፡፡

ጉዞአችን ወደ ነፃነት ነው!! መዳረሻችንም የነፃነት አደባባይ ብቻ ነው!!

አለማችን አንባገነን ስታስተናግድ ወያኔ የመጀመሪያው አይደለም። ዘረኛንም እንዲሁ …….. እኛም ስለነፃነት ብለን ለትግል ሰንነሳ የመጀመሪያዎቹ አይደለንም …… አለማችን እንደየዘመኑና እንደ የወቅቱ አንባገነኖች ያለ የሌለ የመሳሪያና ወታደራዊ ሀይላቸውን በመጠቀም ህዝብን በፍርሀት አሸማቀውና ረግጠው ለመግዛት ሲውተረተሩ በተደጋጋሚ ታይተዋል። በዚያው ልክ ህዝባዊ ሀይልና መመከት ተስኗቸው ሲንኮታኮቱ በተደጋጋሚ የታየ ወደፊትም አናባገነኖች እስከተከሰቱ ድረስ በህዝባዊ ሀይል ተጠራርገው መቀመቅ ሲወርዱ መታየቱ አይቀሬ ነው ። ህዝብ የወደደውን አስተዳዳሪ እንጂ ረግጦ ሊገዛው የሚፈልገውና አንባገነን ተቀብሎ አያውቅም ፤ዛሬም አልተቀበለም ፤ ነገም አይቀበልም ። ይህን በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ በተደጋጋሚና በጉልህ የሚታይ ግዙፍ እውነት መቼም ተቀብለውና ከታሪክ ተምረው ስለማያውቁ አሳፋሪው ውድቀታቸው በተደጋጋሚ ሲታይ አለ።

ሀገራችን የአለማችን አካል እንደመሆኗ አንባገነኖች ተፈራርቀውባታል። አንባገነኖችም በህዝባዊ ሀይል ተጠራርገውባ ታል። ከደቡብ አፍሪካ ቀጥሎ ትልቅ ወታደራዊ ሀይል የነበረው የትናንቱ ደርግ እንደ እንቧይ ካብ ሲናድ ተመልክተናል። አንባገነኖችመናገር እንጂ መስማት የማ ችሉ፤ ማየት እንጂ ማስተዋል የተሳናቸው በመሆናቸው እነሆ ዛሬም የወያኔ ዘረኛው ቡድን ህዝባ ላነሳው የነፃነትና የፍትህ ጥያቄ ያለ የሌለውን ወታደራዊ ሀይል በጠራራ ጸሀይ በማሰለፍ መቼውንም ያልተቻለ ውን ህዝብን በሀይል አሸማቆ ለመግዛት መከራውን ሲያይ ይስተዋላል። ለዚህም ነው ….. ከሌላው የሀገራችን ክልሎች ከፍ ባለ ሁኔታ የህዝባዊ እንቢተኝነት እየታየ ባለበት ጎንደርና አካባቢው በሰራዊት ማጥለቅለቅ የተያያዘው።

ለሚነሱ ህዝባዊ ተቃውሞዎችና ህዝባዊ የመብት ጥያቄዎች የሚሰጡት ምላሾች እስር፤ አፈናና ግድያ ከሆነ ህዝባዊ እንቢተኝነትን ማስከተሉ አይቀሬ ነው። በእስር ፤በአፈናና በግድያ እንዲሁም በሰራዊት ሀይል ህዝብን በማሸማቀቅ በስልጣን መቆየት የሚቻል ቢሆን ደርግም ከቤተ-መንግስት ባልወጣ፤ ወያኔም ዛሬ ከቤተ-መንግስቱ ባልተንፈልለሰ ነበር። ይህ ደግሞ ሊያስተምር በተገባ ነበር።

እስከ ዛሬ የትኛውም አንባገነን ስርአት በሚተማመንበት የወታደራዊ ሀይል አማካይነት የመንኮታኮቻቸውን ሰአት በአንድ ሰኮንድ ማዘግየት የቻለ እንደሌለ ሁሉ ወያኔም ያለ የሌለውን ወታደራዊ ሀይል ሲያርመሰምስ ውሎ ቢያድር ውድ ቀቱን በአንድ ሰኮንድ ማዘግየት እንደማይችል በተለይ እንቢ ለነፃነቴ፤ እንቢ ለሀገሬ… ብለን ለትግል የተነሳን ሀይሎች በመረ ዳት፤ ይበልጡኑ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተቀጣጠለ ያለውን ህዝባዊ እንቢተኝነት ይበልጥ እያሰፋን የጀመርነውን የነፃነት ጉዞ ከነፃነታችን አደባባይ ለማድረስ ሌት ተቀን የመስራት ሀላፊነታችናና መወጣት ይገባናል።

በጎንደር የሚታየውን የአልገዛም ባይነት ትንቅንቅ በሌሎች ክልሎችም በማቀጣጠል፤ በደብረወርቅ የታየውን የመምህራን የስራ ማቆም አድማ ወደ ሌሎች አካባቢዎች በማስፋት፤ እንደ ድምፃችን ይሰማ ሁሉ ተቃውሞን ወደ እንቢተኝነት በማሸጋ ገር …… ወዘተ የነፃነታችንን ቀን ለማቅረብ መከፈል የሚገባውን መክፈል ይገባናል።

Monday, March 23, 2015

DCESON Press release

Press release DCESON has arranged a public meeting and fundraising event on April 18, 2015 from 15 pm to 22 pm, Come and contribute your share to the HULEGEB TIGEL for freedom and democracy.

Let’s support ultimate struggle for building democratic system in Ethiopia.

There was no reign or rule in the history of Ethiopia like the rule of Wayne under which Ethiopians humiliated, undignified, undermined and lost their identity. At present the fundamental trouble of Ethiopia and its citizen is not just an abridgment or depletion of basic democratic and human rights but also the sovereignty of the country is under great danger to continue or prevail as a unified country.

In consequence, our freedom fighters are sacrificing their lives to the freedom of our people and emancipate our country from the imposed danger. For the reason democratic change in Ethiopia support organization Norway will hold grand public meeting and supporting program on April 18 205. Therefore we kindly request all Ethiopians who live in Norway to take part or share by accomplishing all necessary supports and contributions to this historical event. You are invited to the event and requested to invite friends, families and others to the event.

Ethiopia and its citizens have never been endangered and humiliated as under the rule of the woyane junta. The current problem of the country and its people is not only a question of lack of basic human rights, but it is a matter of life and death to the people and existence of Ethiopia as a sovereign country.

ህዳሴም ሆነ ዉዳሴ ክህዝብ የሚደበቅ ምንም ነገር የለም!

ከሰሞኑ አገራችን ኢትዮጵያን በተለይም ብሄራዊ ጥቅሟንና ደህንነቷን በተመለከተ ሁለት አቢይ ዜናዎች የአገራቸን የኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ጉዳዮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸዉን አገሮች የአየር ሞገደች ተቆጣጥረዉት ነበር። ከእነዚህ ዜናዎች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ኢትዮጵያ፤ ሱዳንና ግብፅ የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ ስምምነት ላይ ደረሱ የሚል ዜና ሲሆን ሁለተኛዉ ደግሞ አለም አቀፍ ጋዜጠኞች የህዳሴዉ ግድብ የሚሰራበት ቦታ ድረስ ሄደዉ ባካሄዱት ጥናት መሠረት የህዳሴዉ ግድብ ፕሮጀክት ባጋጠመዉ ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት የተነሳ እንዲዘገይ መወሰኑን የሚያወሳ ዜና ነዉ። አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለሚሰሩ ምንም አይነት ስራዎችና በኢትዮጵያ ህዝብ ስም ከየትኛዉም አገር መንግስትና መንግስታዊ ካልሆነ ተቋም ጋር ለሚደረጉ ስምምነቶችና ዉሎች ሁሉ ባለቤቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ነዉ ብሎ ያምናል፤ ስለሆነም አርበኞች ግንቦት ሰባት የኢትዮጵያን ህዝብ ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት ከሚመለከቱና በሚስጢር መጠበቅ አለባቸዉ ተብሎ ከሚታመኑ አንዳንድ ጉዳዮች ዉጭ ሌላ ምንም ስራ ወይም አለም አቀፍ ስምምነትና ዉል የኢትዮጵያ ህዝብ ሳያዉቀዉና ሳይሰማዉ በድብቅ መደረግ የለበትም የሚል የጸና እምነት አለዉ። ሆኖም ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ አገዛዝ ኢትዮጵያን ከቅኝ ገዢዎች በከፋ መልኩ የሚገዛ የጥቁር ፋሺስቶች አገዛዝ በመሆኑ የሚሰራቸዉ ስራዎችና በአለም አቀፍ ደረጃ የሚፈርማቸዉ ዉሎችና ስምምነቶች የኢትዮጵያን ህዝብ ብሄራዊ ጥቅም የሚጻረሩና የሚጋፉ ድብቅ ስምምነቶች ናቸዉ።

ይህ የወያኔ መሪዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ ጀርባ ላይ ተሸሽገዉ የሚሸርቡት የድብብቆሽ ሴራ ዛሬ የተጀመረ አዲስ ክስተት አይደለም። ባለራዕዩ መሪ የሚል አላስፈላጊ የቅጽል ስም የተሰጠዉ መለስ ዜናዊ በ2004 ዓም ሐምሌ ላይ ከዚህ አለም በሞት ሲለይ ዜናዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተነገረዉ በነኀሴ ወር ማለቂያ ላይ ነበር እሱም ቢሆን ሞትን ያክል ነገር ደብቆ ማቆየት ስለማይቻል ነዉ እንጂ አይነግሩንም ነበር። ከዚህ በተጨማሪ በሰሜናዊዉ የአገራችን ከፍል ወያኔ ከጎረቤት አገር ጋር የተዋዋለዉ መሬት ቆርሶ የመስጠት ዉል የኢትዮጵያ ህዝብ ሳያዉቀዉና ሳይሰማዉ የተደረገ ዉል ወይም ስምምነት ነዉ።

አርበኞች ግንቦት ሰባት አገራችን ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ብቻ ሳይሆን ከግዛቷ ተነስተዉ ወደ ጎረቤት አገሮች በሚፈሱ አለም አቀፍ ወንዞቿና በሌሎችም የአገር ዉስጥ ወንዞቿ ላይ ግደብ የመስራት ማንም ሊጋፋዉ የማይገባ የተፈጥሮ መብት አላት ብሎ ያምናል። በሌላ በኩል ደግሞ አባይን በመሳሰሉ ድንበር ዘለል ወንዞች ላይ የሚሰሩ ምንም አይነት የልማት ፕሮጀክቶች በዛቻና በማንአለብኝነት ሳይሆን በመግባባት፤ በመመካከርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን በሚያዳብሩ መልኩ መሰራት አለባቸዉ ብሎም ያምናል። አርበኞች ግንቦት ሰባት ይህንን የሚለዉ ደግሞ መሠረታዊ ኑሯቸዉ በአባይ ወንዝ ላይ አገሮች ሊያደርሱ የሚችሉትን የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ጫና በመፍራት ሳይሆን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች ከመጀመራቸዉ በፊት ፕሮጀክቶቹን አስመልክቶ ሊነሱ የሚችሉ ዋና ዋና ልዩነቶች መወገድ አለባቸዉ፤ ልዩነቶችን ለማስወገድ ደግሞ የተሻለና አዋጭ የሆነዉ አማራጭ ዲፕሎማሲ ነዉ የሚል ጽኑ አምነት ስላለን በቻ ነዉ።

የወያኔ አገዛዝ እንደ ፈረንጆቹ ዘመን አቆጣጠር በ2011 ዓም የህዳሴዉን ግድብ ስራ ሲጀምር ከአራት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ዶላር ወይም 96 ቢሊዮን ብር በላይ የተገመተዉ ግዙፍ ግድብ ስራ ሙሉ በሙሉ ከአገር ዉስጥ የገንዘብ ምንጮች በሚገኝ ገንዘብ እንደሚሰራና አገዛዙ ግድቡንና የግድቡን ስራ አስመልክቶ ምንም አይነት ድርድር ከማንም አገር ጋር እንደማያደርግ ለለህዝብ ቃል ገብቶ ነበር። የግድቡ ስራ በተጀመረ በጥቂት አመታት ዉስጥ የግድቡ ግንባታ የአገሪቱን የካፒታል ጥሪት ሙጢጥ አድርጎ በመብላቱና በሌሎች በተጀመሩና ሊጀመሩ በእቅድ በተያዙ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ በግልጽ የሚታይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማድረግ በመጀመሩ አለም ባንክ፤ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትና አያሌ ኢትዮጵያዉያን ምሁራን የግድቡ ስራና ግድቡ ላይ የሚፈሰዉ የካፒታል ብዛት እንደገና እንዲታሰብበት ምክር ለግሰዉ ነበር፤ ሆኖም ምክሩ የተሰጠዉ የሚሰማ ጆሮ ለሌለዉ ለወያኔ ነበርና ሰሚ ታጣ። ዛሬ ግድቡ ከተጀመረና ወያኔም በህዳሴዉ ግድብ ላይ ከምንም ከማንም አልደራደርም ካለ ከአራት አመታት በኋላ አንደኛ የግድቡ ፕሮጀክት ስራ በገንዘብ እጥረት የተነሳ እንዲዘገይ ተደርጓል፤ ሁለተኛ ወያኔ የህዳሴዉን ገድብ አስመልክቶ ከግብፅና ከሱዳን መንግስታት ጋር ስምምነት ላይ ደርሶ የፊታችን መጋቢት 14 ቀን ስምምነቱን ለመፈረም ጎንበስ ቀና እያለ ነዉ።

ለመሆኑ ይህ ወያኔ ከሱዳንና ከግብፅ ጋር የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ የሚፈራረመዉ የስምምነት ዉሳኔ ይዘት ምንድነዉ? ዉሳኔዉ በሦስቱ አገር መሪዎች ፊርማ ከመፅደቁ በፊት ለምንድነዉ የዉሳኔዉ ባለቤት የሆነዉ የኢትዮጳያ ህዝብ እንዲያዉቀዉ ያልተደረገዉ? ባለፉት አራት አመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ ምንም አይነት ገቢ ከሌላቸዉ ከተማሪዎችና ከአረጋዉያን ጀምሮ እስከ ቀን ሰራተኛዉ ድረስ ለህዳሴዉ ግድብ ግንባታ ገንዘብ አዋጣ ወይም ቦንድ ግዛ እየተባለ በሩ ያልተንኳኳ ኢትዮጵያዊ የለም። ታዲያ ይህ የኢትዮጵያ ህዝብ በራሱ ገንዘብ ለዕድገቴና ለብልፅግናዬ መሠረት ይሆነኛል ብሎ የሚያሰራዉ ግድብ ስራዉ በገንዘብ እጥረት ሲተጓጎልና በዚሁ ግድብ ዙሪያ ከዉጭ መንግስታት ጋር አለም አቀፍ ስምምነቶች ሲደረጉ ምንም የማይነገረዉ ለምንድነዉ?

የወያኔ መሪዎች ከሱዳንና ከግብጽ መሪዎች ጋር የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ የተዋዋሉትን ዉል እንመራዋለን ብለዉ ከሚናገሩት ህዝብ ቢደብቁም ካርቱምና ካይሮ ወስጥ ሾልከዉ የወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ግብፅ የህዳሴዉ ግደብ ፕሮጀክት ላይ የቁጥጥርና የማነጅመንት ድርሻ አንደሚኖራት እየተነገረ ነዉ።እንደዚህ አይነቶቹ ከዚህ ቀደም በፍጹም የማይሞከሩ ወይም የማይታሰቡ ናቸዉ ተብለዉ ሲነገሩ የነበሩ ስምምነቶችና ዉሎች ዛሬ ተደርገዉና የሶስትዮሽ ስምምነት ተደርሶባቸዉ በፊርማ የሚጸድቁት ግድቡን ሰርቶ ለመጨረስ የሚያስፈልግ ገንዘብ ለማግኘት ነዉ ወይስ ሌላ ድብቅ አላማ አለዉ? ደግሞስ ግድቡ የሚሰራዉ ለህዝብ ግድቡን የሚሰራዉም ህዝብ ሆኖ ሳለ ለምንድነዉ ይህ በዉድም በግድም ገንዘብ ካላዋጣህ ወይም ቦንድ ካልገዛህ እየተባለ ቀንና ማታ ሲጠየቅ የኖረ ህዝብ በዚህ ግድብ ዙሪያ የሚደረጉ ዉሎችንና ስምምነቶችን እንዳያዉቅና ጭራሽ እንዳይሰማ የተደረገዉ? ካይሮና ካርቱም ዉስጥ እንደሚነገረዉ ግብፅ በህዳሴዉ ግድብ ግንባታ ዙሪያ የማነጅመንትና የቁጥጥር ሚና ይኖራታል የተባለዉ ዜና እዉነት ከሆነ እኛ እራሳችን አገራችን ዉስጥ በምንሰራዉ ግድብ ግብፅ ሊኖራት የሚችለዉ የማነጅመንትና ቁጥጥር ድርሻ ዬት ድረስ ነዉ የሚሆነዉ …ለምንስ እንዲህ አይነት ሚና እንዲኖራት ተደረገ?

Thursday, March 19, 2015

መንገዶች ሁሉ ወደበርሃ ያደርሳሉ!

ወያኔ ኢህአዴግ 24 አመታት ሊሞላው እነሆ የሁለት ወራት ገደማ አድሜ ብቻ ቀረው፡፡ ጉድ!!!!! 24 ዓመታት!!!!!


  • 24 የባርነት፡ የውርደት፡ የሰቆቃ፡ የመከራ፡ የፍዳ፡ የስደት፡ የዕልቂት… ዓመታት
  • 24 የርሃብ፡ የጥማት፡ እርዛት፡ የችጋር፡ ጉስቁልና… ዓመታት
  • 24 የመበታተን፡ የጥላቻ፡ ቂም በቀል… ዓመታት
  • 24 የፍርሃት ዓመታት


በእነዚ 24 ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ከላይ ለተዘረዘረው ችግር ሁሉ ምንጭ የሆነው ወያኔ-ኢህአዴግ በጉልበቱ የቀማውን ሉኣላዊ የስልጣን ባለቤትነቱን ለማስመለስ ትግል አካሂዷል፡፡ በዚህም ምክንያት እልፍ አዕላፎች ወደ ወህኒ ተግዘዋል፤ በርካቶች የሚወዷት አገራቸውን ጥለው ተሰድደዋል፤ ብዙዎች ከቀያቸውና ቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል፤ ስፍር ቁጥ የሌላቸው አካላቸው ጎድሏል መንፈሳቸው ተመርዟል፤ አለፍ ሲልም ህልቆ መሳፍርቶች ውድ ህይወታቸውን ከፍለዋል…

ከወያኔ-ኢህአዴግ ጋር የተደረጉት ልዩ ልዩ ትግሎች በአብዛኛው በሰላማዊ ትግል ስልቶች ማዕቀፍ ውስጥ ሊካተቱ የሚችሉ ብቻ ናቸው፡፡ በተጨሚሪም ተመጣጣኝ ባለመሆናቸው የሚፈለገውን ስር ነቀል ለውጥ በሚፈለገው ጊዜ ለማምጣት የሚያስችሉ አልነበሩም፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያን ህዝብ ዋጋ ብቻ እያስከፈሉ ኢትዮጵያ ልትወጣው ትችል ከማትመስልበት በእሳተ ገሞራ የቀለጠ አለት ከሚፈልቅበት የፖለቲካዊ፡ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሸለቆ ውስጥ ተወርውራ ከገባችበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡

አዎ ብዕራቸውን አንስተው በነፃው ፕረስ ትግል ሜዳ ገብተው የተፋለሙ የዘላለም ጀግኖች ናቸው፤ ነገር ግን ወያኔ በብዕር ሳይሆን በጠብመንጃ አረር ሲያነዳቸው ሳይወዱ በግድ በረሃ ወርደዋል፡፡

አዎ ፓርቲ መስርተው ወደምኒልክ ቤተ መንግስተ በታንክ የገባውን ወያኔ በካርድ አናስወጣዋለን ብለው የታገሉ ዛሬም የሚታገሉ ብፁዓን ናቸው፤ ነገር ግን ወያኔ በካርድ ሳይሆን በክላሽን ኮቭ የእሳት ሰደድ ሲያራውጣቸው የታሰሩት ታስረው የሞቱት ሞተው የቀሩት ደግሞ ጫካ ገብተዋል፡፡

ማህበር አቋቁመው ባንድነት ለመታገል የቆረጡ እጅግ ፅኑዎች ናቸው፤ ነገር ግን ወያኔ በመርዛም አስለቃሽ ጭስ በታትኗቸው ዛሬ ተራሮችን እየማሱ ዋሻ ውስጥ ሆኗል ቤታቸው፡፡

አዎ እውነት ነው! ዛሬ ሁሉም የሰላማዊ ትግል አማራጭ በሮች በታላቅ የብረት በር ክርችም ብለው ተዘግተው በጉዋጉንቸር መቆለፋቸው ለሁሉም ሰው ግልፅ ነው፤ ነገር ግን ሁሉም የሰላማዊ ትግል መንገዶች የመጨረሻ መዳረሻቸው በረሃ መሆኑን ሁሉም ሰው በጊዜ ሊገነዘበው ይገባል፡፡

ተቀላቀሉን፤ ካልሆነም በያላችሁት ተደራጁ!

ህወሓት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ስለሚያደርሰው ዘርፈ ብዙ በደል ብዙ የተነገረለትና የተፃፈበት ብቻ ሳይሆን እየኖርንበት ያለ ሀቅ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብም የሚደርስበትን ስቃይ መታገስ ወደማይችልበት ጫፍ መድረሱ በሰበብ አስባቡ በሚፈነዳዱ ተቃውሞዎች የሚታይ ሀቅ ሆኗል።

በሌሎች አገሮች እንዲህ ዓይነት የሕዝብ ምሬት ሲኖር በጥቂት ግለሰቦችና ቡድኖች ጥሪ ሕዝብ ግልብጥ ብሎ አደባባይ ይወጣል። ከሕዝብ አብራክ የወጣው ጦር ሠራዊትና ፓሊስ ከተበደለው ሕዝብ ጎን በመቆም አምባገነኖችን አስወግዶ የሽግግር መንግሥት ያቆማል። በቅርብ ጊዜያት በሕዝባዊ እምቢተኝነት መንግሥት በተቀየረባቸው አገሮች ያየነው እንደዚህ ዓይነቱን ሀቅ ነዉ።

አገራችን ውስጥ ያለው ሁኔታ ግን ከዚህ በእጅጉ ይለያል። ህወሓት ኢትዮጵያ ውስጥ የገነባው የጦርና የፓሊስ ሠራዊት አመራር በዘር የተደራጀ በመሆኑ የሕዝቡን አጠቃላይ ብሶት ደግፎ ሊቆም ይችላል ብሎ መጠበቅ አይቻልም። ሠራዊቱ እንደ ተቋም ከተበደለው ሕዝብ ጎን እንዲቆም በመጀመሪያ በራሱ በሠራዊቱ ውስጥ ሥር ነቀል ለውጥ መካሄድ አለበት።በዚህ አቅጣጫ የሚሠሩ ሥራዎች እንደተጠበቁ ሆነው፤ ሠራዊቱ ዘረኛ ገዢዎቹን አስወግዶ እስኪመጣ መጠበቅ አይቻልም፣ አይገባምም። በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ፣ ሕዝባዊ እምቢተኝነት በሕዝባዊ አመጽ መታገዝ አለበት የሚለው ሁለገብ የትግል የትግል ስትራቴጂ ተመራጭ እንዲሆን ያደረገው ዋነኛ ምክንያት የሠራዊቱ ዘረኛ አወቃቀር ነው። በመረጥነው የትግል ስትራቴጂ መሠረት በሁለቱም ግንባሮች – ማለትም፣ በሕዝባዊ አመጽ እና በሕዝባዊ እምቢተኝነት ግንባሮች ሥራዎች መሠራት አለባቸው። ሁለገብ የትግል ስትራቴጂ እምንፈልገው ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ላይ እንዲያደርሰን የኢትዮጵያ ሕዝብ በሁለቱም የትግል ስትራቴጂዎች አኳያ መደራጀት ይኖርበታል። ሕዝባዊ የአርበኛ ሠራዊት ማደራጀት እንደሚያስፈልግ ሁሉ በኢትዮጵያከተሞችና ገጠሮች፤ በሥራና በመኖሪያ አካባቢዎች በምስጢር የተደራጁ ሕዝባዊ የአርበኛ ሲቪል ክበቦችም በብዛት መደራጀት ይኖርባቸዋል።

በዚህም ምክንያት አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ከህወሓት ዘረኛ ፋሽስታዊ አገዛዝ ነፃ ለመውጣት የሚመኝ ኢትዮጵያዊ ሁሉ እንዲደራጅ ጥሪ ያቀርባል! እያንዳንዱ ነፃነት ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ከሚያምነውና ከሚመስለው ወዳጁ ጋር ይቧደን፤ ቡድኑንም በሥርዓትና በሚስጢር ያደራጅ።

ከእንግዲህ “ምን እንሥራ? ትግሉን እንዴት እንርዳ?” እያሉ ለሚጠይቁ ወገኖቻችን በሙሉ መልሳችን “ከቻላችሁ ተቀላቀሉን፤ ካልሆነም በያላችሁት ተደራጁ” የሚል ነው። ድርጅት ኃይል ነው። መደራጀት በራሱ ትልቅ ሥራ ነው። ድርጅት ድርጅት የሚሆነው ደግሞ በሥርዓት ሲዋቀርና በሥነሥርዓት ሲመራ ነው። ስለሆነም ነፃነት ናፋቂ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሌላ አደራጅና አስተባባሪ እንዲመጣለት ሳይጠብቅ በራስ አነሳሽነት እንዲደራጅ ይህ ጥሪ ተላልፏል።

በሥርዓት የተደራጀ ስብስብ ሲኖር የሚሠራ ሞልቷል። ይህንን መንገርም አያስፈልግም። የተደራጀ ስብስብ ራሱ ሥራዎችን አቅዶ መሥራትም ይችላል። የሚከተሉት ነጥቦች ለአብነት ተዘርዝረዋል።

Monday, March 16, 2015

Ethiopia denies Temesghen Desalegn access to medical care in jail

Nairobi, March 16, 2015

Authorities in Ethiopia have denied medical attention to Ethiopian journalist Temesghen Desalegn, who has been imprisoned since October, according to sources close to the journalist.

Temesghen Desalegn, owner of the now-defunct newsmagazine Feteh (Justice), is serving a three-year term in Ziway Prison, outside Addis Ababa, on charges of defamation, incitement, and false publication in connection with a series of opinion pieces he wrote in Feteh in 2012, according to news reports and a translation of the charge sheet that CPJ reviewed.

Sources close to Temesghen, including two who visit him in prison, told CPJ that Temesghen suffers from stomach and back pain for which he used to receive weekly medical support before he was jailed. The sources said that Temesghen has been denied medical access since he was imprisoned and that his back pain has worsened to the point that walking is difficult for him.

The African Charter on Human and People's Rights, to which Ethiopia is a signatory, states that authorities are obligated to ensure that its citizens receive medical attention when necessary.
CPJ's calls to the Ethiopian justice ministry in Addis Ababa, and CPJ's calls and emails to the Ethiopian embassy in Washington, were not answered.

Earlier this year, prison authorities denied Temesghen prison visits from friends and family for more than a month, according to a public letter by Temesghen's mother, Fanaye Irdachew. Authorities did not provide an explanation, but local journalists told CPJ they suspected Temesghen had been denied prison visits after an article he wrote from prison was published in several Ethiopia news websites. The articles detailed the mistreatment of prisoners at Ziway Prison.

Temesghen often criticized the authorities in his articles. In 2012, he wrote two articles that discussed the peaceful struggles of Ethiopian youth movements for political change, according to the charge sheet that CPJ reviewed. He also wrote two columns that criticized alleged government efforts to violently suppress student protesters and ethnic minorities reviewed.

ልዩነታችን ጌጣችን፤ አንድነታችን ህልውናችን ነው

ኢትዮጵያ ስንል ብዙ የተለያዩ ዘውጎች፤ ብዙ የተለያዩ ቋነወቋዎችና ሀይማኖቶች በአንድነት ይዛና አስተሳስራ ብዙ ፈተ ናዎችን በማለፍ ለረጅም ዘመናት ህልውናዋን ጠብቃ የቆየች ሀገር መሆንዋ መታወቂያዋ ሀገር ማለት ነው። እንዳ ሳለ ፈችው ረጅም ዘመናት ሁሉ እንደየዘመኑ በህልውናዋ ላይ ይቃጣ የነበረውን ጥቃት እነዚያ በዘውጎች፤ በቋነወቋዎችና ሀይ ማኖቶች የተንቆጠቆጡት ልጆችዋ በአንድነት በመሰለፍ ብሎም ድል በመምታት ህልውናዋን አስጠብቀው መዝለቃቸው የነጻነት ሀገር የመሆን መለያዋ ምክንያቶች መሆናቸውንም የሚያሳይ ነው።

ይህ ልዩነታችንን ጌጡ አድርጎ ያስተሳሰረን ኢትዮጵያዊነት በነፃነት የዘለቀ ህዝብ ከማድረግ አልፎ በአንድ ወቅት የስልጣኔ ምንጭና የአለማችን ሀያል ህዝብ ከመሆን ጫፍ አድርሶን እንደነበር አይዘነጋም። በዚያው ልክ ይህ በልዩነታችን ላይ የተገነባ አንድነታችን ሲላላ ህልውናችን ከገደል አፋፍ ላይ የደረሰበት ዘመንም በታሪካችን ውስጥ መታየቱ አልቀረም። “ዘመነ-መሳፍንት” በመባል የሚታወቀው ጥቁር የታሪካችን ክፍል አንዱ ተጠቃሽ ሲሆን ሌላው ዛሬ የምንገኝበት የወያኔ ዘረኛ ዘመን ነው። ትናንት በዘመነ መሳፍንት ህልውናችን አደጋ ላይ ወድቆ ነበር፤ ዛሬም በወያኔ ዘረኞች ዘመን ህልውናችን ከከፋ አደጋ ላይ እንዲገኝ ተደርጓል። በአጭሩ ልዩነታችን ጌጣችን አንድነታችን ደግሞ የህልውናችን ማስጠበቂያ ዋነኛው ቁልፍ መሆኑን መገንዘብ ለማናም አያዳግትም።

ሌላው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በታሪካችን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ በህልውናችው ላይ የከፋ አደጋ ያንዣበበት ወቅት ላይ መገኘታቸው ከማንም የተሰወረ አይደለም። ዘመነ መሳፍንት ትናንት ቋንቋ ዘውግና ሀይማኖት ሳይለይ በእያንዳዱ ኢትዮጵያዊ ህይወት ላይ አስከትሎት የነበረውን ችግርና በሀገሪቱም ከአዘቅት የከተተ ከመሆኑም በላይ ይኸው እስከዛሬ ድረስ ውደ ቀድሞ ታላቅነቷ ለመመለስ ከባድ መሰናክል ተክሎ ማለፉን ከትናንት ታሪካችን መረዳት እየተቻለ ዛሬ በእኛ ዘመን ዳግም ከትናንቱ የከፋ ጥልቅ አዘቅት ውስጥእንድንፈቅ በዘረኞች እየተገፋን መሆኑንና ሊያስከትል የሚችለውንም ውጤት ለመረዳት የተለየ እውቀት አይፈልግም። ዛሬ ይህ ልዩነትን እያጎሉና ቂም በቀልን እየዘሩ መጓዛ የጥቂቶች ፍላጎት መሆኑ ባይካድም ከዚህ ቀደም ያስከተለውንና ዛሬም እየታየ ያለውን አደጋ ተገንዝቦ ከወዲሁ መከላከል የእያንዳዳችን ሀላፊነት ሊሆን ይገባል።

ጥቂቶች የህዝብ አሳቢ በመምሰል የሚረጩት የልዩነት መርዝ በሌሎች ሀገራት ላይ ያስከተለውን ፈተናም እንዲሁ ቆ ም ብሎ መፈተሽና ውጤቱንም መመዘን የፈሰሰ ውሀን አፋሽ ከመሆን ማዳኑን መጠራጠር የለብንም። የሶቭየት ህብረት መ ፍረስ፤ የዩጎዝላቪያ እርስ በርስ መባላት፤ የሶማልያ መቋጫ ያጣ ትርምስ ……. ወዘተ ንፁሀንን በገፍ የበላና ዜጎችን ለኢኮኖሚ ድ ቀት የዳረገ፤ በገፍ ስደትን ያስከተለ፤ የጦርነቶቹ መዘዝ ከልጅ ልጅ የማይታረቅ ቂም እያስቋጠረ መገኘቱ ሲታይ ዛሬ በእ ኛም ሀገር ጥቂት የመገንጠል አባዜ የተጠናወታቸው ይዘውን ሊጓዙ የሚፈልጉበትን መንገድ የት ሊያደርሰን እንደሚችል ከራ ሳችንም ያለፈ ታሪክ ሆነ በአለማችን ላይ የታዩ ክስተቶች ውጤት የሆነውን ትርምስና ሽብር በመመልከት ልንማርበትና ከወዲሁ አንድነታችንን በማጠናከር ለመከላከል መስራት ግድ ይለናል።

ከላይ እንደ ምሳሌ የተጠቀሱት ሀገራት በመበታተን ያተረፉተረ ሽብረ፤ ጦርነት፤ ስደትና ድህነት መሆኑ የታዘብነው የዘመናችን ክስተት ሲሆን ቀደም ሲል ለሁለት ተከፍላ የነበረችው ጀርመን ዳግም ከሁለትነት ወደ አንድነት መምጣቷዋ በሰጣት ሁለንተናዊ ጥንካሬ የዓለምችን ታላላቅና ሀብታም ሀገራት በኢኮኖሚ ውድቀት ሲመቱ ያለአንዳች ጭግር የፈተናውን ወቅት ያለፈች ሀገር ለመሆን መብቃትዋን ከአንድነት ሊገኝ የሚችለውን ሁለንተናዊ ጥንካሬ አጉልቶ የሚያሳይ ነው። ሌላው ከሀ ገራችን ህልውናን የማስጠበቅ ፍልሚያ ታሪኮች ውስጥ ጎላ ብሎ የሚታየው የአድዋ ጦርነትና ድል የአንድነትን ዋጋ ከፍ አድርጎ የሚያሳይ አኩሪ ታሪክ ነው። በዘመናዊ የጦር መሳሪያ ተማምኖ የመጣውን ወራሪ የኢጣልያ ጦር በተመጣጣኝ የጦር መሳሪበ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ ተማምኖ የመጣውን ወራሪ የኢጣልያ ጦር በተመጣጣኝ የጦር መሳሪያና የሰለጠነ ሰራዊት ሳይሆ ን ቋንቋ፤ ዘውግና ሀይማኖት ሳይለያቸው ሁሉም በአንድነት ለሀገራቸው ህልውናና ለነፃነታቸው በአንድነት በመቆማቸው የተ ገኘ ድል መሆኑም መዘንጋት የለበትም።

የነጻነት ትግሉን በየፈርጁ: ከዲሲ ግብረሃይል የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ የአንድነትና የዲሞክራሲ ሃይሎች በጠላት ጥቃት ደርሶባቸው ተጎድተው ተሸማቀው አንገታቸውን እንዲቀብሩ ሲገደዱ አድርባይ ሃይሎች በመድረኩ መቧረቃቸው የሚጠበቅ ነው፤ይህንን ጊዜያዊ ክስተት እንደ ዘላለማዊ ሃቅ የሚወስዱ ካሉ እጣ ክፍላቸው ተስፋ መቁረጥና ጨለምተኝነት ይሆናል። ከጨለማው ባሻገር የኮከቢቱን ብርሃን የሚያዩ ግን ለወያኔ ግፍ የማይበገሩ የሃቅን አሸናፊነት እና የኢትዮጵያን ትንሳኤ አይጠራጠሩም።

ሊነጋጋ ሲል ይጨልማል እንደሚባለው ዛሬ ወያኔ የተባለው መርገምት የጣር በትሩን በዘጠና ሚሊዮን ህዝብ ላይ እያሳረፈ ይገኛል፤ይህን የግፍ አገዛዝ ለመቋቋም ዜጋው ሁሉ እምቢኝ አልገዛም እያለ በሁሉም አቅጣጫ ሁሉንም የትግል አይነት ያልጀመረው ለመጀመር የጀመረው ለመቀጠል እየተሟሟቀ በሚገኝበት በአሁኑ ሰዓት ይህን ሃቅ እያዩ እንዳላዩ እየሰሙ እንዳልሰሙ የሚሆኑት ፍጥሮች ያለመንቃት መብታቸው የተጠበቀ ቢሆንም እኛ ግን ከተስፋው መቁረጥ አለም የሌለንበት ሁሉንም ጸረ ወያኔ ሃይላት የማበረታቻ ቃል ብቻ ሳይሆን አቅማችን የፈቀደውን ሁሉ ለመለገስ በያለንበት ዝግጁ መሆናችንን እንገልጻለን፤ዛሬ በሃገር ቤት ያሉ ተቃዋሚዎች፣ የመብት ጠያቂዎች፣ የድምጻችን ይሰማ ሚሊዮን ሙስሊሞች ሌሎችም ተጠቂ ዜጎች በሙሉ እያስገመገሙት ያለው ህዝባዊ እምቢተኝነት፤ በሌላው ፈርጅ ደግሞ ተምቹን የወያኔ ስርአት በብረት ለመፋለም ስልታቸው ያደረጉ የነጻነት ታጋዮች በሙሉ በየፈርጃቸው ይበርቱ እያልን እኛም በውጪው አለም በስደት ያለነው የዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል አባሎች ከኢትዮጵያ ውጪ ብንሆንም ኢትዮጵያ ግን ከኛ ውጪ አይደለችምና የበለጠ ለመትጋት ያለንን አቋም በኢትዮጵያ ስም ነው የምናረጋግጠው።

እኛ በተለያዩ የትግል ስልት በሚታገሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ስር ያለንና እንዲሁም በአገር ወዳድነት ስም በግልም የምንቀሳቀስ ከሌሎች የመብትና የፍትሕ ተቋሞች ጋር በጋራ እየሰራን ያለን ስንሆን በመጨረሻው ሰዓት ባለው ግፈኛ የወያኔ ስርዓት ላይ ትግሉን በማጧጧፍ ለእምቢተኝነቱ ትግል የአቅማችንን ሁሉ እያደረግን እንዳለን ስንገልጽ አበክረን የምንለው ነገር አለ፤ ለጋራ ሃገራችን ኢትዮጵያ፣ ለሁላችን ጠላት ከሆነው የወያኔ ስርዓት ለመገላገል ዋናው አብነቱ የታጋዮች ህብረት ነውና በማንኛውም አይነት የጸረ ወያኔው የትግል አምባ የተሰለፉት ሁሉ በየፈርጃቸው እንዲተባበሩ እና በጋራ እንዲሰሩ ስንል በትሕትና እንጠይቃለን።

Saturday, March 14, 2015

Freedom House 2015 Report: Ethiopia’s Status NOT FREE

Freedom in the World : Ethiopia

Overview:

In 2014 the Ethiopian government continued to suppress free speech and associational rights, shattering hopes for meaningful reform under Prime Minister Hailemariam Desalegn. Government harassment and arrest of prominent opposition and media members continued, including the April arrest of nine journalists who were charged under Ethiopia’s controversial antiterrorism law. In April and May, massive protests in Oromia Regional State broke out following the announcement of the planned expansion of Addis Ababa into Oromia. At least 17 people died after the military fired on unarmed protesters.

Despite nascent signs of an opening with Eritrea, formal dialogues remain frozen between the two countries. The Ethiopian-Eritrean border remains highly militarized, though no major border clashes were reported in 2014.

Sporadic violence resumed in Ethiopia’s Ogaden region after talks failed in 2013 between the government and the Ogaden National Liberation Front (ONLF), a separatist group that has fought for independence since 1991. In January 2014, two ONLF negotiators dispatched to Nairobi for a third round of talks were abducted and allegedly turned over to Ethiopian authorities by Kenyan police. The kidnappings effectively ended the talks.

Ethiopia ranked 32 out of 52 countries surveyed in the Ibrahim Index of African Governance, below the continental average and among the bottom in East Africa. The country’s modest gains in the index are due to its improvement in human development indicators, but its ranking is held back by low scores in the “Participation and Human Rights” category.
Political Rights and Civil Liberties:

Political Rights: 7 / 40 [Key]

A. Electoral Process: 1 / 12

Ethiopia’s bicameral parliament is made up of a 108-seat upper house, the House of Federation, and a 547-seat lower house, the House of People’s Representatives. The lower house is filled through popular elections, while the upper chamber is selected by the state legislatures; members of both houses serve five-year terms. The lower house selects the prime minister, who holds most executive power, and the president, a largely ceremonial figure who serves up to two six-year terms. Hailemariam has served as prime minister since September 2012, and Mulatu Teshome as president since October 2013.

The 2010 parliamentary and regional elections were tightly controlled by the ruling coalition party Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), with reports of voters being threatened with losing their jobs, homes, or government services if they failed to turn out for the EPRDF. Opposition party meetings were broken up, and candidates were threatened and detained. Opposition-aligned parties saw their 160-seat presence in parliament virtually disappear, with the EPRDF and its allies taking all but 2 of the 547 seats in the lower house. The next elections are scheduled for 2015.

Thursday, March 12, 2015

በህወሓት ላይ የሚቀርቡ ተቃውሞዎች ሁሉ ወደ እምቢተኝነት ይደጉ!

የኢትዮጵያ ሕዝብ በአለፉት 23 ዓመታት በህወሓት ዘረኛ አገዛዝ የደረሰበት ስቃይ እንዲቀንስ፤ ገዢዎቹ ከጫንቃው እንዲወዱ፤ ህወሓትን አውርዶ የሚፈልጋቸው መሪዎችን በነፃነት እንዲመርጥ ሲጠይቅና አቤቱታ ሲያሰማ ቆይቷል። በ1997 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሕዝብ ምኞት የሚሳካ መስሎ የታየ የነበረ ቢሆንም በአገዛዙ አረመኔዓዊ እርምጃ ተሰናክሏል። ከጥቂት ዓመታት ወዲህ “ድምፃችን ይሰማ” የሚሉ አቤታዎች ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች መምጣት ጀምሯል – “ድምፃችን ይሰማ ሙስሊሞች”፣ “ድምፃችን ይሰማ ኦርቶዶክሶች”፣ “ድምፃችን ይሰማ መምህራን”፣ “ድምፃችን ይሰማ ተማሪዎች”፣ … ወዘተ። በተለይ ሙስሊም ወገኖቻችን በተደራጀ መንገድ “ድምፃችን ይሰማ” እያሉ ሲወተውቱ ሦስት ተከታታይ ዓመታት አልፈዋል። ወገኖቻችን “ድምፃችን ይሰማ” በማለታቸው ተደብድበዋል፣ ታስረዋል፣ ተገድለዋል።

አቤቱታ የሚሰማ ጆሮ የሌለው አገዛዝ ሲገጥም ምን ይደረጋል? ለአቤቱታ አቅራቢው ያለው ምርጫ ከሁለት አንድ ነው። ወይ አቤቱታን እርግፍ አድርጎ ጥሎ በደልን ተቀብሎ “እህህ !” እያሉ መኖር፤ አሊያም “በቃኝ፣ እንቢ አልገዛም” ማለት፤ ሦስተኛ ምርጫ የለም።

አቤቱታ ሰሚ ሲያጣ እና ሕዝብ መሮት “እንቢኝ፣ አልገዛም” ሲል ነው ሕዝባዊ እምቢተኝነት ተቀሰቀሰ የሚባለው። ሕዝባዊ እምቢተኝነት ብዙ መልኮችና ቅርጾች ቢኖሩትም ዋነኛዎቹ መገለጫዎች ሁለት ናቸው። አገዛዙ ሕዝብ እንዲያደርግ የሚፈልገውን አለማድረግ እና/ወይም አገዛዙ ሕዝብ እንዲያደርግ የማይፈልገውን ማድረግ።

ለምሳሌ፣ አገዛዙ ሹማምንቱ እንዲከበሩ፣ ሕዝብ እንዲታዘዝላቸው ይፈልጋል፤ እንቢ ያለ ሕዝብ ግን የአገዛዙን ሹማምንት ይንቃል፣ በየደረሱት ያዋርዳቸዋል፣ “አልታዘዛችሁም” ይላቸዋል። ማንኛውም መንግስት የዳኝነት ሥርዓቱ እንዲከበርለት ይፈልጋል፤ በደል የመረረው ሕዝብ ግን የአምባገነኖች ችሎት ውሳኔ አይቀበልም፤ ዳኞችንም ዳኝነትንም አያከብርም። ሕዝብ የመንግሥትን ግብር በወቅቱ እንዲከፍል የማንኛውም መንግሥት ፍላጎት ነው። በመንግሥት ያመረረ ሕዝብ ግን ግብር አይከፍልም፤ መክፈል ግድ ከሆነበትም አዘግይቶ፣ አስለፍቶ ነው። የመረረው ሕዝብ ምሬቱን መፃፍ በሌለበት ቦታ ይጽፋል። በደል የበዛበት ሕዝብ “ዝም በል” ሲሉት ይናገራል፤ “ተናገር” ሲሉት ዝም ይላል።

አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ የሕዝባዊ እምቢተኝተኝነት እርምጃዎች ጅምሮች እየታዩ ነው። በአማራ ክልል፣ ሕዝብ በሹማምንት ላይ የራሱን እርምጃ መውሰድ ጀምሯል። ሕዝብ ራሱ የፓሊስንም የፍርድ ቤትንም ሥራ ተክቶ እየሠራ ነው። ይህ መበረታታት ያለበት ትልቅ እርምጃ ነው። እንደዚሁም ሁሉ በተለይ ወጣቶች ብሶቶቻቸውን በብር ኖቶች ላይ ጽፈው ገበያው እንዲያዘዋውራቸው እያደረጉ ነው። ይህም “የወረቀት ገንዘብን ለተሠራበት ዓላማ ብቻ ተጠቀሙ” የሚለውን ህግ በመጣስ ለቅስቀሳ ሥራ መጠቀም በመሆኑ የሕዝባዊ እምቢተኝነት አካል ነው። በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ በርካታ የወረቀት ገንዘቦች በምሬት መግለጫነት ይውላሉ ተብሎ ይገመታል።

በተጓዳኝ በርካታ አማራጭ ስልቶች ሥራ ላይ መዋል ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ ተቀማጭ ገንዘብን ከህወሓት ባንኮች ማውጣት በቀላሉ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል ስልት ነው። በውጋጋን ባንክ ተጀምሮ ወደ አንበሳ ኢንተርናሽናል ከዚያም ወደ ንግድ ባንክ ማሸጋገር ይቻላል።

Monday, March 9, 2015

የኢትዮጵያ ጠላት ወያኔ – ወያኔ ብቻ ነዉ!

ባለፈዉ ሳምንት አይጋፎረም የሚባለዉና የወያኔን ቱልቱላ በዉጭ አገሮች የሚያናፍሰዉ ድረገጽ ከነብስ አባቱ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ በአደራ የተሰጠዉን አንድ የመላምት ድርሰት የፊት ለፊት ገጹ ላይ ለጥፎት የህዝብን ስሜት የኮረኮረ እየመሰለዉ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ ከሁለት ሺ አመታት በኋላ ይሁዳዊ ክህደት ሲክድ እጅ ከፍንጅ ተይዟል። የሚገርመዉ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዝሙር ሆኖ ሳለ ያንን የመሰለ የክህደት መንፈስ ልቡ ዉስጥ ያስቀመጠለት ሰይጣን እንደሆነ ሁሉ አዲስ ዘመንና አይጋ ላይ የወጣዉን ጽሁፍ የጻፈዉ ግለሰብም የወያኔ ጌቶቹን ምክር ተቀብሎ አሜን አለ እንጂ የዚህ የዉሸት ድርሰት ጠንሳሾች በሰይጣን የሚመሰሉት የወያኔ መሪዎች ናቸዉ። የጽሁፉ ደራሲ ነኝ ግለሰብ የወያኔን ትዕዛዝ ከመቀበል ዉጭ ያደረገዉ ነገር ቢኖር ስሙ ከፅሁፉ አርዕስት ስር እንዲቀመጥ መፍቀዱ ብቻ ነዉ – ለዚያዉም የብዕር ስም!

አገሮች፤ ድርጅቶች ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች የፕሮፓጋንዳ ጦርነት ዉስጥ ሲገቡ በዉሸት ዉስጥ እዉነት ወይም በእዉነት ዉስጥ ዉሸት እየሸነቆሩ ነዉ የፕሮፓጋንዳቸዉ ኢላማ የሆነዉን የህብረተሰብ ክፍል ቀልብ ለመግዛት የሚፍጨረጨሩት እንጂ ዉሸትን በዉሸት ለዉሰዉ ቢያቀርቡማ ህዝብ እንኳን ሊያምናቸዉ ደግሞ ሊሰማቸዉም ፈቃደኛ አይሆንም። ይህ ከሰሞኑ አይጋፎርምና አዲስ ዘመን ላይ የወጣዉ ጽሁፍ ግን ምንም አይነት የፕሮፓጋንዳ ህግ አይከተልም፤ ምክንያቱም ጽሁፉ የተጻፈዉ ህግ የሚባል ነገር በሌለባትና ወያኔና ግብረ አበሮቹ እራሳቸዉ ህግ በሆኑበት አገር ዉስጥ ነዉ። ጽሁፉ ሲጀምር በዉሽት ይጀምርና መሀል ላይ ዉሸቱን በዉሸት አጠናክሮ በዉሸት ይደመደማል። እንደዚህ አይነት የዉሽት ክምር የሚመጣዉ ደግሞ ከሌላ ከየትም ሳይሆን በዉሸት ተወልደዉ፤ በዉሸት አድገዉ በዉሸት ከሸበቱት የወያኔ መሪዎች ብቻ ነዉ። ዉድ አድማጮቻችን የዚህ ጽሁፍ አላማ ለሻዕቢያ ጥብቅና መቆም አይደለም፤ ሻዕቢያ ከኛ በላይ ለራሱ ጥብቅና መቆም ይችላል። የዚህ ጽሁፍ ብቸኛ አላማ የኢትዮጵያ ህዝብ ገንበዙን፤ ሀብቱንና ጉልበቱን አስተባብሮ መዋጋት የሚገባዉ ቀንደኛ ጠላቱ ወያኔ መሆኑን መናገር ነዉ። ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ትናንት ሲከናዉን የምናዉቀዉንና አይናችን ፊት ተፈጽሞ ከ “ሀ” ወደ “ፐ” የተጻፈዉን ታሪክ ዛሬ ወያኔና ቡችሎቹ ከ “ፐ” ወደ “ሀ” ሲያነብቡትና የኢትዮጵያን ህዝብ ለማሳሳት ሲሞክሩ ዝም ብለን አንመለከትምና ይህንን የዉሸት ክምር ከመሰረቱ መናድ እንፈልጋለን።

ይህንን በዉሸት የተጀቦደ የወያኔ ቡትቶ እንዳለ ማቅረቡ የአድማጭን ጆሮ ማደንቆር ስለሚሆን አንሞክረዉም። ሆኖም ወያኔ በተከበበና አንድ እርምጃ ወደማይቀረዉ ዉድቀቱ በቀረበ ቁጥር የሚመዝዛቸዉን አገር የሚገዘግዙ መጋዞች የኢትዮጳያ ህዝብ ከአሁኑ አዉቆ እንዲጠነቀቅ ስለምንፈልግ የፅሁፉን ጎላ ጎላ ያሉ የዉሸት ምሶሶዎች እንዳሉ ለማቅረብ እንገደዳለን።
የመመሪያዉ አይን ያወጣ ዉሸት “በወቅቱ ኢሕአዴግ ከበረሀ ይዞት የመጣው መደበኛ ያልሆነ ሰራዊት ብቻ በእጁ ነበር። ቀድሞ የነበረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሀይል፣ የምድር ጦሩ፣ ታንከኛው፣ መድፈኛው፣ አየር መከላከያው፣ አየርሀይሉ፣ ባህር ኃይሉ፣ ኮማንዶው ሰራዊት፣ ፖሊስና ሌሎችም ሙሉ በሙሉ ተበትነዋል” ይላል። ይህ ዉሸት ከተለመዱት የወያኔ ተራ ዉሸቶች ጋር ሲተያይ ተጠንቶበት በጥንቃቄ የተዋሸ ዉሸት ይመስላል። የቀድሞዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ወራዊት ሰራዊት አባላት በገዛ ፈቃዳቸዉ የተበተኑ ይመስል የዚህ ጽሁፍ ጸሀፊ የቀድሞዉ የመከላከያ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተበትነዋል እያለ ነዉ የሚነግረን። በእርግጥም ቁጥሩ ከ300 መቶ ሺ በላይ የሚሆን ሰራዊት የኢትዮጵያ ሠራዊት መሆኑ ተረስቶ የደርግ ጦር፤ የትምክህተኞች ኃይል ወይም የነፍጠኞች ምሽግ እየተባለ በወያኔ ዘረኞች ተበትኖ በምትኩ በአንድ ዘር የበላይነት ላይ የተመሰረተ የመከላከያ ኃይል ተገንብቷል። የቀድሞዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የማን ሠራዊት እንደነበር፤ ለምንና በማን እንደተበተናና በምትኩም የተገነባዉ ሠራዊት ለማን ጥቅም እንደቆመ የኢትዮጵያ ህዝብ አንደ ጥቁር ነጭ ለያይቶ የሚያዉቀዉ ሀቅ ነዉና ከዚህ በላይ የምንለዉ ምንም አይኖርም።

ከአንድ ወር በፊት የኢትዮጵያ ሳቴላይት ቴሌቭዥንና ሬድዮ ጋዜጠኞች በኢትዮጵያና በኤርትራ ህዝብ መካከል ሊኖር የሚገባዉን ግኑኝነትና ኤርትራ ዉስጥ እየተካሄደ ነዉ የሚባለዉን የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት ትግል እንቅስቃሴ አስመልክቶ እዉነቱን ለህዝብ ለማሳወቅ ታሪካዊ ጉዞ ወደ አስመራና የኤርትራ በረሀዎች አድርገዉ ነበር። በጉዟቸዉ ወቅት ጋዜጠኞቹ ሰፋ ያሉ ጉዳዮችን የዳሰሰ ቃለ መጠይቅ ከኤርትራዉ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር አድርገዉ ነበር። ይህ ማን ምን ሰራ የሚለዉን ጥያቄ በታሪክ ወደ ኋላ እየሄደ የሚመልሰዉና በአይነቱ ልዩ የሆነዉ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለመጠይቅ በመገናኛ አዉታሮች መሰራጨት ሲጀምር የኢትዮጵያ ህዝብ ከደደቢት ዉሸትና ተረት ዉጭ ሌላ ሲሰማ የሚያመዉ ወያኔ እንደለመደዉ ሲወራጭና እዉነትን ለመጋረድ ሲፍጨረጨር ታይቷል።

የኢትዮጵያን ህዝብ እንዳሰኛቸዉ የሚረግጡት፤ የሚያስሩት፤ የሚገድሉትና በተለይ በቅርቡ የመስፋፋትና የማፈናቀል ፖሊሲያቸዉን የሚቃወመዉን ሁሉ “ልክ እናስገባዋለን” ብለዉ የዛቱት የወያኔ መሪዎች የእነሱን ጠላትነትና ስር የሰደደ ፀረ ኢትዮጵያ አቋም ሸፍነዉ ኤርትራን የኢትዮጵያ ዋነኛ ጠላት አድርገዉ ማቅረብ ጀምረዋል። የሚገርመዉ ይህ ሁሉ አልበቃ ብሏቸዉ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ በኢሳት ቴሌቪዥን በሚተላለፍበት ወቅት በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይ ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ ቀድሞዉኑም ከብልጭ ድርግም አልፎ የማያዉቀዉን አሌክትሪክ ጭራሽ እንዲጠፋ አድርገዋል።

Sunday, March 8, 2015

የነዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ

“ሸላሚም እኛ፣ ከሳሽም እኛ!“

አብርሃም ሰለሞን የ25 ዓመት ወጣት ነው፡፡ ያሳደገው ኢሕአዴግ ራሱ(ወይም ዘመነ መንግስቱ) ነው፡፡ በቤተልሄም የመጀመሪያ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ IT መምህር ነበር፡፡ በትምህርት ቤቱ መልካምዝና ነበረው፡፡ በ2006 በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገ ውድድር ላይ ይዞ በቀረበው የመምህራን ዳታ ቤዝ እና የመማሪያ ማኑዋል ዝግጅትንአሸናፊ መሆን ከቻሉ ሦስት ወጣቶች አንዱ ለመሆን በቅቷል፡፡ ጥቅምት 16/2007 - በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሸላሚነት ሲካሄድ በነበረውየሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራዎች የሽልማት ሥነ ስርዓት ላይ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን IT ለማስተማር የሚረዳ የዴስክቶፕሶፍትዌር እና የሞባይል አፕልኬሽን በማዘጋጀት የሜዳልያ ተሸላሚ ተብሎ ተመዝግቧል፡፡ ይሁን እንጂ የዘንድሮውን የስራውን ውጤት በአካልተገኝቶ ሰርተፍኬቱንም፣ ሜዳልያውንም መቀበል አልቻለም፤ በእሱ ፈንታ እናቱ በውክልና ተቀብለውታል፡፡ ምክንያቱም እሱ በሽብር ወንጀልተጠርጥሮ ቂሊንጦ ማቆያ ቤት ይገኛል፡፡

አብርሃምን ስለ አገሪቱ የወደፊት ተስፋ ሰጪ ስራ ሰርተሃል ብሎ በቀኝእጁ የጨበጠው መንግስት፣ በግራ እጁ ደግሞ ለአገሪቱ የወደፊት ተስፋ አደገኛ አሸባሪ ነህ ይለዋል፡፡

“የማይተዋወቁ ግብረ - አበሮች”

በሽብር የሚከሰሱ ሰዎች ከማያውቋቸው ሰዎች ጋር በአንድ መዝገብ (እንደግብረ አበር) የሚታሰሩበት አሰራር የተለመደ ሆኗል፡፡ ለዚህ አንዱ ማሳያ የነዘላለም ወርቅአገኘሁ መዝገብ በመባል የሚታወቀው (መዝገብቁጥር 166/07) አንዱ ነው፡፡ በዚህ መዝገብ አራት የተለያዩ ፓርቲ አባላት እና ሌሎች 6 ተጠርጣሪዎች ተከስሰዋል፡፡ የመጀመሪያዎቹ5 ተከሳሾች (ዘላለም ወርቅአገኘሁ፣ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ አብርሃ ደስታ እና የሺዋስ አሰፋ) በፀረ- ሽብርተኝነት አዋጁአንቀፅ 4 ሲከሰሱ፣ ቀሪዎቹ አምስቱ (ዮናታን ወልዴ፣ አብርሃም ሰለሞን፣ሰለሞን ግርማ፣ ባህሩ ዳኑ፣ እና ተስፋዬ ተፈራ) በአንቀፅ 7/1 እና 9ኛ ተከሳሽ (ባህሩ ዳጉ) በሌላ ክስ በወንጀለኛ መቅጫው288/1 መሰረት ከመከላከያ ሰራዊቱ በመኮብለል ተከስሰዋል፡፡ እነዚህ ሰዎች ክሳቸው በአንድ መዝገብ ታጭቀው ቢመጡም ባብዛኛው እርስበርስ አይተዋወቁም፤ በጋራ የሰሩት ስራም የለም፡፡

በፌስቡክ እንቅስቃሴው በስፋት የሚታወቀው እና የአረና ትግራይ ፓርቲአመራር አባል የነበረው አብርሃ ደስታ ለምሳሌ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባል ከሆነው ሀብታሙ አያሌው በቀር የሌሎቹን ስም እንኳንአብረው ከመከሰሳቸው በፊት አለመስማቱን ይናገራል፡፡ ተሸላሚው አብረሃም ሰለሞንም ከተከሳሾች የሚያውቀው ዘላለምን ብቻ ነው፡፡‹‹እሱንም›› ይላል አብርሃም ‹‹በ2006 አንድም ቀን አግኝቼው አላውቅም››፡፡ ከተከሳሾች መካከል ብዙ ሰው ያውቃል የተባለለት1ኛው ተከሳሽ ዘላለም እንኳን የሚያውቀው ሦስቱን ብቻ ነው - ዮናታን፣ አብርሃምን እና ባሕሩን ብቻ፡፡
“በስልክ የማውራት አሸባሪነት”

በሽብር የተከሰሱ ሰዎች ላይ በተደጋጋሚ እና በተለይ ከሚቀርቡ የማስረጃዓይነቶች አንዱ የስልክ ግንኙነት ነው፡፡ ከላይ በጠቀስነው መዝገብ ውስጥ ብቻ ክስ ሆነው የቀረቡትን የስልክ ግንኙነቶች እንመልከት፡-

* 1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ፣ ‹‹በ 2000 ተድላ ደስታ ከተባለየሽብር ድርጅቱ አባልና አመራር ጋር በስልክ እና በፌስቡክ›› በማውራት፤
* 2ኛ ተከሳሽ ሀብታሙ አያሌው ‹‹ዘመኑ ካሴ ከተባለ የግንቦት ሰባትታጣቂ›› ጋር በጥር 14/2005 በስልክ በማውራት፤
* 3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ ‹‹የግንቦት ሰባት አመራር ከሆነው ፋሲልየኔ አለም ›› ጋር በየካቲት 29/2003 በስልክ በማውራት፤
* 4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ ‹‹የደ.ም.ሕ.ት. አመራር ከሆነው ጎይቶምበርሄ ›› ጋር ጥር 3/2006 በስልክ በማውራት፤
* 5ኛ ተከሳሽ የሺዋስ አሰፋ ‹‹የግንቦት ሰባት አመራር ከሆነው ፋሲልየኔአለም›› ጋር ጥቅምት 14/2006 በስልክ በማውራት፤
* 10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ፣ የግንቦት ሰባት ክንፍ ከሆነው የአ.ዴ.ኃ.ንአባል ጋር ሕዳር 2003 በስልክ በማውራት፤

Thursday, March 5, 2015

የአድዋ ድልን እያከበርን ለዛሬ ነፃነታች ቃል እንግባ!

መቶ አስራ ዘጠነኛውን የአድዋ ድል በዓል እየዘከርን እንገኛለን። እንደዛሬው ሁሉ ያኔም ቀደምቶቻችን በርካታ የውስጥና የውጭ ችግሮች ነበሩባቸው። እንደዛሬው ሁሉ ያኔም በመካከላቸው የሀሳብና የጥቅም ልዩነቶች ነበሩ። ያም ሆኖ ግን ቀደምቶቻችን በአገር ነፃነት ጉዳይ ላይ ሰፋ ያለ መግባባት ላይ መድረስ በመቻላቸው በዘመናዊ የጦር መሣሪያዎችና ድርጅት የተጠናከረውን የአውሮፓ ጦር በጥቁር የጦር አዛዦችና ተዋጊዎች መመከት ቻሉ። ከአድዋ በፊት አፍሪቃ በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ አውሮፓዊያን የተሸነፉባቸው ተናጠል አውደ ውጊያዎች ነበሩ፤ ጦርነትን ሲሸነፉ ግን አድዋ የመጀሪያው ነው። በዚህም ምክንያት ነው የአድዋ ድል የአፍሪቃውያን ከዚያም አልፎ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ ድል ተደርጎ የሚወሰደው።

ዛሬ ግን እኛ ያኔ የነበሩት አያትና ቅድመ አያቶቻችን እደረሱበት የመግባባት ደረጃ ላይ መድረስ ባለመቻላችን አገር በቀሉን ቅኝ ገዢ – ህወሓትን – ከኢትዮጵያዊያን ጫንቃ ላይ ማውረድ አቅቶን አገራችንና ሕዝቧን ከባዕድ በባሰ ሁኔታ እያዋረደ በመግዛት ላይ ይገኛል።
ያኔ ለሀገሩ፣ ለነፃነቱና ለክብሩ ቀናዒ የሆነው ኢትዮጵያዊ ራሱን ወታደር አድርጎ በየጎበዝ አለቃው አዝማችነት በጠላት ላይ ዘምቶ ድልን ተቀዳጅቷል። ዛሬ ግን ቁጥሩ ቀላል ያልሆነ የመከላከያ ሠራዊት አባል ለህወሓት አዛዦች ሎሌነት አድሮ የራሱን ወገን ይፈጃል። ያኔ በአገዛዙ ላይ ብሶት የነበረው እንኳን ሳይቀር ብሶቱን ችሎ ለሀገር ሉዓላውነትና ክብር ሲል ተዋድቋል። ዛሬ ግን ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ወገኖቻችን የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም ከብሶቶቻቸው በላይ አሻግረው መመልከት ተስኗቸዋል።

ዛሬ 119ኛውን የአድዋ ድል በዓል አያቶቻችንን በማድነቅ ብቻ ልናሳልፈው አይገባም። የአያቶቻችንን ገድል ስናከብር ዛሬ የምንገኝበትን ሁኔታ መመዘን ይገባናል። ራሳችንን ከእነሱ ጋር በማስተያየት እንደምን ያለን ውለታ መላሽ ያልሆንን የልጅ ልጆች መሆናችንን መመዘን እና ራሳችንን መውቀስ ይገባናል። የሚሳዝነው ዛሬ ራሱን ከሚወቅሰው በላይ አያቶቹን የሚወቅስ መብዛቱ ነው። እነሱ ችግሮችን ተሻግረው የምንኮራበትን ድል አቀዳጅተውን አልፈዋል። እኛ ግን እነሱ ያቆዩልንን ድል እንኳን ማስጠበቅ አልቻልንም። ከአድዋ ድል አንድ መቶ አስራ ዘጠኝ ዓመታት በኋላ አገራችንን ለህወሓት የአገር ውስጥ ቅኝ አገዛዝ ማስረከባችን ሊያመንና ሊያንገበግበን ሲገባ ድሮ ሊደረጉ ሲችሉ አልተደረጉም በምንላቸው ነገሮች ላይ እየተከራከርን ግዜያችንን እናጠፋለን።

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ታላቁን የአድዋን ድል ለአጎናፀፉን ቀደምቶቻችን ያለንን ክብር መግለጽ ያለብን ዛሬ አገራችን ከህወሓት የአገር ውስጥ ቅኝ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት በምንገባው ቃል ኪዳን ነው ብሎ ያምናል። አገራችንን በቅኝ ግዛትነት እያስገዛን የቀደምቶቻችንን ድል መዘከር ለእኛ ለልጆቻቸዉ የሚያሳፍር ተግባር ነው ብሎ ያምናል። አርበኞች ግንቦት 7 የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አገር በቀል ቅኝ ገዥ በሆነው ሕወሓት እየተመራ የኢትዮጵያን ሕዝብ የማዳከሙን ተግባር በአስቸኳይ ማቆም ይኖርበታል ብሎ ያምናል። ስለሆነም የመከላከያ ሠራዊት አባላት ልባችሁንም ክንዳችሁንም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር አድርጉ። ቀደምት አባቶቻችን አድዋ ላይ ድል የነሱት ቅኝ ገዥ ዛሬ ቀለሙን ለውጦ “ህወሓት” ተሰኝቶ ያንተ አዛዥ ሆኗል። መሣሪያህን በህወሓት አዛዦችህ ላይ የምታዞርበት ወቅት አሁን ነው። ንቃ፤ ተነስ!

Ethiopia: Amnesty International Report 2014/15

Federal Democratic Republic of Ethiopia
Head of state: Mulatu Teshome Wirtu
Head of government: Hailemariam Desalegn

Freedom of expression continued to be subject to serious restrictions. The government was hostile to suggestions of dissent, and often made pre-emptive arrests to prevent dissent from manifesting. Independent media publications were subject to further attack. Peaceful protesters, journalists, and members of opposition political parties were arbitrarily arrested. The Charities and Societies Proclamation continued to obstruct the work of human rights organizations. Arbitrary detention and torture and other ill-treatment were widespread, often used as part of a system for silencing actual or suspected dissent.

Background

Economic growth continued apace, along with significant foreign investment including in the agriculture, construction and manufacturing sectors, large-scale development projects such as hydroelectric dam building and plantations, and widespread land-leasing, often to foreign companies.

The government used multiple channels and methods to enforce political control on the population, including politicizing access to job and education opportunities and development assistance, and high levels of physical and technological surveillance.

The politicization of the investigative branch of the police and of the judiciary meant that it was not possible to receive a fair hearing in politically motivated trials.

Federal and regional security services were responsible for violations throughout the country, including arbitrary arrests, the use of excessive force, torture and extrajudicial executions. They operated with near-total impunity.

Armed opposition groups remained in several parts of the country or in neighbouring countries, although in most cases with small numbers of fighters and low levels of activity.

Access to some parts of the Somali region continued to be severely restricted. There were continuing reports of serious violations of human rights, including arbitrary arrests and extrajudicial executions. There were also multiple allegations of the rape of women and girls by members of the security services.

Excessive use of force ‒ extrajudicial executions

In April and May, protests took place across Oromia region against a proposed “Integrated Master Plan” to expand the capital Addis Ababa into Oromia regional territory. The government said the plan would bring services to remote areas, but many Oromo people feared it would damage the interests of Oromo farmers and lead to large-scale displacement.

Security services, comprising federal police and military special forces, responded with excessive force, firing live ammunition at protesters in Ambo and Guder towns and Wallega and Madawalabu universities, resulting in the deaths of at least 30 people, including children. Hundreds of people were beaten by security service agents during and after the protests, including protesters, bystanders, and parents of protesters for failing to “control” their children, resulting in scores of injuries.

Thousands of people were arbitrarily arrested. Large numbers were detained without charge for several months, and some were held incommunicado. Hundreds were held in unofficial places of detention, including Senkele police training camp. Some detainees were transferred to Maikelawi federal police detention centre in Addis Ababa. Over 100 people continued to be detained in Kelem Wallega, Jimma and Ambo by security service agents after courts ordered their release on bail or unconditionally.

Monday, March 2, 2015

አሁንም ደግመን እንነግራችኋለን

ኢትዮጵያችን እግዚአብሔርንና ሰውን በማይፈሩ ጨካኞች እጅ ወድቃ የመከራ አገር ከሆነች ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ ተቆጥረዋል። በህዝባችን ላይ የተመዘዘው የመከራ ሰይፍም ወደ ሰገባው የሚመለስ አልሆነም። እንዲያውም በህዝባችን ላይ ሲዘንብ የቆየው የመከራ መንፈስ እንደገና ታድሶ ገና “ልክ እናስገባችኋለን” የሚል የጣዕረ ሞት ድምፅ ከህወሃት መንደር እየተሰማ ነው።

አባይ ፀሃይ የሚባለው ወላዋይና አደር ባይ ግለሰብ በህዝቡ ላይ ሲፈፅመው በኖረው ወንጀል ገና የረካ አይመስልም። ሌላ ግዲያ፤ ሌላ ስደት፤ ሌላ የላቀ መከራ ለኢትዮጵያዊያን ደግሶላቸዋል። አባይ ፀሃይ ለአዲስ አበባ ከተማ ልቀት እርሱ ብቻ አሳቢ፤ እርሱ ብቻ ተቆርቋሪ ሁኖ ራሱን ሹሟል።የአዲስ አበባም ሆነ በአካባቢው የሚኖረው ኗሪ ህዝብ ግን አባይ ፀሃይን የሚያውቁት በእኩይ ተግባሩ እንጂ በደግ ተግባሩ እንዳለሆነ እኛ ልናስታውሰው እንወዳለን። በዚህ ግለሰብ አማካሪነት የተጀመረው ኗሪውን ህዝብ የማፈናቀል፤ ቤተሰብን የመበተን፤ የህዝቡን አብሮነት የማፍረስ ተግባር ገና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል “ገና ልክ እናስገባችኋለን” በሚል መፈክር ሥር እንደሚቀጥል ታቅዷል። አዲስ አበባን በማስፋፋት ሰበብ ብዙ ገበሬዎች ከኖሩበት መንደር ያለምንም ካሳ ተፈናቅለው የሌላ ሎሌ እንዲሆኑ መደረጉ የሚረሳ አይደለም። ይሄን የአንድን ህዝብ ማንነት የማጥፋት ድርጊትን የተቃወሙ ብዙ ወጣቶች በሞት እና በእሥራት እንደተቀጡም አረሳነውም። ትላንት የፈሰሰው ደም ሳይደርቅ፤ የፈሰሰው እንባ ሳይታበስ፤የተበተነው ሳይሰበሰብ፤ የተሰበረው ሳይጠገን እንደገና ለሌላ ዙር ጥፋት እየተዘጋጁ እንደሆነ ነግረውናል።

አባይ ፀሃይ “ልክ እናስገባችኋለን” ሲል የተማመነው ጠመንጃ ያነገተውን ኢትዮጵያዊ ወታደር እንጂ ህዝብን እንዳልሆነ እናውቃለን። ወታደር አገሩን መጠበቅ፤ ህዝቡንም ከጥፋት መታደግ፤ አጠቃላይ የአገሪቷን ህግም ማስከበር ዋናው ተልዕኮው ነበር። የአገራችን ወታደሮች ግን ዋናውን ተልእኳቸውን ትተው ኢትዮጵያን እንደ አገር እንዳትቀጥል የሚያደርጉ ቡድኖችን እድሜያቸውን ለማራዘም እየሰሩ እንደሆነ እያየን ነው።በአገራችን ጠመንጃ የታጠቁ ኃይሎች መከላከያ ኃይል አባላት፤ የፖሊስ አባላት፤ የፌዴራል ፖሊስ አባላት እና በአገራችን ታሪክ በነፍሰ ገዳይነቱ የሚታወቀው አግዓዚ የተባለው ክፍለ ጦር አባላት እና የአገር ውስጥ ደህንነት አባላት የህወሃትን ዕድሜ ለማራዘም ከልብ የመነጨ ፍላጎት አላቸው ብለን አናምንም። እነዚህ ኃይሎች የወጡበትን ጎጆ፤ ነገ ዞሮ መግቢያ የሚሆናቸውን ማህበረሰብ ወደውና ፈቅደው ያፈርሳሉ ብለን ለማሰብ ይቸግረናል።በሌላ በኩል ደግሞ ድርጊታቸው ብዙዎችን እያስከፋ እንደሆነም እናውቃለን።

አሁንም ደግመን ደጋግመን በኢትዮጵያችን ጠመንጃ ላነገቱ ኃይሎች መልዕክት መላካችንን አናቋርጥም። ጠመንጃውን ያነገቱ ኃይሎች ካነገቱት ጠመንጃ የተለዩ ናቸው። እነዚህ ኃይሎች ስሜት አሏቸው፤ ፍላጎት አሏቸው፤ ማሰብ የሚችል አዕምሮም እንዳሏቸውም የሚካድ አይደለም።የሚያዝንና የሚደሰት ስሜት፤ ለመኖር ፍላጎት፤ በጎውን ከክፉ ለመለየት የሚያስችል አዕምሮ ያሏቸው ስለሆነ ፈፅሞ እስከ ሚመሽ ድረስ መልዕክታችንን ከመስደድ አናቆምም። መልዕክታችንም አጭርና ግልፅ ነው። በዚያች አገር ውስጥ ጠመንጃ የታጠቀው ኃይል ጋር ጠላትነት የለንም።በእኛ እምነት መከላከያ ኃይል፤ ፖሊስ እና የደህንነት ሠራተኞች ጠላቶቻችን አይደሉም። እኛ ጠላት የምንለው ጠመንጃ የታጠቀውን ድሃ እና ከርታታ ኢትዮጵያዊ ሳይሆን ይህን ኃይል በገዛ ወገኑ ላይ ሰይፉን እንዲመዝ እና የንፁሃንን ደም እንዲያፈስ የሚያደርገውን ኃይል ነው።የአገሪቷ መከላከያ ኃይል አሁን ባለበት ሁኔታ ለተሻለ ውጤት የሚያበቃው አማራጭ ስለሌለው ሂሊናው እየወቀሰውም ቢሆን የገዛ ወገኑን ደም እያፈሰሰ ለመቆየት የተገደደ ይመስላል። ይህን ማለታችን የድርጊቱን መፈፀም ትክክል ነው እያልን አይደለም። በማንኛውም መለኪያ የንፁህ ሰውን ደም ማፍሰስ ትክክል አይደለም። በሰማይ በእግዚአብሄር ፊት የሚያስጠይቅ፤ በምድር በሰው ዘንድም የሚያስወቅስ ክፉ ተግባር መሆኑን ሳንናገር አናልፍም።

Sunday, March 1, 2015

አድዋ!


ዋ! አድዋ ፤ ያ ሑዳዴ
መድፍን ፈንጅን ፤ በጎራዴ
ባሕር ተሻግሮ ፤ የሐበሻን ምድር
ቅኝ ሊገዛ ፤ ይሄ ደፋር!
አንች አድዋ ፤ የበኩር ልጅ
ላንቺ ውልደት ፤ ስንቱ ሲፈጅ
ተጸንሰሽ ፤ ከውጫሌ
ለደም መሬት ፤ ለአሞሌ
እርግዝናሽ ፤ ዘጠኝ ወሩ
ዓመታትን ፤ ማስቆጠሩ
ክፉውን ቀን ፤ ይዞ አሳሩ
ከብቱ እረግፎ ፤ ባገር ምድሩ
ሰው ሁሉ አልቆ ፤ በችጋሩ
በፋሽስት ሸር ፤ በእኩይ ግብሩ
ከብት የሚፈጅ ፤ ደዌ ረጭቶ
በምን ታርሶ ፣ በምን ለምቶ
የገበሬው ፤ ሀብት ጠፍቶ
አከርካሪው ፤ ተመትቶ
የሚቀመስ ፤ እህል ታጥቶ
ረሀቡ ፤ ሕዝቡን በልቶ
ምኑ ተብሎ ፤ ስንቱን ነግሮ
የግፍ ግፉ ፤ ተዘርዝሮ
ዝም ይሻላል ፤ ምን ተቆጥሮ
በክፉው ቀን ፤ ራብ ደክሞ
ያለቀ ሕዝብ ፤ በአዋጅ ተሞ
በዚያ ድቀት ፤ ተጎድቶ
አፈር ልሶ ፤ ግድ ተነሥቶ
አይቀር ነገር ፤ የሀገር ጥሪ
ነፍሱ የሷ ፤ እሱ አኗሪ
ጉልበት ሆኖት ፤ የሀገር ፍቅሩ
አስቆጥቶት ፤ መደፈሩ
ገሰገሰ ፤ ወደ አድዋ
ጠላት ሊግት ፤ የሞት ጽዋ
አድዋ ላይ ፤ ከግንባሩ
ሊሞሻለቅ ፤ ሲተም ጦሩ
እንደ ሙላት ፤ ደራሹ ጎርፍ
ሲያስገመግም ፤ ጠላት ሊቀስፍ
ከተፍ ሲል ፤ ፊት ለፊቱ
ጥሊያን ራደ ፤ ልብ አጥቶ
ባለ የሌለ ፤ መሣሪያ አጉል
እያስጓራ ፤ ሲከላከል
በመድፍ አረር ፤ በመትረየስ
ግማሽ ሲቀር ፤ ሲሠዋ ነፍስ
ጠጋ ሲባል ፤ ወደ ምሽግ
ሌላ አሳር ፤ ምን ይደረግ?
በስል ችንካር ፤ በውጋቱ
በጠርሙስ ጦር ፤ በስለቱ
ምሽግ ማዶ ፤ በተከለው
አርበኛውን ፤ እንዲያስቀረው
ጠርሙስ አልፎ ፤ የፈንጅ ንጣፍ
ፋኖ የሚፈጅ ፤ በነፍስ ወከፍ
ያ ባዶ እግር ፤ ቢቀረደድ
ቢሸረከት ፤ ቢጎራረድ
ማን ተሰምቶት ፤ ለማን ታውቆ?
በፈንጅውም ፤ ረግፎ አልቆ