Sunday, October 20, 2013

ሰይጣን ለማስመሰል ከመጽሃፍ ቅዱስ ይጠቅሳል

የኢህአዴግ ስርዓት ገዥዎች ያጥቱን የህዝብ Aመኔታ ለማግኘት ሲሉ ሓቀኛ መስለው በመቅረብ የኢትዮጵያን ህዝብና የዓለም ማህበረሰብን በማምታታት የስልጣን እድሜን ማራዘም በሚል ፖሊሲ በያዝነው ሳምንት አዲስ የሚመስል የማደናገሪያ ስልት ይዘው ብቅ ብለዋል። መቸም እብሪተኞች ምን ግዜም ቢሆን ከራሳቸው ሌላ አዋቂ አለ ብለው አያስቡምና የኢህአዴግ አመራሮች በዚሁ አዲስ የሚመስል ስልታዊ ድራማ እራሳቸውን ንጹህ አድርገው በማቅረብና በመተወን የህዝቡን ቀልብ በመሳብ ህዝቡ ስለነሱ ንጽህና እንዲናገርላቸውና ስርዓቱ ሙስናን በቆራጥነት እየተዋጋ እንደሆነ በማስመሰል የኢትዮጵያንና የዓለምን ማህበረሰብን ለማደናገር የሚደረግ የተለመደ ተንኮል ይዘው መምጣታቸው የሚያስገርም አይደለም ። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ ኢህአዴጎች እንደሚያሱቡት ሳይሆን የስርዓቱን ባህሪ በሚገባ የሚያውቅ ህዝብ በመሆኑ በእንዲህ አይነቱ ተንኮል ህዝቡን ማደናገር የሚቻል አይደለም። ምክንያቱ የኢህAዴግ አመራሮች በእንዲህ አይነቱ የማስመሰል ድራማ ብጹአን መስለው ለመታየት ቢሞኩሩም ስልጣናቸውን አለአግባብ በመጠቀም በማን አለብኝነት የሃገርንና የህዝብን ሃብት በመዝረፍ ያካበቱት የሃብት ዝርዝር ተደጋግሞ የተገለጸ ዓለም ያወቀው ጸሃይ የሞቀው ሃቅ ስለሆነ እርቃናቸውን ያወጣቸዋል። ሙስና በሃገሪቱ ስር እንደሰደደና የስርዓቱ ባለስልጣናትም ምን ያህል በሙስና መጨማለቃቸውን ከታች ባለው የባለስጣንቱ ሃብት ዝርዝር መረዳት ይቻላል። 

1-መለስ ዜናዊ/ጠቅላይ ሚኒስቴር……………………….3 ቢልዮን ዶላር 
2-ወ/ሮ አዜብ መስፍን…………………………………..3 ቢልዮን ዶላር 
3-ስብሓት ነጋ …………………………………………..2.5 ቢልዮን ዶላር  
4-ብርሃነ ገ/ክርስቶስ………………………………………2 ቢልዮን ዶላር 
5-ሳሙኤል ታፈሰ………………………………………...1.5 ቢልዮን ዶላር 
6-ስዩም መስፍን…………………………………………..1 ቢልዮን ዶላር 
7-አባዲ ዘሞ……………………………………………….500 ሚልዮን ዶላር 
8-ግርማ ብሩ………………………………………………300 ሚልዮን ዶላር 
9-ታደሰ ሃይሉ……………………………………………..250 ሚልዮን ዶላር 
10- ቴዎድሮስ ሓጎስ(የህወሓት ጽ/ቤት ሃላፊ……………..200 ሚልዮን ዶላር 
11-አብደላሂ ባገርሽ(በጉና ትሬዲንግ የሚሰራ)……………150 ሚልዮን ዶላር 
12-ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል………………………………….100 ሚልዮን ዶላር 
13-በረከት ስምኦን…………………………………………..100 ሚልዮን ዶላር 

ይህ እንደ አብነት ለመቀስ ያህል የቀረበ እንጂ ሁሉም ከዝቅተኛው እስከ ከፍተኛው የስልጣን እርከን የሚገኙ የስርዓቱ ባለስልጣናት እንደየ ዓቅማቸው የህዝብንና የሃገርን ሃብት በመዝረፍ ሃብት ያላካበተ ባለስልጣን አለ ብሎ ማለት ያስቸግራል። ሁኔታው Aዲስና ከህዝብም የተሰወረ ሳይሆን በሁሉም የመንግስት ተቋማት ሲሰራበት የቆየ የተለመደ Aሰራር ነው ። ሃቁ ይህ እያለ “ ሰይጣን ለማስመሰል ከመጽሃፍ ቁድስ ይጠቅሳል” እንዲሉ የስርዓቱ አመራሮች ብጹአን መስለው ደግመው ደጋግመው ሊያደናግሩን ይሞክራሉ። 

ምንጭ፡ http://demhitonline.blogspot.com/

No comments:

Post a Comment