Saturday, October 19, 2013

ስብሐት ነጋና አሜሪካ የሚኖረዉ አግአዚ ኢትዮጵያዊዉን ደብድበዉ ተሰወሩ

ኢትዮጵያ ዉስጥ ባለፉት ሃያ ሁለት አመታት አይኑ አይቶ ያልወደደዉን ሁሉ እንዳሰኘዉ ሲያስር፤ ሲደበድብና ሲገድል የኖረዉ ወንጀለኛዉ ሽማግሌ ስብሐት ነጋ ያንን የለመደዉን ወንጀል አሜሪካ ድረስ ይዞ በመምጣት እየተከተለዉ ቪድዮ ሲቀርጸዉ የነበረዉን አንድ ወጣት ኢትዮጵያዊ ከአጃቢዉ ጋር ደብድቦ መሰወሩን አሜሪካ ግዛት ቨርጂኒያ ዉስጥ የሚገኙ ምንጮቻችን በላኩልን ዜና ገለጹ። ከአሜሪካዋ መናገሻ ከዋሺንግተን ዲሲ በስተደቡብ አስራ አምስት ኪሎ ሜትር ወጣ ብላ በምትገኘዉ አሌክሳንደሪያ ቨርጂኒያ ዉስጥ ነበር ስብሐት ነጋና እዚሁ ዋሺንግተን ዲሲ አካባቢ የሚኖረዉ ታምራት ገ/መድህን የተባለ የህወሃት ሰላይ መስፍን ወርቅነህ የተባለዉን ሰላማዊ ኢትዮጵያዊ ለምን ቪድዮ ትቀርጸናለህ ብለዉ ያለበት ቦታ ድረስ ሄደዉ የደበደቡት። ተደብዳቢዉ መስፍን ወርቅነህ የተባለዉ ወጣት ጉዳት ደርሶበት እዚያዉ አለክሳንደሪያ ዉስጥ ወደሚገኘዉ ሆስፒታል ተወስዶ የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና ዕርዳታ የተደረገለት ሲሆን የድብደባዉን ዜና የሰማዉ የአሌክሳንደሪያ ከተማ ፖሊስ ወንጀሉ ወደተፈጸመበት ቦታ ደርሶ ተጠርጣሪዎቹን ቢፈልግም ወንጀሉን የፈጸሙት ስብሐት ነጋና አጃቢዉ ታምራት ገ/መድህን ለግዜዉ ከፖሊስ መሰወራቸዉ ታዉቋል። የድብደባዉን ዜና ከኢሳትና ከሌሎች የተለያዩ የአካባቢዉ የዜና ማሰራጫዎች የሰሙት ኢትዮጵያዉያን የህግ ባለሙያዎችና የሲቪክ ማህበረት መሪዎች በስብሐት ነጋና በአጃቢዉ ላይ ክስ መስርተዉ ጉዳዩ በፖሊስ በመጣራት ላይ ነዉ። ይህ በዚህ አንዳለ የአሌክንደሪያ ፖሊሶች የነስብሐት ነጋ ጥቃት ሰለባ የሆነዉን መስፍን ወርቅነህን ድብደባዉን አስመልክቶ አነጋግረዉ የምስክርነት ቃሉን ተቀብለዋል።

የስብሐት ነጋና የአጃቢዉ የታምራት ገ/መድህን ድፍረት ዲሲ፤ ቨርጂኒያና ሜሪላንድ ግዛቶች ዉስጥ የሚኖረዉን ኢትዮጵያዊ ያስቆጣ ሲሆን ኢትዮጵያዉዉያኑ ፖሊስና ፍርድ ቤት በሁለቱ ወንጀለኞች ላይ የሚወስዱትን እርምጃ ለማወቅ በጉጉት በመጠባበቅ ላይ ናቸዉ። የዚህ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ያናገራቸዉ አንድ በቅርቡ ከኢትዮጵያ የመጡ ታደለ ጉርሙ የተባሉ ግለሰብ “የእነሱን ድብደባና እርግጫ ላለማየት አገሬን ጥዬ መጣሁ እነዚህ አይነ ደረቆች እዚህም እያመጡ ሰዉ ይደበድባሉ እንዴ” ካሉ በኋላ ደግነቱ አገሩ አሜሪካ ነዉና ሌላ ቢቀር እኛን አገራችን ዉስጥ የነፈጉንን ፍትህ እነሱ እዚህ በአይናቸዉ ያያሉ ብለዋል።

ኢትዮጵያ ዉስጥ በመካሄድ ላይ ያለዉ ህዝባዊ እንቅስቃሴ መጎልበት፤ የተቃዋሚ ኃይሎች ጡንቻ መፈርጠምና የቱባ ቱባ የህወሃት ባለስልጣኖች አገር ጥሎ መፈርጠጥ ያሳሰባቸዉ የወያኔ ሹማምንት በትዕቢተኛዉ መሪያቸዉ በስብሐት ነጋ መሪነት እዚህ አሜሪካ መጥተዉ ከአሜሪካ መንግስት ባለስልኖች፤ እግሬ አዉጭኝ ብለዉ ከፈረጠጡ አባላቶቻቸዉና ከጥቂት ሆዳም ደጋፊዎቻቸዉ ጋር በመነጋገር ላይ መሆናቸዉ በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች መዘገቡ የሚታወስ ነዉ። ትላልቅ የአገዛዙን የደህንነት ባለስልጣኖች ጨምሮ ከፍተኛ የህወሃት መሪዎችን ይዞ አሜሪካ የገባዉ የወያኔ ቡድን አሜሪካ ደርሶ እንቅስቃሴዉን እስኪጀምር ድረስ ትግርኛ ተናጋሪ ከሆኑት የኤምባሰዉ ሰራተኞች ዉጭ ግርማ ብሩን ጨምሮ ሌሎቹ ከፍተኛ የኤምባሲዉ ባለስልጣኖች በፍጹም አለመስማታቸዉን ከዉስጥ አዋቂ ምንጮች የተገኘዉ መረጃ ያለመክታል። ከፍተኛ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት አሜሪካ ሲመጡ አሜሪካ ዉስጥ የሚገኘዉ የኢትዮጵያ አምባሳደር አለማዉቁ የሚያሳየዉ አስፈላጊ በሆኑ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ወያኔ ከትግርኛ ተናጋሪዎች ዉጭ ማንንም የማያምን ዘረኛ ድርጅት መሆኑን ነዉ ሲሉ ብዙዎች ትችት ይሰነዝራሉ።

No comments:

Post a Comment