Wednesday, December 18, 2013

ህወሓት/ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ብሔራዊ የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት የማስጠበቅ ጥያቄ ላይ ሊታመን አይችልም!

ታህሳስ 8፣ 2006 (ዲሰምበር 17፣ 2013)  

ያለፉት አራት አሥርት ዓመታት የህወሓት/ኢህአዴግ ታሪክ ያስገነዘበን ነገር ቢኖር ገና ከጅምሩ በጠባብ ብሔረተኝነት አጀንዳ የራሱን ጥቅምና ሥልጣን የማስከበርና የማቆየት ዓላማ እንዳለው ብቻ ነው። ይህንንም ተልዕኮውን እውን ለማድረግ የተከተላቸው ፖሊሲዎችና አካሄዶች በተለያዩ ጊዚያት የኢትዮጵያን ግዛታዊ አንድነትና ሉዓላዊነት የሚጻረሩ ሆነው እንደቆዩ እንረዳለን።    
መለስ ዜናዊና የአገዛዙ አባላት ከግልብ የፖለቲካ አመለካከት፤እንዲሁም ከገደብ የለሽ የሥልጣንና ራስ ወዳድነት የተነሳ፤ ዕኩይ ዓላማቸውን በሥራ ላይ ለማዋል ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ተቀናቃኞች ጋር ባደረጉት ድርድሮች የራሳቸውን ማንነት ከመካድ እስከ አገር መሸጥ የሚደርስ ሸፍጥ ማካሄዳችው የአደባባይ ምስጢር ነው።
  
በተለይም በዚህ ወቅት በዋንኛነት ሊጠቀስ የሚገባው ህወሓት/ኢህአዴግ ገና ቀደም ብሎ ከትጥቅ ትግል አጋሩ ከሻዕቢያና፤ ከፍተኛ ድጋፍና አሰተዋፅዖ ሲያደርግለት ከነበረው ከሱዳን መንግሥት ጋር በምስጢር ያደረጉት ስምምነት ነው።የመለስና የሕወሃት/ኢህአዴግ አመራር አባላት በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት መጠበቅ ላይ ግድ ያለመኖርና በአገሪቱ ብሔራዊ ሉዓላዊነት ላይም ባላቸው ሥር የሰደደ ጥላቻ የተነሳ፤ ገና ከጅምሩ ከማንም የበለጠ በዋነኛነት የኤርትራ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ተቆርቋሪና አራማጅ ብቻ ሳይሆን የሱዳን የድንበር መሬት ይገባኛል ጥያቄም ደጋፊና አቀንቃኝ ሆነው መቆየታቸው የሚታወስ ነው። 

ሙሉን መግለጫ ከታች የቀረበውን ሊንክ በመክፈት ያንብቡ፤ 

No comments:

Post a Comment