Saturday, November 23, 2013

አዜብ ህወሀትን ለመልቀቅ ማመከቻ ማስገበቷ ተሰማ

የቀድሞዉ ጠ/ሚኒስቴር ባለቤት የሆነችዉና የሙስናዋ እመቤት በመባል የምትታወቀዉ አዜብ መስፍን ከወጣትነት እድሜዋ ጀምሮ የገለገለችዉን ህወሀት ፓርቲ በቃኝ ብላ ለመተዉ ለፓርቲዉ ማ/ኮሚቴ የመልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባቷን ዉስጥ አዋቂ ምንጮች አስታወቁ። ከባለቤቷ ከመለስ ዜናዊ ህልፈት በኋላ በፓርቲው የነበራት ተሰሚነትና የበላይነት እየተሸረሸረ በመምጣቱ፤ ከኤፈርት ሃላፊነቷ ሳትወድ በግድ በመነሳቷና እንዲሁም ጓግታለት የነበረው የአዲስ አበባ ከንቲባነት ስልጣን በማጣቷ፣ የተበሳጨችዉ አዜብ ተስፋ መቁረጥ መጀመሯ ፓርቲውን ለመልቀቋ ዋና ምክንያት እንደሆነ ምንጮቹ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ አዜብ የምትተማመንባቸዉ አብዛኞቹ የህወሀት ባለስልጣኖች ከስልጣን ተባርረዉ መታሰራቸዉና እንዲሁም በስብሃት ነጋ ቡድን እየተወሰደባት ያለው ፖለቲካዊ የበላይነት መቋቋም ስለተሳናት ከፓርቲው በግዜ መሰናበቷ ሌላ አማራጭ የሌለዉ መሆኑን በቅርብ የሚያዉቋት ሰዎች በመናገር ላይ ናቸዉ። የህወሀት ማዕከላዊ ኮሚቴ በቅርብ ቀን ዉስጥ ተሰብስቦ የአዜብ መስፍንን ጥያቄ እልባት እንደሚሰጠዉ የጠቆሙት ምንጮች ከዚሁ ጋር አያይዘው ጥያቄው ተቀባይነት ካገኘ አዜብ በሲውዲን ወይም አሜሪካ ቨርጂኒያ ግዛት ዉስጥ በገዛቸዉ መኖሪያ ቤት ለመኖር ጓዟን እንደምትጠቀልል አመልክተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዘረኛዉና ለብዙ ሰላማዊ ዜጎች ሞት ተጠያቂ የሆነዉ ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ከኢታማጆር ሹምነቱ ቦታ ተነስቶ በምትኩ በቅርቡ የሌፍቴናነት ጄኔራልነት ሹመት የተሰጠዉ ጄ/ል ዮሃንስ ገ/መስቀልን ሊተካ እንደሚችል አዲስ አበባ ዉስጥ የሚገኙ ወታደራዊ ቃል አቀባዮቻችን ገለጹ።

No comments:

Post a Comment