Friday, October 10, 2014

ትምክህተኛና ጠባብ ማን ነው!!!



ከአስገደ ገ/ስላሴ (መቀሌ)

የህወሓት ኢህአደግ መንግስት ፖሊሲና ስትራተተጂ ስልጠና በሚል ሽፋን ተማሪዎች በሃገር ደረጃ ከ300 ሺ በላይ የፍትህ አካላት ማለት ዳኞች ቸቃብያን ሕግ ፖሊሶች በሙሉ መጀመርያ በየ ክልሉ ለ15 ቀናት ስልጠና ተሰጣቸው በተለይ በትግራይ የፈትህ አካላት በውቅሮ 15 ቀን በአክሱም ከዛ በላይ እየሰለጠኑ ይገኛሉ::
...
በዚሁ ስልጠና በሁሉም ቦታ ማለት ይቻላል:: የድሮ ነገስት በማንሳት በፊሊም የተቀረፀ እነዛ ነገስታት የትምክህትና የጠባብነት ምንጭ መሆናቸው:: ሃገራችን ዘር ሃይማኖት ቢሄር ከቢሄር እያጋጩ የትምክህትና ጠባብነት መፈንጫ አድርጎዋታል በማለት ሲያማርሩ ከርመዋል:: በሌላ በኩል የህወሓት ኢህአደግ መንግስት ካለፉት ስርዓቶች የበለጠ ሃገራችን እንደቀየረ ሲነግሩን ከርመዋል::

በተሰብሳቢዎች ግን የምትነግሩን ያላቹሁ በንቃተህልናቸው አሁን ካለው ትውልድ እጅጉን የወረዱ ነበሩ:: ያም ሆኖ ሃገራችን አንድነቷና ሉኦላዊነቷ ጠብቃ እንድትኖር አድርጓታል:: እናንተ ግን የዚህች ሃገር ሉኦላውነቷ ያስደፈራቹሁ ናቹሁ:: ኢትዮዽያ የባህር በሯን አሳልፋቹሁ ሰጥታቹሁ በሁሉም ነገረ ጠገኛ አድርጋቹሁን አላቹሁ ሃገራችን በቋንቋ በወንዝ እንድትከለልና ዜጎች በፈለጉት በሃገራቸው ክልል ሰርተው እንዳይኖሩ በማደረግ ጠባብነና ትምክህት እንዲነግስ ከማድረጋቹሁ አልፎ የሃይማኖት የቢሄር ግጭት ተስፋፍቶ ዜጎች እርስ በእርሳቸው እንዳይተማመኑ አድርጋቹሁ እነ አፀይ ዩሃንስ አፀይ ምንሊክ የቴክኖሎጂ እውቀት ባልነበረባቸው ምንም እንኳ አንዳንድ ስህተቶች ቢኖሩዋቸው እቺ ሃገረ ስትደፈር የኢዮዽያ ህዝብ እንደ አንድ ሰው ሆኖው ሕብርና ሃገራዊ ወኔን በመፍጠር ሃገራችን ከባዕድ ወረራ ተከላክለው አቆይቶውናል:: እናንተ ግን በጥቂት የፓርቲ አመራር ውሳኔ ብዙ ስህተት ፈፅማቹሃል:: በተጨማሪም ለህዝቡ ይሁን ለመንግስት ሰራተኛ በአንድ ወጥ በማስተማር ፈንታ የትግራይና የኦሮሞ ህዝብ የአፀይ ምንሊክ መጥፎ ገፅታ በፊልም በማሳየት በአማራም በኦሮሞ ወይም የትግራይ ነገስታት መጥፎ ገፅታ በማሳየት በሌሎች ቢሄሮች ቢሄረሰቦችም እንደዚሁ እንዲናናቁ አድርጋቹሃል ተብለዋል::




በኔ እምነትም ትምክህትና ጠባብነት እንዲስፋፉ የሚያባብሱት ያላቹሁ የህወሓት ኢህአደግ መሪዎች ናቸው:: ስለዚህ ትምክህተኛና ጠባብ ማንው ለሚለው መልሱ ኢህአደግ ነው:: ይህ ደግሞ የኢህአደግ መሪዎች ሕብረተሰቡ በትምክህትና ጠባብነት ስሜት ካልከፋፈሉት ስልጣናቸው እድሜ የለውም:: ሌላ የኢህአደግ መሪዎች የትምክህት ቋት መሆናቸው መረጋገጫ በዚህች ሃገር ከኛ ፖለቲካዊ አስተሳሰብ (አይዶሎጂ) ወዲያ የለም ከነሱ እምነት ውጭ የራሱን ሃሳብ ይዞ የተነሳ ፓርቲ ወይም ቡድን ወይም ግለሰብ እንቢ ላለ ሰው ጥይት አጉርሰው ነው መልሱ:: ሌላ ቀርቶ የሃገራችን የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ እየተነተኑ ለህዝብ መረጃ የሚያደርሱ ጋዜጤኖች አምዳውያን የደሀረ ገፅ ጦማርያን የፓርቲ መሪዎች ከሃገር ውጭ እንዲሰደዱ በወህኒ ቤት ታስረው እንዲበሰብሱ ሌሎችም ተሸማቅቀው እንዲኖሩ ተደርገዋል እየተደረጉን ናቸው::

መላው የኢትዮዽያ ህዝብ ሙሁራን ተማሪዎች የመንግስት ሰራተኖች የህወሓት ኢህአደግ መሪዎች አሰተሳሰብ ካልተቀበለ ከሁሉም የስራ እድል ጥቅማ ጥቅም የማግኘት ነፃ ሆኖ እንዳይንቀሳቀስ ተደርገዋል ድርጊቱ እየቀጠለ ነው:: አሁንማ የኢትዮዽያ ህዝብ የመሬት ባለቤትነቱ ተነጥቆ የኢሀአደግ መሪዎች ጢሰኛ (ተጠማኝ) እንዲሆን ተደርገዋል:: የሃገሪተቱ አበዛኛው ብዙ ገንዘብ ሊያስገኙ የሚችሉ የእንድስትሪ ማእከላት በኢሀአደግ መሪዎች ጠፍረው በመያዝ የግል ባለሃብቶች እንዲቆረቁዙ አድርጎዋቸዋል:: በሌላ በኩል የሞያ የሰራተኛ የሴቶች የወጣት ማሕበራት የእምነት ተቋማት በሙሉ የኢህአደግ አደረጉዋቸው:: እምነቶች በመመርያ ካልተጓዙ የማይኖሩበት ሁኔታ ተፈጥረዋል::

የተቃዋሚ ፓርቲዎች በአስሳሰብ የላቁ ሆኖው ካልተገኙ አስተሳሰባቸውን በሰላማዊ ውድድር እንደማሸነፍ መጥፎ ስሞች በመለጠፍ ትምክህተኛ ፈላጭ ቆራጭ ሕግ በማፅደቅ እንዲደቁ ተደርገዋል እየተደረጉ ይገኛሉ:: በዚሀ ምክኒያት የህወሓት ኢህአደግ ፓርቲ በፈጠረው የጠባብነት ባህሪያትና ተግባር ጠንቅ ብዙ የተቃዋሚ ኃይሎች ነፍጥ አነሱ ልክ ትምክህተኛው ህወሓት ወደ ስልጣን በመጣበት መንገድ ስልጣን ለመያዝ በረሃ ገብተዋል እየገቡም ይገኛሉ:: ሌሎችም በአሸባሪነት ሰበብ በየ ወህኒ ቤቱ ታጉረዋል:: የዚህ አደጋ ውጤት የህወሓት መሪዎች ከደርግና ሌሎች መንግስታት ትምክህትና ጠባብነት ከፈጠሩት ተሞክሮ እንደማሻሻል ፈንታ የባሰው ትምክህተኛ ጠባብነት አንግሰዋል:: ለዚህ ጉዳይ ቆም ብለው አስበው ሰክነው በሰላም ካልፈቱት ሃገራችን ኢትዮዽያ ከባድ አደጋ እያንጃበባት ነው:: ለሚፈጠረው አደጋ ደግሞ ተጠያቂዎች የህወሓት ኢህአደግ መሪዎች ናቸው:: የኢትዮዽያ ህዝቦች እንደሆን በቦታችን ነን አንበረከክም::




No comments:

Post a Comment