Sunday, May 17, 2015

ለቀድሞው የአንድነት አመራር “ እናርድሃለን፣…ራስህን በጥይት እንበትነዋለን….” የሚል ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው

የመንግሥት ደህንነቶች ለቀድሞው የአንድነት ፓርቲ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት ተክሌ በቀለ የመጨረሻያሉትን እናርድሃለን፣…ራስህን በጥይት እንበትነዋለን..የሚል ማሰጠንቀቂ መስጠታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ማስጠንቀቂያውና ማስፈራሪው በሌሎቹም የቀድሞው የፓርቲ አመራሮች ላይም የቀጠለ ሲሆን፣በዛው ዕለት የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አባልና የማኀበራዊ ጉዳይ ኃላፊ የነበረው አቶ አለነ ማፀንቱ መታሰሩ ታውቋል፡፡በተለይ የአቶ ተክሌ በቀለ ሁኔታን በተመለከተ ራሳቸው በአጭሩ እንደሚከተለው አስቀምጠውታል፡፡

ለሆነ ጎዳይ ከእንድ ጓደኛየ ጋር ዛሬ ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡30 ላይ ከቦሌ ተነስተን ኮተቤ(02) አካባቤ ሄድን፡፡ የቤት ታርጋ የለጠፈች ነጭ መኪና 4 ጎሮምሶችን ይዛ ትከተን ነበር፡፡ ቦታ ስተን ኑሮ የሆነ መታጠፊያ ላይ ወደ ኋላ ስንዞር ተገጣጠምን፡፡ ባንድ መስመር ስዞር ቦታ የዘጋሁባቸዉ መስሎኝ ይቅርታ ስጠይቃቸዉ የሚነዳው ወንድም መኪናዉን አቁሞ ሳይወርድ የስድብ መዓት አወረደብኝ፡፡ ያ ያገሬ ልጅ! ከዚያም ሄዱ፡፡እነማን እንደ ሆኑም ገባኝ፡፡ ጓደኛየ ወደ ቢሮዉ ገብቶ ጉዳዩን ጨርሶ እስኪወጣ ወርጄ ስጠብቀዉ በመኪኗ ተመልሰዉ መጡ፡፡ በማዶ ላይ የቀን ሰራተኞች ምሳ በልተዉ ሰዓቱ እስኪደርስ ጥላ ላይ ያረፉ ነበሩ፡፡ሁኔታዉን ይከታተሉ ኖሮ ትተዉኝ ሲሄዱ መጥተዉ ጠየቁኝ፡፡የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባል እንደነበርኩና አሁን እንደሌለሁበት፤የስርኣቱ ደህንነት ነን ባዮች ሲሆኑ እያስፈራሩኝ መሆኑንም ስነግራቸዉ በጣም ተናደዱ፡፡ለምን ግርግር አትፈጥርም ነበር አንለቃቸዉም ነበር…..ክብር ለዜጎች! ውድ ህይወት ተከፍሎበት በነበረ ስርዓት ውስጥ፤ህግ አክባሪና ሃይማኖተኛ በሆነ ማህበረሰብ ዉስጥ ተወልዶ ያደገ፤ከድሃ ግብር ደሞዝ የሚበላ የደህንነት ሰራተኛ ነኝ ባይ “እናርዳሃለን….መንግስት ነን፣ ራስህን በጥይት እንበትነዋለን…የምትሰራዉን ሁሉ እናዉቃለን…እድሉን ተጠቀምበት የመጨረሻህ ነዉ….” የሚሉ ቃላት እንዲናገሩ ሰልጥነዉ ሲላኩ በእዉነት ያሳፍራል፡፡ ዱላ ቀረሽ ስድብ አዝንበዉብኝ መኪናቸዉን አስነስተዉ እብስ አሉ፡፡ የመጀመሪያየ ባይሆንም የከዚህ ቀደሞቹ ግን ጨዋዎች ነበሩ! ግን፤ አርፈንም እንድናርፍ አይፈቀድልንም እንዴ? እኛ እንሰራው የነበረው ፖለቲካ ፍጽም ሰላማዊና ህገ መንግስታዊ ነበር፡፡ አሁንም መብታችን ነዉ፡፡ የነአሞራዉ ደም የፈሰሰዉ ለዚህም እንደነበር እንረዳለን፡፡ተሸብራችሁ ከሆነ በስራችሁ እንጂ በኛ አይደልም፡፡ እኛ ግን ለግዜው ከጨዋታው ውጪ ስላደረጋችሁን በጨዋታው ሜዳ የለንበትም፡፡ ለማስጠንቀቂያውም ለመረጃውም ስርዓት አለው፡፡ የመንግስት አካል የሆነ ተቋም በፈለገዉ መንገድ ህጋዊ ሆኖ ማናገር ይችላል፡፡ መንግስትነት ትልቅ ሃላፊነትና ተቋም መሆኑን ልንነግራችሁ አቅም የለንም፡፡ የተበተነን የቀድሞ የፓርቲ አመራር ማስፈራራትና ማሰር ተራ ብቀላ ይመስላል፡፡ ተራ ህይወት እየመራንም፤አርፈን ተቀምጠንም ልትተዉን ካልቻላችሁ በግፉ መንገድ ግፉበት፡፡ እኛ ከማን እንበልጣለንና ነው!!!

No comments:

Post a Comment