Monday, April 13, 2015

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ አባሎች እንዲሁም ትውልደ ኢትዮጵያ በሙሉ!

ኢትዮጵያዊን እንደ ወያኔ ዘመን የተዋረዱበት የተናቁበትና የተበደሉበት ጊዜ የለም። በአሁኑ ወቅት አገሪቱ ና ህዝቧ ከፊታቸው የተጋረጠው ችግር የመሰረታዊ የዲሞክራሲ ና የሰብኣዊ መብቶች አለመከበር ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የሕልውና ጥያቄ ና ኢትዮጵያ እንደ አገር የመቀጠልና ያለመቀጠል ጉዳይ ሆኖዋል።

በመሆኑም በኖርዌይ የምንኖር ኢትዮጵያውያን ይህንን ወቅቱ የሚጠይቀውን ታሪካዊ እና አንጸባራቂ የትግል ድጋፍጥያቄ አቅማችን በፈቀደው መንገድ ለመደገፍ የዲሞክራሲዊለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ በፕሪል18፣2015 ታላቅ ህዝባዊ ስብስባ ና ድጋፍ ማስባሰቢያ ዝግጅት አዘጋጅቶል እርሰወም በዝጅቱላይ አስፈላጊውን ድጋፍ እንድታረጉ በአክብሮት እየጠየቅን በማያያዝም በዚህ ፕሮግራም ላይ በመገኘት እንዲሁም ሌሎችንም በመጋበዝ ታሪካዊና ወቅታዊ አገራዊ ግዴታችንን እንድንወጣ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ቀኑ፣ አፕሪል 18፣ 2015
ሰአት፣ 14፣00 ጀምሮ
ቦታ ከተጨማሪ ማብራሪያ ጋር በቅርብ ቀን ይገለጻል

ጓደኛዎትን በኤቨንቱ ላይ ይጋብዙ፣
ነፃነት፣ ፍትህ፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ተከብራ ትኖራለች !!!

የዲሞክራሲዊለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ!!

No comments:

Post a Comment