Sunday, September 7, 2014

የግንቦት 7 የፍትህ፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አለማቀፍ ህዝባዊ ስብሰባዎች ተሳካ ሁኔታ ተካሄዱ

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በመላው ዓለም ከሚገኙ አባላት፣ ደጋፊዎቹና በአጠቃላይ ከኢትዮጵያውያን ጋር በወቅታዊ አገራዊ ሁኔታዎች ላይ ለመመካከር በ 30 ታላላቅ ከተሞች ካሰናዳቸው ህዝባዊ ስብሰባዎች መካከል አብዛኞቹ ባሳለፍነው እሁድ ኦገስት 31 ቀን 2014 አ.ም በድምቀ በመካሄዳቸውን ዘጋቢዎቻችን ያደረሱን መረጃ ያመለክታል። በእነዚህ በአምስት አህጉራት፤ በዘጠኝ አገሮችና 17 ከተሞች በተካሄዱት ህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ ኢትዮጵያውያን በነቂስ በመውጣት የታደሙበት እንደነበር ያደረሱን ዘጋቢዎቻችን አገር ወዳድ ኢትዮጵያኑ ከንቅናቄው ከፍተኛ አመራሮች ጋር ሰፊ አገራዊ ውይይት ያካሄዱበት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። ኢትዮጵያውያን በዘር በሃይማኖት በጎሳ ሳይለያዩ በአንድነት በመሰባሰብ በአገራቸው ጉዳይ ላይ በሰፊው የመከሩበት፤ ኢትዮጵያዊነት እጅግ አምሮና አሸብርቆ የታየበት በአይነቱ ልዮ የሆነ ህዝባዊ ስብሰባ እንደነበር በርካቶች ምስክርነት እንደሰጡም ዘጋቢዎቻችንን አመልክተዋል። የንቅናቄው ከፍተኛ አመራሮች በክብር እንግድነት በተገኙባቸውና በስካይፒ በመሩዋቸው ህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ ከተሳታፊው የደመቀ አቀባበል እንደተደረገላቸውም ለማወቅ የተቻለ ሲሆን አመራሮቹ ከተሳታፊዎች ለቀረበላቸው በርካታ አገራዊ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። በህዝባዊ ስብሰባዎቹ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት በአሜሪካ የዋሽንግተን ዲሲ ግዛት የንቅናቄው ዋና ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፤ በአትላንታ አቶ ነአምን ዘለቀ፤ በቦስተን የንቅናቄው የህዝብ ግንኙነት ተጠሪ አቶ ኤፍሬም ማዴቦ፤ በካናዳ ቶሮንቶ አቶ አንድነት ሃይሉ፤ በጀርመን ሙኒክ አቶ ብዙነህ ጽጌ በኖርዌይ ኦስሎ የንቅናቄው ም/ ሊቀመንበር አቶ አበበ ቦጋለ ሲሆኑ በስካፒ የተደረጉትን ስብሰባዎች የመሩት በደቡብ አፍሪቃ ደርባን፡ ጆሃንስበርግና ቬሪኒንገን ዶ/ር ታደሰ ብሩ፤ በሩስተምበርግ አቶ ቸኮል ጌታሁንና በአውስትራሊያ ፐርዝ የተካሄደውን አቶ ብዙነህ ጽጌ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።

በህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ በየመን የፀጥታ ሃይሎች ተይዘው አለማቀፍ ህግን በጣሰ አካሄድ ለጉጅሌዎቹ ተላልፈው የተሰጡት የንቅናቄው ዋና ፀሐፊ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሥራዎች በምስልና በቪዲዮ ተቀናብረው ለእይታ የቀረቡ ሲሆን የነፃነት አርበኛው የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ስራዎችና አሁን ላይ በጠላት እጅ መውደቃቸው ኢትዮጵያውያኑን በቁጭት አስነብቷል፤ በበለጠ ትግሉ ለሚጠይቀው ማንኛውም መስዋዕትነት በእልህና በቁጣ ያነሳሱዋቸው እንደነበሩም ለማወቅ ተችሏል።


ኢትዮጵያውያኑ ፋሽስቱ ወያኔን ማስወገድ በሚቻልባቸው የትግል ስልቶች ላይ ሰፊ ውይይት ከድርጅቱ አመራሮች ጋር ያደረጉ ሲሆን ኢትዮጵያውያኑ በንቅናቄው የተነደፉትን የትግል ስሎች በማድነቅ ወደፊትም የጉጅሌው ወያኔን በመገርሰስ ትግሉን ከዳር ለማድረስ ለሚጠይቃቸው ማንኛውም አይነት መስዋዕትነት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፤ ኢትዮጵያውያኑ በአንድነት እጅ ለእጅ በመያያዝም ትግሉን ከዳር ለማድረስ ቃል ኪዳን መግባታቸው ተዘግቧል። ትግሉን ከዳር ለማድረስ በገንዘብ፤ በሰው ሃይልና በዕውቀት ረገድ ድጋፍ በማድረግ ከንቅናቄው ጎን እንደሚሰለፉ ቃል መግባታቸውንም ዘጋቢዎቻችን አመልክተዋል። በቅርቡ የተሰማው ውህደትን የተመለከተው የብስራት ዜና ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ተቀራርቦ በጋራ መስራት የሚቻልበት ሁኔታዎች መመቻቸት እንዳለበት ኢትዮጵያውያኑ ማሳሰባቸው ታውቋል።

በመጨረሻም የነፃነት ትግሉ የደረሰበትን ደረጃ በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡት የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች አሁን ወሳኝ የትግል ምዕራፍ ላይ ደርሰናልና ሁሉም አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በአንድነት ልንረባረብ ይገባል በማለት ኑ! ኢትዮጵያ አገራችንን፣ ኢትዮጵያዊ ወገናችንን እና ራሳችን ነፃ ለማውጣት እና በሀገራችን ፍትህና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ለማድረግ በምናደርገው ትግል ተቀላቀሉን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። ለቀረበውን አገር አድን ጥሪ ምላሽ በመስጠት በሁሉም የህዝባዊው ስብሰባ ቦታዎች ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን በትግሉ ለማሳተፍ በአባልነትና ደጋፊነት አስተዋዕጽኦ ለማበርከት መመዝገባቸውንም ለማወቅ ተችሏል። በተጨማሪም በአገር ውስጥና በውጭ አገር ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች፤ እና ለኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የጉጅሌው ወያኔን አገዛዝ ለማስወገድ እየተደረገ ያለውን የሞት ሽረት ትግል እንዲቀላቀሉ ጥሪ መቅረቡንም ለማወቅ ተችሏል።

No comments:

Post a Comment